ራስ ጋይንት የገብርየ ልጅ

ራስ ጋይንት የገብርየ ልጅ Communicated

"አዎጅ" "አዎጅ" በል" የስማህ ላስማ አስማ"የአማራ ክልል የአብክመ ፍርድ ቤት በስሩ የሚገኙትን የአስተዳደርስራተኞችን ጥቅም፣የስራ ልምድ፣ ሳያስከብር በቸልተኝነትመመልከቱ የዘመኑን የፍትህ ...
10/03/2025

"አዎጅ" "አዎጅ" በል" የስማህ ላስማ አስማ"
የአማራ ክልል የአብክመ ፍርድ ቤት በስሩ የሚገኙትን የአስተዳደር
ስራተኞችን ጥቅም፣የስራ ልምድ፣ ሳያስከብር በቸልተኝነት
መመልከቱ የዘመኑን የፍትህ ደረጃ ምን ላይ እደደረስ የሚያሳይ
ነው። እኛ የፍ/ቤት የአስተዳደር ስራተኞች በአሽባሪነት የተፈረጅን
የማፊያ ስብስብ ወይንም የፖለቲካ ቀስቃሺ ፓርቲ ሳንሆን
እራበን፣ጠማን፣ በምንስራው ልክ ይከፈለን፣የስራችን ጥቅሙና
አግባብነቱ ይታወቅልን፣ እደማንኛውም የኢትዮጵያ የመንግስት
ስራተኞች ጥቅማችንና መብታችን ይከበርልን ብለን የምንጠይቅ
ሚስኪንና ሀገር ወዳድ፣ህዝብ አገልጋይ ዜጎች ነን።
ቢሆንም ግን የዳኞች አስተዳደር ጉባኤና የፍርድ ቤት ሺማምንቶች
የራሳቸውን ጥሩ ኑሮ ከነ ደመወዙ እየበሉ፣ለልጆቻቸው ቤታቸውን
እየስሩ፣ልጆቻቸውን እያስተማሩ የእኛን የመብት ጥያቄ በአግባቡ
መዝኖ አለመመለስ የስግብግብነት እጁን ያረዘመ የታወረ የፍትህ
ስርዓት ላይ እየዎኘን መሆኑን በግልፅ ያሳየናል።
በአጠቃላይ ከፍትህ ተቋም እየስራን ፍትህ ያጣን፣ ድምፃችን
የታፈነ፣ ብሎም የተረገጥን በመሆናችንና ፍርድ ቤት ማለት
በሚዛን የተወከለ ሁሉም እኩል የሚስፈርበት ቢሆንም የፍርድ
ቤት የአስተዳደር ስራተኞችን ስንመለከት ጥግ የሌለው በደል
እየደረስብን ይገኛል።
የአብክመ ፍርድ ቤት በስሩ የሚገኙትን የአስተዳደር ስራተኞች
የሞራላዊ ድሺቀት፣በኑሮ ማበሳቆል፣ የበይ ተመልካች
ማድረግ፣የመብት ጥያቄወችን ማፈንና መርገጡን " አዎጅ"
"አዎጅ" "አዎጅ" ብለን ቀስቅስን በጋራ በቃ ልንለው ይገባል!!
ስራችንን በቅንነት እየስራን መብታችንን እንጠይቅ። ለዳኞች ብቻ
የተቋቋመውን ኢትዮጵያዊ ግብረ ስናይ ድርጅት የሆነውን የፍርድ
ቤት የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በቃህ ልንለው ይገባል።
"ፍትህን እየደገፍን ፍትህ እንጠይቃለን "

3 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው። ለፈተና በቂ ዝግጅት ስላላደረጉ ለመሸወድ ፈለጉ። በዚህም ምክንያት አንድ መላ ዘየዱ። ራሳቸውን ግሪስ ቀቡና ራሳቸውን በሚገባ በማቆሸሽ ከሌክቸረሩ ፊት በመቅረ...
06/06/2023

3 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው። ለፈተና በቂ ዝግጅት ስላላደረጉ ለመሸወድ ፈለጉ። በዚህም ምክንያት አንድ መላ ዘየዱ። ራሳቸውን ግሪስ ቀቡና ራሳቸውን በሚገባ በማቆሸሽ ከሌክቸረሩ ፊት በመቅረብ እንዲህ ሲሉ ምክንያታቸውን አቀረቡ፦

ኢንስትራክተር በጣም እናዝናለን፤ ፈተናውን ለመፈተን የማያስችል እንከን ገጥሞናል። ምክንያታቸውን አስከተሉ፦

አንድ ሰርግ ላይ ታድመን ነበር፤ እናም ከፕሮግራሙ በኋላ በመመለስ ላይ እያለን በመንገዳችን ላይ መኪናችን ብልሽት ገጠማት። የመኪናችንን ብልሽት ለመጠገን እንደምትመለከተን በአስቀያሚ ሁኔታ ቆሽሸናል።

#ሌክቸረሩም ከምክንያተቸው በመነሳት ተረዳቸውና ወደቤታቸው እንዲመለሱ ለፈተና ዝግጅት 3ት ቀን ሰጣቸውና አሰናበታቸው።

ከ3ት ቀን በኋላ ለተዘጋጀላቸው ፈተና በበቂ ሁኔታ አጥንተውና ተዘጋጅተው መጡ።

ሌክቸረሩ አንድ ውሳኔ ወሰነና እንዲህ አደረገ ...

ሶስቱም ተራርቀው የተለያየ ወንበር ላይ እንዲቀመጡ አዘዘ። ተማሪዎቹም በጣም ተራርቀው ተቀመጡ፤ የፈተና ወረቀትም ተሰጣቸው። ጥያቄዎቹ የሚከተሉት ነበሩ፦

ጥያቄ ቁጥር 1 - ማን ነበር ያገባው ? (25 % ማርክ)

ጥያቄ ቁጥር 2 - የት ነበር የሠርግ ፕሮግራሙ የተካሄደው ? (25 % ማርክ)

ጥያቄ ቁጥር 3 - መኪናዋ የተበላሸችበት ትክክለኛ ቦታ የት ነው ? (25 % ማርክ)

ጥያቄ ቁጥር 4 - የተበላሸችው መኪና ሞዴሏ ምን አይነት ነው ? (25% ማርክ)

ከጥያቄዎቹ መጨረሻም #ማስጠንቀቂያው እንዲህ ይላል - መልሳችሁ የግድ ተመሳሳይ መሆን አለበት !!!
_______

Africa 10 ን ላይ - ተወስዶ የተተረጎመ

Address

Dubai
WWW.FB.COM

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ራስ ጋይንት የገብርየ ልጅ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share