WolloPedia

WolloPedia Organic Wollo

ጀግናው ኮረኔል በዛብህ ፔጥሮስ !
21/09/2025

ጀግናው ኮረኔል በዛብህ ፔጥሮስ !

ዶናልድ ትራምፕ "የህዳሴ ግድብ የግብፅን ህዝብ ህይወት የሚወክል በመሆኑ በፍጥነት መፍትሄ መፈለግ አለብን፤ የሚባክን ጊዜ የለንም" እያለ ነው🤔ሽማግሌው ምን አገባው ቆይ 😏😏
21/09/2025

ዶናልድ ትራምፕ "የህዳሴ ግድብ የግብፅን ህዝብ ህይወት የሚወክል በመሆኑ በፍጥነት መፍትሄ መፈለግ አለብን፤ የሚባክን ጊዜ የለንም" እያለ ነው🤔

ሽማግሌው ምን አገባው ቆይ 😏😏

የሃማስን ሮኬት መገንቢያ አገኘሁት ! /እስራኤል /ሃማስን እስከወዲያኛው ለማጥፋት ብሎም ጋዛን ለመቆጣጠር ካለፈዉ ማክሰኞ ጀምሮ እግረኛ ጦሯን ያሰማራችዉ እስራኤል በራማላ የቡድኑን የሮኬት ማ...
20/09/2025

የሃማስን ሮኬት መገንቢያ አገኘሁት ! /እስራኤል /

ሃማስን እስከወዲያኛው ለማጥፋት ብሎም ጋዛን ለመቆጣጠር ካለፈዉ ማክሰኞ ጀምሮ እግረኛ ጦሯን ያሰማራችዉ እስራኤል በራማላ የቡድኑን የሮኬት ማምረቻ ማግኘቷን አሳወቀች ።

የእስራኤል የጸጥታ ሃይሎች በራማላ አካባቢ የፍልስጤም ነፃነት አስጠባቂ ነኝ ሲል የሚደመጠዉን ሃማስ ሮኬቶችን የሚያመርትባቸዉን ቦታ ከበርካታ መሳርያዎች ጋር ማግኘታቸውን የእስራኤል መከላከያ ሃይል አርብ ዕለት አስታዉቋል።

ሮኬቶችን ለማምረት የሚውሉ ፈንጂዎች፣ቦንቦች ቀለሃወችና ልዩ ልዩ ለከባድ መሳርያ ግንባታ መስርያ የሚዉሉ ቁሳቁሶች ከሶስት ተጠርጣሪዎች ጋር ማግኘቱንና ማምረቻዉ ከተለያዩ ንጥረ ነገሮች ጋር ሙሉ ለሙሉ መውደማቸውንም የአይዲኤፍ አክሏል።

ሰራዊቱ ከማምረቻዉ በአቅራቢያው በምትገኘው የፍልስጤም መንደር የካፍር ኒማ የማይሰሩ የሮኬት ቀልሀወች ማግኘቱን ተከትሎ ባደረገዉ ጠንሳራ አሰሳ ይህን በተደጋጋሚ ወደ እስራኤል የሚወነጨፉ ሮኬቶች የሚመረቱበትን ማምረቻ ማግኘቱን በዉስጡም በጋዛ ይገኛሉ ተብለዉ የማይታመኑ ቴክኖሎጂዎች መሳርያዎች መገኘታቸውን በመግለጫው ገልጿል ።

ከተያያዘ ዜና የየሻ ካውንስል እስራኤል በጋዛ እየፈፀመችዉ የሚገኘዉን" ሽብርን" ለመከላከል ጠንከር ያለ እርምጃ እንዲወስድ እና ሉዓላዊነቱን በአካባቢያቸው ላይ እንዲተገበር አሳስቧል።

"የእስራኤል መንግስት መንተባተቡን በሚቀጥልበት ጊዜ ለነፃነታቸው የሚታገሉ ጋዛዉያን ሉአላዊነታቸዉን ለማስከበር በመሃል ሀገሪቱ ቴላቪቭ ጥቃት እንዲፈፅሙ ይጋብዛል። በእስራኤል የሚፈፀመዉ ሽብር እንደገና አንገቱን ወደ ላይ ከፍ በማድረግ እየጠነከረ ይሄዳል። ብሏል ሲሉ ያስነበቡት ጀሩሳሌም ፖስትና ዘ ትሪቡን ናቸዉ ።

የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ

ሩሲያ የኢትዮጵያን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫግንባታ ለመደገፍ ዝግጁነቷን አረጋገጠችበሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ፣ ከሩሲያ መንግሥት ኮርፖሬሽን ሮሳቶም ምክትል ዳይሬክተር ኒኮላይ ስ...
20/09/2025

ሩሲያ የኢትዮጵያን የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ
ግንባታ ለመደገፍ ዝግጁነቷን አረጋገጠች

በሩሲያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ፣ ከሩሲያ መንግሥት ኮርፖሬሽን ሮሳቶም ምክትል ዳይሬክተር ኒኮላይ ስፓስኪ ጋር ትናንት መገናኘታቸውን ኤምባሲው ይፋ አድርጓል።

በውይይቱ ኃላፊው ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ወሳኝ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል የኒውክሌር ኃይል ጣቢያ ለመገንባት ሩሲያ ተገቢውን ትብብር ለማድረግ ፍላጎትና ቁርጠኝነት እንዳላት ገልፀዋል።

አምባሳደር ገነት በበኩላቸው፤ ሀገራት የኃይል ማመንጨት አቅማቸውን በኒውክሌር ኃይል ሊያሰፉ እንደሚገባ አፅንኦት በመስጠት፤ ሩሲያ በዚህ ረገድ ባለፉት ሰማንያ ዓመታት ያስመዘገበችውን ስኬት አድንቀዋል።

ስፓስኪ፤ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የገንዘብ መዋጮ የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቁንም አድንቀዋል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል።

እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የብሔራዊ ባንክ ገዥ ሆነው ተሾሙ።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመስከረም 9 ቀን ጀምሮ ለሁለት አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል።በዚህም1ኛ. ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ...
19/09/2025

እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የብሔራዊ ባንክ ገዥ ሆነው ተሾሙ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመስከረም 9 ቀን ጀምሮ ለሁለት አመራሮች ሹመት ሰጥተዋል።

በዚህም

1ኛ. ዶ/ር እዮብ ተካልኝ - የብሔራዊ ባንክ ገዥ
2ኛ. ወ/ሮ እናታለም መለስ - በሚኒስትር ማዕረግ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሃላፊ አድርገው ሾመዋል።

አንድ ጡብ ሳታቀብል በባዶ ሜዳ አታለቃቅስ !!ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ትፈልጋለህ? ተጨባጭ ሥራን ሥራ!አቅም ካለህ አቅምህን ተጠቅመህ፣ አቅም ከሌለህ አቅም ካላቸው ጋር አብረህ (ብ ይጠብቃል) ...
19/09/2025

አንድ ጡብ ሳታቀብል በባዶ ሜዳ አታለቃቅስ !!

ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ትፈልጋለህ? ተጨባጭ ሥራን ሥራ!
አቅም ካለህ አቅምህን ተጠቅመህ፣ አቅም ከሌለህ አቅም ካላቸው ጋር አብረህ (ብ ይጠብቃል) ዘላቂ ለሆነ ለውጥ ሥራ!
ለውጥ በዚህ መንገድ ቅርብ ነው!

እንደ ፀደቀ ይሁኔ ህልም ሠርተህ ገንዘብህን ሆጨጭ አድርገህ ትምህርት ቤት ገንባና 100% ተማሪዎችህን በሙሉ አሳልፈህ ደረትህን ንፋ!
ይህ አንዱ የመለወጥና የመለወጥ መንገድ ነው!! (አንዷን 'ለ' አጥብቃት)

እንዴት? ካልከኝ
በኢንጂነር ፀደቀ ይሁኔ ሙሉ ወጭ ደሴ ላይ የተመሠረተው ይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ12ኛ ክፍል ሀገርአቀፍ ፈተና ካስፈተናቸው 52 ተማሪዎች 21ዱ ከ 500 በላይ ሲያመጡ ቀሪዎቹ 31 ተማሪዎች ከ408አስከ 499 ድረስ ውጤት ያመጡ መሆናቸውን እነግርሃለሁ!!

ስለዚህ
በይሁኔ ወልዱ ትምህርት ቤት ፀደቀ እንጅ ወደቀ የሚለው ቃል ሲያለቃቅስ አታገኝም!!

ሀገር መውደድ ሀገር መጥቀም ማለት ይሄው ነው!

ኢንጂነር ፀደቀ ይሁኔ ለሠሩትም ለአርአያነታቸውም ኮፍያ አናነሳላቸው ዘንድ እንገደዳለን!! ብሎ ያጋራን Tesfaye Mamo ነው።

"በጥቂት ሀገራት የሚዘወረው የአለም አቀፍ ስርአት አብቅቷል" _የኢራኑ ፕሬዚዳንት ‎‎እንደ ኢራን እና ሩሲያ ባሉ ገለልተኛ ሀገራት መካከል ያለው ትብብር እንደሚቀጥልና የጥቂት ሀገራት የበላይ...
18/09/2025

"በጥቂት ሀገራት የሚዘወረው የአለም አቀፍ ስርአት አብቅቷል" _የኢራኑ ፕሬዚዳንት

‎እንደ ኢራን እና ሩሲያ ባሉ ገለልተኛ ሀገራት መካከል ያለው ትብብር እንደሚቀጥልና የጥቂት ሀገራት የበላይነት የሚዘወረዉ የአለም አቀፍ ስርአት ማብቃቱን የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን መናገራቸዉ ተሰማ ።

‎ፔዝሽኪያን ይህንን አስተያየት የሰጡት በቴህራን ከሩሲያ ኢነርጂ ሚኒስትር ሰርጌይ ፂቪሌቭ ጋር ካደረጉት ቆይታ በኋላ ነዉ።

‎ፔዝሽኪያን ከሲቪሌቭ ጋር ባደረጉት ውይይት በኢራን እና በሩሲያ መካከል ስላለው ትብብር ያላቸውን ተስፋ ገልፀው የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በፍጥነት ተግባራዊ ለማድረግም ተናግረዋል ።

‎የኢራን መሪ ታስኒም የዜና አገልግሎት እንደዘገበው ማሱድ ፔዝሽኪያን ሁለቱ ሀገራት ስምምነቶቻቸውን በተለይም በትራንስፖርት፣ በሃይል እና በሃይል ማመንጫ ዘርፎች ላይ ያላቸውን ቁርጠኝነት አጽንኦት ሰጥተዋል። ውጤቱን ከኤክስፐርቶች ስብሰባ ወደ ተግባር መቀየር አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው እነዚህን ግቦች ለማሳካት ሚኒስትሮች እና የቴክኒክ ቡድኖች ጥረት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

‎የኢራኑ ፕሬዝዳንት በኢራን እና በሩሲያ መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ልውውጦች የወዳጅነት ግንኙነታቸውን ሰፋ ያለ እድገት እንደሚያስገኙ ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል። ለሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሞቅ ያለ ሰላምታ እንዲሰጥ ሰርጌይ ፂቪሌቭ አሳስቧል።
‎.
‎በምላሹ ሰርጌይ ፂቪሌቭ የፑቲንን ሰላምታ አስተላልፈዉ እና በኢራን ውስጥ ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር ስለሁለትዮሽ ስምምነቶች አተገባበር በተለይም በጋራ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ጊዜ የተፈጠሩትን ጉዳዮች በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮችን አካፍለዋል።

‎ሩሲያ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በፍጥነት ለመተግበር ዝግጁ መሆኗን ገልፀው ምንም አይነት እንቅፋት፣ ጫና እና ማዕቀብ በሁለቱ ሀገራት የንግድ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ላይ ተጽዕኖ ሊያሳድር አይችልሕ ሲሉም አክለዋል።

‎በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና ቲያንጂን ከሻንጋይ የትብብር ድርጅት (ኤስ.ኦ.ኦ) ጉባኤ ጎን ለጎን ከፔዝሽኪያን ጋር መገናኘታቸዉን ያስታወሰዉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኤክስ ላይ ባወጣው መግለጫ “ፕሬዝዳንት ቭላድሚር #ፑቲን ከኤስ.ሲ.ኦ የመሪዎች ጉባኤ ጎን በተነጋገሩበት ወቅት ከፕሬዝዳንት ዶ/ር ፔዝሽኪያን ጋር ባደረጉት ንግግር፡ በተለይ የግንኙነታችንን ወዳጃዊ ባህሪ እና የሩስያ-ኢራንን ሁለገብ ግንኙነት ልዩ ባህሪ ማጉላት እፈልጋለሁ ብለዋል ሲል ያስነበበው ቴህራን ፖስት ነዉ ።

ሲሲ ከ1979 በኋላ እስራኤልን ለመጀመሪያ ጊዜ “ጠላት” ሀገር ናት ሲሉ ፈርጀዋል።እስራኤል በግብጽ ብሔራዊ ደህንነት ላይ አደጋ ደቅናለች ብለዋል ፕረዝደንት ሲሲ። የግብጹ መሪ ፍረጃ መነሻ እ...
18/09/2025

ሲሲ ከ1979 በኋላ እስራኤልን ለመጀመሪያ ጊዜ “ጠላት” ሀገር ናት ሲሉ ፈርጀዋል።

እስራኤል በግብጽ ብሔራዊ ደህንነት ላይ አደጋ ደቅናለች ብለዋል ፕረዝደንት ሲሲ።

የግብጹ መሪ ፍረጃ መነሻ እስራኤል የጋዛ ነዋሪዎችን በራፋ ድንበር በኩል ወደ ግብጽ ስናይ ሰርጥ ታባርራለች ከሚል ፍራቻ የመነጨ ነው ተብሏል።

ፕረዝዳንቱ ይህን ያሉት በሳምንቱ መጀመሪያ በተካሄደው በዶሃው ዓረብ - ሙስሊም ሀገራት ስብሰባ ማጠቃለያ መዝጊያ ንግግር ባደረጉበት ወቅት ነው።

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለኢትዮጵያ ወደብ ለመስጠት ተስማምተው እንደነበር ያውቃሉ?ጊዜው 2009 ዓ.ም ላይ ነው፡፡ የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ትኩረታቸው...
18/09/2025

ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለኢትዮጵያ ወደብ ለመስጠት ተስማምተው እንደነበር ያውቃሉ?

ጊዜው 2009 ዓ.ም ላይ ነው፡፡ የወቅቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ትኩረታቸውን የአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ያደረጉበት ጊዜ ነው፡፡ አቶ ሀይለማሪያም የፖለቲካ ጉዳዮች የመወሰን ስልጣናቸው በህወሓት አመራሮች የተገደበ እና የተነጠቀ ስለነበር በስልጣን ዘመናቸው ኢኮኖሚው ላይ አተኩረው መስራት እንደመረጡ ይነገራል፡፡ በዚህም የመለስን ሌጋሲ በማስቀጠል ረገድ በመጠኑ ተሳክቶላቸዋል ይባላል፡፡ በእንዲህ ሁኔታ ከፖለቲካዊ ጉዳዮች ይልቅ ኢኮኖሚው ላይ ያተኮሩት የውሃ ሳይንስ ሊቁ፤ ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት እንድትሆን እና ወደ ቀይ ባህር እንድትወጣ እንቅስቃሴ አድርገው ነበር፡፡

ሀይለማሪያም በቻይና መንግስት እገዛ ባደረጉት እንቅስቃሴ አገሪቱ የወደብ ባለቤት እነድትሆን ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በጓዳ ከስምምነት ደርሰውም ነበር፡፡ ፕሬዝዳንት ኢሳያሥ የጢዖ ወደብን ለኢትዮጵያ በመስጠት፤ በምትኩ ኢሕአዴግ ከሽንጠ ረጅሙ የሁመራ መሬት ለመረብ መላሽ ሰዎች የሁመራን መሬት ገምሶ ለመስጠት ተስምምተዋል፡፡ ይህ ስምምነት በሻቢያ እና ኢሕአዴግ መሀል እንዲደረግ የቻይና መንግሥት ትልቅ ሚና እንደተጫወተ የቤተመንግስት ሰነዶች ይጠቁማሉ፡፡ ሀይለማሪያም በስምምነቱ መሰረት ከስፍራው አንስቶ አዲስአበባ ድረስ የሚዘልቅ የባቡር ሀዲድ ለመዘርጋትም ወጥነው ነበር፡፡

ይሁንና ግን ይህ ስምምነት በፊርማ ሳይጸና እና ወደ ትግበራ ሳይገባ ከሽፏል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ በወቅቱ በኢትዮጵያ የነበረው ሕዝባዊ አመጽ እና የኢሕአዴግ የውስጥ ሽኩቻ በምክንያትነት ይጠቀሳል፡፡ ኢህአዴግ ሙሉ ትኩረቱን የውስጥ አመጾችን ለማፈን እና ስልጣኑን ለማዳን ራሱ ላይ ትኩረት በማድረጉ ያ ኢትዮጵያን ወደ ቀይ ባህር ሊመልስ የነበረው ስምምነት እንዲቋረጥ ሆኗል፡፡

ጥቂት ስለ ጢኦ ወደብ

ስለ ኢትጵያ ወደቦች ሲነሳ ስሟ ብዙ አይነገርም፡፡ ምናልባትም አሰብ ጉያ ስር የተሸጎጠች መሆኗ ስሟ እንዳይገን አድርጓት ይሆናል፡፡ ነገር ግን በደርግ ዘመነ መንግስት ሶስተኛዋ የአገሪቱ የወደብ ከተማ የነበረች ሚጢጢዬ ነገር ግን የቀይባህር ማጮለቂያ ናት፡፡ የምናወራው ከምጽዋ 360 ኪሎሜትር ከምትርቀው አሰብ ኪስ ውስጥ ስላለቺው ጢዖ ወደብ ነው፡፡

ጢኦ ከአሰብ አምስት አውራጃዎች አንዷ የነበረችና በቀይ ባህር ላይ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ናት፡፡ በብዙ አቅጣጫ ከአሰብ ጋር የተያያዘ ሕይወት ስላላት ስለ አሰብ አንስቶ ጢዖን መተው አይቻልም፡፡ በደርግ ዘመነ መንግስት ይህቺ ሚጢጢዬ የወደብ ከተማ እንደ ሶስተኛ የአገሪቱ ወደብ ትታይ ስለነበር፤ የወቅቱ የባህር ትራንስፖርት ባለስልጣን አካባቢውን ለማሳደግና ከተማዋንም ለማስፋፋት ወደቡን ለመገንባት ጥረት እንዳደረገ የታሪክ ሰነዶች ያመላክታሉ፡፡ የጀልባ መጠጊያው በተሻለ ሁኔታ ተሰርቶ መለስተኛ ጀልባዎች እንዲጠጉ አስችሏል፡፡

ከምጽዋ ወደብ 360 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን፤ ትግራይ በኩል ወደ አፋር በራሕለ ዳሎል በኩል 60 ኪሎሜትር ርቅት ላይ ትገኛለች፡፡

ለዚህ ትንታኔ የጀነራል ዩሐንስ ገብረመስቀልን "አዙሪት" መጽሐፍ እና የዩሐንስ ተፈራን አሰብ ቀይ ባህር እና ወደባችን በዚያን ጊዜ መጽሐፍ ተጠቅመናል።

Via andafta

በጸረ- ሙስና በተቀሰቀሰ ሕዝባዊ ተቃውሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥልጣን ለቀቁ የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር በሕዝባዊ ተቃውሞ ከሥልጣን መልቀቃቸውን ተከትሎ ፓርላማው በእሳት ነዷል።የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስ...
11/09/2025

በጸረ- ሙስና በተቀሰቀሰ ሕዝባዊ ተቃውሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥልጣን ለቀቁ

የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር በሕዝባዊ ተቃውሞ ከሥልጣን መልቀቃቸውን ተከትሎ ፓርላማው በእሳት ነዷል።

የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር ኬፒ ሻርማ ኦሊ በአገሪቱ በጸረ- ሙስና በተቀሰቀሰ ሕዝባዊ ተቃውሞ ሳቢያ በደረሰባቸው ጫና ከስልጣናቸው እንደተነሱ ቢቢሲ ነው የዘገበው።

በአስርት ዓመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ አለመረጋጋት እየተናወጠች ባለችው ኔፓል ተቃዋሚዎች በዋና መዲናዋ ካታማንዱ የሚገኘውን ፓርላማ እሳት ለኩሰውበታል።

በተጨማሪም በአገሪቱ የሚገኙ የመንግሥት ህንጻዎች እና የፖለቲካ አመራሮች መኖሪያ ቤቶች ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል።

በአገሪቱ ከተቀሰቀሰው የጸረ ሙስና ተቃውሞ ጋር ተያይዞ ከፖሊስ ጋር በነበረ ግጭት 19 ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎ በርካቶች ቁጣቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።

የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ በ2030 ዓለም አቀፍ የበረራ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተባለየቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ5 ዓመታት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ ዓለም አቀፍ የበረራ ...
11/09/2025

የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ በ2030 ዓለም አቀፍ የበረራ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተባለ

የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በ5 ዓመታት ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ ዓለም አቀፍ የበረራ አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር መታቀዱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው ገለጹ።

የአዲሱ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ሲጠናቀቅ የኢትዮጵያ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪን ትልቅ እመርታ ላይ የሚያደርስ መሆኑንም ነው አቶ መስፍን የ2018 የኢትዮጵያውያን አዲስ ዓመትን በማስመልከት ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ የተናገሩት።

አየር መንገዱ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን በማስፋፋትና አዳዲስ የበረራ መስመሮችን በመክፈት በከፍታ ላይ መሆኑን በመጥቀስ፤ በ2018 በጀት ዓመት የአዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን ለማስጀመር ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል።

ተነሺ አርሶ አደሮችን ወደ አዲስ ቦታ ለማዘዋወር የቤቶች ግንባታ እየተጠናቀቀ መሆኑን በመግለጽ፤ ለአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታም ፋይናንስ እያፈላለግን ነው ብለዋል።

ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያው እጅግ ዘመናዊ ተርሚናል ያለውና ከዓለም ታላላቅ አውሮፕላን ማረፊያዎች ተርታ እንደሚሰለፍ በመጥቀስ፤ አየር መንገዱን ከዓለም ስመ ገናናዎች አንዱ ያደርገዋል ብለዋል።

የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሥራ ሲጀምር የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕን ማረፊያም እጅግ ዘምኖ የሀገር ውስጥ በረራን በዓለም አቀፍ የአገልግሎት ደረጃ እንዲሰጥ እንደሚደረግ አስረድተዋል።

አዲሱ ዓመት ለመላው ኢትዮጵያውያን እንዲሁም ለአየር መንገዱ ደንበኞችና ሠራተኞች የደስታ፣ የፍቅርና የብልፅግና እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Adresse

Vienna

Webseite

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von WolloPedia erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Service Kontaktieren

Nachricht an WolloPedia senden:

Fördern

Teilen