WolloPedia

WolloPedia Organic Wollo

የአማራ ሊግ ውድድር በደሴ ከተማ ተጀመረ፣በታሪካዊቷ የደሴ ከተማ የሚካሄደው የ2018 ዓ.ም የአማራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር በይፋ ተጀምሯል። ከሚያዚያ 25 እስከ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ....
03/05/2026

የአማራ ሊግ ውድድር በደሴ ከተማ ተጀመረ፣

በታሪካዊቷ የደሴ ከተማ የሚካሄደው የ2018 ዓ.ም የአማራ ሊግ የእግር ኳስ ውድድር በይፋ ተጀምሯል። ከሚያዚያ 25 እስከ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ሳምንታት በሚቆየው በዚህ ክልላዊ መድረክ ላይ አስር ክለቦች በሁለት ምድብ ተከፍለው ብርቱ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

​ውድድሩ በክልሉ ያለውን የስፖርት እንቅስቃሴ ከማነቃቃት ባለፈ በፀጥታ ችግሮች ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ማህበራዊ ትስስር ዳግም ለማጠናከር ትልቅ ተስፋ ሰንቋል።

​የደሴ ከተማ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰይድ አራጋው ፤ ከተማ አስተዳደሩ ውድድሩ በሰላም ተጀምሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን የሜዳና የሎጂስቲክስ ዝግጅት በከፍተኛ ጥንቃቄ የተከናወነ ሲሆን፣ ውድድሩ ለደሴ ከተማ ልዩ ትርጉም እንዳለው የገለጹት ኃላፊው፣ በሂደቱ የሚገኘው ተሞክሮ በቀጣይ ከተማዋ ለምታስተናግዳቸው ክልላዊና አገር አቀፍ ስፖርታዊ ኩነቶች ልምድ የሚወሰድበት መሆኑን ጠቁመዋል።

​በአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ የስፖርት ማህበራት ስልጠናና ውድድር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሉሌ ፤ ባለፉት ዓመታት በክልሉ በነበረው የሰላም እጦት ምክንያት የስፖርቱ ዘርፍ ክፉኛ ተጎድቶ መቆየቱን አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ ይህ ውድድር ከሦስት ዓመታት መቋረጥ በኋላ ዳግም መጀመሩ ለተጫዋቾችና ለስፖርት ቤተሰቡ ትልቅ የምስራች መሆኑን ገልጸዋል።

​ዳይሬክተሩ አክለውም መሰል መድረኮች ተተኪ ስፖርተኞችን ለማፍራትና ብቁ ክለቦችን ለመገንባት ያላቸው ፋይዳ የጎላ መሆኑን በመጥቀስ፣ የክልሉ መንግስት ዘርፉን ለመደገፍ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

​በአጠቃላይ በክልሉ በሁለት ምድብ ተከፍለው ሲወዳደሩ ከቆዩ ሀያ ክለቦች መካከል የማጣሪያ ጨዋታዎች ተካሂደው "የአሸናፊዎች አሸናፊ" የሚለየው ክለብ ክልሉን በመወከል በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው ውድድር ላይ ተሳታፊ ይሆናል።

​ለዚህ ውድድር ዝግጅታቸውን ሲያደርጉ የቆዩ ተጫዋቾች በሰጡት አስተያየት፣ ውድድሩ ዳግም መጀመሩ የአካል ብቃትና የክህሎት ደረጃቸውን ለመለካት ዕድል ከመስጠቱም በላይ፣ በተለያዩ አካባቢዎች ከሚመጡ ስፖርተኞች ጋር የእርስ በርስ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።

ዘጋቢ:- ሰልሀዲን ሰይድ

ደሴ፣ ሚያዚያ 25/2018 ዓ.ም (አሚኮ ደሴ)

👉የድሬዳዋ ነዋሪ የነበሩት የልጅ እያሱ ልጅ በምስሉ ላይ የሚታዩት ልጅ ምኒልክ ይባላሉ። ልጅ ምኒልክ - የልጅ እያሱ ልጅ ሲሆኑ ለአፄ ምኒልክ ደግሞ የልጅ ልጅ ልጅ ናቸው። እናታቸው ፋጡማ መ...
02/05/2026

👉የድሬዳዋ ነዋሪ የነበሩት የልጅ እያሱ ልጅ

በምስሉ ላይ የሚታዩት ልጅ ምኒልክ ይባላሉ። ልጅ ምኒልክ - የልጅ እያሱ ልጅ ሲሆኑ ለአፄ ምኒልክ ደግሞ የልጅ ልጅ ልጅ ናቸው።

እናታቸው ፋጡማ መሐመድ አቡበከር ባሻ ይባሉ ነበረ። የፋጡማ አባት አቡበከር መሐመድ የታጁራ ሱልጣኔት የ"ነጋድራስ መሀመድ" ልጅ ሲሆኑ ይኸም በዘር ሀረጋቸው በዘይላ ሀሶባ ውስጥ ካለው የአፋር ኦባካርቶ የሚመዘዝ ያደርገዋል።

ልጅ ምኒልክ በአፄ ኃይለ ሥላሴ የሥልጣን ዘመን ብዙውን ዕድሜያቸው የቁም እስረኛ ሆነው ነው ያሳለፉት። ድሬዳዋ ውስጥ የመኖሪያ ቤታቸው ድልጮራ ሆስፒታል አካባቢ ነበር።
✍️Jemal abdulaziz

👉Calvert Advert ደግሞ ይህን ትውስታውን አካፍሎናል 👇👇👇

ምኒልክ እያሱ ድሬዳዋ ከዚራ ወደ
ኮካኮላ መታጠፊያ ጫፍ ላይ ያለ አሁን ደሳለኝ ካፌ እና ፋርማሲ የሆነው (ጊቢው ለሁለት ተከፍሎ) ማለት ነው ምኒልክ እያሱ ያረፉትም በ80ዎቹ መጀመሪያ ላይ ይመስለኛል።

ልጅ እያሱ አንድ ሐኪም መርፌ ሲወጋቸው አረፉ ሲባል ወሬው በሰፊው ሲወራ ልጆች ሆነን እሰማ ነበር።

የምማርበት ከቤታቸው ፊት ለፊት ከዚራ ት/ቤት ስለነበረ ልጅ ልጃቸው በእናቷ የአረብ ዝርያ ያላት አንድ በቅርብ የማውቀው ተስቲ(ደስታ) ማለት ነው በአማርኛ እሱን በ90ዎቹ ላይ አግብታ ለገሃሬ አካባቢ መኖሯን ትዝ ይለኛል።

01/05/2026


"የተፈጥሮ ድንቅ ውበት - የአልቡኮ ጎሴ ሜዳ!

በደቡብ ወሎ ዞን አልቡኮ ወረዳ የሚገኘው የጎሴ ሜዳ ልዩ የተፈጥሮ ውበት፣ ማራኪ አረንጓዴ ገጽታ እና መንፈስን የሚያድስ አየር ያለው ድንቅ ቦታ ነው።

ተፈጥሮን ለሚወድና አእምሮውን ማዝናናት ለሚፈልግ ሰው ሁሉ ፍጹም ምርጫ ነው። ይህንን ውብ ስፍራ አይታችሁታል? ካልጎበኛችሁት ሊያመልጣችሁ የማይገባ የምድራችን ጸጋ ነው! 🇪🇹

#አልቡኮ #ጎሴሜዳ

ህገ ወጥ ታሪፍ ለመጠቆም የስልክ አድራሻወች ከዚህ በታች ተቀምጠዋልህገ ወጥ  ታሪፍ ጭማሪን ለመከላከልና የተጓዦችን መብት ለማስጠበቅ ህብረተሰቡ ከትራንስፖርት ታሪፍ ጋር የተያያዙ ህገወጥ ድር...
01/05/2026

ህገ ወጥ ታሪፍ ለመጠቆም የስልክ አድራሻወች ከዚህ በታች ተቀምጠዋል

ህገ ወጥ ታሪፍ ጭማሪን ለመከላከልና የተጓዦችን መብት ለማስጠበቅ ህብረተሰቡ ከትራንስፖርት ታሪፍ ጋር የተያያዙ ህገወጥ ድርጊቶችን ለመከላከልበስልክ ጥቆማእንዲያቀርብ የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ወንጀል መከላከል ምክትልመምሪያ የመንግድ ትራፊክ ደህንነት ዋና ክፍል ሃላፊ ዋ/ኢ/ር ከተማው ታደሰ ገልጿል።

ህብረተሰቡ በየአካባቢው የሚፈጸሙ ህገወጥ የታሪፍ ጭማሪዎችን፣ የተሳፋሪዎች እንግልትን እና ሌሎች ከመጓጓዣ አገልግሎት ጋር የተያያዙ ችግሮችን ህጋዊ ሥርዓት እንዲከበር የድርሻውን እንዲወጣ ተጠይቋል። ማህበረስቡ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ስልኮች ጥቆማ እንዲስጥ ተጠቁሟል።

➥መምሪያ
📞0973033596
📞0914715565
📞0914057274
📞0910964989

➥1ኛ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ 📞0914710725
➥2ኛ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ 📞0911366770
➥3ኛ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ 📞0920770227
➥4ኛ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ 📞0931623410
➥5ኛ ዋና ፖሊሰ ጣቢያ 📞0914604929

➥የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ መረጃ ፡- 033-111-7748
‎➲ 1ኛ ጣቢያ 033 111 11 07
‎➲ 2ኛ ጣቢያ 033 111 16 01
‎➲ 3ኛ ጣቢያ 033 111 10 11
‎➲ 4ኛ ጣቢያ 033 111 51 19
‎➲ 5ኛ ጣቢያ 033 312 36 69

በእነዚህ ቁጥሮች በመደዉል መረጃ እና ጥቆማ መሠጠት ይቻላሉ።

የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ወንጀል መከላከል ምክትል መምሪያ የመንግድ ትራፊክ ደህንነት ዋና ክፍልየሚቀርቡ ጥቆማዎች በሚስጥር እንደሚያዙ እና በተሰጠው መረጃ መሰረት ፈጣን የቁጥጥርና የህግ እርምጃ እንደሚወሰድ ገልጿል።

(ደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያህዝብ ግንኙነት)
ደሴ _ማያዚያ 23/2018ዓ,ም

ሜ/ጄነራል ሁሴን አህመድበቀድሞ አጠራር ወሎ ጠቅላይ ግዛት ፣ ደሴ ዙሪያ ፣ ከድጆ ውስጥ ምጣን ጎራ በተባለች መንደር የካቲት 21 ቀን 1930 ዓ/ም ተወለዱ :: ሜጀር ጄኔራል ሁሴን አህመድ ...
30/04/2026

ሜ/ጄነራል ሁሴን አህመድ

በቀድሞ አጠራር ወሎ ጠቅላይ ግዛት ፣ ደሴ ዙሪያ ፣ ከድጆ ውስጥ ምጣን ጎራ በተባለች መንደር የካቲት 21 ቀን 1930 ዓ/ም ተወለዱ :: ሜጀር ጄኔራል ሁሴን አህመድ ገና በልጅነታቸው አባታቸው አቶ አህመድ አሊ ከድጆን ለቅቀው ደሴ ከተማ በመግባታቸው ህጻኑ ሁሴን የከተማ ልጅ ለመሆን በቁ ፡፡ ደሴ እንደገቡ የፊደል ትምህርታቸውን ጨርሰው ማንበብ እንዳጠናቀቁ አባታቸው የእስልምና ትምህርት እንዲማሩ አደረጓቸው፡፡

የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በንጉሥ ሚካኤል ትምህርት ቤት እና በወይዘሮ ስህን ትምህርት ቤት ተምረው የፀኛ ከፍል መልቀቂያ ፈተና በማለፉቸው በ1946 ዓ/ም አዲስ አበባ በሚገኘው የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ገቡ፡፡ በወቅቱ ተፈሪ መኮንን ከየክፍለ ሀገሩ ጎበዝ ተማሪዎችን ሰብስበው ያስተምሩ ነበር፡፡ ተማሪው ሁሴን 2ኛ ደረጃ ትምህርቱን ማጠናቀቂያ ዓመት ላይ (በ1949 ዓ/ም) ተማሪዎች አመጽ በማስነሳታቸው በአመጽ ተጠርጥሮ ወደ ሐረር መድኃኒዓለም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተዛውሮ እንደጨረሰ ታሪኩ ይላል::

ተማሪው ሁሴን የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በማለፍ በወርሃ መስከረም 1950 ዓ/ም ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በሚባል ከሚታወቀው ኮሌጅ በመግባት ትምህርታቸውን መከታተል ጀመሩ፡፡ በዚያው ዓመት የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት መገባደጃ ላይ በሀገሪቱ ላይ አዲስ ነገር ተከፈተ፤ የኢትዮጵያ ጦር አካዳሚ፡፡ የኢትዮጵያ ጦር አካዳሚ ከሁሉም ትምህርት ቤቶች ብቁ ተማሪዎችን መልምሎ ማሰልጠን ይፈልግ ነበር፡፡ ተማሪው ሁሴን ከመጀመሪያዎቹ 40 የኢትዮጵያ ጦር አካዳሚ ትምህርት ቤት ተማሪዎች አንዱ በመሆን የኢትዮጵያ ጦር አካዳሚን ተቀላቀለ፡፡

ለውትድርና የሚያበቃውን ስልጠና በሚገባ አጠናቅቀው መስከረም 21 ቀን 1953 ዓ/ም አፄ ኃይለሥላሴ በተገኙበት የምክትል መቶ አለቅና እና የሁለተኛ ዓመት የኮሌጅ ዲፕሎማ በማግኘት ኩራት በፊት ለሀገርና ለንጉሠ ነገሥት በሚል የመሐላ ቃል ተመረቁ፡፡ ጥቅምት ወር 1953 ዓ/ም በሆለታ ገነት ጦር ትምህርት ቤት በአሰልጣኝነት የተመደቡት ሁሴን አህመድ ከሦስት ዓመታት ሥራ በኋላ ጀምረውት የነበረውን የሁለት ዓመት የኮሌጅ ትምህርት ለመቀጠል አዲስ አበባ ኮሌጅ በመግባት በሕዝብ አስተዳደር ዘርፍ በቢኤ ዲግሪ ተመረቁ፡፡

በወርሃ መስከረም 1958 ዓ/ም በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ትዕዛዝ ለተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ወታደራዊ የሰላም ተቆጣጣሪ ልዑክ አባል በመሆን ኰንጎ፣ ጋዛና ፓኪስታን በመሄድ ለስድስት ወራት የቆዩ የሰላም ጥበቃ ግዳጃቸውን ተወጥተዋል፡፡ ወደ ሀገራቸው እንደተመለሱ የሆለታ ገነት ጦር ትምህርት ቤት የአሰልጣኝነት ሥራቸውን ቀጠሉ፡፡ በዓመቱ ጰጉሜ 1959 ዓ/ም የሻምበልነት ማዕረግ ደረሱ፡፡ በ 1960 ዓ/ም የምድር ጦር ጠቅላይ መምሪያ መኮንኖች አስተዳደር ቢሮ በመመደባቸው ወደ አዲስ አበባ ገቡ፡፡

በወርሃ ታኅሣሥ 1967 ዓ/ም ለከፍተኛ መኮንንነት የአስተዳደር ትምህርት ለመማር ወደ አሜሪካ በመቅናት የሌተናል ኮሎኔልነት ማዕረግ ተቀበሉ፡፡ ሚያዝያ 1969 ዓ/ም የሶማሊያ ወረራ ወቅት የሚሊሻ ብርጌድ አዛዥ በመሆን እናት ሀገርን ታድገዋል፡፡ የሶማሊያ ጦርነት ገና ሳይጠናቀቅ በሰሜን የሀገራችን ክፍል ሕወሓት እና ሻዕቢያ የመገንጠል ጥያቄ ይዘው ተነሱ፡፡ እኒህ የጦር መኮንን በሐምሌ ወር 1969 ዓ/ም ለወታደራዊ ግዳጅ ብርጌድ ጦር ይዘው በአውሮፕላን ኤርትራ ገቡ፡፡ ከሐምሌ 1969 ዓ/ም እስከ 1983 ዓ/ ም ድረስ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ የኤርትራ የሁለተኛው አብዮታዊ ሠራዊት የጦር አዛዥ በመሆን እናት ሀገራቸውን ጠብቀዋል፡፡ የሜጀር ጄኔራልነት ማዕረግ ያገኙትም ኤርትራ በረሃ ውስጥ ነው::

የጦር መኮንኑ በኤርትራ ውስጥ በነበሩበት ዘመን በብዙ ኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን ለአብነትም:-

የግንቦት 8 1981 ዓ/ም ተሞክሮ በከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት የሁለተኛ አብዮታዊ ሰራዊት ዋና አዛዥ የነበሩት የሜጀር ጄኔራል ደምሴ ቡልቶ መገደል ተከትሎ ኤርትራ የነበረውን ግዙፍና ጠንካራውን ሁለነ ዋና አዛዥነት እስከ ግንቦት 1983 ዓ/ም መርተዋል፡፡

በ1973 ዓ/ም በጥቅምት ወር የውቃው ዕዝ የ506ኛው ግብረ ኃይል ምክትል አዛዥ በመሆን በሱዳን ጠረፍ በአልጌና እና ቃሮራ በኩል የነበረውን ግዳጅ በአግባቡ ተወጥተዋል፡፡

በመጨረሻም ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ/ም ማከሰኞ ዕለት መንግሥቱ ኃይለማርያም መኮብለላቸውን ሌ/ጄኔራል አዲስ ተድላ ለሜጀር ጄኔራል ሁሴን አህመድ ይነግሯቸዋል፡፡ ደጀን የሚሆን ጦር ከአብ ለማጓጓዝ እጅግ አስቸጋሪ በመሆኑ የኤርትራ ጉዳይ ማከተሙን ይገነዘባሉ፡፡ ሻዕቢያ አስመራን ለመያዝ ተቃርቧል፤ ሕወሓት በወሎ ወለጋ ብሎ እምብርት ገብቷል፡፡ የጦር መኮንኑ ራሳቸውን ማትረፍ እንዳለባቸው ወሰኑ፡፡ በሱዳን በኩል ለመውጣት አስበው የሱዳን መንግሥት እጃቸውን ይዞ ለሻዕቢያ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው የተረዱት የጦር መኮንኑ ግንቦት 15 ቀን 1983 ዓ/ም ጉዟቸውን ወደ የመን አድርገው በሳዑዲ አረቢያ ለአራት ዓመታት ከቆዩ በኋላ ኑሯቸውን በሀገረ አሜሪካ አድርገዋል፡፡

ጀግናው የጦር መኮንን ወይዘሮ በለጡ ምህረትነን ጥቅምት 17 ቀን 1960 ዓ/ም አግብተው ሦስት ልጆችን ወልደዋል፡፡ ሜጀር ጄኔራል ሁሴን አህመድ በ1997 ዓ/ም ፅናት በተከታይም እራት የተሰኙ መጽሐፍ ጽፈው ለንባብ አብቅተዋል፡፡ መጽሐፉቸው ብዙ ቁምነገር የያዘ በመሆኑ በተገኘበት ታድኖ ይነበብ፡፡ ከታሪክ ማህደር

የቦረና አውራጃ አፍለኞች በ/ቦ/ከ/ት"""""""""""""""''''''""''"'"''''''''"""""""'"'''''''''''ከቀለም ጋር ግብግብ ገጥመን ትኩስና የአፍላነት ዘመናችንን ያሳለፍ...
12/03/2026

የቦረና አውራጃ አፍለኞች በ/ቦ/ከ/ት
"""""""""""""""''''''""''"'"''''''''"""""""'"'''''''''''
ከቀለም ጋር ግብግብ ገጥመን ትኩስና የአፍላነት ዘመናችንን ያሳለፍንበት ብዙዎች ነን ። በዘመኑ እዚያ ተምረን ከተንጠባጠብነው በስተቀር የአያሌ ግምቱ ምህራን መፍለቂያነቱን በተጨባጭ ያስመሰከረ አንጋፋና ታዋቂ ነው ። ቦረና ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህር ቤት ። ቦ/ ከ / ት !!

የቦረና ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በትምህርት ፣ በህክምና ፣ በግብርና ፣ በኢኮኖሚ ፣ በህግ ፣ በፍልስፍና ፣ በጥበብ ፣ በፖለቲካውና በሌሎችም ዘርፎች ጫፍ የነኩ ዕወቅ ምህራንን የሰራ በስስት የምንመለከተው አንድ ለእናቱ የእውቀት አድባራችን ነበረ ።

ከ4ቱም ወረዳዎች በመሰባሰብ በፍልቅልቋ መካነሰላም ከተማ ሃይስኩል ላይ ጣፋጭ የትምህርት ጊዚያችሁን ያሳለፋችሁ ሁሉ በያላችሁበት ሰላምታየ ይድረስልኝ ብያለሁ ።

የህይወት እጣ ፈንታችን ሆነና ከተለያየን ዘመናትን ያስከነዳን ቢሆንም በቦረና ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያሳለፍነው አይረሴ የአፍላነት ዘመን ትዝታ አብሯችሁ እንደሚገኝ ግን አምናለሁ ።

" ነገርን _ ነገር ያነሳዋል እንድሉ " ዛሬ ቦረና ወረዳ መካነሰላም ከተማ መጥቼ የሃይስኩል ትዝታዬ እንደገና ተቀሰቀሰብኝና በዚያ ዘመን ስሜት ላይ ሆኘ ይሄን ፃፍኩኝ ።

በትዝታ ፈረስ በናፍቆት ባቡር
መጣሁ ስገሰግስ ቦረና ምድር ።
እንደት ነው ቦረና ዙሪያ ገመገሙ
የነሸግየ አገር የነአይጠገቡ ።

በል ! በል ! በል ! በል አለኝ ።......

እናም ጥቂት ጓደኞቸን በትዝታ ባቡር አሳፍሬ ወደ ሃይስኩል ዘመናችን ስጥም ብየ ገባሁ ። ወደዚያ ጣፋጭ ጊዜ ። ወደዚያ ወደ ገናናው ቦረና አውራጃ ትምህርት ቤት ነጎድኩኝ ።

የኛ ትዝታ በአብዛኛው ከዚያ ይጀምራል ። ትዝታችን የቀድሞውን ከአሁኑ ጋር የሚያስተያይ የዘመን መደላድልና የሁኔታ ነፀብራቅ ነው ። የፍቅር ፣ የመተሳሰብ ፣ የአንድነትና የጋራ የዘመን ላይ ድልድይ !!

እኛ ማለትም ----- ሰለሞን ፣ በለጠ ፣ ብርሃኑ ፣ ተስፋዬ ፣ ጌታቸው ፣ ዘበናይ፣ ገለታ ፣ አማረች ፣ ዋጋየ ፣ አለሙና መሐመድ በአንድ ሌማት የበላን ፣ በአንድ ኩራዝ ያጠናን ፣ የአንድ ሃይስኩል እና የአንድ ጀመዓ ቅምጥሎች ነን ።

አስተሳሰባችንም - አመለካከታችንም አንድ የነበረ በአካልና በመንፈስ የተዋሃድን ሽቅርቅሮች እኛ ነን ።

ውበት ፣ ቁንጅና ፣ ለዛ ፣ ዝነጣ ፣ ጀግንነት ፣ እኛ ላይ ብቻ የተፈጠረ እስኪመስለን ድረስ የምንጠራራ የቦረና ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አፍለኞች ነበርን ኮ ።

ያይኔ አበባነሽን የዘመርን ፣ እሸት በላሁኝን ያቀነቀንን፣ የፊክሽን መጽሃፍ በጉያችን ይዘን የዞርን ፣ ከስመመን - የአቤልን ፣
ከፍቅር እስከ መቃብር የሰብለን - ገጸ ባህሪ ለመላበስ የምንፍጨረጨር ፣ እንደ ጉዱ ካሳም የሚቃጣን ልበ ተራሮች ነበርን ።

እስካርቭ ከአንገታችን የማይጠፋ ፣ በአለባበስ ፣ በአረማመድ ፣ በአነጋገር ፣ ልክ እንደ ቲቸር አረጋ ለመሸለል ነጠር - ነጠር የሚያደርገን የመካነሰላም ወላፈኖች ነበርን ።

አንዳንዶቻችንም በተለየ ሁኔታ ትምህርት አቀባበል ፣ ጨዋታ አዋቂነትና ፀባየ ሸጋነት መለያችን የሆነ_ መረብ ኳስ ፣ ቅርጫት ኳስ ፣ እግር ኳስ ፣ ቴንስ ሲሉን ጨርቃችንን ጥለን የምናብድ ስፖርት አምላኩና ጆላዮችም ነበርን ።

የትምህርት አይነቱን ሁላ በእኩል የሚያስተናግዱ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ፣ የኋላ ኋላም ሁሉን ነገር እርግፍ አድርገው ትተው ወደ ሃይማኖት የገቡና በዘርፉ ሊቅ የሆኑ ምርጦችም አሉን ።

በጥበብ ዘርፍም ጥግ ድረስ እንደሚደርሱ ምልክት የሚታይባቸው ጀለሶችም ነበሩን ። እውነትም ታዲያ ዛሬ በየመድረኩ የነገሱ ፣ በዝናና በገንዘብ የናጠጡ እንደፈርጥ አንፀባራቂ ሰወችም ሆነዋል ።

የህይወትን ጥሪ ተቀብለው በአሁኑ ሰዓት በአውሮፓ ፣ በአሜሪካና በአረብ አገሮች ውስጥ ኑሯቸውን ያደረጉም ለሽ ናቸው ።

እኛም በመንደራችን ውስጥ ሆነን ይሄን fb ላይ እንቸከችካለን ።

ሰለሞን ግን እስካሁን አልተለየኝም ። ሁሌም ሰሌ እያልኩነው የምጠራው ። በጨዋታችን መሃል የሃይስኩል ትዝታችንን መለስ እያልን እንቃኘዋለን ።

ሰሌ ይሄን ትዝታ እጅግ ይወደዋል ። ያጣጥመዋል ። የዛሬውን ከትናንቱ ጋር እያወሃደ ዘመንን የሚመለከትበት የህይወት ኮምፓሱ አድርጎታል ።

" ሰሌ የአንተን ነገር ወፍ ትልቀመው " ብየ ትዝታችንን ሳነሳበት ፈገግ ማለት ይጀምራል ። ጨዋታ አዋቂ፣ መልከ ቀናና ፣ ለዛ ያለው ልጅ ነው ። አንድ ቀን ግን የነካውን እንጃ የአንድ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ጉድ አድርጎን ያውቃል ።

የሶየ ልጆች የኔን ከንፈር ወዳጂ በክፉ አዩብኝ በሚል አጉል ቅናት ሀጋ ለይተን በሽመል እንድንቀራደድ ፈርዶብናል ። ይሄን ሳነሳበት ከልቡ ይንከተከትና

" አይይይይ..... ፈንቲ የስራሽን ይስጥሽ ። " ይላል ።

ፈንቲ ይማም ሁሌም ተበችሳ በሆነ ቁጥር " ሸጌ የዱላው ለት " የሚለውን የልጃገረዶች ግጥም በዜማ የምታቀነቅንለት የከንፈር ወዳጁ ነች ። ግጥሙ ለሱ ብቻ የተፃፈ ይመስለዋል ።
" አባይ ወድህ ማዶ ቦረና ነው ቤቴ
ማተብና ድንብል ላክልኝ በሞቴ ማተቡም ይቅርብኝ ድንብሉም ይቅርብኝ
ሸጌ የዱላው ለት እንዳትቀርብኝ
ሸጌ የዱላው ለት የቀረህ እንደሆን
እንኳን ከንፈር ወዳጀ ጎረቤትም አንሆን

ትልና ......
" አይኑን በቀጫጭን የተኳኳለው
ጥርሱን ጉራማይሌ የተዋቀረው
ሰለሞን ተሰማ ይላሙ ያለው ። "

የሚለውን ትጨምርለታለች ።

ይሄን - ይሄን ሳስታውሰው ሰሌ የሚሆነውን ያጣል ። " አሁን ሁሉንም ነገር እያነሳህ አደባባይ ባታሰጣው ምን አለ ? " ይለኛል ።

" ሰው የሰራው በጎም ይሁን - ክፉ ነገር የህይወቱ አንድ ክፍል ሆኖ ታሪክ ይመዘገብለታል ። እናም ከሃይስኩል ታሪክህ ትንሽ ቀነጨብኩ ። " እለዋለሁ ።

" ተው - ተው ጋሽቲ ሸጋ ሸጋውን ክተብ " ይልና

ቦረና በተነሳ ቁጥር የሚያሳየውን ደማቅ ፈገግታ ይጨምርበታል ።

እኛ እንደዚህ ነን ። በዘመን እየተሸመን ፣ በጋራ እየተገመድን ፣ እዚህ የደረስን የቅብብሎሽ ልቃቂቶች ። የዚያ ዘመን የቦረና አውራጃ አፍለኞች እኛ እንደዚህ ነን !!
አበቃ !!
ጋሻው መኮንን
ከመካነሰላም ፒያሳ

የደሴ ከተማ ዘመን ተሻጋሪ ብርሃናማ ከዋክብት ...⭐️🌟💫ታይታኒክ በተሰኜው ዝነኛ ፊልም ላይ "ጃክ" የሚባለው ዋና ገፅ ባህሪ እንዲህ የሚል ቃለ ተውኔት አለው "I like the night. ...
05/03/2026

የደሴ ከተማ ዘመን ተሻጋሪ ብርሃናማ ከዋክብት ...⭐️🌟💫
ታይታኒክ በተሰኜው ዝነኛ ፊልም ላይ "ጃክ" የሚባለው ዋና ገፅ ባህሪ እንዲህ የሚል ቃለ ተውኔት አለው "I like the night. Without the dark, we'd never see the stars." በእርግጥም ጨለማ ከሌለ ከዋክብትን በፍፁም አናያቸውም። አስፈሪው ጨለማ አቅም የሚያጣው ውብ እና ብርሃን የሚተፉ ከዋክብት በሰማዩ ላይ ሲፈሱ ብቻ ነው። ልዩነቱ በደሴ ከተማ ሰማዩ ብቻ ሳይሆን ምድሩም በርካታ ከዋክብትን አፍርቷል። እድለኛዋ ደሴ ከተማ በዬዘመናቱ ከሰማይ ብቻ ሳይሆን ከምድርም ከዋክብትን ትታደላለች። ደሴ የማይነጥፍባት የብርሃን ምንጭ ናት። ጊዜ እንደፈቀደ ለዛሬ የአንዱን ብርሃናማ የደሴ ከተማ ኮከብ እንቃኝ።
ወይዘሮ አሰለፈች ካሣ ዘወትር ወደ ደሴ መድኃኒያለም እየሄዱ ልጅ እንዲሰጣቸው በድኃኒያለምን ይለምናሉ። 'ልጅ ከሰጠኸኝ አገልጋይህ ይሆናል" በማለት ተስለውም ነበር። የአቶ ገበየሁ እሰየም ፀሎት ልጅ ነው። እግዚአብሔር ፀሎታቸውን ሰምቶ በ1932ዓ.ም ሜጠሮ በሚባለው ሰፈር ወንድ ልጅ ሰጣቸው። ይህ ልጅ አድጎ ሊቀ ጳጳስ ይሆናል ብሎ ማን አሰበ ? ህፃኑ በቀዝቃዛው የደሴ ሰማይ ከጦሳ ተራራ ስር እየቦረቀ አደገ። እድሜው ለትምህርት ሲደርስ እናቱ ወደተሳለችው ደብር ወደ ደሴ መድኃኔዓለም የኔታ ክፍሌ ( አባ ክፍለ ማርያም) ዘንድ ላከቺው። ፊደል መቁጠር ጀመረ።
ይህ ሰው በሀገር ውስጥ ከ8 ከዳማትና አድባራት በላይ ተዟዙረው የተማሩ፣ በብጹዕ አቡነ ቴዎፍሎስ አመካኝነት ወደ ግሪክ ተልከው "በደሴተ ፍጥሞ" ለሁለት ዓመት መንፈሳዊ ትምህርት ተምረው ዲፕሎማ የተመረቁ፣ ከአቴንስ ዩኒቨርስቲ በሥነ መለኮት የማስትሬት ዲግሪ የተቀበሉ፣ ከስዊዘርላንድ ፍሪበሪን ዩኒቨርሲቲ በፈረንሳይኛ ቋንቋ የተመረቁ፣ በኢየሩሳሌም ደብረ ጽዮን የግሪክ መንፈሳዊ ኮሌጅ ውስጥ በመግባት በአረብኛ ቋንቋ ትምህር የተመረቁ፣ አምስት አይነት የውጭ ቋንቋዎችን አቀላጥፈው የሚናገሩ ... የደሴው ልጅ ብጹዕ አቡነ ጎርጎሪዮስ ናቸው።
አባታችን "የቤተ ክርስቲያን ታሪክ" ተብሎ በታተመው እና ቀድመው ባዘጋጁት መፅሐፍ ላይ ስለ ልጅነታቸው ሲያወሱ "እንደማንኛውም የደሴ ልጅ ቦርከና ዋኝቻለሁ፣ የጦሳን ገደል እሩጨበታለሁ፣ ፈረንጅ አምባ ስራገጥ በመዋሌ በጉማሬ ተገርፊያለሁ (ፈረንጅ አምባ ፒያሳ ነው)፣ አሬራ ሄጄ ሀጋምና ቀጋ ለቅሚያለሁ፣ ስልካምባ ሄጀ በስልክ አውርቻለሁ፣ አልቅሼ ስቂያለሁ ... ብቻ በአጭሩ የደሴ ትዝታ ከልብ በቀላሉ የሚወጣ አይደለም" በማለት ልጅነታቸውን አስታውሰዋል።
የሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ በነበራቸው ጊዜ በርካታ ሥራዎችን በመስራት ለትውልድ መሰረት መጣል የቻሉ አባት ናቸው፡፡ የወንጌልና የታሪክ ብርሃንን በተለይ በወጣቱ ሕይወት ላይ የፈነጠቁት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ሐምሌ 22/1982 ዓ.ም ወደ መቂ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለአገልግሎት ሲሄዱ በድንገተኛ የመኪና አደጋ በተወለዱ በሃምሳ ዓመታቸው ሕይወታቸውን ያጡ እንቁ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባት እና በደሴ ከተማ ሰማይ ያበሩ ኮከብ ናቸው።
@ሜላት ሰሎሞን የመነን ልጅ

የጥቁር ሕዝቦች አኩሪ ድል! የአሸናፊነት ማዕዘን፤ አድዋእንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በአል አደረሳችሁ
02/03/2026

የጥቁር ሕዝቦች አኩሪ ድል! የአሸናፊነት ማዕዘን፤ አድዋ

እንኳን ለ130ኛው የአድዋ ድል በአል አደረሳችሁ

28/02/2026
I've just reached 50K followers! Thank you for continuing support. I could never have made it without each one of you. 🙏...
27/02/2026

I've just reached 50K followers! Thank you for continuing support. I could never have made it without each one of you. 🙏🤗🎉

Adresse

Vienna

Webseite

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von WolloPedia erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Service Kontaktieren

Nachricht an WolloPedia senden:

Teilen