Wadila-Delanta Media

Wadila-Delanta Media Standing for our people

የአንድ መንግስት ዋና ዋና ሃላፊነቶች!1. የህዝብ ደህንነት መጠበቅ - የዜጎችን ሕይወት፣ ንብረትና መብት ከውስጣዊና ውጫዊ አደጋዎች መጠበቅ።2. ህግን ማስከበር - ፍትሃዊ ህጎችን ማውጣትና ...
04/06/2026

የአንድ መንግስት ዋና ዋና ሃላፊነቶች!

1. የህዝብ ደህንነት መጠበቅ - የዜጎችን ሕይወት፣ ንብረትና መብት ከውስጣዊና ውጫዊ አደጋዎች መጠበቅ።

2. ህግን ማስከበር - ፍትሃዊ ህጎችን ማውጣትና ተግባራዊ ማድረግ፣ የፍርድ ስርዓትን ማስከበር።

3. መሠረታዊ አገልግሎቶችን መስጠት - እንደ ትምህርት፣ ጤና፣ ውሃ፣ ኤሌክትሪክ፣ መጓጓዣ እና መገናኛ ያሉ አገልግሎቶች።

4. ኢኮኖሚን ማስተዳደር - የሀገርን ኢኮኖሚ ማረጋጋት፣ ሥራ መፍጠር፣ የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ ኢንቨስትመንትን ማበረታታት።

5. ማህበራዊ ፍትህ ማስከበር - ሀብትን ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ማከፋፈል፣ ድህነትን መቀነስ፣ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ማድረግ።

6. አካባቢን መጠበቅ - የተፈጥሮ ሃብትን ማስጠበቅ፣ ብክለትን መቆጣጠር፣ ዘላቂ ልማት ማስፈን።

7. ዓለም አቀፍ ግንኙነት - ከሌሎች ሀገራት ጋር ቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መፍጠርና ማስጠበቅ።

8. የህዝብ ጤና መከላከል – ወረርሽኞችን መከላከል፣ የምግብ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የመድሀኒት አቅርቦት ማስተዳደር እና የህዝብ ጤና ፖሊሲዎችን መተግበር።

9. የመሠረተ ልማት ግንባታ – መንገዶች፣ ድልድዮች፣ ባቡር መስመሮች፣ ኤርፖርቶች፣ ወደቦች እና የውኃ ማጠራቀሚያዎች መገንባትና ጥገና።

10. የጋዜጠኝነት ነፃነትና የመረጃ ፍሰት – መረጃ ማግኘት መብትን ማስከበር፣ ጋዜጠኞችን መጠበቅ፣ ብሔራዊ ደህንነትን ሳያበላሹ ነፃ የመገናኛ ሚዲያ መፍቀድ።

11. የማህበረሰብ አንድነት መጠበቅ – ብሔርተኝነትን፣ ሃይማኖታዊ ጥላቻን እና ሌሎች ማህበራዊ ክፍፍሎችን መከላከል፣ ሰላማዊ አብሮነት ማስፈን።

12. የሸማች መብት ጥበቃ – ግልጽ ያልሆኑ የንግድ ልምዶችን መከላከል፣ የምርት ደህንነት ደረጃዎችን ማስከበር፣ ዋጋ መጨመርን መቆጣጠር።

"የፋኖ አደረጃጀትን ተጠቅመን፣ የአማራ ክልልን ተበቅለናል" - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የጽንፈኛው ህወሓት አንጃ ቡድን መሪ የሆኑት ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ሰሞኑን በነበራቸው ውይይት በትግርኛ ...
04/06/2026

"የፋኖ አደረጃጀትን ተጠቅመን፣ የአማራ ክልልን ተበቅለናል" - ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል

የጽንፈኛው ህወሓት አንጃ ቡድን መሪ የሆኑት ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ሰሞኑን በነበራቸው ውይይት በትግርኛ ቋንቋ የተናገሩት !

ክልሉን በኢኮኖሚ ለማዳከምና ደካማ ክልል ለማድረግ ፋኖን መጠቀም ትክክለኛ አማራጭ መሆኑን የተናገሩት ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የፋኖን አደረጃጀት እንደፈለግን የምናዝዘው፣ ተልዕኮ የምንሰጠው እኛ ነን ሲሉም ተደምጠዋል።

#ጽንፈኝነት #አጥፊ #ነው!!

🐘 የአፍሪካ ዝሆን – የምድር ግዙፉ ግን ብልሁ ፍጥረትየአፍሪካ ዝሆን በምድር ላይ ከሚገኙ የመሬት እንስሳት ሁሉ ትልቁ ነው። በመጀመሪያ ሲታይ በግዙፍ አካሉ ምክንያት አስፈሪ ሊመስል ይችላል፤...
04/06/2026

🐘 የአፍሪካ ዝሆን – የምድር ግዙፉ ግን ብልሁ ፍጥረት

የአፍሪካ ዝሆን በምድር ላይ ከሚገኙ የመሬት እንስሳት ሁሉ ትልቁ ነው። በመጀመሪያ ሲታይ በግዙፍ አካሉ ምክንያት አስፈሪ ሊመስል ይችላል፤ ነገር ግን ከጥንካሬው በላይ የሚያስደንቀው ብልህነቱ ነው። አንድ ወንድ ዝሆን እስከ 7 ቶን ሊመዝን እና እስከ 4 ሜትር ሊረዝም ይችላል። ይህ ከብዙ መኪናዎች ክብደት የሚበልጥ መጠን ነው።

ዝሆኖች እጅግ የተሻለ የማስታወስ ችሎታ አላቸው። ከብዙ ዓመታት በኋላም የውሃ ምንጮችን፣ የጉዞ መንገዶችን እና የቤተሰባቸውን አባላት ማስታወስ ይችላሉ። ሳይንቲስቶች ዝሆኖች ሀዘን፣ ደስታ፣ ፍቅር እና ርህራሄ እንደሚሰማቸው ያምናሉ። አንዳንድ ጊዜ የሞቱ ዝሆኖችን አጥንት እየነኩ እንደሚያስታውሷቸውም ተስተውሏል።

ከሁሉም በላይ የሚያስደንቀው ግንዳቸው ነው። ይህ ልዩ አካል ከ40,000 በላይ ጡንቻዎችን ይይዛል። በእርሱ መተንፈስ፣ መጠጣት፣ ማሽተት፣ ከባድ ነገሮችን ማንሳት እና ትንሽ ነገሮችን እንኳን በጥንቃቄ ማንሳት ይችላሉ። በተጨማሪም ትልልቅ ጆሮዎቻቸው ለመስማት ብቻ ሳይሆን ሰውነታቸውን ከሙቀት ለማቀዝቀዝ ይረዷቸዋል።

የአፍሪካ ዝሆኖች በጠንካራ ቤተሰባዊ ትስስር ይኖራሉ። መንጋውን ብዙውን ጊዜ በዕድሜ የገፋች ሴት ዝሆን ትመራለች። ወጣቶቹን ይከባከባሉ፣ ለታመሙ አባላት ይረዳሉ፣ አደጋ ሲመጣም አንድ ላይ ቆመው ይከላከላሉ። ይህ ትብብር ዝሆኖች ለሰዎችም ብዙ የሚያስተምሩ ፍጥረታት እንዲሆኑ አድርጓቸዋል።

ዝሆኖች ለተፈጥሮም ታላቅ ጥቅም አላቸው። ዘሮችን በየቦታው በመበተን አዳዲስ ዛፎች እንዲያድጉ ያደርጋሉ፣ ውሃ ለማግኘት ጉድጓድ በመቆፈርም ሌሎች እንስሳት ውሃ እንዲያገኙ ይረዳሉ። በዚህ ምክንያት ብዙ ሳይንቲስቶች “የሥነ-ምህዳር መሐንዲሶች” ብለው ይጠሯቸዋል።

ከሁሉም አስገራሚው እውነታ ደግሞ የእርግዝና ጊዜያቸው 22 ወራት መሆኑ ነው። ይህ በምድር ላይ ከሚገኙ የየብስ እንስሳት ሁሉ ረጅሙ የእርግዝና ጊዜ ነው። የአፍሪካ ዝሆን በግዙፍ አካሉ ብቻ ሳይሆን በብልህነቱ፣ በቤተሰባዊ ፍቅሩ እና ለተፈጥሮ በሚያበረክተው አስፈላጊ ሚና ከዓለም እጅግ አስደናቂ ፍጥረታት አንዱ ሆኖ ይቆያል። 🐘✨

03/06/2026
➾ይሄ መረጃ የውሸት ፕሮፓጋንዳ ሊመስላችሁ ይችላል። መረጃው ግን በፍፁም ውሸት አይደለም‼በአርሲ በተደጋጋሚ በንፁሃን የኦርቶዶክስ አማኞች ላይ በሸኔ ታጣቂዎች ጥቃት ሲደርስባቸው ዘመነ ካሴ እ...
03/06/2026

➾ይሄ መረጃ የውሸት ፕሮፓጋንዳ ሊመስላችሁ ይችላል።
መረጃው ግን በፍፁም ውሸት አይደለም‼

በአርሲ በተደጋጋሚ በንፁሃን የኦርቶዶክስ አማኞች ላይ በሸኔ ታጣቂዎች ጥቃት ሲደርስባቸው ዘመነ ካሴ እኮ ትንፍሽ ብሎ አያውቅም ።

ሸኔ እና ፋኖ የአማራና ኦሮሚያ ክልል አዋሳኞች ላይ በጋራ ነው የሚሰሩት።

እነዚህ ሁለት ፅንፈኛ ሀይሎች እንግዲህ በአማራ ህዝብ ስም እና በኦሮሞ ህዝብ ስም እየታገሉ ኑሯቸውን የሚያስቀጥሉ ቡድኖች ናቸው።

የአማራው ፋኖ እንደ ህዝብ Implicitly ጠላት የሚያደርገው የኦሮሞን ሲሆን የኦሮሞው ሸኔ ደግሞ የአማራን ህዝብ ነው። ይህን የሚያደርጉት እንታገልለታለን ለሚሉት ህዝብ አስበው ሳይሆን ራሳቸውን የሚያደልቡትና የሚያስቀጥሉት በዚህ መልኩ ስለሆነ ነው።

ሁለቱ ሀይሎች ለምሳሌ በምስራቅ ወለጋ ጊዳ ኪረሙ እና በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ላይ በጋራ መከላከያ ሰራዊትን ይዋጋሉ። በጋራ ይንቀሳቀሳሉ በጋራ ይሰፍራሉ። ይሄንን መረጃ እዚያ አካባቢ የሚኖር የትኛውንም ሰው ጠይቆ ማጣራት ይቻላል።

በዘመነ ካሴ የሚመራ ፋኖ በጃል መሮ ከሚመራው ኦነግ ጋር ከፍተኛ ቅንጅት አላቸው።

ሸኔና ፋኖ ድንበር ለድንበር ቢውሉም አብረው ይንቀሳቀሳሉ እንጅ አንድም ቀን እርስበርሳቸው ተዋግተው አያውቁም።
በመሀል ሲያስፈልጋቸው የሴራ እርምጃ ያቅዱና ከኦሮሞውም ከአማራውም ገድለው ነገሩን ያጦዙታል።
ለነርሱ ግድያ ፖለቲካ ነው ። ቢዝነስ ነው! ንፁሀን በብሔር ተኮር ግድያ ሲያልቁ እነርሱ ጋር እልልታ ነው። አጀንዳ ተገኘ ማለት ነው። ገንዘብ ማሰባሰቢያ ፤ ፖለቲካ ማጧጧፊያ ካርድ ተገኘ ማለት ነው።

በዚህ መሀል ሁለቱ ህዝቦች ይጠላላሉ ለደም ይፈላለጋሉ ። ያ ለነርሱ ትልቅ ስኬት ነው። ሁለቱ ህዝቦች ከተዋሀዱ ህልውናቸው ስለሚያበቃ። በማን ይቀሰቅሳሉ?!

እናም መሬት ላይ ያለው ተጨባጭ ሀቅ ይሄ ነው። አሁን ይሄንን የሁለቱም ፅንፈኛ ቡድኖች ሲያስተባብሉት ታዩታላችሁ። ፍላጎታቸው እውነት ስላልሆነ። እውነት ቢሆን ፍላጎታቸው " ይሄ ነገር እውነት ይሆን እንዴ እስኪ እናጣራ" ብለው ቆም ብለው ይጠይቁ ነበር።

ከሁለቱም ወገን ያለው መሀይምነትን ከገዳይነት የቀላቀለና የቀየጠ ትግል ታዲያ ሀገራችንን የደም አላባ እያደረጋት ይገኛል።

  !!!በተለይ በድሀ ወላጆችህ!!!1. በድሃ ወላጆችህ አትፈርአንተ ለማሳደግ ነው ሁሉንም ነገር ያጡት!2. በድሃ ጓደኞችህ አትፈር፦የአእምሮ ድሃ እንጂ የገንዘብ ሰርቶ ይቀየራል!3. በአሮጌ ...
02/06/2026

!!!
በተለይ በድሀ ወላጆችህ!!!

1. በድሃ ወላጆችህ አትፈር
አንተ ለማሳደግ ነው ሁሉንም ነገር ያጡት!

2. በድሃ ጓደኞችህ አትፈር፦
የአእምሮ ድሃ እንጂ የገንዘብ ሰርቶ ይቀየራል!

3. በአሮጌ ልብሶችህ አትፈር
ፋሽን ማሳደድ፣ የሐብት መገለጫ አይደለም!

4. ቀለል ባለ አኗኗርህ አትፈር
ብዙዎች በጭንቀት የሚኖሩት ማቅለል
ስላልቻሉ ነው!

5. ለሕልምህ ስለምትለፋ አትፈር
ብዙ ሰው የሚንገላታው የሚታገልለት ሕልም አጥቶ ነው።

መጽሐፍ

"የጎጃም ፋኖዎች የኦርቶዶክስ እምነት ለማጥፋት እየሰሩ ነዉ" ጋዜጠኛ ኤሊያስ ደባሱ ***************የቀድሞው የጽንፈኛው ቡድን አባል የነበረው አሁን ላይ ለሰላም እጅ የሰጠው ጋዜጠኛ ...
02/06/2026

"የጎጃም ፋኖዎች የኦርቶዶክስ እምነት ለማጥፋት እየሰሩ ነዉ" ጋዜጠኛ ኤሊያስ ደባሱ
***************
የቀድሞው የጽንፈኛው ቡድን አባል የነበረው አሁን ላይ ለሰላም እጅ የሰጠው ጋዜጠኛ ኤልያስ ፣ በጎጃም የሚንቀሳቀሱ የፋኖ አመራሮች የኦርቶዶክስ ዕምነትን ለመከፋፈልና ለማጥፋት ቆርጠው መነሳታቸውን ይፋ አድርጓል ፡፡
በዚህም አስረስ የቅባት ዕምነት ተከታይ ፣ ዘመነ ደግሞ የዓለም ብርሃን የተባለ የኦርቶዶክስ ክፋይ ተከታይ እንደሆኑና ሌላም ሞዓ ተዋህዶ እያሉ ዋናውን የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ሃይማኖትን ሊበርዙ ውስጥ ለውስጥ እየሰሩ እንደሆነ ማረጋጫ ሰጥቷል ።

በእምነት ምክኒያት በዘመነ እና አስረስ መካከል ልዩነት ተስፋፍቶ ከስሩ ያሉት ታጣቂዎች ለሁለት ጎራ ተከፋፍለዉ በጎሪት እየተያዩ እንደሚገኙ አረጋግጧል፡፡

" ይቺም ሻማና ነብስ ይማር ሰልችቶናል!" 😥(ሀዉለት አህመድ እንደጻፉት)==============="በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃ...
02/06/2026

" ይቺም ሻማና ነብስ ይማር ሰልችቶናል!" 😥

(ሀዉለት አህመድ እንደጻፉት)
===============

"በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃላይ ሳናይ የምንሞተው ነገር የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ''ኃላፊነቴን በአግባቡ ስላልተወጣሁ ሥራዬን በፈቃዴ ለቅቄያለሁ፤ ከ'ኔ የተሻለ ሰው ይምራው'' የሚለው ነው።

በአርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና አማኞች እና አብያተ-ክርስትያናት ላይ በተደጋጋሚ ጥቃቶች እየተሰነዘሩ ብዙ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ሞተ፤ አብያተ-ክርስትያናት እና ቅርሶችም ወደሙ፤ በነዋሪዎቹ ዘንድ ሥጋትና ጥርጣሬ ሰፈነ።

ይሄን ተደጋጋሚ ጥቃት ለማስቀረት የተሠራ ሥራ አለ? ሰላም ማስከበር 100% የክልሉ መንግሥት ሥራ አይደለም እንዴ? ምን አድርጓል? ሰላም ማስከበር ካቃታቸው በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ''አልቻልንም፤ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ ይግባልን'' ይባላል እኮ! መቼም ''እኔ ለዚህ ኃላፊነት ብቁ ሆኜ አልተገኘሁም፤ የተሻለ ብስለትና ልምድ ያለው ሰው ይተካኝ'' የሚሉ ኃላፊዎችን በሕይወት እያለን እንደማናይ ዕሙን ነው።

ሰው ባለቀ ቁጥር ይቺን ሻማ ብልጭ ማድረግ ምን ፋይዳ አለው? ይሰለቻል። የክልሉ መንግሥት ለዚህ ዞን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሕዝቡን ይጠብቅ። በጊዜ መፍትሔ ካልተሰጠው የዚህ ዳፋ የማይተርፈው ሰው የለም።

እንደ አንድ ተራ ዜጋ በደረሰው ጉዳት ሐዘኔን ለመግለጽ እወዳለሁ።"

የፍጥረት ሁለት ገጽታዎች፦ የሥርዓተ-ጾታ ሕግ The Law of Genderበአጽናፈ ዓለማዊ ትምህርት Universal Education ውስጥ ካሉት ሰባቱ ታላላቅ ሕግጋት መካከል የመጨረሻውና እጅ...
01/06/2026

የፍጥረት ሁለት ገጽታዎች፦ የሥርዓተ-ጾታ ሕግ The Law of Gender

በአጽናፈ ዓለማዊ ትምህርት Universal Education ውስጥ ካሉት ሰባቱ ታላላቅ ሕግጋት መካከል የመጨረሻውና እጅግ ረቂቁ የሥርዓተ ጾታ ሕግ ነው። ይህ ሕግ ሲነገር ወዲያውኑ ወደ አእምሯችን የሚመጣው ወንድና ሴት የሚለው ባዮሎጂካዊ ልዩነት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በአጽናፈ ዓለማዊ እይታ ጾታ Gender ማለት ከሥጋዊ ማንነት በላይ የሆነ፣ በሁሉም የሕይወት ዘርፎች ውስጥ የሚገኝ የፈጣሪነት እና የምርት መሠረት ነው።

ሕጉ እንዲህ ይላል፤ በሁሉም ነገር ውስጥ የሥርዓተ ጾታ መርህ አለ፤ ሁሉም ነገር ተባዕታይ Masculine እና አንስታይ Feminine ገጽታዎች አሉት። እነዚህ ሁለት ኃይሎች ካልተገናኙ በስተቀር ምንም ዓይነት አዲስ ነገር ሊፈጠር፣ ሊመረት ወይም ሊወለድ አይችልም።

ይህንን ሕግ በተለያዩ የሳይንስና የሕይወት ዘርፎች ውስጥ እናገኘዋለን። በፊዚክስና ኬሚስትሪ ውስጥ በአቶም ውስጥ ያሉት ፕሮቶን Positive እና ኤሌክትሮን Negative ኃይሎች የዚህ መርህ ምሳሌ ናቸው። እነዚህ ሁለት ተቃራኒ ኃይሎች ባይኖሩ ኖሮ ቁስ አካል ሊገነባ አይችልም ነበር። ማግኔት እንኳ የሚሠራው በሁለት ተቃራኒ ዋልታዎች መኖር ነው።

በተፈጥሮም ይህንን ሕግ እናያለን። አንድ ዘር መሬት ውስጥ ሳይገባ እና መሬቷ ዘሩን ተቀብላ ሳታሳድገው ተክል ሊበቅል አይችልም። ዘሩ ብቻውን ውጤት የለውም፤ መሬቷም ያለ ዘር ፍሬ አታፈራም።

በሰው ልጅ አእምሮ ውስጥም ተመሳሳይ መርህ ይሠራል። ንቃተ ህሊናችን Conscious Mind እንደ ተባዕታይ ኃይል ሆኖ ሃሳብንና ፍላጎትን ይዘራል። ድብቅ አእምሯችን Subconscious Mind ደግሞ እንደ አንስታይ ኃይል ሆኖ ያንን ሃሳብ ተቀብሎ ያሳድገዋል፣ ወደ ውጤትም ይለውጠዋል።

ተባዕታይ ኃይል Masculine Energy የድርጊት፣ የሎጂክ፣ የፈቃድ እና የጥበቃ ኃይል ነው። ወደ ውጭ የሚወጣ ኃይል ሲሆን ዓላማን ለመምታትና ነገሮችን ለመቀየር ይሠራል። አንስታይ ኃይል Feminine Energy ደግሞ የፈጠራ፣ የተቀባይነት፣ የፍቅር እና የውስጣዊ ጥበብ Intuition ኃይል ነው። ወደ ውስጥ የሚመለከት ኃይል ሲሆን ነገሮችን የማለስለስና የማሳደግ ኃላፊነት አለበት።

ከዚህ የሥርዓተ ጾታ ሕግ የምንማረው ትልቁ አጽናፈ ዓለማዊ ትምህርት ሚዛን Balance እንደሚያስፈልግ ነው። ትልቁ ስኬት የሚገኘው በእነዚህ ሁለት ኃይሎች መካከል ሚዛን ሲኖር ነው። አንድ ሰው በተባዕታይ ኃይሉ ብቻ የሚመራ ከሆነ ሕይወቱ በውጥረትና በጭንቀት ሊሞላ ይችላል። በአንስታይ ኃይሉ ብቻ የሚመራ ከሆነ ደግሞ ሃሳቡን ወደ ተግባር ለመለወጥ ሊቸገር ይችላል።

ሕይወትህ ፍሬያማ እንዲሆን ከፈለግህ ሃሳብህን በድፍረት ዝራ፣ ነገር ግን እንዲበስል ትዕግሥትና እንክብካቤ ስጠው። በሎጂክ አስብ፣ ነገር ግን የውስጥህን ስሜትና ጥበብ አትዘንጋ።

ይህ ሕግ የመብሰያ ጊዜ Gestation Period እንዳለም ያስተምረናል። አንድ ዘር ከተዘራ በኋላ ለመብቀል ጊዜ እንደሚወስድ ሁሉ፣ ያንተም ትልልቅ ሕልሞች ወደ እውነታ ለመለወጥ ጊዜ ያስፈልጋቸዋል። ዛሬ ላይ ሆነህ ውጤቱ ካልታየህ፣ ሕጉ በውስጥህ እያመረተ መሆኑን አውቀህ በጽናት ጠብቅ።

አንተ በውስጥህ እነዚህን ሁለት ታላላቅ የፍጥረት ኃይሎች የያዝክ ሙሉ ፍጥረት ነህ። ሚዛንህን ስትጠብቅ፣ ሕይወትህ እንደ ውብ የአትክልት ስፍራ ያብባል።

ቤት ሲቃጠል 😂አለቃ ገብረሐና ኪንታሮት አሟቸው ናበጋ ጊዮርጊስ ተኝተው ሳሉ በዛን ወቅት በጋለ ብረት እጢም ሆነ እባጭ ማቃጠል (መተኮስ) የተለመደ ነበር። የቄያቸው ብልህ ገበሬ የአለቃ ገብረ...
01/06/2026

ቤት ሲቃጠል 😂

አለቃ ገብረሐና ኪንታሮት አሟቸው ናበጋ ጊዮርጊስ ተኝተው ሳሉ በዛን ወቅት በጋለ ብረት እጢም ሆነ እባጭ ማቃጠል (መተኮስ) የተለመደ ነበር። የቄያቸው ብልህ ገበሬ የአለቃ ገብረሐናን ኪንታሮት ሲያቃጥል፤ አለቃ ገብረሐና በድንገት ያመልጣቸዋል። ይህ ብልህ ገበሬ "ምነው አለቃ?" ቢላቸው፤ ምነው ጃል "ቤት ሲቃጠል ጓዝ አይወጣም" ብለው መለሱለት።😂😂

Adresse

Vienna

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Wadila-Delanta Media erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Teilen