Wadila-Delanta Media

Wadila-Delanta Media Standing for our people

የሻቢያ አሽከር የሆነው ህወሃት በአጣብቅኝ ውስጥ ገብቷልመቀሌ የሚገኙ  ታጣቂዎች ዓመፅ አስነስተዋል።በመቀሌ ከጥቅማ ጥቅም ጋር ተያይዞ ተቃዎሞ ያነሱ የ TDF ታጣቂዎች መንገድ መዝጋት ጀምረዋ...
13/10/2025

የሻቢያ አሽከር የሆነው ህወሃት በአጣብቅኝ ውስጥ ገብቷል

መቀሌ የሚገኙ ታጣቂዎች ዓመፅ አስነስተዋል።በመቀሌ ከጥቅማ ጥቅም ጋር ተያይዞ ተቃዎሞ ያነሱ የ TDF ታጣቂዎች መንገድ መዝጋት ጀምረዋል። በዚህ ሰዓት ከኩሀ ወደ መቀሌ መንገድ ዝግ መሆኑን ምንጮቻችን ጠቁመዋል።

የሃውልቲ የነ መንጆሪኖ ቢሮዎችን ከባዋል ፣ መንገዶችን ዘግተዋል። ሻዕቢያዎቹ የነ ስብሃት ቤተሰቦች ለጥቅማቸው ለ50 ዓመታት እንደፈለጉ ከአካል እስከ ነፍስ ሲያስገብሯቸው የነበሩ ወጣት ታጣቂዎች ዛሬ "በቃ" በሚል አምርረው ወጥተዋል።

የህውሃት ሻዕቢያ አገዛዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ከኢትዮጵያ ምድር መወገድ አለበት።

ታላቋ የሊቃውንት ምድር፣ የታሪክ ማህደር ፣ የቅርስ መገኛ የነጃ ቅ/ሚካኤል  ፣ የአመዴ ዋሻ፣  የክፍሌ ዋሻ የፃርቃኔ ዋሻ መገኛ፣ የማእድኗ አገር፣ የአፕሏ  አገር ፣ የመቻቻልና የአብሮነት ...
10/10/2025

ታላቋ የሊቃውንት ምድር፣ የታሪክ ማህደር ፣ የቅርስ መገኛ የነጃ ቅ/ሚካኤል ፣ የአመዴ ዋሻ፣ የክፍሌ ዋሻ
የፃርቃኔ ዋሻ መገኛ፣ የማእድኗ አገር፣ የአፕሏ አገር ፣ የመቻቻልና የአብሮነት ከተማዋ ዋድላ ወረዳ ከዘራፊው ቡድን ነጻ ወጥታለች!

#ክብር ለሀገር ሠከላከያ ሰራዊታችን !
#ክብር ለጥምር ጸጥታ ሀይሎቻችን!

  30 የፋኖ አባላት ተረ*ሸኑ! ፋኖ ከገረገራና ላስታ አከባቢዎች ያንቀሳቀሰው ታጣቂ ጋሸና ለመያዝ ቢሞክርም የገጠመው ሃይል የሚቻል ባለመሆኑ በፍጥነት ወደ ኋላ ተመልሶ ልዩ ስሙ  #ድብኮ ከ...
09/10/2025



30 የፋኖ አባላት ተረ*ሸኑ!

ፋኖ ከገረገራና ላስታ አከባቢዎች ያንቀሳቀሰው ታጣቂ ጋሸና ለመያዝ ቢሞክርም የገጠመው ሃይል የሚቻል ባለመሆኑ በፍጥነት ወደ ኋላ ተመልሶ ልዩ ስሙ #ድብኮ ከተባለ ስፍራ በምሽት ሲደርሱ በዚሁ ስፍራ ከበላይ አለቃ የመጣ ትዕዛዝ ነው በሚል ከ150 በላይ ፋኖዎች ውስጥ 30 የሚሆኑት ግምገማ በሚል ሰበብ በጓዶቻቸው ፊት መረ*ሸና*ቸው የውስጥ አዋቂ መረጃዎች አድርሰውናል።

በወቅታዊ  የሰላም ጉዳይ የጋራ ዉይይት ተደረገ።መስከረም:-29/2018ዓ.ም          ጋሸና!!በሰሜን ወሎ ዞን የጋሸና ከተማ አስተዳደር ከደጋማ ወረዳዎች ከጠቅላላ አመራር እና ሚኒ ካቢኔ...
09/10/2025

በወቅታዊ የሰላም ጉዳይ የጋራ ዉይይት ተደረገ።

መስከረም:-29/2018ዓ.ም
ጋሸና!!

በሰሜን ወሎ ዞን የጋሸና ከተማ አስተዳደር ከደጋማ ወረዳዎች ከጠቅላላ አመራር እና ሚኒ ካቢኔ ጋር የጋራ የዉይይት መድረክ በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ውይይት ተካሒዷል።
የሃገር መከላከያ ሰራዊታችን ዞናችን የገጠመውን የፀጥ ችግር ለመቀልበስ በፅንፈኛ ሐይሉ ላይ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ በማጠናከር ከመከላከያ ሰራዊታችን እና ጥምር ጦሩ ጎን በመሰለፍ ይበልጥ የዞናችን እና ወረዳዎቻችን ሰላም በማረጋገጥ ወደ ልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎቻችን መመለስ አለብን በሚል ውይይቱ ተካሒዷል።

ዉይይቱንም የጋሸና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ፀጋ ዉቤ፣የጋዞ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሃብቴ ካሰዉ፣የዳዉንት ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ አያሌዉ እና የግዳን ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አማኑኤል አያሌዉ በጋራ በመሆን መርተዉታል።

08/10/2025

አማራ ሆነህ የጠላት/የሻቢያና tplf ተላላኪ እንደመሆን ውርደት የለም!!!!

ሰበር የድል ዜና ‼️ በምስሉ ላይ የሚታዩት ሰሜን ወሎ ዋድላ ሀሙሲት ቀበሌ ገቢ የተደረጉ የህውሐት ታጣቂዎች ናቸው።
07/10/2025

ሰበር የድል ዜና ‼️

በምስሉ ላይ የሚታዩት ሰሜን ወሎ ዋድላ ሀሙሲት ቀበሌ ገቢ የተደረጉ የህውሐት ታጣቂዎች ናቸው።

07/10/2025

"ሞኝ ቤቱ ሲቃጠል አብሮ ያጨበጭባል"

ከህወሀት እና ሻዕቢያ ጋር ወዳጅ ለሆነው ፋኖ ካጨበጨብክ "ሞኝ" ነህ ማለት ነው !!!!

የፋኖ የጭካኔ ጥግ 😭😭የፀረ ሰላም ሃይሉ ጃውሳ ለጆሮ የሚከብድ ጥቃት በመካነሰላም በሚገኝ በአንድ መስጂድ ላይ ፈፅሟል። በዚህም በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በመካነሰላም በሚገኝ ሃጅ ንስሩ ...
04/10/2025

የፋኖ የጭካኔ ጥግ 😭😭

የፀረ ሰላም ሃይሉ ጃውሳ ለጆሮ የሚከብድ ጥቃት በመካነሰላም በሚገኝ በአንድ መስጂድ ላይ ፈፅሟል።

በዚህም በደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በመካነሰላም በሚገኝ ሃጅ ንስሩ መስጂድ ላይ በፈፀመው ጥቃት በርካታ ሼሆችን እና የሃይማኖቱ ተከዮችን በግፍ ጨፍጭፏል።

በጥቃቱ ህይወታቸውን ካጡት መካከል የመስጂዱ ኢማም የሆኑት ሼህ ጀማል ከማል፣ የመስጂዱ ጥበቃ ሼህ ይማም እና ሌሎች ሁለት የመስጂዱ አገልጋዮች ይገኛል። እጅግ ልብ የሚሰብረው የመስጂዱ ኢማም የተገደሉት በኢሻ ሰላት ላይ አዛን ሲያሰሙ በነበረ ሰዓት መሆኑ ነው። እንግዲህ ቡድኑ መስጂድ ውስጥ በሃይል መግባቱ ሳያንሰው ውስጥ ገብቶ የተከበሩ የሃይማኖት አባቶችን በግፍ ጨፍጭፏል ማለት ነው። ታዲያ ይህ ከአልሸ,ባብ፣ አልቃይዳ እና ከመሳሰሉት የሽብር ቡድኖች በምን ይለያል?

ነው
#ፋኖ ፀረ_ህዝብ_ነው

አንበሳ ጫካ ውስጥ አንድ ህፃን ልጅ ያገኛል። ህፃኑንም ይዞ ዋሻ ውስጥ ያስቀምጠውና የሚበላውን እያበላ ያሳድገዋል። አንበሳው ለአደን የሚወጡትን ሁሉ እየገደለ ጦራቸውን እየያዘ ወደ ዋሻው ያከ...
03/10/2025

አንበሳ ጫካ ውስጥ አንድ ህፃን ልጅ ያገኛል። ህፃኑንም ይዞ ዋሻ ውስጥ ያስቀምጠውና የሚበላውን እያበላ ያሳድገዋል። አንበሳው ለአደን የሚወጡትን ሁሉ እየገደለ ጦራቸውን እየያዘ ወደ ዋሻው ያከማቻል። በዚህ ሁኔታ ልጁም አድጎ ትልቅ ሆነ።
ጎረምሳውም ያሳደገውን አንበሳ "እባክህ ፍቀድልኝና መሰሎቼን አግኝቼ ተጫውቼ ልምጣ " ብሎ ጠየቀው። አንበሳውም "እሺ ሂድ ግን እባክህ እንዳታማኝ ፣ ስለኔ ምንም መጥፎ ነገር አትናገር" ብሎ ሸኘው።
ጎረምሳውም ሄደ ከመሰሎቹ ጋር ተገናኘ። መሰሎቹ ስለ አንበሳው ብዙ መረጃ ለመጠየቅ ቢሞክሩም ምንም ሳይነግራቸው ቀረ። ነገር ግን ሰዎቹ በጣም ጨቀጨቁት ያን ጊዜ እንዲህ አላቸው።

"አንበሳው መልካም አሳዳጊ ነው ነገር ግን አብረን ስንተኛ ብብቱ ይሸታል ማታ ማታ ፌንጣ ይበላል ከዛ በተረፈ ማለፊያ ነው።" አላቸው።
አንበሳው ተደብቆት መጥቶ ስለነበር ወጣቱ ልጅ ያለውን በሙሉ ሰምቶ እጅግ አዝኖ ወደ ዋሻው ሄደ። ልጁም ወደ ዋሻው እንደተመለሰ

"ልጄ ከነዚህ ጦሮች ውስጥ ጠንካራውን ምረጥና በደንብ አድርገህ ውጋኝ " አለው።

ልጁም ፍፁም እንደማይችልና እንደሚወደው ገለፀለት። አንበሳው ግን " በሰው ፊት አምተኸኛልና እባክህ ጦሩን አንስተህ ውጋኝ ያንን የማታደርግ ከሆነ ግን እንደማትወደኝ ነው የማረጋግጠው " አለው።
ልጁም ጠንካራውን ጦር አነሳና በሃይል ወጋው ። ጦሩ ሙሉ በሙሉ በአንበሳው ሰውነት ውስጥ ተሰነቀረ። አንበሳውም "ንቀለው" አለው። ልጁም ነቀለለት።
እናም አንበሳው እንዲህ አለ። "ልጄ እኔ ከልጅነትህ ጀምሮ ብዙ ዋጋ ከፍዬ እያደንኩ አሳድጌሃለሁ። አንተ ደግሞ በተራህ አሁን ታስታምመኛለህ " አለው።
ልጁም በተካነበት የአደን ስልት በሬውንም ፣ ጎሹንም እያደነ እያመጣ አንበሳውን መቀለብ ጀመረ። አንበሳውም ወደ ቀድሞ ጤንነቱ ተመለሰ። ሙሉ ለሙሉ ከተሻለው በኋላ ልጁን እንዲህ አለው።
" ልጄ ጦሩ የገባበት ቦታ ቁስል እንዳለ እስኪ ተመልከት" አለው።
ልጁም ቢፈልግ ፣ ቢፈልግ ቁስል የሚባል ነገር አጣ።
ያን ጊዜ አንበሳ "አየህ ልጄ በጦር የወጋኸኝ ድኗል በምላስህ ያቆሰልከኝ ግን እስካሁን አልዳነም" አለው። ይባላል።

ቁስልም ይድናል የምላስ በትር ግን በመድሃኒትና በምግብ ሊድን አይችልምና ለምንናገረው ነገር ሃላፊነት እንውሰድ።

እዚሁ መንደር አግኝተነው አስተማሪ ሆኖ ስላገኘነው አጋራናችሁ።

~ አንፖል ተቃጠለ ተብሎ ቤት አይቀየርም !!አበቦች ሲፈኩ እንደሚደርቁ ያውቃሉ ።ግን እደርቃለሁ ብለው ሳይፈኩ አይቀሩም።ሰውም ሟች ነው ግን ሟች ነኝ ብሎ መተው የለበትም ።ሁሉም ሰው በየመስ...
03/10/2025

~ አንፖል ተቃጠለ ተብሎ ቤት አይቀየርም !!

አበቦች ሲፈኩ እንደሚደርቁ ያውቃሉ ።ግን እደርቃለሁ ብለው ሳይፈኩ አይቀሩም።ሰውም ሟች ነው ግን ሟች ነኝ ብሎ መተው የለበትም ።ሁሉም ሰው በየመስኩ ያብብ ወዳጀ ሆይ ይች አለም ትልቅ ደመራ ናት አንተ በደመራው ስር ያለህ ችቦ ነክ አንተ ስትጠፋ የደመራው ብርሀን ይጠፋል።የቻልከውን ያክል ብራ አንተ ከነገሮች በላይ ነህ.በነገሮች አትረበሽ አየህ አንፖል ተቃጠለ ተብሎ ቤት አይቀርም። አንፖል ተቃጥሏል ብሎ ቤት የሚቀይር ሞኝ ነው አንተም አንዱ የህይወቴ ጉዳይ አልተሳካም ብለህ እራስህን አታጥፋ ይልቁንስ አንፖልህን ቀይረው ችግርህን ተጋፈጠው ጭንቀትህን አስጨንቀው ።ካህሊል ጀብራል እንዲህ ይላል ህይወት ልክ እንደ ክራር ጨዋታ ነው ።
አጨዋወቱን ያወቀ ጥሩ ሙዚቃ ይሰማል ያላወቀ ደግሞ ዝብርቅርቅ ጩኸቱን ለመስማት ይገደዳል።
አሁንም እልሀለው ህይወት በደመ ነፍስ አትሄድም ስልቷን እወቀው ። በህይወትህ ትላንት ያለፈውን የህይወት ታሪክህን መቀየር ማስተካከል መሰረዝ አትችልም ።የምትችለው አምኖ መቀበልና ለተሻለ ነገር መስራት ብቻ ነው ።
መቀየር የማንችላቸውን ነገር መቀበል ማለት ተስፋ መቁረጥ ሳይሆን አቅማችን የሚፈቅደው ነገር ላይ
ማዋል ማለት ነው በፍፁም ተስፋ አትቁረጥ ግን አቅምህን የምትችለው ነገር ላይ አውለው !!!

ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል !!!

03/10/2025

ከትላንትህ ተምረህ አስተውለህ ካልተራመድክ በስተቀር ነገም የከፉ አወዳደቅ ትወድቃለህ!!

ኢትዮጵያ የኤርትራ አገርነት  እውቅና ማንሳት ትችላለች‼️➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ኢትዮጵያ የኤርትራ አገርነት እውቅና ማንሳት ትችላለች።  “Mother State’s Permission “ በሚል ዓለማ...
03/10/2025

ኢትዮጵያ የኤርትራ አገርነት እውቅና ማንሳት ትችላለች‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

ኢትዮጵያ የኤርትራ አገርነት እውቅና ማንሳት ትችላለች። “Mother State’s Permission “ በሚል ዓለማቀፍ ህግ መሰረት በ1987 ዓ.ም መለስ ዜናዊ ለኤርትራ የሰጠውን የሃገርነት እውቅና አሁን ያለው መንግስት ማንሳት ይችላል።

Adresse

Vienna

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Wadila-Delanta Media erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Fördern

Teilen