Wadila-Delanta Media

Wadila-Delanta Media Standing for our people

  የከፋ የሚያደርጉ   ነባር ቅርሶች ክፍል  #1=================================እንደሚታወቀው የሀገራችን የፖለቲካ ሹመት እና የአሜሪካን ዲቪ የማይደርሰው ይኖራል ተብሎ ...
23/07/2025

የከፋ የሚያደርጉ ነባር ቅርሶች
ክፍል #1
=================================
እንደሚታወቀው የሀገራችን የፖለቲካ ሹመት እና የአሜሪካን ዲቪ የማይደርሰው ይኖራል ተብሎ አይገመትም።

ሁለቱም ድንገት የሚከሰቱ ዕድሎች ናቸው ልዩነታቸው ያው ከሹመት ስትወርድና ወደአሜሪካን ከበረርክ በኃላ እንጂ አመጣጣቸው ድንገት ነው።
ማናችንም ብንሆን ሹመት የሚሰጠን ለመውረድ እንጂ እስከዘላለም አለመሆኑ ሀቅ ነው ስለዚህ አንድ ተሿሚ ከሹመት መውረዱን እርግጠኛ መሆን ያለበት የተሾመ ቀን እንጂ የወረደ ቀን አዲስ ሊሆንለት አይገባም ከሆነም ልክ አይደለም። ለዛሬ ድህረ ሹመት የሚገጥሙንን ሲወርዱ ስዋረዱ የየሚመጡ ገጠመኞችን ጀባ ልበላችሁ!

#በባለፈው በዓል እንኳን አደረሰህ ተብለው ከተላኩ አንድ ሺ አንድ ሜሴጆች መካከል በአሁኑ በአል አምስቱ ሰዎች ብቻ ይልኩልሀል እነሱም አባትህ; እናትህ; ወንድምህ እህትህ እና አንድ በስህተት መውረድህን ያልሰማ ሰው።

#ትናንት "ማቲ ወይም ማርክ" ብለው የሚጠሩህ ዛሬ መውረድህን ስላወቁ "ማቴዎስ ወይም ማርቆስ" ብለው ሙሉ ስምህን ይጠራሉ አይድነቅህ ትንሽ ስቆዩ "ማቶሳ ወይም ማርቆሳ" ማለታቸው አይቀርም የተለመደ ነው።

#የሞባይልህ ጥሪ ይናፍቅሀል ትናንት እናቱ ጥላው ገበያ እንደሄደች ህፃን ስጮህብን የነበረው ሞባይልህ ጥሪውን አቁሞ በሚስትህ ሞባይል ራስህ ደውለህ ጥሪውን አለመቀየሩን ታረጋግጣለህ ኖርማል ነው።

#በጣም የሚቀርቡህ ሰዎች መንገድ ላይ ሲያገኙህ "ወይኔ ቀፎ ቀይሬ የአንተ ስልክ የድሮው ቀፎ ላይ ቀርቶ ሳልደውልልህ" ይሉሀል የያዘው ቀፎ አንተ ከመሾምህ በፊት የገዛውን ነው። "ነው እንዴ" ብለህ እለፈው
#በእግርህ ስትሄድ ያዩህ ሰዎች "ወይኔ ምን ሆነህ ነው" ሲሉህ አትደንግጥ ምንም አልሆንክም ከአይኑ ነው!

#ምደባ ጥየቃ ደብዳቤ ይዘህ ሰው ሀብቶች ጋ ስትሄድ ለምን መጥተህ ነው ይሉሀል? የመጣሁበትን ታውቃለህ በል! ቀጥሎ የትምህርት ዝግጅትህን ይጠይቅና አጣርቼ ነግርሃለው ይልሀል። ምንም የሚያጣራው የለም ተመልሰህ ስትመጣ በአንተ ሙያ መደብ የለንም ይልሀል። አንተ መደብ አጣርተህ የመጣህ መሆኑን እያወቀ
#ሆቴል አንድ ቡናና ግማሽ ሊትር ውሃ ተጠቅመህ አታችመንት ይሁን ካሽ የሚልህ አስተናጋጅ በቅንነት መሆኑን ተረዳ መውረድህን አልሰማም::

#ልጆችህ ምን ሆኖ ነው ጋሼ ቤት መዋል አበዛ ሊሉህ ይችላሉ አትደንግጥ በሹመት ዘመን ያለህን ትርፍ ጊዜ በሙሉ ለእነርሱ አውለህ ከሆነ ኖርማል ይሆናቸዋል ያለበለዚያ ማስረዳቱ ከባድ ነው የዘመኑ ልጅ መልስ ስትሰጠው ሌላ ጥያቄ ማብዛቱ አይቀርም።

#ብሶት አናዛዥ ከአንተ ቀድሞ የወረደ ተሿሚ ያለወትሮው አንተ ጋ ደጋግሞ ሊመጣ ይችላል አታቅርበው የስራ ፈጠራ ሀሳብ አይነግርህ ተጨማሪ ብሶት ነው የሚጭንብህ።

#ከሹመትህ የወረድክ ቀን በሹመትህ ምክንያት የቀረቡህ ጓዶች በሙሉ እንዳትቀርቡ ተብለው ግልባጭ ስለሚደረግላቸው አትደንግጥ ትናንት የወረዱት ገጥሟቸው ነገ የሚወርዱትም ይገጥማቸዋል።

#ኃለቃ (ቦስ) የሚልህ ሾፌርህ "friend ሰላም ነው?" ካለህ "አለው friend እንዴት ነህ?" ብለህ በማዕረግህ መልስለት በቃ አንተን ማዕረግህ "friend" ሆኖ ቆይቷል። ይህም ማዕረግ የሚሠጥህ መልካም ኃለቃ ከሆንክ ነው አለበለዚያ የከፋም አለ።

ክፍል ሁለት ላይ መፍትሔውን ይዤላችሁ እመልስበታለሁ

የአልበርት አንስታይን ድንቅና አስተማሪ አባባሎች!~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~1. ‹‹ ሠላምን በጉልበት ማስጠበቅ አይቻልም፡፡ ሠላምን ማስጠበቅ የሚቻለው በመግባባት ብቻ ነው፡፡ ›› 2...
16/07/2025

የአልበርት አንስታይን ድንቅና አስተማሪ አባባሎች!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
1. ‹‹ ሠላምን በጉልበት ማስጠበቅ አይቻልም፡፡ ሠላምን ማስጠበቅ የሚቻለው በመግባባት ብቻ ነው፡፡ ››

2. ‹‹ ስህተት ሠርቶ የማያውቅ ሠው ምንም ነገር ሞክሮ አያውቅም ማለት ነው፡፡ ››

3. ‹‹ ሁሉም ሠው ብሩህ ጭንቅላት አለው፡፡ ነገር ግን አሣን ዛፍ መዝለል አይችልም ብለህ ችሎታውን ካጣጣልከው በህይወትህ ሙሉ አሣ ደደብ እንደሆነ ታስባለህ፡፡ ››

4. ‹‹ ዓይነ ሕሊና ከዕውቀት የላቀ አስፈላጊ ነው፡፡ ››

5. ‹‹ ትምህርት አዕምሯችን የበለጠ እንዲያስብ እንጂ ጥሬ ሃቆችን ለመለማመድ አይደለም፡፡ ››

6. ‹‹ ሙከራህን እስከምታቆም ድረስ በህይወት አትሸነፍም፡፡ ››

7. ‹‹ አንድን ነገር በቀላል ቋንቋ መግለፅ ካልቻልክ ነገሩን አልተረዳኸውም ማለት ነው፡፡ ››

8. ‹‹ እብደት ማለት አንድን ነገር በተመሳሳይ ዘዴ ደግሞ ደጋግሞ በመስራት የተለየ ውጤት መጠበቅ ነው፡፡ ››

9. ‹‹ ደስተኛ ሕይወት ለመኖር ከፈለግክ አንተነትህን ከሠዎች ወይም ከነገሮች ጋር ከማወዳደር ይልቅ ከግብህ ወይም ከዓላማህ ጋር ራስህን እሠር፡፡ ››

10. ‹‹ ስኬታማ ለመሆን ከፈለግክ የስኬት ፍላጎትህ እወድቃለሁ ብለህ ከምትፈራው ፍርሃትህ በእጅጉ የበለጠ መሆን አለበት፡፡ ››

11. ‹‹ መቀራረብ በፍቅር ለመውደቅ ዋስትና አይሆንም፡፡ ››

12. ‹‹ ዋጋ ያለህ ሠው ለመሆን ሞክር እንጂ ስኬታማ ብቻ ለመሆን አትሞክር፡፡ ››

13. ‹‹ ምክንያታዊነት ከአንድ ቦታ አንስቶ ወደሌላ ቦታ ሊወስድህ ይችላል፡፡ ዓይነ ሕሊና ግን የትም ይወስድሃል፡፡ ››

14. ‹‹ ጎበዝ ሠው ችግሮችን ይፈታል፡፡ ብልህ ሠው ግን ችግሮቹ መልሠው እንዳይፈጠሩ ያስወግዳቸዋል፡፡ ››

15. ‹‹ ተፈጥሮን በጥልቀት ተመልከት፡፡ ያን ጊዜ ሁሉንም ነገሮች በተሻለ ትረዳለህ፡፡ ››

16. ‹‹ ሴቶች ብዙ ጊዜ የሚጨነቁበት ወንዶች ጨርሠው በረሷቸው ነገሮች ላይ ነው፡፡ ወንዶችም ብዙ ጊዜ የሚጨነቁበት ጉዳይ ሴቶቹ በማያስታውሷቸው ነገሮች ላይ ነው፡፡ ››

17. ‹‹ ቅዱሱን ጉጉትህን አትጣለው፡፡ ››

18. ‹‹ የአመለካከት ድክመት እየቆየ ሲሄድ የባህሪ ድክመት ይሆናል፡፡ ››

19. ‹‹ ሞትን መፍራት ማለት ተገቢ ባልሆኑ ፍርሃቶች መንቦቅቦቅ ነው፡፡ ምንም ስጋት የሌለበት ሠው ቢኖር የሞተ ሠው ብቻ ነው፡፡ ››

20. ‹‹ ፍፁም የማይመስለውን የሚሞክሩ የማይቻለውን የሚችሉ ናቸው፡፡

የትኞቹን አባባሎች ወደዳችኋቸው አድርጉልን።

ወደ ፌዝቡክ ሰዎች"እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን "የሚለውን መዝሙር ማን ደረሰው?አንዳንድ ሰዎች አሉ ፣ ጥግ ድረስ ዘልቀው የሚጠበቡ ታሪካቸው ግን እንደ ሞኝ ወርቅ ዓይንም ጆሮም የተነፈገ። የ...
13/07/2025

ወደ ፌዝቡክ ሰዎች

"እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን "የሚለውን መዝሙር ማን ደረሰው?

አንዳንድ ሰዎች አሉ ፣ ጥግ ድረስ ዘልቀው የሚጠበቡ ታሪካቸው ግን እንደ ሞኝ ወርቅ ዓይንም ጆሮም የተነፈገ።

የዛሬን አያድርገውና ባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ እንዲህ ነበር ።
በሥጋ ሲኖር ማንም የማያስታውሰው ፣ ምኑን (የተናቀ) በባዶ እግሩ የሚጓዝ እና ከድሆች ተርታም የሚመደብ ሰው ነበር።

ሥራዎቹን ከሥር ከሥሩ እየተከተሉ የሚለቅሙ ሳይቀሩ ሰውነቱን ይፀየፉት ይርቁትም ነበር። በጣም ከረፈደ እና ይህችን ዓለም ከተሰናበተ በኋላ ግን የእኔም ጓደኛ ነበር፣ የእኔ እንትን ነበር የሚሉ እንደ አሸን ፈሉ።

ቢያንስ ዶክመተሪም ሠሩለት፣ የተወሰኑ ግጥሞቹንም በማሳተም ለአዲሱ ትውልድ አስተዋወቁት።

ትናንት በአጋጣሚ የሲራክ ታደሰን ልጅ የመተዋወቅ እድሉን አግኝቼ አወራሁት። አባቱን ለማስተዋወቅ ሥራዎቹን ቲክታክ ላይ የሠራቸውን ቪዲዮዎችም ሁሉንም አየሁ። በጣም ነበር የተገረምኩት።

ጎበዝ ምን አይነት እርግማናሞች ነን ግን?
ለምን ይሆን የምር ጠቢባንን የማናስታውሳቸው?

ሲራክ ታደሰ እንደ አያ ሙሌ ተጎሳቁሎ ተገፍቶ ባያልፍም፣ በመባል ደረጃ ግን ምንም ያልተባለለት ሰው ነው። ከልጁ (ፍስሐ ሲራክ ታደሰ) አንዳንድ ማስታዎሻዎች እንደተረዳሁት ይህ ሰው በገጣሚነቱ እጅግ ድንቅ ሰው ነበር።

ሲራክ የዋድላ ደላንታ ሰው ነው። አመጣጡም ከቤተክህነት ወገን ነውም አሉ። ይህ የአስተዳደግ አጋጣሚውም ማለትም ቅኔ" ሀ "ተብሎ ከተጀመረበት ዋድላ መወለዱ እና ማደጉም ሳይሆን አይቀርም እንዲህ አይነት ሰይፋማ ጠቢብ ያደረገው።

ሰይፍ በሁለቱም ነው ስለቱ፣ በሁለቱም ይቆርጣል። የሲራክ አይነት አስተዳደግ ያላቸው ሰዎች ወደ ጥበቡ ሲገቡም እንዲሁ ናቸው ዝም ብሎ ይሳካላቸዋል። ምንም ቢጽፉ ያምርላቸዋል።

እኛ ግን እርግማን አለብን አይደል ? እንመንጂ!

ሲራክ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ በጣም ብዙ ግጥም ከሰጡት ከነ አያሙሌ ፣ ከነ አበበ መለሰ ትይዩ ነበርም ማለት ይቻላል።

"እንደቸርነትህ አቤቱ ማረን" የሚለው ታዋቂ እና ጥንታዊ መዝሙርም ደራሲው ይሄው የጥበብ ሰው ነው።

በትወና እና በኮሜዲ ዘርምፍ በርከት ያለ ተሳትፎ ያደረገ ሰው ነው። በጥቅሉ ሁለገብ አርቲስት ነው ሲራክ።

ግን ለምን ብዙ አልተነገረለትም?
እኔ ስላልሰማሁ ይሆናል እንዳልል ቁጭቱ ከልጁ ላይም አለ።

እንዴውም "ቲፎዞ ስለሌለው ነው" ነው የሚለው ልጁ ፍስሐ ሲራክ ታደሰ

የምር የተሻሉትን ስለማንሰማ ይሆንዴ እነ እገሌን የጣለብን?
መጠርጠር ጥሩ ነው እንደዚያ ነው የሚሆነው።


በቀጣይ አሥርት ዓመታት ብዙ ጸሐፍትን ባለ ቅኔዎችን መዘከር አስቤያለሁ

ሼር እያደረግን ወገን!

©️Daniel Wodaj

መረጃ‼️ቡሬን ያየ ጽንፈኛ ራሱን ነጻ ያውጣ======ቡሬ ከተማና በዙሪያው የሆነው ለሌላው አካባቢ ጽንፈኛም ትምህርት ነው‼️በተለያየ አካባቢ ተሳባስቦ   ወደቡሬ ከተማ ለመግባት   ሙከራ ያደ...
13/07/2025

መረጃ‼️
ቡሬን ያየ ጽንፈኛ ራሱን ነጻ ያውጣ
======
ቡሬ ከተማና በዙሪያው የሆነው ለሌላው አካባቢ ጽንፈኛም ትምህርት ነው‼️

በተለያየ አካባቢ ተሳባስቦ ወደቡሬ ከተማ ለመግባት ሙከራ ያደረገው ጽንፈኛ በከበባ ተይዞ መውጫ አጥቶ ተወቅጧል።

መውጫ አጥቶ ተወቅጦ የወደቀው እየተለቀመ፤ የቆሰለው እየተነሳ ነው። የተረፈው እግሬ አውጪኝ ብሎ ብሎ ተበታትኗል። 15 የጽንፈኛው አባላት ተማርከዋል።

በስፍራው የሚገኘው ጀግናው ጥምር ጦር በጥዋቱ 10 ክላሽ፣ 20 የቃታ መሳሪያ በቆጠራ ላይ የሚገኝ ተተኳሽ በእጁ አስገብቷል።

የዛሬ ዓመት እና ዛሬ አንድ አይደለም። ዛሬ አማራ ሕዝብም ሆነ የመንግስት የጸጥታ መዋቅር ከመጣህ በጋራ ይለቅምሃል እንጅ ቦታ አይለቅልህም። አትድከም።

የአማራን ሕዝብ በአደባባይ እየዘረፍክ የምትደበቅበት የጫካ ኑሮ በቃኝ ከተማ ልግባ ካልክ መሳሪያህን አኑረህ ሕዝብና መንግሥትን ይቅርታ ጠይቀህ መግባት ትችላለህ።

ከዚህ በሗላ በሰላም እንጅ አፈሙዝ ይዘህ እንድትገባ የሚፈቅድል አካል የለም። ምክንያቱም ትናንት ዛሬ አይደለም።

አማራ አማራ የሚሉት ለሽፋን ነው======ፖለቲካ ውስጥ ስልጣን ለብቻ ለመቆጣጠር ስም ማጥፋት ያለ እና የተለመደ አካሄድ ነው። ከሌላው ብቻ ተመርጣችሁ እናንተ ላይ ዘመቻ የተደረገው በምክንያት...
08/07/2025

አማራ አማራ የሚሉት ለሽፋን ነው
======
ፖለቲካ ውስጥ ስልጣን ለብቻ ለመቆጣጠር ስም ማጥፋት ያለ እና የተለመደ አካሄድ ነው። ከሌላው ብቻ ተመርጣችሁ እናንተ ላይ ዘመቻ የተደረገው በምክንያት ነው። አካዳሚካሊ ጥሩ ናችሁ፣ የመጣችሁበት አካባቢ የተለየ ስለሆነ፣ ያ ክልል ውስጥ ስልጣኑም፣ ሃብቱም በእኛ ቁጥጥር ስር መሆን አለበት ብሎ የሚዶልት ሃይል አለ።

አማራ አማራ የሚሉት ለሽፋን ነው። ይሄ ቡድን ከራሱ ጥቅም ውጪ ሌሎችን ማየት መስማት አይፈልግም። በተደጋጋሚ በማስረጃ ተፈትሸው ወድቀዋል፤ ሙስሊም ስለሆንን የሚል ግምት እንዳትይዙ፣ ወሎዬ የሆነ ግለሰብ ሁሉ ኦሮሞ እያደረጉ መፈረጅ ከተጀመረ ቆይቷል።

ያ ክልል መዋቅሩ ብልሹ እና ቆሻሻ ነው። እንደ አዲስ መደራጀት አለበት የምንለው በምክንያት ነው። በጣም ቀፋፊ ክልል ነው። ከላይ እስከታች በመጥፎ ሁኔታ የተደራጀ ስብስብ ነው። ፖለቲካ ላይ ምንም አይነት ይሉንታ የሚባል ነገር የለም።

የሌሎችን መብት አለመንካት እንጂ የመጣችሁበት አካባቢ ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ጥቅም እና ስልጣን ተካፋይ ማድረግ ትክክል ነው። በእናንተ ላይ ስም ማጥፋት ዘመቻ ያደረገው ልጅ ከኪሱ መዞት እንዳይመስላችሁ፤ ተልኮ ነው። በደንብ ታቅዶበት የሚሰራ ፕሮፓጋንዳ ነው።

- ያ ክልል ስልጣን ክፍፍል ፍጹም ልክ አይደለም
- የሃብት ስርጭቱም ፍጹም ልክ አይደለም
- የስራ ክፍፍሉም በፍጹም የህዝቡን ስብጥር የሚወክል

አይደለም እናም ወንድሞች ቆራጥ መሆን ይገባል። ማንንም እንዳትለማመጡ፣ ወሎዬን ሁሉ ኦሮሞ እያሉ መፈረጅ እና ስም ማጥፋት አዲስ ፕሮፓጋንዳ አይደለችም። እውቀት እና አቅም ያላችሁ ግለሰቦች ስለሆናችሁ ለስልጣን ስለምታሰጉ ነው እናም ሁሉም የራሱ አካባቢ ማስተዳደር እና በእኩል መወከል አለበት።

የሃብት ክፍፍሉም በስርዓት መከፋፈል አለበት። መላቀቅ የለም። የክልሉ በጀት ሰባራ ሳንቲም ሳይቀር ለሁሉም እኩል መካፈል አለበት።
አይዞን አለን 💪💪
Getachew

ትሁት የሚያደርግህ ስህተትህ፤ ጉረኛ ከሚያደርግህ ስኬትህ በእጅጉ ይበልጣል!(እ.ብ.ይ.)አንዳንድ ውድቀት ሰውን ትሁት ያደርጋል፡፡ አንዳንድ ስኬት ደግሞ ሰውን ጉረኛ ያደርጋል፡፡ በስኬትህ መኩ...
01/07/2025

ትሁት የሚያደርግህ ስህተትህ፤ ጉረኛ ከሚያደርግህ ስኬትህ በእጅጉ ይበልጣል!
(እ.ብ.ይ.)

አንዳንድ ውድቀት ሰውን ትሁት ያደርጋል፡፡ አንዳንድ ስኬት ደግሞ ሰውን ጉረኛ ያደርጋል፡፡ በስኬትህ መኩራትና ጉረኛ መሆን የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ being proud and arrogance are very different. ኩራት ውስጣዊ ነው፤ ጉረኝነት ግን ሌሎች ላይ የምናንፀባርቀው አጉል ባህሪ ነው፡፡ ብዙ ሰው ሲያገኝም ሆነ ሲያጣ ይለወጣል፡፡ የሚለወጠው ኑሮው ብቻ ሳይሆን ባህሪውም ጭምር ነው፡፡ ቀድሞ ሃይማኖተኛ፣ ትሁት፣ የተረጋጋ የነበረው ሰው ወይ ኪሱ ሲሞላ፣ አልያም ስልጣን ሲያገኝ፤ አልፎም ተርፎም ስምና ዝና ሲጎርፍለት ከሃይማኖቱና ከመልካም ባህሪው ሲያፈነግጥ ይታያል፡፡ ማግኘት እጥረትን እንደሚሞላ ሁሉ ባህሪንም ሊያጎድል ይችላል፡፡ ገንዘብ ጓዳህን እየሞላ ነፍስህን የሚያጎድል ከሆነ ትርጉም የለውም፡፡ ሰው በማግኘቱ መልካም ባህሪውን የሚያጠፋ፤ ሃይማኖቱን የሚያስተጓጉልና የእውነት መንገዱን የሚቀይር ከሆነ ማግኘቱ አልጠቀመውም ማለት ነው፡፡ እውነተኛ ስኬት የልፋታችንን ዋጋ የምንቀበልበት እንጂ መልካም ባህሪያችንን የምናጠፋበት አይደለም፡፡

አንዳንድ ሰው የእንጀራ እውቀት ብቻ ነው ያለው፡፡ በዚች በአንዲት ዕውቀት ነው ከእኔ በላይ ላሳር የሚለው፡፡ የህይወት እውቀት የሌለው ሰው ብዙ ነው፡፡ በአንድ እውቀት ብቻ ስኬታማ መሆን አይቻልም፡፡ ለዚህ ነው ፈላስፋው ወልደሕይወት በሀተታው… ‹‹ትምህርትን በመማር ደካማ አትሁን፡፡ በመላ የሕይወት ዘመንህም አትዋትት፡፡ ደግሞም በአንድ ትምህርት አትኑር፡፡ ይሄ ስንፍና ነውና፡፡ ልክ ንቦች የተለያዩ መዓዛ ያላቸውን አበቦች እየቀሰሙ ጣፋጭ ማር እንደሚሰሩ ሁሉ አንተም ከተለያዩ ትምህርቶች ሁሉ ጥበብን ሰብስብ›› …የሚለው፡፡ የስሜትና የመንፈስ ዕውቀት ሁሉን ተሸካሚ ጥበብ ነውና በአንዲቷ የእንጀራ እውቀት ብቻ አትመካ፡፡

ትህትና ጥበብ ነው፡፡ ትህትና ራስን መጨቆን ማለት አይደለም፡፡ ትህትና የምትችለውን ነገር በአግባቡና በስርዓት መከወን መቻል ነው፡፡ ትህትና በሆነ ባልሆነው ራስን ማሳነስም አይደለም፡፡ ትህትና ከማንም እንደማትበልጥና ከማንም እንደማታንስ ማወቅም ጭምር ነው፡፡ ትሁት መሆን ማለት ማስመሰል አይደለም፡፡ ትህትትና ሰው እየመረጥክ፤ ማዕረግ እየለየህ፤ ኪስ እየፈተሽክ የምትተገብረው ባህሪ አይደለም፡፡ ትህትና ለትንሽ ለትልቁ፤ ለድሃውም ለሃብታሙም፤ ለሊቁም ለደቂቁም እኩል የምታካፍለው መልካም ባህሪይ ነው፡፡ በአፋቸው ትሁት የሆኑ በስራቸው ግን ብዙዎችን የሚያሳምሙ ጨካኞች በየአካባቢያችን ሞልተዋል፡፡ እነዚህ በትህትና ስም የሚነግዱ የለየላቸው ነጋዴዎች ናቸው፡፡

ተምሮ አዋቂ መሆን ማለት ጉረኛ መሆን ማለት አይደለም፡፡ እንደውም እያወቅክ ስትሄድ ገና ማወቅ የሚገባህ ብዙ ነገር እንዳለ እንድታውቅ ያደርግሃል፡፡ እውቀት ትሁት እንጂ ተመጻዳቂ አያደርግም፡፡ እውነተኛ እውቀት አለማወቅህን የምትመሰክርበት እንጂ ሁሉን ጠንቅቄ አውቂያለሁ ብለህ የምትደሰኩርበት አይደለም፡፡ ምን እንደምታወራ ማወቅ እውቀት ነው፤ መቼ ማውራት እንዳለብህ ማወቅ ደግሞ ጥበብ ነው፡፡ (What to speak is knowledge, when to speak is intelligence)፡፡ ትክክለኛውን የእውቀት መንገድ የጀመሩ ሰዎች ኢምንት ማወቅ መጀመራቸውን እንጂ አውቀው መጨረሳቸውን አያውቁም፡፡ ተምሮ መመረቅ፤ ዲግሪ ማስተር መሰብሰብ ባሳደገህ ማህበረሰብ ላይ እንድትመፃደቅ የሚያደርግህ ከሆነ ምርቃትህ ወደእርግማን እንደተለወጠ ቁጠረው፡፡

ዋረን ቡፌት ‹‹ስሜትህን መቆጣጠር ካልቻልክ ገንዘብህንም መቆጣጠር አትችልም (If you can not control your emotions, you can not control your money)›› እንዳለው እውቀትህን፣ ስኬትህን፣ ማግኘትህን፣ ደስታህን በወጉ ካላስተዳደርከው አደጋ ያመጣብሃል፡፡ የስሜት ብስለት የሌለው ሰው በሚያገኘውም ሆነ በሚያጣው ነገር ይጠፋበታል፡፡ መቼ ምን ማውራት እንዳለበት አያውቅም፡፡ ማጣቱን ማስታመም፤ ማግኘቱን ማስከን፤ ረሃቡን ማስታገስ፤ ጥጋቡን ማብረድ አይችልበትም፡፡ ሲያጣም ችግር ነው፤ ሲያገኝም መከራ ነው፡፡ ማግኘትም ማጣትም በአእምሯዊ ማንነትህ ላይ አሉታዊ ለውጥ እንዳያመጣ ልታሰለጥነው ይገባል፡፡ በስኬትህም ሆነ በውድቀትህ፤ በረሃብህም ሆነ በጥጋብህ፤ በጤንነትህም ሆነ በህመምህ ወጥ አቋም፤ የተረጋጋ ስሜት እንዲኖርህ ጠንክረህ ካልሰራህ ኑሮህ በተለዋወጠ ቁጥር አንተም ትለዋወጣለህ፡፡

ወዳጄ ሆይ…. “ትሁት የሚያደርግህ ስህተትህ፤ ጉረኛ ከሚያደርግህ ስኬትህ በእጅጉ ይልቃል” (A mistake that makes you humble is better than an achievement that makes you arrogant)፡፡ ስህተትህ መልካምነትን የሚያስተምርህ፤ ውድቀትህ የሚያረጋጋህ፤ ጥፋትህ ውስጣዊ ማንነትህን የሚያስተካክል ከሆነ ተጠቀምክ እንጂ አልተጎዳህም፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ስኬትህ ከሰውነትህ የሚያርቅህ፤ ከእውነትህ የሚያሸሽህ፤ ከሃይማኖትህ የሚያፈናቅልህ ከሆነ ግን ሊጎዳህ እንጂ ሊጠቅምህ አልመጣም ማለት ነው፡፡ ከሁሉም ከሁሉም ግን ከውድቀትህና ከስህተትህ ፊደል ቁጠር፡፡ ስኬትህ ልብህን አሳብጦ እንዳያጠፋህ ተጠንቅቀህ ያዘው፡፡ ትህትናን ተለማመድ፡፡ በአፍ ብቻ ትሁት አትሁን፡፡ መካከለኝነትን፣ ማስተዋልን፣ መጠንን ማወቅ ተማር፡፡ እንዳትወድቅ ሚዛንህን ጠብቅ!! ደስታም ሆነ ሀዘን፤ ስኬትም ሆነ ውድቀት መጠን አለው፡፡ ጨርሰህ በሁሉም አትውደቅ!!!!

ቸር ሚዛን! ደግ መጠን! ድንቅ ማስተዋል!

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ለዘላለም ይኑሩ!

______________________
እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
ሠኞ ሰኔ ፳፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.

የዕለቱ ፎቶ‼️ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቤተመንግስት ካደገዉ ከ4ተኛ ልጃቸዉ ሚሊዮን አብይ ጋር።📷 OPME
28/06/2025

የዕለቱ ፎቶ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቤተመንግስት ካደገዉ ከ4ተኛ ልጃቸዉ ሚሊዮን አብይ ጋር።
📷 OPME

የአካባቢያችን ተወላጅ የሆነው አቶ አለምነው አበበ እንዲህ ይላልየደጎች ምድርየእግር ኳሱ ንጉስ ሙሉጌታ ከበደ (ወሎዬው) ዜና እረፍት እንደሰማሁ የተሰማኝን ሀዘንና ከሆጤ ሜዳ እስከ ወይዘሮ ስ...
12/06/2025

የአካባቢያችን ተወላጅ የሆነው አቶ አለምነው አበበ እንዲህ ይላል

የደጎች ምድር

የእግር ኳሱ ንጉስ ሙሉጌታ ከበደ (ወሎዬው) ዜና እረፍት እንደሰማሁ የተሰማኝን ሀዘንና ከሆጤ ሜዳ እስከ ወይዘሮ ስህን ት/ቤት ድረስ ትዝታዬን አጋርቸ ነበር፡፡ በሀዘን ስሜት የተቀሰቀሰ ትዝታ ከዕድሜ ጋር ተጋግዞ በቀላሉ ተመልሶ እንዲደበቅ አያደርግምና እስካሁን የሚያስገርመኝን አንድ ሌላ ትዝታ እንዳካፍል ገፋፋኝ፡፡

የእኔና የሙሌ ትውልድ በአንድ በኩል ‘’አብዮት’’ በሚባል የቅራኔ ማዕበል እየተናጠ በደርግ መንግስትና የመነግስትን ስልጣን በአመጽ ለመንጠቅ የከተማ ውስጥ ሽምቅ ውጊያና የነፍስ ግድያ ላይ ሳይቀር በተሰማሩ ኃይሎች የመጠፋፋት ትግል የሚሰቃይበት ነበር፡፡ ‘’በነጭ ሽብር‘’ እና ‘’በቀይ ሽብር‘’ ውስጥ ንጹህ ደም ሲፈስና ሬሳ ጎዳና ላይ ሲወድቅበአይኑ የተመለከተበት የጭካኔ ወቅት ነበር፡፡

በሌላ በኩል ይሄው አብዮትና አመጽ ወለድ መከራ ተሸካሚ ትውልድ ደሙ አስፋልት ላይ እየፈሰሰ ከስፖርታዊ እንቅስቀሴ ያልታቀበም ትውልድ ነበር፡፡ በዚህ ‘’የቀይና ነጭ ሽብር‘’ ፍጻሜ ዘመን ነበር በደሴ ከተማ ከፍተኛ 2 ቀበሌ 1 (ጉምሩክ አካባቢ) ወጣቶች ተሰባስበን የእግር ኳስ ቡድን በመፍጠር ከሌሎች ቀበሌዎቸ ወጣቶች (ከነሙሉጌታ ከበደ የሆጤ ቀበሌ ወጣቶች ጋር ጭምር) ጋር መወዳደር የጀመርነው፡፡

ዛሬ ድረስ እጅግ የሚገርመኝ የእኛን የወጣቶችን የጋለ የስፖርት አፍቃሪነትና አልሸነፍ ባይ የተወዳዳሪነት እልህ ይከታተሉ የነበሩ የቀበሌያችን ሙስሊም ነጋዴዎች በራሳቸው ተነሳሽነት ያደረጉልን የሞራልና የወተት መጠጫ ገንዘብ ድጋፍ ከአዕምሮዬ አይጠፋም፡፡ ልብ አድርጉ! እኛ ወጣቶቹ ስፖርቱ በተለይ የእግር ኳስ ፍቅሩ ባሳደረብን የጋለ ስሜት ገፊነት የምናካሂደው ውድድር እንጂ ሳንቲም ለመለመን የማንንም በር አንኳኩተን አናውቅም፡፡

ትክክለኛ ቀኑን ባላስታውሰውም ዓመቱ ግን 1971 እንደነበር ትዝ ይለኛል፡፡ ‘’ስጋ ተራ ‘’በሚባለው ሰፈር ሱቅ የነበራቸው ሀጂ አህመድ ሙሳ የሚባሉ ነጋዴ እንደሚፈልጉን ሰማንና ተሰበሰብን፡፡ ብዙ የታሸገ ዕቃ ደርድረዋል፡፡ እኛ ሳናያቸው የእግር ኳስ እንቅስቀሴያችንን ይከታተሉ እንደነበር ገልጸው የእግር ኳስ ችሎታችንን፣ እልህና ወኔያችንንና ጠንካራ የእግር ኳስ ተወዳዳሪነታችን በአድናቆት ገልጸው በደስታ ያስፈነደቀንን ስጦታ አበረከቱልን!

ለሁላችንም ምርጥ ማሊያ ከምርጥ ታኬታ ጫማ ጋር!!የማሊያና ታኬቴታው ዝም ብሎ እንዳይመስላችሁ! የአዲዳስ ምርት ነው፡፡ ብዙዎቻችን በተቀደደና በቆሸሸ ሸራ ጫማ የምንወዳደር ስለነበር የተሰማንን ደስታ በቃል መግለጽ ከባድ ሆነብን፡፡ በነገራችን ላይ ‘’ወሎ ደግነትንና ሩህሩህነት ሞልቶ የጠጠጠረፈበት አገር ነው‘’ የሚባለው እውነት ስለመሆኑ እኔ ምስክር ነኝ፡፡ በተለይ የትልልቅ ሱቆችና የምግብ ቤቶች ባለቤት የሆኑት ደጋጎቹ ሸሆችና ሀጂዎች ለኛ ለወጣቶች፣ በአጠቃላይም ለሰው ልጅ የነበራቸው ፍቅር ሳስታውሰው እስካሁን ስሜታዊ ያደርገኛል፡፡

ስፖርት ሰርተን ወይም ከሌላ ቀበሌ ወጣቶች ጋር ውድድር አካሂደን በቀበሌያችን ውስጥ ቁርስ ለመመገብና ሻይ ለመጠጣት ስንገባ የሚያሳዩን ፍቅር ብቻ ሳይሆን ሳንቲም እንዳንከፍል ቀድመው ሂሳቡን በመዝጋት የሚዲርጉልን ድጋፍ ያስገርማል፡፡ በእነዚህ ደጋግ ሸሆችና ሀጂዎች ድጋፍና ማበረታቻ ከደሴ ከተማ ሌሎች ቀበሌዎች ጋር ከመወዳደረር አልፈን ከኮምቦልቻ፣ ከሚሴኔና ባቲ ወጣቶች ጋር ውድድር እንድካሂድ የትራንስፖርት ወጭያችንን ሸፍነውልናል፡፡

የወሎዬዎችን ደግነት የሚመሰክር አንድ የራሴ ሌላ ገጠመኝ ልጨምር፡፡በአንድ ወቅት (ቀኑ የጥምቀት ቀን እንደሆነ አስታውሳለሁ)የቀበሌያችን ወጣቶች በቀጠሮአችን መመሰረት ለእግር ኳስ ልምምድ/ጨዋታ በሌሊት ተሰባስበን በሆጤ ሜዴዳ ተገናኘን፡፡ የደሴን የጧትና ማታ ቅዝቃዜ የሚያውቅ ያውቀዋል፡፡ ሆጤ ሜዳው በወጣቶች የተጨናነቀ ስለሆነ በቦርከና ወንዝ ዳር ክፍት ቦታ ፈልገንና ለብርድ መከላከያነት የለበስነውን በአንድ ቦታ ላይ አስቀምጠን የእግር ኳስ እብደቱን ተያያዝነው፡፡

በመጨረሻ ለብርድ መከላከያነት የለበስነውን አንስተን ወደ ቤታችን ለመመለስ ስንሞክር የኔ ‘’ጋቢ‘’ በአስቀመጥኩበት ቦታ ላይ የለም፣ ጠፍቷል፡፡ ደነገጥኩ፡፡ ጋቢው ገጠር ያለችው እናቴ ለኔ ብርድ መከላከያ ብላ በማሰራት የላከችልኝ ነበር፡፡በሀዘን ተውጨ ወደ ቤት ስመለስ ለምታስተምረኝና እጅግ ለምትወደኝ አክስቴ ጋቢዬ መጥፋቱን ነገርኳት፡፡ ‘’ተወው ይጥፋ፣ እኔ እህትህ አሰራልሀለሁ ‘’ነበር ያለችኝ፡፡ እስካሁንም በሚያስገርመኝ ሁኔታ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከጠፋው ጋቢ እጅግ የተሻለ ጋቢ ባለቤት ሆንኩ፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው-በጓደኞቸ በኩል የኔ ጋቢ መጥፋት በሰፈር ውሰጥ ተወራ!!በዚህን ጊዜ አኔን በአካል የሚውቁኝና የሚያበታቱኝ የሰፈራችን እናቶች በድብቅ ተመካክረው ገንዘብ በማዋጣት ምርጥ ጋቢ በመግዛት አክስቴ እንድታስረክበኝ ሰጧት፡፡ እናም አክስቴ የጋቢውን ምስጢር ይፋ አድርጋና ያስባበሩትን የነእማማ ብዙዬማስረሻና እማማ ሀዋን ስም ጠርታ ጋቢውን አለበሰችኝ፡፡ደስታዬ ወደር አልነበረውም፡፡ከልጆቻቸወው ጋር እኩል እያጎረሱ ፍቅራቸውን የሚገልጹልኝ የሰፈሬ እናቶች ጋቢ አለበሱኝ፡፡

እኔ በዘመኔ የማወቀው የደጋጎች አገር ወሎ እንዲህ ነበር፡፤ ዛሬ ግን አላውቅም፡፡ የደግነት ትዝታውን ተሸክሜና አገር ላገር ስዞር ኖሬ አሁን በአዳነች አበቤዌዋ ውብ ከተማ አዲስ አአበባ ውስጥ እገኛለሁ፡፡ ታኬታው በባቡር ተሳፍሮ ሀረር ከደረሰ በኋላ ከኢንስትራክተር አንተነህ እሸቴ (ነፍሱን ይማረውና) ጋር የፈጠረውን ግብግብ አጋራችሁ ይሆናል---ከፈለጋችሁ ነው፡፡

አፋልጉኝ ወደ ወገል ጤናአባትና ልጁን በሕይወት ለማገናኘት ሸር አድርጉከፎቶው ላይ በፊት በኩልየምትመለከቱት  አቶ ቢያልፈው ሽፈራው ይባላል ።ለ34ዓመት ልጁን አግኝቶ አያውቅም።በ80ዎቹ መጀመ...
11/06/2025

አፋልጉኝ ወደ ወገል ጤና

አባትና ልጁን በሕይወት ለማገናኘት ሸር አድርጉ

ከፎቶው ላይ በፊት በኩል

የምትመለከቱት አቶ ቢያልፈው ሽፈራው ይባላል ።
ለ34ዓመት ልጁን አግኝቶ አያውቅም።

በ80ዎቹ መጀመሪያ ወታደር በነበረበት ጊዜ በወሎ ክፍለሀገር ወገል ጤና ወረዳ እንደሱ አነጋገር ከከተማ ወጣ ብሎ ጨው ቁጥር ከምትባል ልዩ ቦታ የደርግ መካናይዝድ መቀመጫ የነበረበት አካባቢ ወይዘሮ አማሩ አዳነ መለሰ የምትባል ሴት በማግባት ወንድ ልጅ እንደወለደ

ስሙንም አሻገረ ቢያልፈው በማለት እንዳወጣለት
ይገልጻል። ወደ ቀየው ሲመለስም ሙሉ አዳራሻ ዝርዝር ሰጥቶ የተመለሰ ሲሆን በገጠራማ አኗኗር ውስጥ ሁኖ ልጁን እየናፈቀ ዘመናትን ሲገፋ ኑሯል። በወቅቱ ጦርነቱ ተጠናቆ ወደትውልድ ቀየው በየዳ ከተመለሰበት

ከ1984 ጀምሮ ልጁን ማግኘት አልቻለም ስለልጁም መረጃ የለውም። ሁሌም በልጅ ናፍቆት ይሰቃያል ።አሻገረ ቢያልፈውን ለማግኜት ሁላችሁም ተባበሩን

በተለይ ዋድላ ደላንታ ወገልጤና ዙሪያ የተጠቀሱትን ቤተሰብ የምታውቁ ካላችሁ

በልጅ አምላክ መረጃውን በማድረስ ተባበሩን



0918525253 ፈንታሁን ተስፉ

መምህር ኤፍሬም ተስፋ የአጎት ልጆች

11/06/2025
"በመንግሥት እና በሕዝብ መካከል የተፈጠሩ የግንኙነት ችግሮችን መርምረን መፍትሄ ማፍለቅ ይኖርብናል" አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)*******የክልል እና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በደቡብ ወሎ ዞ...
31/05/2025

"በመንግሥት እና በሕዝብ መካከል የተፈጠሩ የግንኙነት ችግሮችን መርምረን መፍትሄ ማፍለቅ ይኖርብናል" አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)
*******
የክልል እና የዞን ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በደቡብ ወሎ ዞን ከደላንታ ወረዳ እና ከወገልጤና ከተማ አሥተዳደር ከተውጣጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አካሂደዋል።

ውይይቱን የመሩት የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) በሀገር ደረጃ ሰላም እንዲኖር ማኅበረሰብ ትውፊቶቹን ጠብቆ ሊኖር ይገባዋል ብለዋል።

ለምን የአባቶቻችንን መስመር ሳትን? ለምን እሴቶቻችንን አጣን ? ብለን ጠይቀን መፍትሄ ስናፈልቅ የችግራችንን ምንጭ እናደርቃለን ብለዋል ምክትል ርእሰ መሥተዳድሩ።

በመንግሥት እና በሕዝብ መካከል የተፈጠሩ የግንኙነት እና የቁርኝት ችግሮችን መርምረን መፍትሄ ማፍለቅ ይኖርብናልም ብለዋል።

ደላንታ ወረዳ በተፈጥሮ ሀብት እና በማኅበራዊ እሴት የበለፀገ ነው ያሉት ምክትል ርእሰ መሥተዳድሩ እሴቶቹ ግን በሂደት ተሸርሽረዋል ብለዋል። ስለዚህ ለምን እና እንዴት ብለን መምከር ይገባል፣ በዚህ ላይ መምከር ካልቻልን ማኅበረሰብ እንደ ማኅበረሰብ አይቀጥልም ብለዋል።

መክረን መልስ ማግኘት ከቻልን እና ራሳችንን የመፍትሄ ምንጭ ኾነን ከሠራን ሁለንተናዊ ሀብታችንን ተጠቅመን ራሳችንን እናበለፅጋለን ሲሉ አስረድተዋል።

በመኾኑም የችግሩ ምንጭ፣ የችግሩ መፍትሄም ደላንታዊ ነው፣ በችግሩ እና በመፍትሄው ላይ ልንመክር ይገባል ሲሉ አሳስበዋል ሲል የዘገበው አሚኮ ነው።
አሚኮ

ህዝበኝነት እና ብልጽግና Brook Abegaz የአማራ ክልል ሕዝብ ከህዝበኛ እና ባለ መንታ ምላሶች ይልቅ እውነትን በሚገባ የሚያስረዱ ደፋር መሪዎችን ይሻልየአማራ ክልል አሁን ያለበት እጅግ ...
30/05/2025

ህዝበኝነት እና ብልጽግና Brook Abegaz

የአማራ ክልል ሕዝብ ከህዝበኛ እና ባለ መንታ ምላሶች ይልቅ እውነትን በሚገባ የሚያስረዱ ደፋር መሪዎችን ይሻል

የአማራ ክልል አሁን ያለበት እጅግ አስቀያሚ ሁኔታ ላይ የደረሠው በክልሉ መንግስታዊ መዋቅር በየደረጃው በተቀመጡ ህዝበኛ እና ባለመንታ ምላስ መሪዎች ነው። ጠሚ ዓቢይ ወደ ስልጣን ከመምጣታቸው በፊት ገና በዋዜማው ጀምሮ የክልሉ አመራሮች የሄዱበት የህዝበኝት መስመር መሪዎችን ከመብላት ጀምሮ ክልሉ በታሪኩ የማያውቀውን እጅግ ነውረኛ እና ጭካኔ የተሞላበት ሥርዓተ አልበኝነት ፈጥሯል። ህዝበኝነት የክልሉ አመራሮች ዋነኛ መገለጫ ሆኖ አመራሩ ለህዝብ የሚጠቅመውን ከመሥራት እና ከመናገር ይልቅ የማህበራዊ ሜዲያ ርካሽ ጭብጨባና ውዳሴ ለማግኘት ሲሮጥ ነበር።

ከደመቀ መኮነን እና ገዱ አንዳርጋቸው ጀምሮ እስከ ታችኛው ቀበሌ አመራር ህዝበኝነት ተጠናውቶት ክልሉን የነውር መናሀሪያ አደርጎታል። ህዝበኝነት እንደ ዶ/ር ዓለምነው መኮነን አይነት እውነትን ፊትለፊት የሚናገሩ ደፋር መሪዎችን ከጨዋታ ውጭ በማድረግ ተጀምሮ፣ ነፍሱን ይማርና በህዝበኝነት የሠከረው ብ/ጀነራል አሳምነው ጽጌ ራሱን እንዲበላ መጠኑ ይነስ እንጂ በዚሁ ህዝበኝነት ተጠፍንገው የነበሩ ለውጥ ፈጣሪ መሪወችን በልቶ ከቀጠለ በኋላ በመጨረሻም ክልሉን አፍርሶ መጫወቻ አድርጎታል።

ነፍሳቸውን ይማርና እነ ዶ/ር አምባቸው ህዝበኝነት አስሮ ባይዛቸው ኖሮ ገና በጧቱ ብ/ጀነራል አሳምነው ጽጌ ላይ ተገቢውን የእስር እርምጃ ወስደው ቢሆን እሱም ባልሞተ እነሱም ባልሞቱ ነበር። ህዝበኝነት ለህዝብ ጥቅም ሲባል የወጡ አዋጅ፣ ህግና መመሪያወችን ሁሉ እንዳይሠሩ ያደርጋል። ህዝበኝነት ሲወስድ እያሳሳቀ በመሆኑ ብዙዎቻችን ውጤቱን የተረዳነው አሁን ያለንበት የሰቆቃ ሁኔታ ውስጥ ስንገባ መሆኑ ያሳዝናል። ይበልጥ የሚያሳዝነው ግን ህዝበኝነት ያመጣብንን አደጋ መረዳት ያልቻሉ መሪዎች አሁንም ካሉ ነው።

ከዚህ አንጻር የቀድሞው የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳዳሪ እና የአሁኑ የአማራ ክልል ምክትል አስተዳዳር ዶ/ር አብዱ ሁሴን የሚያምኑትን እውነትን ሳይሽኮረመሙ ፊትለፊት በድፍረት የሚናገሩ አና ለተሰለፉበት መስመር ግንባራቸውን የማያጥፉ እንደሆኑ ከሚያውቋቸው ሰዎች ለመረዳት ችያለሁ። አንዳንድ ክልሉ ላይ ያሉ ወዳጆቼ "ይሄን የእናንተ አገር ሰው በጣም ደፋር ነው፣ ቀስ በል በሉት ፣ አስመሳዮቹ እንዳያስበሉት..." ወዘተ ሲሉኝ ፤ ክልሉ የሚያስፈልገው ግን ያጣው እንዲህ ዓይነት ሰው ነው፤ እናንተ እንደምትሉት ከሆነ እግዜሩ ይጠብቀው የሚል ነበር ምላሼ።

ላለፈው አንድ ወር ድሮ በሰላሙ ዘመን በእነ Abdu Hussen Ibirahim ደረጃ ያሉ አመራሮች የማይሄዱባቸው የገጠር ወረዳ ቀበሌዎች ድረስ በመሄድ ህዝብን ማወያየት እና የህዝብን የሰቆቃ ለማድመጥ የሚደረገው ጥረት እንደ ቀላል የሚታይ አይደለም። ምናልባትም ወደ አንዳንድ የገጠር ቀበሌዎች ለስብሰባ የሚደረገው ጉዞ በመንገድ ላይ ከፋኖዎቸም ጋር በመታኮስ ጭምር እንደሆነ ሰምቻለሁ። ክልሉን ከማረጋጋት አንጻር በዚህ ደረጃ የሚደረገው ጥረት ግን ገብቶ ከመውጣት ባለፈ በዘለቄታዊነት ሰላም የሚያመጣ መሆን ይገባዋል።

ለሠላም አለመኖር እና ለተንዛዛ ጦርነት ምክንያቱ መንግስትን በትጥቅ ከሚፋለሙት ፋኖዎች በላይ ሁኔታው የተመቻቸው እና የሀብት ምንጭ የሆነላቸው የሠራዊቱ አመራሮችም ጭምር እንደሆኑ ብዙ ማስረጃወች/ማሳያወች አሉ። ተራው ሠራዊት በየአቅጣጫው ህይወቱን እየከፈለ ቢሆንም በክትትልና ቁጥጥር ሥርዓት አለመኖር ወይም ድከመት የሠራዊቱ አመራሮች (ሁሉም ሳይሆን ጥቂቶቹ) በሠላም አስከባሪነት አልያም በሌላ ያላገኙትን ሀብት በዚህ ጦርነት እየሰበሰቡ ነው። በዚህም ምክንያት አንዳንዶቹ ክልሉ ላይ ያለው የአሁኑ ሁኔታ በዚሁ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉ ማሳያወችን ማቅረብ ይቻላል።

ሠላምን ለማምጣት በየገጠር ወረዳው ህዝብን ቀርቦ ማነጋገሩ ገቡና ወጡ ሆኖ እንዳይቀርና ህዝቡ ወደለየለት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ እንዳይገባ ዘለቄታዊነቱ ላይ መበርታት እና ማተኮር ተገቢ ነው። የክልሉ መሪዎችም በዚህ ደረጃ በድፍረት የምታደርጉት ጥረት ፍሬ እንዲያፈራ የክትትልና የቁጥጥር ሥርአት መፍጠርና የችግሮችን ምንጭ በሚገባ ለይቶ ማድረቅ ተገቢ ነው።

Adresse

Vienna

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Wadila-Delanta Media erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Teilen