26/11/2025
አድስ መገለጫ ከኢትዮጵያ ነገድ ባንክ
የተከበራችሁ የባንካችን ደንበኞች
****
ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ ነገ ረቡዕ ህዳር 17 ቀን 2018 ከሌሊቱ 9:00 ሰዓት እስከ 11፡30 ድረስ ሁሉም የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አገልግሎቶች ማለትም በሞባይል ባንኪንግ፣ በሲቢኢ ብር ፣ በኢንተርኔት ባንኪንግ፣ በኤቲኤም ማሽኖች እንዲሁም በፖስ ማሽኖች እና በኮር ባንኪንግ የሚሰጡ አገልግሎቶች (Core Banking Services) በጊዜያዊነት ይቋረጣሉ።
በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህን አውቃችሁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እያሳወቅን፣ ለሚፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል ይቅርታ እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!