05/05/2026
ሰበር ዜና፡
ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። የፌዴራል መንግስት ባለፈዉ ወር የትግራይ ፕረዚደንት አድርጎ የሾማቸዉ ጀነራል ታደሰ፡ “አሁንም የትግራይ ፕረዚደንት እኔ ነኝ” እያሉ ነዉ።
በትግራይ ክልል ለሦስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የክልሉ ምክር ቤት በድጋሜ በመሰባሰብ ባካሄደው ጉባኤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤልን የክልሉ ፕሬዝዳንት አድርጎ መረጠ። ምክር ቤቱ ወ/ሮ ኪሮስ ሓጎስን አፈ ጉባኤ፣ ወ/ሮ ምህረት በርሄን ደግሞ ምክትል አፈ ጉባኤ አድርጎ በመሾም ጉባኤውን አጠናቋል።
የፌዴራል መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ እስካሁን ያለዉ ነገር የለም።