Tikus Neger

Tikus Neger Tikus N***r features the latest celebrity news, untold life stories, musician biographies, relations
(3)

11/25/2025

*** የሴቶችን ጥቃት በጋራ እንከላከል***
እስቲ እባካችሁ ለእንደነዚህ ምስኪኖች እንድረስ መረጃም ለሚመለከተው እናድርስ። እንደነዚህ አይነት የስራ ቦታዎች መዘጋት አለባቸው።

***አለማድነቅ ንፉግነት ነው!***ለአንገቷ ወርቅ አጥታ ነው?!ለአንገቷ ዳይመንድ አጥታ ነው?!ለአንገቷ የተለያዩ የሀገራችን የባህል ጌጣጌጦች አጥታ ነው?! ይህች ሞገስ የተሞላባት ለባልዋ ክ...
11/25/2025

***አለማድነቅ ንፉግነት ነው!***
ለአንገቷ ወርቅ አጥታ ነው?!
ለአንገቷ ዳይመንድ አጥታ ነው?!
ለአንገቷ የተለያዩ የሀገራችን የባህል ጌጣጌጦች አጥታ ነው?!
ይህች ሞገስ የተሞላባት ለባልዋ ክብር የሆነች ሴት ምን ሆና ነው?!

11/25/2025

ሰዎች ሶሻል ሚዲያ መከታተል ያለባቸው ከእንደዚህ አይነቶች አደጋ እራስን ለመከላከል ነው።
እንድሚታወቀው ትኩስ ነገር ሚዲይ ለእናንተ ለተከታታዮቼ ምን ግዜም በዚህ ፔጅ የማቀርብላችሁ እንደዚህ አይነት ወንጀልና ፈጣን መረጃዎችን እንደመሆኑ መጠን መረጃዎችን በመከታተል ከእንደዚህ አይነቶች ተደጋጋሚ አደጋዎች ቀድሞ በመገንዘብ እራሳችሁን ጠብቁ ለሌሎችም አጋሩ እላለሁ። ፔጃችንንም ፎሎ በማድረግ መረጃ ቶሎ እንዲደርሳችሁ አድርጉ።

11/24/2025

ውድ የትኩስ ነገር ተከታታዮቼ ይሄ የምታዩትን አይነት መልዕክት በጣም ተደጋግሞ እየመጣ ነውና ምክንያቱን ወይም ምንጩ ከየት እንደሆነ የምታቁ ካላችሁ ሼር ብንደራረግና የሚመለከተው ጋር እንዲደርስ ብናደርግና እራሳችንን ከአደጋና ከመክሰር ብንተርፍ እላሁ።

11/23/2025

አመጣጣቸው ከየት እንደሆነ የማይታወቁ የኮስሞቲክስ ቅባቶች እንደዚህ አይነት አደራዎች በአንዳንዶች ላይ እያደረሰ ስለሆነ ተጠንቀቁ። #ተጠንቀቁ #ኮስሞቲክስ #ኢትዮጵያ

11/21/2025

ተጠንቀቁ! ተጠንቀቁ! በሳሻል ሚዲያ የሚሸጥ ነገር ቢቀርብንስ!

11/20/2025

ሲዘዋወር ካገኘሁ አስገራሚ ነገር! የልጆች ታማኝነት ምን ያህል ጥግ ድረስ እንደሆነ በዚህች እናት ልጅ ተመልከቱ።

***ሰበር ብታምኑ ባታምኑም ነገሩ ከሯል።***እንደገና ትምህርት ሚኒስቴር፦ በተማሪዎች አለባበስ፣ በሞባይል አጠቃቀም፣በትምህርት ቤት ውስጥ በሚደረጉ ጭፈራዎችእና በትምህርት ቤቶች ዙሪያ ባሉ ...
11/20/2025

***ሰበር ብታምኑ ባታምኑም ነገሩ ከሯል።***

እንደገና ትምህርት ሚኒስቴር፦
በተማሪዎች አለባበስ፣
በሞባይል አጠቃቀም፣
በትምህርት ቤት ውስጥ በሚደረጉ ጭፈራዎች
እና በትምህርት ቤቶች ዙሪያ ባሉ ንግዶች ላይ አዲስና ጥብቅ መመሪያ አወጣ::

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ቤቶችን ሥነ-ምግባር እና የመማር ማስተማር ሂደትን ለማሻሻል አዲስ የረቂቅ መመሪያ ያዘጋጀ ሲሆን፣ በዚህም መሠረት የሚከተሉት ክልከላዎች ተቀምጠዋል፡፡
1. የተማሪዎች አለባበስ እና ራስ አጠባበቅ ላይ የተጣሉ ክልከላዎች (በተለይ ለሴቶች)፡-

ማንኛውም ዓይነት የመኳኳያ (ሜካፕ)፣ የጥፍርና የከንፈር ቀለም፣ እንዲሁም ቅንድብ መቀንደብ ተከልክሏል፡፡

አርቴፊሻል ፀጉር (ዊግ) መቀጠል አይቻልም፤ ተፈጥሮአዊ ፀጉር ብቻ ይፈቀዳል፡፡

የሴቶች የደንብ ልብስ (ቀሚስ) ርዝመት ከጉልበት በታች መሆን አለበት፡፡

በሰውነት ላይ ንቅሳትን ማድረግ ወይም አሳይቶ መገኘት ያስቀጣል፡፡
2. በትምህርት ቤት ውስጥ የተከለከሉ ነገሮች፡-

ማንኛውም ተማሪ ሞባይል ስልክ እና የሙዚቃ ማዳመጫ ወደ ትምህርት ቤት ግቢ ማስገባት አይችልም፡፡

እንደ "ክሬዚ ዴይ"፣ "ቫላንታይን"፣ "ከለር ዴይ" እና የመሳሰሉ የውጭ ባህል ያላቸውን በዓላት ትምህርት ቤት ውስጥ ማክበር በጥብቅ ተከልክሏል፡፡

ማንኛውም የፖለቲካ እና የኃይማኖት እንቅስቃሴ ማድረግ ወይም ምልክቶችን ይዞ መገኘት አይፈቀድም፡፡
3. በትምህርት ቤቶች ዙሪያ (በ500 ሜትር ራዲየስ)
የተከለከሉ ንግዶች፡-
የትምህርት ቤት አካባቢን ከረብሻ ነፃ ለማድረግ የሚከተሉት ተቋማት ከትምህርት ቤቶች ቢያንስ 500 ሜትር መራቅ እንዳለባቸው ረቂቁ አዘዞል፡-

የጫት፣ የሺሻ እና የአልኮል መሸጫዎች

ፑል፣ ጆተኒ፣ ፕሌይ ስቴሽን፣ እና ፊልም ቤቶች (DSTV)

የእንግዳ ማረፊያዎች እና ማሳጅ ቤቶች
ቅጣቱ ምንድን ነው?
ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በተደጋጋሚ የዲሲፕሊን ጥፋት ካጠፉ እንደ ጥፋቱ ክብደት እስከ 1 ዓመት ከትምህርት ሊታገዱ እንደሚችሉ መመሪያው አስቀምጧል፡፡
Via ሸገር ኤፍ ኤም
ይህ አዲስ መመሪያ በትምህርት ጥራት እና በተማሪዎች ሥነ-ምግባር ላይ ለውጥ ያመጣል ብለው ያስባሉ? ሀሳብዎን ያጋሩን!

በሐዋሳ (ኢንደስትሪያል ፓርክ) ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ በሚገኘው ቶዮ ሶላር ካምፓኒይ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች በቻይና አለቆቻቸው ድብደባና ጥቃት እየደረሰባቸው እንደሆነ እና ስለጉዳዩ ደጋግመን ብናመልከትም የሚሰማን አጥተናል ሲሉ የፋብሪካው ሰራተኞች ነግረውኛል።
ይህ የምታዩት ወጣትም በአንድ ቻይናዊ ራሱን እስኪስት ድረስ ድብደባ ተፈፅሞበት ነው። ተደብዳቢው የፋብሪካው ሰራተኛ የህክምና እርዳታ ለማግኘት ወደ ሆስፒታል እየተወሰደ ባለበት ወቅትም ራሱ ቻይናዊው ስሜታዊ ሆኖ ነበርም ብለውኛል።
ቶዮ ሶላር ከፀሐይ ብርሃን ኃይል ማመንጨት የሚያስችሉ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ሶላር ፓናሎችን እያመረተ የሚገኝ ፋብሪካ ነው::
Via Minase wako
ቪዲዮውን የጉርሻ ቲጂ ላይ ተመልከቱት
ከዚህ ቀደም የዛሬ 4 ዓመት ገደማ በአፍሪካዊቷ ሀገር ኬንያ ቻይናዎች ተመሳሳይ ነገር ሲያደርጉ ነበር በጊዜው በኬንያ መንግስት በህግ እንደተቀጡ ጉርሻዎች ፖስተንም ነበር::
አሁን ደሞ ይሄ ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ መጥቷል::

11/20/2025

በዚህ ስራ በጠፋበት ዘመን የኦንላይን ስራ እናሰራችሁ እያሉ የሚያጭበረብሩ ከውጭ ሀገርም ከሀገር ውስጥ ስለበዙ እባካችሁ እንዳትጭበረበሩ ተጠንቀቁ። #ተጠንቀቁ

*** ሰበር የሚዲያው ተጽእኖ ድል እንደቀጠለ ነው። በሴቶች እግርኳ ተጫዋቾች ላይ የነበረው የሚዲያ ቅሬታ እልባት ሊያገኝ ነው። አስቸኳይ መግለጫ! *** የኢትዮጵያ የሴቶች እግር ኳስ አሠልጣ...
11/19/2025

*** ሰበር የሚዲያው ተጽእኖ ድል እንደቀጠለ ነው። በሴቶች እግርኳ ተጫዋቾች ላይ የነበረው የሚዲያ ቅሬታ እልባት ሊያገኝ ነው። አስቸኳይ መግለጫ! ***

የኢትዮጵያ የሴቶች እግር ኳስ አሠልጣኞች ማህበር አስቸኳይ መግለጫ አውጥቷል:-
ዋና ዋና ነጥቦች፡
* ተጫዋቾች በህግ እንዲጠየቁ፣ ማገገሚያ እንዲገቡ ወይም በምክር እንዲመለሱ ውሳኔ ተላልፏል።
* የጉዳዩን አጣሪ የምርመራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ መግባቱ ተገልጿል።
* ፌዴሬሽኑ በጉዳዩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ ተጫዋቾችን የተቀበለ ክለብ ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
ሙሉ የመግለጫው ይዘትና የውይይቱ ዝርዝር
የኢትዮጵያ የሴቶች እግር ኳስ አሠልጣኞች ማህበር ከሴቶች እግር ኳስ ተጫዋቾች ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት እየተሰራጨ ባለው አሳሳቢ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል።
የመንግስት አካላት ምላሽ እና የተሰጠው አቅጣጫ
ጉዳዩ ለሚዲያ ከቀረበ በኋላ በመንግሥት አካላት ትኩረት ተሰጥቶት ሰሞኑን ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
መንግስት ለዚህ "አፀያፊ ተግባር" ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሠራ አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን፣ የሚመለከታቸውን ባለድርሻ አካላት ሰብስቦ አወያይቷል።
በውይይቱ የተሳተፉ አካላት:
* የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን
* የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
* ስፖርት ኮሚሽን
* የኢትዮጵያ የሴቶች እግር ኳስ አሠልጣኞች የሙያ ማህበር
* የኢትዮጵያ እግር ኳስ ደጋፊዎች ማህበር
* የCD ስፖርት አዘጋጆች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት።
በጉዳዩ ላይ የተላለፉ ቁልፍ ውሳኔዎች
በስብሰባው ላይ ጉዳዩን የሚያጣራ የምርመራ ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ መገባቱ ተገልጿል።
በዚህ ተግባር ተሳታፊ ሆነው ጉዳያቸው በማስረጃ የተረጋገጠ ተጨዋቾች ላይ በደረጃው የሚከተሉት ውሳኔዎች እንደሚሰጡ ተመላክቷል፦
* በህግ እንዲጠየቁ
* ማገገሚያ እንዲገቡ
* በምክር እንዲመለሱ
* የፌዴሬሽኑ አቋም:
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለዚህ ተግባር በቂ እርምጃ እንደሚወሰድ ያረጋገጠ ሲሆን፣ በጉዳዩ ላይ በቂ ማስረጃ የተገኘባቸው ተጫዋቾች በየትኛውም ክለብ ገብተው እንደማይጫወቱ አሳውቋል።
እነዚህን ተጫዋቾች የተቀበለ ክለብ ላይም እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል። አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ፌዴሬሽኑ ሊጉን ለመዝጋት ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
* ሁሉም የፕሪሚየር ሊግ እና የከፍተኛ ሊግ ክለቦች አድራሻቸውን ለፖሊስ እንዲያሳውቁ ጥብቅ መመሪያ ተላልፏል።
ፖሊስና ኢንሳ በፈለጉበት ጊዜና ሰዓት በክለቦቹ በመገኘት ምርመራ የሚያደርጉ ሲሆን የክለብ ባለቤቶችን፣ አሠልጣኞችን እና ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን አካላት እንደሚያነጋግሩ ተገልጿል።
ማህበሩ አባላቱን በሙሉ መንግስት ለሚጠይቀው ጥያቄ ተባባሪ በመሆን ይህንን አገርን እና እግር ኳስን የሚጎዳ ተግባር ለማጥፋት ጥሪ አቅርቧል።
በዚሁ ሂደት ንፁህ ለሆኑ ተጫዋቾች ከለላ ሊደረግላቸው እንደሚገባ አሳስቧል። ማህበሩ ይህንን ጎጂ ተግባር በፅኑ እንደሚያወግዝ እና ንፁህ ዜጋና ንፁህ እግር ኳስ በሴቶች እንዲኖር እንደሚሰራ አረጋግጧል።
ምንጭ: የኢ/የሴ/እ/አሠ/የሙያ ማህበር
ቀን: ህዳር 10/03/18 ዓ/ም
በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ /ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል/ የቀረበ ነው።

11/18/2025

ወላጆች በዚህ ውጥንቅጥ ጊዜ መጠንቀቅ ያለባችሁ ነገር!

*** ሰበር የ13 አመት ሴት ልጅ በስለት ጉዳት ደረሰባት***ርብቃ የምትባል ልጅ(13አመቷ ነው) በአንድ ቤተሰብ ውስጥ በአዲስ አበባ ከተማ 24 ኮንዶሚኒየም ሰፈር የቤት ሰራተኛ ሆና በመስራ...
11/18/2025

*** ሰበር የ13 አመት ሴት ልጅ በስለት ጉዳት ደረሰባት***

ርብቃ የምትባል ልጅ(13አመቷ ነው) በአንድ ቤተሰብ ውስጥ በአዲስ አበባ ከተማ 24 ኮንዶሚኒየም ሰፈር የቤት ሰራተኛ ሆና በመስራት እያለች በአሰሪዋ በአንዲት እርጉዝ ሴት ፊትዋን በጋለ ቢለማ ያቆሰለች ድርጊቱን ከፈፀመች በኋላ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውላለች!
ድርጊቱን የፈጸመችው ሴት እና ባለቤቷ በመገናኛ አካባቢ በሚገኘው ጬፌ ፖሊስ ጣቢያ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል።
እንደዚህ አይነት ጭካኔ አንድ እርጉዝ ከሆነች ግለሰብ መፈፀሙ እያነጋገረ ነው!!

Address

Toronto, ON

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tikus Neger posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tikus Neger:

Share

Category