ETV ዜና

ETV ዜና Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ETV ዜና, Newspaper, washington, Toronto, ON.

ነዳጅ መሬት ላይ በማርከፍከፍ ምረቃውን ያከበረው ማደያ ተቀጣለህዝብ ጥቅም የሚውልን ነዳጅ ያላአግባብ ያፈሰሱ አካላት እገዳ ተጣለባቸውከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጥቶበት ወደ አገር የሚገባን ነዳጅ...
01/10/2026

ነዳጅ መሬት ላይ በማርከፍከፍ ምረቃውን ያከበረው ማደያ ተቀጣ

ለህዝብ ጥቅም የሚውልን ነዳጅ ያላአግባብ ያፈሰሱ አካላት እገዳ ተጣለባቸው

ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጥቶበት ወደ አገር የሚገባን ነዳጅ ኃላፊነት በተሞላው መንግድ ለህዝብ ጥቅም ማዋል ሲገባው ያለአግባብ እንዲፈስ ያደረገ ማደያ ለሶስት ወር ከነዳጅ ጭነት ትስስር እገዳ ተጣለበት፡፡

በአርሲ ዞን ዳክሲሰ በሚባል ቦታ ሥራ የጀመረ ግሎባል የሚባል ማደያ ከነዳጅ መቅጃ ማሽን ነዳጅን ሲያርከፈክፍ በማህበራዊ ትስስር ገፆች መታየቱን ተከትሎ ባለስልጣኑ ጉዳዩን በማጣራት ድርጊቱን መፈጸሙን በማረጋገጡ ይህን ድርጊት የፈጸመው ማደያ በነዳጅ ግብይት አዋጅ ቁጥር 1363/2017 አንቀጽ 7(10)ስር ያለዉን ግዴታ በመጣስ በአንቀጽ 11(9)መሠረት ህገ ወጥ ድርጊት ፈጽሞ ስለተገኘ የወንጀል ተጠያቂነቱ የሚቀጥል ሆኖ በአዋጁ አንቀጽ 23(1)መሠረት ለ3ወራት ፈቃዱ ታግዷል፡፡

ከባለስልጣን መ/ቤቱ የማደያ ፈቃድ አውጥተው ምርቱን ለህብረተሰቡ በአግባቡ ተደራሽ ለማድረግ ፈቃድ ሲሰጥ ከሚገቡ የፈቃድ ግዴታዎች መካከል አንዱ የነዳጅ ደህንነቱን እና ደረጃውን በጠበቀ ማዳያ በቂ የሆነ የድንገተኛ አደጋ መከላከያ ግብዓቶችን አሟልቶ በወጣው የእለታዊ ዋጋ በጥብቅ ዲስፕሊን እና ጥንቃቄ ለተጠቃሚው መሸጥ ግዴታዎችን የጣሱ በመሆኑ ባለስልጣን መ/ቤቱ ጉዳዩን ተከታትሎ ተገቢው የህግ ውሳኔ ተፈጻሚ እንዲሆን ክትትል እንደሚያደርግ ይታወቅልኝ ብሏል። ህገወጥ የነዳጅ ግብይትን የመከላከል ስራ የመላው ህዝብ ኃላፊነት በመሆኑ ይህን ድርጊት ለጠቆሙ ወገኖችም ምስጋናውን አቅርቧል።

''ተጠባቂ እለት'' የሩሲያ እና  የዩናትድ አረብ ኢምሬት የጦር ጄቶች በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ሊበሩ ነው። ሩሲያን ጨምሮ የአምስት ሀገራት አየር ኃይሎች ቢሾፍቱ ላይ የሚያሳዩት ተጠባቂው ትርኢ...
01/05/2026

''ተጠባቂ እለት'' የሩሲያ እና የዩናትድ አረብ ኢምሬት የጦር ጄቶች በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ሊበሩ ነው።

ሩሲያን ጨምሮ የአምስት ሀገራት አየር ኃይሎች ቢሾፍቱ ላይ የሚያሳዩት ተጠባቂው ትርኢት በጥቁር አንበሳ" ተሰይሟል።

ተሳታፊ ሀገራት፡-
🇪🇹 የኢትዮጵያ
🇷🇺 የሩሲያ
🇦🇪 የተባበሩት የአረብ ኤምሬቶች
🇲🇦 የሞሮኮ እና
🇨🇿 የቼክ ሪፐብሊክ አየር ኃይሎች እንደሆኑ ተሰምቷል።

ከጥር 15-19/2018ዓም የኢትዮጵያ አየር ኃይል ምሥረታ 90ኛ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ በአይነቱ ልዩ የሆነ ትርኢት እንደሚደረግ ከሰጠው ገለፃ ለመረዳት ተችሏል።

የኢትዮጲያን ሰማይ ለሰው ሀገር የጦር ጄት ማብረሪያ መፈቀድ ተገቢ ነው ይላሉ? ሀሳብዎን ያካፍሉን?

አሜሪካ በቬንዙዌላ የሚገኘውን የሩሲያ የጸረ-አውሮፕላን መከላከያ ደመሰሰች ታህሳስ 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በደቡብ አሜሪካ የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ግጭት ወደ ከፋ ደረጃ መሸጋገሩን ተ...
01/05/2026

አሜሪካ በቬንዙዌላ የሚገኘውን የሩሲያ የጸረ-አውሮፕላን መከላከያ ደመሰሰች

ታህሳስ 26 ቀን 2018(መናኸሪያ ሬዲዮ) በደቡብ አሜሪካ የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ግጭት ወደ ከፋ ደረጃ መሸጋገሩን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር በቬንዙዌላ የሚገኘውን የሩሲያ ስሪት ቡክ-ኤም 2 ኢ (Buk-M2E) የዘመነ የአየር መከላከያ ዘዴን ሙሉ በሙሉ ማውደሙ ተረጋግጧል።

በሚሊታርኒ እና ሌሎች የደህንነት ምንጮች የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ ጥቃቱ የተፈጸመው በካራካስ ከተማ በሚገኘው ላ ካርሎታ ወታደራዊ አየር ማረፊያ ላይ ሲሆን ይህም የማዱሮ አገዛዝ የአየር ክልሉን ለመከላከል የነበረውን አቅም በእጅጉ አዳክሞታል።
ይህ የአየር ድብደባ አሜሪካ በምዕራቡ ንፍቀ ክበብ የሚገኘውን የሩሲያ ወታደራዊ ቁሳቁስና ተፅዕኖ በቀጥታ ኢላማ ያደረገችበት እርምጃ ተደርጎ ተወስዷል።
ጥቃቱ የተፈጸመው አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ በጀመረችው ሰፊ ወታደራዊ ዘመቻ ውስጥ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ወቅት ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ በአሜሪካ ልዩ ኃይሎች ተይዘው ለፍርድ ወደ ኒውዮርክ መወሰዳቸው የአለምን ትኩረት ስቧል።

የአሜሪካ ጦር ከዚህ መከላከያ ዘዴ በተጨማሪ በሩሲያ የተሰሩ ኤስ-300 (S-300) የተሰኙ የረጅም ርቀት ሚሳኤል መቃወሚያዎችንም መደምሰሱ ተዘግቧል።

በአሁኑ ወቅት በቬንዙዌላ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚታይ ሲሆን፣ የሩሲያ የጦር መሳሪያዎች የአሜሪካን ጥቃት መቋቋም አለመቻላቸው በሞስኮ እና በዋሽንግተን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ይበልጥ አፋፍሞታል።

የኒኮላስ ማዱሮ የፖለቲካ ጉዞ ከባስ አሽከርካሪነት እስከ ፕሬዝዳንትነትኒኮላስ ማዱሮ ለብዙ ዓመታት በቬንዙዌላ ፖለቲካ ውስጥ ቁልፍ ሰው የነበሩ ሲሆን ወደ ስልጣን ማማው የወጡት እና ፖለቲካ ከ...
01/05/2026

የኒኮላስ ማዱሮ የፖለቲካ ጉዞ ከባስ አሽከርካሪነት እስከ ፕሬዝዳንትነት

ኒኮላስ ማዱሮ ለብዙ ዓመታት በቬንዙዌላ ፖለቲካ ውስጥ ቁልፍ ሰው የነበሩ ሲሆን ወደ ስልጣን ማማው የወጡት እና ፖለቲካ ከመጀመራቸው በፊት በካራካስ ከተማ የሕዝብ ትራንስፖርት (ባስ) አሽከርካሪ ነበሩ በወቅቱ በነበራቸው ጠንካራ የተቃውሞ እና የንግግር ችሎታ የሰራተኞች ማህበር መሪ በመሆን ታዋቂነትን አትርፈዋል።

የማዱሮ የፖለቲካ ህይወት የተቀየረው የቀድሞውን የቬንዙዌላ ፕሬዝዳንት ሁጎ ቻቬዝን ካወቁ በኋላ ነው።

እ.ኤ.አ. በ1992 ቻቬዝ በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ታስረው በነበረበት ወቅት ማዱሮ እና የወደፊት ባለቤታቸው ሲሊያ ፍሎሬስ (ጠበቃ ነበሩ) ቻቬዝ እንዲፈቱ ከፍተኛ የቅስቀሳ ስራ ሰርተዋል።

ቻቬዝ እ.ኤ.አ. በ1998 ፕሬዝዳንት ሆነው ከተመረጡ በኋላ ማዱሮ በፍጥነት በስልጣን እርከኖች ላይ ወጡ፦

* እ.ኤ.አ. 2000-2006፦ የብሔራዊ ምክር ቤት (ፓርላማ) አባል እና በኋላም አፈ-ጉባኤ ሆኑ።

* እ.ኤ.አ. 2006-2012፦ የቬንዙዌላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመሆን ለ6 ዓመታት አገልግለዋል።

* እ.ኤ.አ. 2012፦ በፕሬዝዳንት ቻቬዝ ተወካይ (ምክትል ፕሬዝዳንት) ሆነው ተሾሙ።

ሁጎ ቻቬዝ በካንሰር በሽታ ምክንያት ህይወታቸው ከመለፉ በፊት ማዱሮ ተተኪያቸው እንዲሆኑ በይፋ ተናግረው ነበር።

እ.ኤ.አ. መጋቢት 2013 ቻቬዝ ሲያርፉ ማዱሮ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ሆኑ።

ከአንድ ወር በኋላ በተካሄደው ልዩ ምርጫ ተቃዋሚያቸውን ሄንሪኬ ካፕሪሌስን በጠባብ ውጤት በማሸነፍ በይፋ ፕሬዝዳንት ሆኑ።

ማዱሮ እ.ኤ.አ. በ2018 ለሁለተኛ ጊዜ መመረጣቸውን ቢያውጁም አሜሪካን ጨምሮ በርካታ የምዕራብ ሀገራት ምርጫው ፍትሃዊ አይደለም በማለት ሳይቀበሉት ቀርተዋል።

በቅርቡ እ.ኤ.አ. በ2024 በተካሄደው ምርጫም በተመሳሳይ ውዝግብ ውስጥ የቆዩ ሲሆን በመጨረሻም እ.ኤ.አ. ጥር 3 ቀን 2026 በአሜሪካ ልዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ውለዋል።

አሰብን ወደ ኢትዮጵያ ያካለለው ካርታ በመከላከያ ገፅ ላይ ተመልክተናል። ዛሬ የብላቴ ማሠልጠኛ ማዕከል ያሠለጠናቸው ምልምል ወታደሮች ሲያስመርቅ አዲስ ነገር ታይቷል።የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠል...
01/05/2026

አሰብን ወደ ኢትዮጵያ ያካለለው ካርታ በመከላከያ ገፅ ላይ ተመልክተናል።

ዛሬ የብላቴ ማሠልጠኛ ማዕከል ያሠለጠናቸው ምልምል ወታደሮች ሲያስመርቅ አዲስ ነገር ታይቷል።

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሠልጠኛ ማዕከል ለወራት ያሰለጠናቸውን መሠረታዊ ምልምል ወታደሮችን ነው በዛሬው ያስመረቀው።በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ በተደረገ የሽልማት ስነ ስርዓት ላይ አሰብን ወደ ኢትየዮጵያ ያካለለ ካርታ ተበርክቷል።ምስሉ በመከላከያ ይፋዊ ገፅ ላይ ሰፍሯል።

🗣️ ጄራርድ ፒኬ ስለ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሲናገር 🇵🇹"ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በሁሉም ነገር የተሟላ ተጫዋች ነው። እሱ እውነተኛ የጎል ማሽን። https://app.buzzerfan.com/home/re...
12/23/2025

🗣️ ጄራርድ ፒኬ ስለ ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሲናገር 🇵🇹

"ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በሁሉም ነገር የተሟላ ተጫዋች ነው። እሱ እውነተኛ የጎል ማሽን።

https://app.buzzerfan.com/home/reels/d43bda64-543a-4da8-b666-ffaad4acbbe2

ከእሱ ጋር መጫወት እጅግ በጣም ከባድ ነበር።

ሁሉንም ነገር ነበረው - የቀኝ እግር፣ የግራ እግር፣ የጭንቅላት ኳስ፣ የፍፁም ቅጣት ምት፣ ፣ ኃይል፣ ፍጥነት… ሁሉም ነገር። ፍጹም የሆነ የሰውነት ብቃት ተጫዋች ነው።" ሲል ተናግሯል

በጋዛ በትምህርት ቤት ላይ በተፈጸመ የእስራኤል ጥቃት 6 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ።የቅርብ ጊዜውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ እስራኤል 6 ፍልስጤማውያን በጋዛ ወደ ትምህር ቤት በተቀየረ መ...
12/21/2025

በጋዛ በትምህርት ቤት ላይ በተፈጸመ የእስራኤል ጥቃት 6 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ።

የቅርብ ጊዜውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ እስራኤል 6 ፍልስጤማውያን በጋዛ ወደ ትምህር ቤት በተቀየረ መጠለያ ላይ ባደረሰችው ጥቃት መግደሏ ተዘግቧል።

በጥቃቱ ህጻናትን ጨምሮ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸው ተነግሯል።

ጥቃቱ የደረሰው በምስራቅ ጋዛ ከተማ ቱፋህ ሰፈር በሚገኘው ትምህርት ቤት ላይ ነው ተብሏል።

የአሜሪካው ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ፥ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ በሚቀጥለው ምዕራፍ ላይ ለመወያየት የኳታር፣ ግብፅ እና ቱርኪዬ ከፍተኛ ባለስልጣናትን በማያሚ፣ ፍሎሪዳ ያስተናግዳሉ።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፥ ሀማስን ትጥቅ ማስፈታት ይገባል ሲሉ ያሳሰቡ ሲሆን፥ አንድ የሃማስ ከፍተኛ ባለስልጣን በበኩላቸው ንግግሮቹ የእስራኤልን የተኩስ አቁም ጥሰቶች ለማስቆምም መሆን አለባቸው ማለታቸውን የዘገበው አልጀዚራ ነው።

ግማሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ ሲቀበሉ "እጅ ከፍንጅ" የተያዙት የፍትሕ ሚኒስቴር ዐቃቤ ሕግ እና ግብረ አበሮቻቸው ክስ ተመሰረተባቸውበፍትሕ ሚኒስቴር የዐቃቤ ሕግነት የሥራ መደብ ላይ ተመድበው ሲሰሩ...
12/19/2025

ግማሽ ሚሊዮን ብር ጉቦ ሲቀበሉ "እጅ ከፍንጅ" የተያዙት የፍትሕ ሚኒስቴር ዐቃቤ ሕግ እና ግብረ አበሮቻቸው ክስ ተመሰረተባቸው

በፍትሕ ሚኒስቴር የዐቃቤ ሕግነት የሥራ መደብ ላይ ተመድበው ሲሰሩ የነበሩ ግለሰብ እና ግብረ አበሮቻቸው፣ ከአንድ ባለጉዳይ 1 ሚሊዮን ብር ጉቦ ለመቀበል ሲደራደሩና ግማሽ ሚሊዮኑን ተቀብለው ደረሰኝ ሲሰጡ "እጅ ከፍንጅ" ተይዘው ክስ እንደተመሰረተባቸው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አስታወቀ።

እንደ ሚኒስቴሩ መግለጫ፣ ተከሳሾቹ በወንጀል ተጠርጥረው በምርመራ ላይ በነበሩ ግለሰብ ላይ "የወንጀል ክስ እንዳይቀርብ እናደርጋለን" በማለት 1 ሚሊዮን ብር እንዲከፈላቸው ሲደራደሩ ቆይተዋል።

ይህንን ድርጊት የተገነዘቡ ጠቋሚዎች ለፍትሕ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች መረጃውን በማቀበላቸው፣ ከፌዴራል ፖሊስ ጋር በመቀናጀት ጥብቅ ክትትል ሲደረግ ቆይቷል።

ሕዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም ተከሳሾቹ ከባለጉዳዩ ቤተሰቦች 500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር ለጊዜው ባልተያዘ ግብረ አበራቸው የባንክ ሒሳብ በኩል እንዲገባ ካደረጉ በኋላ....

አሜሪካ በየዓመቱ የምታካሂደውን የዲቪ ሎተሪ አቆመች!ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት በብራውን ዩኒቨርሲቲ በተፈጸመ የጅምላ ጥቃት ሁለት ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ የአሜሪካን ግሪን ...
12/19/2025

አሜሪካ በየዓመቱ የምታካሂደውን የዲቪ ሎተሪ አቆመች!

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት በብራውን ዩኒቨርሲቲ በተፈጸመ የጅምላ ጥቃት ሁለት ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ የአሜሪካን ግሪን ካርድ ሎተሪን (ዲቪ) አገዱ።ጥቃቱን ፈጽሟል ተብሎ የተጠረጠረው እና ሐሙስ ዕለት ሞቶ የተገኘው ፖርቹጋላዊው በአውሮፓውያኑ 2017 ዲቪ ሎተሪ አሸንፎ ወደ አገሪቱ የገባ ሲሆን ግሪን ካርድም ተሰጥቶታል።

የአገር ውስጥ ደኅንነት ሚኒስትር የሆኑት ክሪስቲ ኖም "በዚህ አስከፊ ፕሮግራም አሜሪካውያን ከእንግዲህ እንዳይጎዱ ለማረጋገጥ" በሚል ትራምፕ በሰጡት መመሪያ መሠረት የቪዛ መርሃ ግብሩን ለጊዜው እንዲቋረጥ መደረጉን ተናግረዋል።የአሜሪካ ባለሥልጣናት ተጠርጣሪው የ48 ዓመቱ ክላውዲዮ ኔቭስ ቫለንቴ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ የማሳቹሴትስ የቴክኖሎጂ ተቋም ፕሮፌሰር ኑኖ ሉሬሮንም ገድሏል ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራሙ በአሜሪካ በስደተኝነት በቂ ድርሻን ላላገኙ አገራት ዜጎች በየዓመቱ 50 ሺህ ቪዛዎችን ይሰጣል። ይህ ደግሞ የአሜሪካ ዜግነትን ለማግኘትም በር ከፋች ነው።ኖም በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ትራምፕ ቀደም ሲል በኒው ዮርክ ከተማ ስምንት ሰዎች በጭነት መኪና ተገጭተው ከተገደሉ በኋላ ፕሮግራሙን ለማስቆም "ታግለዋል" ብለዋል።

ኖም እንዳሉት የኡዝቤኪስታን ተወላጅ የሆነው ሳይፉሎ ሳይፖቭ፣ የኢስላሚክ ስቴት ደጋፊ የሆነ እና ለተፈጸሙ ጥቃቶች በርካታ የዕድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት ግለሰብ በዲቪ1 ፕሮግራም መሠረት ወደ አሜሪካ ገብቷል።

''ቤተክርስቲያን ለዶክተር አብይ ትፀልያለች'' አቡነ ሳዊሮስ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ለጠቅላይ ሚኒስትር  አብይ አህመድ አሊ ሳትፀልይ ውላ አድራ አታውቅም ትፀልይለታለች ብለዋል አቡነ ሳዊ...
12/19/2025

''ቤተክርስቲያን ለዶክተር አብይ ትፀልያለች'' አቡነ ሳዊሮስ

የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አሊ ሳትፀልይ ውላ አድራ አታውቅም ትፀልይለታለች ብለዋል አቡነ ሳዊሮስ

አክለውም ኢትዮጵያ በዘመኗ እንደ ዶክተር አብይ አህመድ ያለ መሪ አግኝታ አታውቅም ያሉ ሲሆን በእጅ የያዙት ወርቅ እንደ መዳብ ይቆጠራል እንደሚባለው ተረት ሆነና ነውጅ ለመሪያችን በየ እምነታችን ነጋ ጠባ መፀለይ አለብን ሲሉ ተደምጠዋል።

አቡነ ሳዊሮስ ከሰሞኑ ከተናገሩት የተወሰደ

FAM ዛሬ አሪፍ የሆነ information ላጋራቹ 👀ልክ እንደ YouTube  ነው 🫴 Long Video በማየት እና በመልቀቅ   Like,  Comment, Subscribe በማድረግ Dollar ...
12/15/2025

FAM ዛሬ አሪፍ የሆነ information ላጋራቹ 👀
ልክ እንደ YouTube ነው 🫴

Long Video በማየት እና በመልቀቅ
Like, Comment, Subscribe በማድረግ

Dollar 💰(USDT $) መስራት የምትችሉበት
⚡️ ገራሚ App አለ

https://app.buzzerfan.com/referral-invite/rs1748dbe85fd0488e990f2f99901c9937

በ ፈለጋችሁት ሰዓት Withdrew ማድረግ ትችላላችሁ ✌️

Withdrawal proof 100% ✅

💵 App Link 👉 👇👇
https://app.buzzerfan.com/referral-invite/rs1748dbe85fd0488e990f2f99901c9937

https://app.buzzerfan.com/home/reels/a837627f-0f3b-4e7e-98a0-b3ff71dec4c8

You've been invited by Solomon Ayal to join Buzzer. Sign up now and instantly receive Buzzer Points as a welcome gift.

የትግራይ ኃይሎች ከምክትል ፕሬዝዳንቱ ጋር ንግግር ቢያደርጉም የፕሬዚዳንት ጽ/ቤትን ለቀው ለመውጣት ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተገለፀ!መቀሌ፡ የትግራይ ኃይሎች ዛሬ ሐሙስ ጠዋት በመቀለ የሚገኘውን ...
12/04/2025

የትግራይ ኃይሎች ከምክትል ፕሬዝዳንቱ ጋር ንግግር ቢያደርጉም የፕሬዚዳንት ጽ/ቤትን ለቀው ለመውጣት ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተገለፀ!

መቀሌ፡ የትግራይ ኃይሎች ዛሬ ሐሙስ ጠዋት በመቀለ የሚገኘውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ዙሪያ ለአጭር ጊዜ ከበባ አድርገው በቅጥር ግቢው ዙሪያ እንቅስቃሴና ትራንስፖርት ተስተጓጎለ።

አዲስ ስታንዳርድ እንዳረጋገጠው፣ ኃይሎቹ ወደ ጽህፈት ቤቱ የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት ጽ/ቤቱን ከበዋል። በዚህም የፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት እና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሰራተኞች እንዳይገቡ ከልክለው ውጪ እንዲቆዩ አስገድደዋል።

የአዲስ ስታንዳርድ ምንጮች እንደጠቆሙት፣ ወደ 70 የሚጠጉ የአርሚ 31 ወታደሮች በክስተቱ ውስጥ ተሳትፈዋል።

በስፍራው የሚገኝ የአዲስ ስታንዳርድ ዘጋቢ እንዳረጋገጠው፣ ኃይሎቹ በኋላ ላይ የከበቡትን አካባቢ መንገዶች ለቀው በመውጣታቸው ትራፊክ እና መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲቀጥል የተደረገ ሲሆን ከፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት መግቢያ በር ግን ለወው አልወጡም።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አማኑኤል አሰፋ ከኃይሎቹ ጋር መነጋገራቸው የተገለፀ ቢሆንም፤ ኃይሎቹ ከፕሬዝዳንቱ ጋር ስብሰባ ለማድረግ ካልተፈቀደላቸው በስተቀር ለመልቀቅ ፍቃደኛ አልሆኑም ሲሉ ምንጮች ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል፡፡

Address

Washington
Toronto, ON

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ETV ዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category