
06/22/2025
"ትራምፕን አመሰግናለሁ፤ ታሪክ ቀያሪ ስራ ነው የሰራው"
- ቤንያሚን ኔታንያሁ
+++++++++++++++
| የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ቦታዎች ላይ የቦምብ ጥቃት በማድረሳቸው አመስግነዋለሁ አሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር አሜሪካ የኢራንን የኒውክሌር ዒላማዎች ለማጥቃት መወሰኗ ትክክል መሆኑን ገልጸው፤ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በከፍተኛ ኃይል የወሰዱት እርምጃ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል ብሏል ሮዮርተርስ።
ኔታንያሁ አክለውም ትራምፕ በጣም አደገኛ የሆነውን መንግስት እጅግ አደገኛ መሳሪያ እንዳይጠቀም ለማድረግ የወሰዱት እርምጃ እንደሆነ በታሪክ ይመዘገባል ብለዋል።
የዩኤስ የጦር አውሮፕላኖች የኢራንን ሶስት የኒውክሌር ዒላማዎች ማለትም ፎርዶው፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃን ላይ በጣም የተሳካ ጥቃት መፈጸማቸውን ዋይት ሀውስ ካረጋገጠ በኋላ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት።
የእስራኤል ባለስልጣንን ጠቅሶ የእስራኤል ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን እንደዘገበው፤ ቴል አቪቭ በኢራን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አሜሪካን ሙሉ በሙሉ አስተባብራለች።
ከፍተኛ ባለስልጣኑ ትራምፕ ጥቃቱን የሚፈጽምበትን ጊዜ ለናታንያሁ ትናንት ምሽት ማሳወቃቸውን አስታውቀዋል ብለዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጥቃቱ በኋላ በትራምፕ እና በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ መካከል የስልክ ጥሪ መደረጉን የእስራኤል ዘገባዎች አመልክተዋል።