ETV ዜና

ETV ዜና Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ETV ዜና, Newspaper, washington, Toronto, ON.

FAM ዛሬ አሪፍ የሆነ information ላጋራቹ 👀ልክ እንደ YouTube  ነው 🫴 Long Video በማየት እና በመልቀቅ   Like,  Comment, Subscribe በማድረግ Dollar ...
12/15/2025

FAM ዛሬ አሪፍ የሆነ information ላጋራቹ 👀
ልክ እንደ YouTube ነው 🫴

Long Video በማየት እና በመልቀቅ
Like, Comment, Subscribe በማድረግ

Dollar 💰(USDT $) መስራት የምትችሉበት
⚡️ ገራሚ App አለ

https://app.buzzerfan.com/referral-invite/rs1748dbe85fd0488e990f2f99901c9937

በ ፈለጋችሁት ሰዓት Withdrew ማድረግ ትችላላችሁ ✌️

Withdrawal proof 100% ✅

💵 App Link 👉 👇👇
https://app.buzzerfan.com/referral-invite/rs1748dbe85fd0488e990f2f99901c9937

https://app.buzzerfan.com/home/reels/a837627f-0f3b-4e7e-98a0-b3ff71dec4c8

You've been invited by Solomon Ayal to join Buzzer. Sign up now and instantly receive Buzzer Points as a welcome gift.

የትግራይ ኃይሎች ከምክትል ፕሬዝዳንቱ ጋር ንግግር ቢያደርጉም የፕሬዚዳንት ጽ/ቤትን ለቀው ለመውጣት ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተገለፀ!መቀሌ፡ የትግራይ ኃይሎች ዛሬ ሐሙስ ጠዋት በመቀለ የሚገኘውን ...
12/04/2025

የትግራይ ኃይሎች ከምክትል ፕሬዝዳንቱ ጋር ንግግር ቢያደርጉም የፕሬዚዳንት ጽ/ቤትን ለቀው ለመውጣት ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተገለፀ!

መቀሌ፡ የትግራይ ኃይሎች ዛሬ ሐሙስ ጠዋት በመቀለ የሚገኘውን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ዙሪያ ለአጭር ጊዜ ከበባ አድርገው በቅጥር ግቢው ዙሪያ እንቅስቃሴና ትራንስፖርት ተስተጓጎለ።

አዲስ ስታንዳርድ እንዳረጋገጠው፣ ኃይሎቹ ወደ ጽህፈት ቤቱ የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት ጽ/ቤቱን ከበዋል። በዚህም የፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት እና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሰራተኞች እንዳይገቡ ከልክለው ውጪ እንዲቆዩ አስገድደዋል።

የአዲስ ስታንዳርድ ምንጮች እንደጠቆሙት፣ ወደ 70 የሚጠጉ የአርሚ 31 ወታደሮች በክስተቱ ውስጥ ተሳትፈዋል።

በስፍራው የሚገኝ የአዲስ ስታንዳርድ ዘጋቢ እንዳረጋገጠው፣ ኃይሎቹ በኋላ ላይ የከበቡትን አካባቢ መንገዶች ለቀው በመውጣታቸው ትራፊክ እና መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲቀጥል የተደረገ ሲሆን ከፕሬዚዳንቱ ጽህፈት ቤት መግቢያ በር ግን ለወው አልወጡም።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት አማኑኤል አሰፋ ከኃይሎቹ ጋር መነጋገራቸው የተገለፀ ቢሆንም፤ ኃይሎቹ ከፕሬዝዳንቱ ጋር ስብሰባ ለማድረግ ካልተፈቀደላቸው በስተቀር ለመልቀቅ ፍቃደኛ አልሆኑም ሲሉ ምንጮች ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግረዋል፡፡

ከአየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ በወንጀል የተከሰሱት እነ ዮሃንስ ዳንኤል ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ተሰጠአዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1...
12/03/2025

ከአየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ በወንጀል የተከሰሱት እነ ዮሃንስ ዳንኤል ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ልዩ ልዩ ከባድ ወንጀል ችሎት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ በወንጀል የተከሰሱት እነ ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል) በእስራት እንዲቀጡ ወስኖ የታሰሩት በቂ ስለሆነ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጠ።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ በዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ እና ይዲድያ ነጻነት ላይ በነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ በግምት 3፡30 ሰዓት ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ ወደ መቐለ ከተማ ለመጓዝ አውሮፕላኑ ለበረራ ዝግጁ ቢሆንም የአየር ሁኔታ ለበረራ አዳጋች በመሆኑ በረራው ቢደረግ የሚያደርሰውን ከባድ አደጋ ለመከላከል ጉዞው ተሰርዞ መንገደኞች ከአውሮፕላኑ እንዲወርዱ ሲነገራቸው በረራው በግድ መደረግ አለበት አንወርድም በማለት ቀሪ ተሳፋሪዎችም እንዳይወርዱ በመክልከል አሳድመዋል በሚል በዝርዝር ጠቅሶ ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በተጨማሪም ዐቃቤ ሕግ 1ኛ ተከሳሽ ጆን ዳንኤል ላይ በ3ኛ ክስ የኮምፒዩተር ወንጀል ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 958/2008 አንቀጽ 13 ንዑስ ቁጥር 3 ሥር የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ ክስተቱን ቲክቶክ በተባለ ማህበራዊ ሚዲያ በተንቀሳቃሽ ምስል ቀርጾ በቀጥታ ስርጭት ማስተላለፍ የሚል ክስ አቅርቦበት ነበር።

ተከሳሾቹ በተከሰሱበት የህግ አንቀፅ ጥፋተኛ የተባሉ ሲሆን ችሎቱ በዛሬው ዕለት የዐቃቤ ሕግን የቅጣት ማክበጃ እና የተከሳሾችን የቅጣት ማቅለያ መርምሮ ውሳኔ አሳልፏል።

በዚህም ተከሶሾቹ የተከሱበት የህግ አንቀፅ ቀላል እስራትን የሚያስከትል በመሆኑ 1ኛ ተከሳሽ በአንድ አመት ከአራት ወር፤ 2ኛ፣ 3ኛ እና 6ኛ ተከሳሾች በስምንት ወር እንዲሁም 4ኛ ተከሳሽ በ10 ወር እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።

በመሆኑም ተከሳሾቹ በእስር ላይ የቆዩበት ጊዜ ተሰልቶ ተከሳሾቹ እንዲፈቱ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ልዩ ልዩ ከባድ ወንጀል ችሎት ውሳኔ አሳልፏል።

በሲፈን መኮንን

''ጠመንጃ አንስቶ የብልፅግና መንግሥት ለመገልበጥ የሚሮጥ ቡድን አልደግፍም። የ ስለ እናት ምድር ፊልም ደራሲ እና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ተሾመ''ስለ እናት ምድር'' መከላከያ ሰራዊት ይህ ፊል...
11/20/2025

''ጠመንጃ አንስቶ የብልፅግና መንግሥት ለመገልበጥ የሚሮጥ ቡድን አልደግፍም። የ ስለ እናት ምድር ፊልም ደራሲ እና ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ተሾመ

''ስለ እናት ምድር'' መከላከያ ሰራዊት ይህ ፊልም ተውንልኝ ብሎ ሲሰጠኝ ጥያቄው ኢትዮጵያዊ ነህ ወይስ አይደለህም ነበር፤ መከላከያ ይህን ታሪኬን ስራልኝ ሲል በደስታ ተቀብያለሁ ምክንያቱም ስራው ለልጆችህ የምትናገረው ሌጋሲ ነው።

እናም ይህ ስራ ለልጆቸ በኩራት የማወራው እስካሁን ከሰራሗቸው ስራዎቸ ሁሉ የምኮራበት እና ለአለም የምረጨው ስራየ ነው በማለት ተናግሯል።

ቀጥሎም መከላከያን ብቻ ነው የምደግፈው መከላከያን የምደግፈው ደግሞ የፓለቲካ ደጋፊ ስለሆንኩ ስላልሆክ አይደለም፤ መከላከያ የኢትዮጵያ ክንድ ነው። በዚህ ጉዳይ የሚሰድቡኝ አሉ መከላከያ ህይዎቱን ይሰዋየለደ እንኳን ለስድብ ሲል ተደምጧል አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ።

ቀጥሎም መከላከያን መደገፍ የኢትዮጵያዊነት ኩራት ነው ወደ ፊትም እደግመዋለሁ እኔ ሀገር ወክሎ ስለ ሀገር የሚቆም መከላከያ ደጋፊ ነኝ። ባለፈውም ነበርኩ አሁንም ነኝ ወደፊትም ነኝ ምንም አትጠራጠሩ በዚህ ሲል ተናግሯል።

እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ በኢትዮጵያ መቀጠል የማምን ስለ ኢትዮጵያ ማንኛውንም መሰዋትነት ለመክፈል የተዘጋጀሁ ጀርባየ ራሱ ወታደር የነበረ ኢትዮጵያዊ ነኝ በማለት መልሷል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ መካሄድ ጀመረየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በዛሬው ዕለት መካሄድ ጀምሯል።ጉባዔውን ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ...
10/22/2025

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በዛሬው ዕለት መካሄድ ጀምሯል።

ጉባዔውን ብፁእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በፀሎት አስጀምረዋል።

በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፤ በተለያዩ መንገዶች እየተከናወኑ የሚገኙ ቤተክርስቲያንን የመዳፈር ተግባራት ለመፍታት በሕግ አግባብ መንቀሳቀስ ይገባል።

የነገ ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን የሚሆነው ሰላምና አንድነት ሲኖር በመሆኑ ሁሉም ለሀገር ሰላምና አንድነት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም ጉባዔው የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግ አሳስበዋል።

በምልዓተ ጉባዔው ላይ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የመጡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የተገኙ ሲሆን በቤተክርስቲያኗ እና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

"ትራምፕን አመሰግናለሁ፤ ታሪክ ቀያሪ ስራ ነው የሰራው"- ቤንያሚን ኔታንያሁ+++++++++++++++  | የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ...
06/22/2025

"ትራምፕን አመሰግናለሁ፤ ታሪክ ቀያሪ ስራ ነው የሰራው"

- ቤንያሚን ኔታንያሁ
+++++++++++++++

| የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ቦታዎች ላይ የቦምብ ጥቃት በማድረሳቸው አመስግነዋለሁ አሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግር አሜሪካ የኢራንን የኒውክሌር ዒላማዎች ለማጥቃት መወሰኗ ትክክል መሆኑን ገልጸው፤ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በከፍተኛ ኃይል የወሰዱት እርምጃ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል ብሏል ሮዮርተርስ።

ኔታንያሁ አክለውም ትራምፕ በጣም አደገኛ የሆነውን መንግስት እጅግ አደገኛ መሳሪያ እንዳይጠቀም ለማድረግ የወሰዱት እርምጃ እንደሆነ በታሪክ ይመዘገባል ብለዋል።

የዩኤስ የጦር አውሮፕላኖች የኢራንን ሶስት የኒውክሌር ዒላማዎች ማለትም ፎርዶው፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃን ላይ በጣም የተሳካ ጥቃት መፈጸማቸውን ዋይት ሀውስ ካረጋገጠ በኋላ ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ያሉት።

የእስራኤል ባለስልጣንን ጠቅሶ የእስራኤል ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን እንደዘገበው፤ ቴል አቪቭ በኢራን ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አሜሪካን ሙሉ በሙሉ አስተባብራለች።

ከፍተኛ ባለስልጣኑ ትራምፕ ጥቃቱን የሚፈጽምበትን ጊዜ ለናታንያሁ ትናንት ምሽት ማሳወቃቸውን አስታውቀዋል ብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጥቃቱ በኋላ በትራምፕ እና በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ መካከል የስልክ ጥሪ መደረጉን የእስራኤል ዘገባዎች አመልክተዋል።

02/14/2025

Check out S O L A’s video.

የያህያ ሲንዋር መገደል የጦርነቱ ፍጻሜ አይደለም-  ጠ/ሚ ኔታንያሁይህን ተከትሎም የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በሰጡት መግለጫ÷ የያህያ ሲንዋር መገደል ከፍተኛ ድል ቢሆንም ...
10/18/2024

የያህያ ሲንዋር መገደል የጦርነቱ ፍጻሜ አይደለም- ጠ/ሚ ኔታንያሁ

ይህን ተከትሎም የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በሰጡት መግለጫ÷ የያህያ ሲንዋር መገደል ከፍተኛ ድል ቢሆንም የጦርነቱ ፍጻሜ እንዳልሆነ አስታውቀዋል፡፡

በዚሁ መሠረት በሀማስ እገታ ሥር የሚገኙ እስራኤላውያን እስከሚለቀቁ ድረስ ጦርነቱ ይቀጥላል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

በርካታ እስራኤላውያን እንዲገደሉ እና እንዲታገቱ በተደረገበት የጥቅምት 7 ጥቃት የያህያ ሲንዋር ሚና ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ የመሪው መገደል በአካባቢው ያለውን ሁኔታ ሊቀይረው እንደሚችል አመላክተዋል፡፡

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በበኩላቸው የያህያ ሲንዋር መገደል ለእስራኤል ብሎም ለአሜሪካ ትልቅ ድል መሆኑን ገልጸው÷ የመሪው መገደል ምን አልባትም ጦርነቱ በአጭር ጊዜ እንዲቋጭ ሊያደርገው ይችላል ብለዋል፡፡

በአንጻሩ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የኢራን ልዩ መልዕክተኛ በበኩላቸው÷ የያህያ ሲንዋር መገደል እስራኤልን ከምን ጊዜውም በላይ ለመፋለም የሚያነሳሳ የመንፈስ ጥንካሬ ይሰጠናል ብለዋል፡፡

ሁኔታው ጦርነቱን ከማብረድ ይልቅ ሊያባብሰው እንደሚችልም ነው ያስረዱት፡፡

ህወሓት መፈንቅለ ስልጣን  አደረገብኝ  ሲል የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር አስታወቀበዶክተር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 13 የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር...
10/07/2024

ህወሓት መፈንቅለ ስልጣን አደረገብኝ ሲል የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር አስታወቀ

በዶክተር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል የሚመራው ህወሓት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 13 የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ባለስልጣናትን ከስልጣናቸው እንዲወርዱ መወሰኑን ካሳወቀ በኋላ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር፣ የህወሓቱ ቡድን በግልፅ "መፈንቅለ ስልጣን እንዲደረግብኝ አውጇል" ሲል ዛሬ ማምሻውን ባሰራጨው መግለጫ አስታውቋል። ይህም "ስርዓተ አልበኝነት እንዲሰፍን ፍላጎት እንዳለው ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ነው ሲል በመግለጫው አመልክቷል። «ከዚህ በፊትም የተለያዩ ማደናገርያዎችን እያሰራጨ ቆይቷል ሲልም ህወሃትን ከሷል። የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር በዚህ «የጥፋት ኃይል» ባለው ቡድን ላይ ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚጀምር ፤በዚህ ሰበብም ለሚፈጠር ማንኛውም ጥፋትም ተጠያቂዎቹ ቡድኑ እና አመራሩ ይሆናሉ ብሏል።

https://t.me/EtvNewsRoom

ኢትዮጵያና ዑጋንዳ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ። ባሕር ዳር: መስከረም 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ውድድር ዛሬ ከዑጋንዳ ጋር ጨዋታቸውን ያደ...
10/07/2024

ኢትዮጵያና ዑጋንዳ ዛሬ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

ባሕር ዳር: መስከረም 27/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ ውድድር ዛሬ ከዑጋንዳ ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋል፡፡
👇👇👇

ወቅታዊ ፈጣን ዜና ለማግኘት 👇
https://t.me/EtvNewsRoom

❗️በትራፊክ አደጋ የ2 ሰዎች ሕይወት አለፈበደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡አደጋው ከኮንታ ዞን ጭዳ ወ...
10/07/2024

❗️በትራፊክ አደጋ የ2 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው ከኮንታ ዞን ጭዳ ወደ ወላይታ ሶዶ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው የደረሰው፡፡

በአደጋው የሁለት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን÷በሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ትናንት ምሽት 12 ሰዓት ላይ በደረሰው አደጋ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ወቅታዊ ፈጣን ዜና ለማግኘት 👇
https://t.me/EtvNewsRoom

በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ ቤቶችን ማፍረሱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀበአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ትናንት ምሽት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ መኖሪያ ...
10/07/2024

በአዋሽ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ ቤቶችን ማፍረሱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ

በአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ትናንት ምሽት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ መኖሪያ ቤቶችን ማፍረሱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ባወጣው መረጃው አመልክቷል። በመሬት መንቀጥቀጡ መሬት መሰንጠቁንም ዩኒቨርቲው ዛሬ ሰኞ ማለዳ አስታውቋል።

https://t.me/EtvNewsRoom

በፈንታሌ ተራራ ላይ ተከስቶ ንዝረቱ አዲስ አበባ ከተማ ድረስ የተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ከሁለት ሳምንታት በላይ በተለያየ አጋጣሚ መከሰቱን ባለሞያዎቹ ገልፀዋል። ትናንት መስከረም 26/2017 ምሽት 2፡10 ገደማ የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበበት ነበር።

ከሰሞኑ የሚስተዋለው የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ከፍተኛ ሥጋት ፈጥሯል ያለው ዩኒቨርሲቲው፣ አደጋው በተከሰተበት ሳቡሬ ቀበሌ ተገኝቶ መረጃ የመሰብሰብ እና ለማህበረሰቡ ጥንቃቄ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ መሥራቱንም ገልጿል።

የዩኒቨርሲቲው ጂኦሎጂስቶች ነዋሪዎች ከፈንታሌ ኮረብታማ ቦታ እና ከከሰም ግድብ ርቀው እንዲቆዩ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።

እሑድ ምሽት የተከሰተውና በአዲስ አበባ በነዋሪዎች ላይ መደናገጥ የፈጠረው የመሬት መንቀጥጠጥ ለ18 ሴኮንድ የቆየ እንደነበረ ባለሞያዎች ተናግረዋል።

https://t.me/EtvNewsRoom

Address

Washington
Toronto, ON

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ETV ዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category