Silta Mass Media

የስልጤ ማህበረሰብ ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በአብሮነት የመኖር ባህል የዳበረ ከመሆኑም ባለፈ  የሄደበትን አካባቢ በማልማት የሚታወቅ ህዝብ ነው ሲሉ  የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር...
27/07/2025

የስልጤ ማህበረሰብ ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር በአብሮነት የመኖር ባህል የዳበረ ከመሆኑም ባለፈ የሄደበትን አካባቢ በማልማት የሚታወቅ ህዝብ ነው ሲሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሀት ካሚል ተናገሩ ።

ሚኒስትሯ ይህንን ያሉት የስልጤ ልማት ማሕበር ለ2ኛ ጊዜ ያዘጋጀው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በስልጤ ዞን በአልቾ ውሪሮ ወረዳ በተካሄደበት ወቅት ነው ።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈርያት ካሚል በዚህ ወቅት እንዳሉት የስልጤ ማህበረሰብ የሄደበትን አካባቢ ከማልማት በተጨማሪ የትውልዱ አካባቢውንም የማልማትና የማሳደግ ሃላፊነት እንዳለበት ተናግረዋል።

ማህበረሰቡ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ጋር አብሮ የመኖር ባህልን ያዳበረ ከመሆኑም ባለፈ የሄደበትን አካባቢ በማልማት የጠንካራ የስራ ባለቤት መሆኑን አስመስክሯል ብለዋል።

የስልጤ ማህበረሰብ ጥንካሬ ኢትዮጵያን ለመገንባት የሚደረገውን እንቅስቃሴ እውን ለማድረግ ያግዛል ያሉት ሚኒስትሯ የልማት ማህበሩ ከምስረታው ጀምሮ በአካባቢ የሚታዩ የጤና፣ የትምህርት የመንገድና የአረንጓዴ ልማት የመሳሰሉ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ከመቅረፉም ባለፈ የህብረተሰቡን ማህበራዊ ግንኙነት ለማጠናከር ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ገልፀዋል።

ዞኑ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የቱሪስት መዳረሻዎች ባለቤት በመሆኑ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን በማልማት የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ መሰራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

አቶ አደም ኑሪ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊና የስልጤ ልማት ማህበር ምክትል ሰብሳቢ በበኩላቸው የስልጤ ልማት ማህበር ከተመሠረተበት 1994 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

የስልጤ ልማት ማህበር የማህበረሰቡን ችግር ለመቅረፍ በርካታ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱን የጠቀሱት ምክትል ሰብሳቢው ይህንን ተግባሩን በውጤታማነት ለማስቀጠል የአስር ዓመታት ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

የስልጤ ልማት ማህበር ከሚሰራቸው የልማት ስራዎች ጎን ለጎን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የችግኝ ተከላ ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸው የልማት ማህበሩን እቅድ ከግብ ለማድረስ ተግባር ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካ በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ካለው ፋይዳ በተጨማሪ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

የስልጤ ልማት ማህበር ከሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች በተጨማሪ በየዓመቱ የሚከናወን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አንዱ መሆኑን ያነሱት ዋና አስተዳዳሪው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ በዞኑ ከ400 ሚሊዮን በላይ ችግኝ በመትከል የዞኑን የደን ሽፋን 19.5 በመቶ ማሳደግ መቻሉን ገልፀዋል ።

የዞኑ መንግስት ማህበሩ የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች በማገዝ የበኩሉን እንደሚወጣ ገልፀዋል ።

በመርኃግብሩ ላይ የተገኙት የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አሰተዳዳሪ ወ/ሮ መህዲያ ሀሰን ወረዳው የአምስቱ የስልጤ ቀደምት እናቶች መገኛ ከዞኑ በቅርብ ርቀት የሚገኝ ፣ ለኑሮ ምቹ እንዲሁም በርካታ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎች ባለቤት ከመሆኑም ባለፈ የተለያዩ የሰብልና የፍራፍሬ አይነቶችን ለማልማት ምቹ አካባቢ መሆኑን ተናግረዋል።

የስልጤ ልማት ማህበር ባዘጋጀው ሁለተኛው ዙር የችግኝ ተከላ መርሃግብር ላይ የተሳተፉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በበኩላቸው ሀገራዊ የአረንጓዴ ልማት ተግባር እውን ለማድረግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

ቀጣይ የስልጤ ልማት ማህበር (ስልማ 3) የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ፕሮግራም በዞኑ ከላንፉሮ ወረዳና ጦራ ከተማ አስተዳደር በጋራ የሚያዘጋጁ መሆኑም ተገልጿል ።

በመርሃ ግብሩ ላይ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ የፌዴራል፣የክልል፣የዞን እና የወረዳ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ የስልጤ ብሔረሰብ ተወላጆች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተሳትፈዋል።

በመጂብ ጁሃር

"ዛሬ ላይ በጡረታ ብገለልም ሀገሬ ተደፍራ አልቀመጥም" በጦር ሜዳ የልተቋጨው የሀገር ፍቅር ፦ የቀድሞው ወታደር ሸምበል ረዲ   ። ። ። ። ። ። ። ።ሻምበል ረዲ ረሺድ መሐመድ ይባላሉ ትው...
20/07/2025

"ዛሬ ላይ በጡረታ ብገለልም ሀገሬ ተደፍራ አልቀመጥም" በጦር ሜዳ የልተቋጨው የሀገር ፍቅር ፦ የቀድሞው ወታደር ሸምበል ረዲ
። ። ። ። ። ። ። ።
ሻምበል ረዲ ረሺድ መሐመድ ይባላሉ ትውልድና እድገታቸው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በአልቾ ዉሪሮ ወረዳ ቀረሶ ቀበሌ ልዩ ስሙ ጣንዤ በሚባል መንደር ሲሆን በኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ ከ23 አመታት በላይ በተለያዩ ግዳጆችና የአመራርነት የስራ ድርሻዎች ሀገራቸውን አገልግለዋል።

ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በዘለቀው የዉትድርና ህይወታቸው በርካታ ውጣ ውረዶችን፣ የመከራና የደስታ ጊዜያትን ያሳለፉ ሲሆን በሀገር መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ዕዝ ማሰልጠኛ ትምህርትና ዝግጅት ክፍል አስተባባሪና አሰልጣኝ በመሆን ለበርካታ ዓመታት አገልግለዋል።

በሰሜን ዕዝ የኢፌድሪ የሀገር መከላከያ ስራዊት ከተራ ወታደርነት አንስቶ በውትድርና ሙያ አሰልጣኝነት ፣በቴክኒክና ጥገና ክፍል አስተባባሪነት ያገለገሉ ሲሆን በሀገር መከላከያ ስር በሚገኙ ማሰልጠኛ ተቋማት ላበረከቱት አስተዋጽኦ በ2000 ዓ.ም በሰሜን ዕዝ በተከበረው የሚሊኒየም በዓል ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እጅ የሪዶ ስዓት እና ሰርተፊኬት ተቀብለዋል።

ኢትዮጵያ በሰላም ማስከበር ተልዕኮ በአፍሪካም ይሁን ከአፍሪካ ውጭ ባሉ ሀገራት መልካም ስም ያላት በመሆኑ ከበርካታ ሀገራት ጋር በመልካም ወዳጅነት እንድትታወቅ አድርጎታል የሚሉት ሻምበል ረዲ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላም መረጋገጥ በምታደርገው ጥረት በተለይም በተባበሩት መንግታት ድርጅት ስር በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ከ2003 እስከ 2005 ዓ.ም የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪ ኃይል ጋር በመሆን በሱዳን አብዬና አጎክ ግዛቶች ላይ ለ2 ዓመታት በአካባቢው የነበረውን ግጭት በመፍታት ተልዕኮአቸውን በሚገባ መወጣት ችለዋል።

ምንም እንኳን በአሁኑ ሰዓት ከሀገር መከላከያ ሰራዊት አባልነት በጡረታ የተገለሉ ቢሆንም "ሀገሬ በፈለገችኝና ባስፈለግኳት ጊዜ ሁሉ ጠላቷን ለመመከት ዝግጁ ነኝ "የሚሉት ሻምበል ረዲ ስለ ኢትዮጵያ ሲነሳ የሀገር ፍቅር ስሜታቸውን በእንባ ይገልፃሉ።

የቀድሞው ወታደር በተለይም ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በሰሜን ዕዝ በሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈፀመውን የክህደት በትር በቀጥታ የተካፈሉ፣ አስቸጋሪውን የቆላ ተንቤን መልክዓ ምድር ችለው የታገሉና የተጋፈጡ ሲሆን በውቅቱ የደረሰባቸውን ሰቆቃና ግፍ ዛሬም ድረስ በቁጭት መንፈስ ሆነው ነው የሚያስታውሱት ።

ከጦር ሜዳ የቀጠለው ትጋታቸው ዛሬም ድረስ ከገጽታቸው ያልጠፋው የቀድሞ ወታደር ሻምበል ረዲ በ 2013 ዓ.ም ከውትድርናው ዓለም በጡረታ ቢገለሉም ወደ ትውልድ አካባቢያቸው በመመለስ በተለያዩ የመንግስት የስራ ሀላፊነት ከማገልገላቸውም ባለፈ ሰዎችን የመርዳትና ችግራቸውን የመካፈል ፣አስታራቂ ሽማግሌ፣ የዝግጅቶች አድማቂ፣ የልማት አርበኛ በመሆን ዛሬም ድረስ በትጋታቸው ቀጥለዋል።

በጡረታ ከተገለሉበት ከ 2013 ዓ.ም ከመጋቢት ወር ጀምሮ በስልጤ ዞን አልቾ ዉሪሮ ወረዳ ሚሊሻ ጽህፈት ቤት ሀላፊ በመሆን በመከላከያ ሰራዊት አባልነት በቆዩባቸው ዓመታት ያካበቱትን እውቀትና ልምድ በመጠቀም አልፎ አልፎ የሚታዩ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት፣ የጽህፈት ቤታቸውን ስራ አፈጻጸም ከፍ ከማድረጋቸውም ባለፈ ወጣቶች አገራቸውን እንዲወዱና ስነ ምግባር እንዲኖራቸው በመምከርና እንደ አባት በመገሰጽ በወረዳው ማህበረሰብ ተወዳጅነትን አትርፈዋል ።

የዞኑ መንግስት ይህንን ልምዳቸውንና ትጋታቸውን በበለጠ ለመጠቀም እንዲቻል በማሰብ ባደረገው ጥረት ከ 2014 ዓ.ም ጀምሮ የዞኑ ሚልሻ ጽህፈት ቤት ሀላፊ በመሆን አገልግለዋል።

በሃላፊነት በቆዩባቸው ጊዜያት የዞኑን ሰላምና ጸጥታ ከማስጠበቃቸውም ባለፈ በተለያዩ ጊዜያት በዞኑ በሚዘጋጁ የተለያዩ ኩነቶች ላይ የክብር እንግዶችን በማጀብ እና ደህንነታቸውን በመጠበቅ ለፕሮግራሞች ድምቀት በመስጠት ይታወቃሉ።

በተለያዩ አካባቢዎች አልፎ አልፎ በግጦሽ መሬት፣ የድንበርና የቤተሰብ ግጭት በሚያጋጥምበት ጊዜም ቢሆን ለችግሮች አፋጣኝ መፍትሄ በማበጀት የመሪነትና የሽምግልና ሚናቸውን በመወጣት ሰላም በማውረድ አንቱታን አትርፈዋል።

"ዛሬ ላይ በጡረታ ብገለልም ሀገሬ ተደፈራ አልቀመጥም "የሚሉት ሻምበል ረዲ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት በሚደረጉ ድጋፎች ላይ ግምባር ቀደም በመሆን የስልጤ ዞን ለሀገር መከላከያ ሰራዊት የተለያዩ ድጋፎችን ባደረገበት ወቅት ግንባር ድረስ በማቅናት ስጦታዎችን ከማበርከታቸው ባለፈ ኢትዮጵያ ከውስጥና ከዉጭ ፈተናዎች በገጠሟት ያለፉት ወቅቶች ወጣቶች የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል እንዲሆኑ በመመልመልና በማሰልጠን ለአራት ተከታታይ ግዜያት በርካቶችን ወደ ግንባር ሸኝተዋል።

የዘማች የሠራዊት አባላትን ቤተሰቦች በመደገፍ የሚታወቁትና "ሰዎችን መርዳትና ችግራቸውን መካፈል ከፍተኛ ደስታ ይሰጠኛል "የሚሉት ሻምበል ረዲ በግንባር በቆዩባቸው አመታት ከደሞዛቸው በመቀነስ ለተማሪዎች ደብተር፣ እስክርቢቶ ፣ዩኒፎርምና ቦርሳ በመግዛት ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውንና ይህንን በጎ ዓላማ በማስቀጠል የአቅም ውስንነት ላለባቸው ቤተሰቦችና ወላጅ አልባ ህፃናት ከትምህርት ገበታቸው እንዳይርቁ የተለያዩ ድጋፎችን ያደርጋሉ።

የዞኑ መንግስት የህብረተሰቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት በሚያደርገው ጥረት ውስጥ ተሳታፊ በመሆን በተለይም በህብረተሰብ ተሳትፎ ለሚገነቡ ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ተቋማት፣ የመንገድና ውሃ የመሳሰሉ የልማት ስራዎች በከተማ የሚኖረውን የነጋዴ ማህበረሰብ ፣ባለሃብቶችንና ታዋቂ ግለሰቦችን በማስተባበር የሚታወቁ ሲሆን ለአብነትም በቅርቡ በትውልድ አካባቢያቸው ለሚገነባው መለስተኛ ጤና ጣቢያ ከሌሎች ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን በርካታ ሚሊዮን ብሮችን በማሰባሰብ የጤና ጣቢያውን ግንባታ አስጀምረዋል።

"ወላጆች ልጆቻቸውን በስነ ምግባርና በእውቀት ኮትኩተው በማሳደግ የሀገር ፍቅር እንዲኖራቸው ማድረግ ይገባል" የሚሉት ሻምበል ረዲ ወጣቶችም ሀገራቸውን በመውደድ ከዚህ አለፍ ሲልም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል በመሆን እናት ሀገራቸውን ማገልገል ይገባቸዋል ይላሉ።

በአሁኑ ወቅት ኑሮአቸውን በወራቤ ከተማ አስተዳደር ያደረጉት ሻምበል ረዲ የአምስት ልጆች አባትና የአንድ ልጅ አያት ሲሆኑ ልጆቻቸውን በስነ ምግባርና በሀገር ፍቅር ስሜት በማሳደግ በአካባቢው ማህበረሰብ አርአያ ናቸው።

✍️ ሙጂብ ጁሀር

የኢማም ሱጋቶ ዘይኔ የተቀናጀ አመራርና የ"ጎጎት" ስርዓትበ20ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ የስልጤን ህዝብ የመሩት ኢማም ሱጋቶ ዘይኔ፣ አመራራቸው በሁለት ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የተመሰ...
12/07/2025

የኢማም ሱጋቶ ዘይኔ የተቀናጀ አመራርና የ"ጎጎት" ስርዓት

በ20ኛው ክፍለ ዘመን የመጀመሪያ አጋማሽ የስልጤን ህዝብ የመሩት ኢማም ሱጋቶ ዘይኔ፣ አመራራቸው በሁለት ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የተመሰረተ ነበር፤ ይኸውም የፖለቲካ ብልሀታቸው እና የእምነት መሪነታቸው ነው።

"ጎጎት" የተሰኘው የአስተዳደር ስርዓታቸው፣ የስልጤንና የአካባቢውን ማህበረሰቦች በማሰባሰብ የጋራ ሰላምና ደህንነትን ለማስጠበቅ አስችሏል።

በጀግንነታቸውና በጦረኝነታቸው የውጭ ጥቃቶችን በመመከት ህዝባቸውን ሲከላከሉ፣ በ"ኢማምነታቸው" ደግሞ ፍትህን በማስፈን፣ የሞራል ልዕልናን በማላበስና የማህበረሰቡን ስነ-ምግባር በማነጽ ኢማም ሆነው አገልግለዋል።

📜 የስልጣኔ ማህተም የሆነው ታሪካዊው ፎቅ

የኢማም ሱጋቶ አስተዳደርና ስልጣኔ ህያው ምስክር የሆነው ታሪካዊው ፎቃቸው ሲሆን፣ ከ90-100 ዓመታት እድሜን አስቆጥሯል።

ይህ ፎቅ የመኖሪያቸው ማዕከል ብቻ ሳይሆን፣ ህዝቡን ያስተባበሩበትና የመሩበት የአስተዳደር ማዕከልም ነበር።

ፎቁ የኢማም ሱጋቶ አመራር ጥበብ ከእምነት ጽናት ጋር ሲዋሃድ ምን ያህል ጠንካራና ዘላቂ ማህበረሰብ መገንባት እንደሚቻል በተጨባጭ ያሳያል።

📜 የስነ-ህንጻ ጥበብና ባህላዊ ትስስር

የኢማም ሱጋቶ ፎቅ የተገነባው እንደ ሀበሻ ጥድ እና ቀርከሃ ባሉ የአካባቢው ቁሳቁሶች ሲሆን፣ አሰራሩ ከታሪካዊው የጅማው አባ ጅፋር ቤተ መንግስት ጋር ተመሳሳይነት ማሳየቱ በወቅቱ በነበሩት መሪዎች መካከል የነበረውን ጠንካራ ግንኙነት እና የልምድ ልውውጥ ያመላክታል።

ባለ አንድ ደረጃ፣ ሶስት በሮችና ሶስት መስኮቶች ያሉት ይህ ፎቅ፣ እያንዳንዱ አካሉ የራሱ ትርጉም ያለውና የስልጤን ህዝብ የስነ-ህንጻ ጥበብ፣ የአኗኗር ዘይቤና ማህበራዊ አደረጃጀት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የኪነ-ህንጻ ጥበብ ውጤት ነው።

ይህ ታሪካዊ ቅርስ በስልጤ ዞን፣ ምዕራብ አዘርነት በርበሬ ወረዳ፣ ከወራቤ ከተማ 83 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ዱና የሚገኝ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓትም በወረዳው አስተዳደር እንክብካቤ ይደረግለታል።

መረጃዎቹ ከተለያዩ ምንጮች የተገኙና ተጨምቀው የተፃፉ ናቸው። #የኢማምሱጋቶፎቅ #የስልጤታሪክ #የኢትዮጵያቅርስ #ታሪክ #ስልጣኔ

"የስልጤ ጀግኖች በአድዋ ጦርነት "             በሙጂብ ጁሀር የአውሮፓ አገራት፣ ከኢትዮጵያና ከላይቤሪያ በስተቀር በርካታ የአፍሪካ አገራትን ወርረው ቅኝ ተገዥ እንዳደረጉት ሁሉ፣ የጣ...
02/03/2024

"የስልጤ ጀግኖች በአድዋ ጦርነት "
በሙጂብ ጁሀር
የአውሮፓ አገራት፣ ከኢትዮጵያና ከላይቤሪያ በስተቀር በርካታ የአፍሪካ አገራትን ወርረው ቅኝ ተገዥ እንዳደረጉት ሁሉ፣ የጣሊያ ወራሪ ፋሺስት ጦርም፣ አልተሳካለትም እንጂ ኢትዮጵያን ወርሮ ለማስገበር ሞክሮ ነበር፡፡ ጀግኖቹ አያት ቅድመአያቶቻችን፤ ወንድ ሴት፣ ወጣት ሽማግሌ ሳይሉ “እምቢኝ ለአገሬ! በሕይወት እያለሁ አገሬን ጠላት አይገዛትም! ብለው፣ ረሃብና ችግር ሳይበግራቸው በዱር በገደሉ ለአምስት ዓመት መሽገው ጠላትን ተፋልመዋል፡፡

የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ዘመናዊ የጦር መሳሪያ፣ መድፍና መትረዬስ እስከ አፍንጫው የታጠቀውን የጣሊያን ወራሪ ጦር ተጋፍጠው (ያውም በጥቂት ኋላ ቀር ጠመንጃዎች፣ በጦር፣ በጋሻና ጐራዴ) በጀግንነት በመፋለም አጥንታቸውን ከስክሰውና ደማቸውን አፍስስው ነፃ ሀገር፣ ነፃ ኢትዮጵያን ያስረከቡን በእነዚህ ተራሮች (የአድዋ ተራራ) ላይ ተዋግተው ነው፡፡

የአድዋ የድል በዓል ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ጣልያንን ድል በማድረግ የአውሮፓውየንን የመስፋፋት ዓላማ እንዲገታ ከማድረጉ በተጨማሪ ነጻ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ካርታ ለዘላለም እንዲታተም ያደረገ ስለሆነ ለእኛ ኢትዮጵያውያን ታላቅ በዓል ሆኖ ለዘላለም ይከበራል፡፡

አድዋ የኢትዮጵያውያን ሁሉ ተሳትፎ ነው፤ በዓድዋ ጦርነት ከበርካታ ነገዶች የተውጣጡ፣ የእስልምና፣ የክርስትና አልያም ሌላ አምልኮ ያላቸው ኢትዮጵያውያን ከጠላት ጋር ተናንቀው ተነባብረው የወደቁበት ድልም ያገኙበት ነው። ራስ ወሌ ብጡል ከዓድዋ ጀግኖች መካከል በቀደምትነት የሚጠቀሱ ናቸው፤ ከየጁ፣ ከላስታ፣ ከራያ፣ ከዋድላና ደላንታ የተውጣጣ ከ3000 በላይ ጦርም አሰለፈዋል። በዚህ በእሳቸው ብርጌድ በልጃቸው በራስ ጉግሳ ወሌ ሥር ሆነው የሙስሊሙን ጦር የመሩት ሙስሊሞቹ የጦር አበጋዞች ሚና የማይናቅ ነበር። ከእነዚህ ሙስሊም አበጋዞች መካከል ቀኝ አዝማች ሀምዛ አበጋዝ፣ ቀኝ አዝማች ሞሀመድ በረንቶ፣ ባላምባራስ ይማም አምቡሎ፣ ፊታውራሪ ዓሊ ይማም፣ ሼኽ ሞሀመድ ሚዐዋ ወዘተ የሚጠቀሱ ናቸው። እነዚህ ሁሉ የዋርካው የሼኹ የአባ ጌትዬ ተወላጆች ናቸው፤ የክርስትያኖቹ የእነ ራስ ወሌ ብጡል የእነ እቴጌ ጣይቱ ብጡል፣ የእነ ደጅ አዝማች አያሌው ብሩ ወዘተ የሩቅ ዘመዶች ናቸው።

ስልጤ በሀገራችን ከሚገኙ በርካታ ብሔሮች: ብሔረሰቦችና ህዝቦች አንዱ ነው: ብሔረሰቡ በአዲስ አበባ-ሆሳዕና መንገድ በ172 ኪ.ሜ ርቀት ከመንገዱ ግራና ቀኝ 60 ኪ.ሜ ያህል ገባ ብሎ በሚገኘው በደቡብ ክልል ስልጤ ዞን በስፋት ይኖራል የዞኑ ጠቅላላ ስፋት 3ሺkm² ነው:: እኤአ 2004 በተደረገ ቆጠራ በዞኑ የሚኖረው 850ሺ በዞኑ መስደደር ቢቻ የነበረ ሲሆን የዞኑ ተወላጆች ያዞኑ ህዝብ በሁኑ ሰዓት ከ1ሚሊዮን በለይ ይሆናል ተቢሎ ይታሰበል ።ከዞኑ በተጨማሪ ከ1 ሚሊዬን በለይ ከዞኑ ጎራቤት ካጉራጌ፣ካሀድያ ፣ካሀለበ ና ካኦሮሞ ብሔራሰቦች ታቀለቅሎ ሳፍሮወል እነም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎችና የውጪ ሀገራትም በስፋት ተሰራጭተው ይኖራል። ግብርና ዋነኛ የኢኮኖሚ መሠረት ሲሆን ከብት አርባታና ንግድም እንዲሁ የብሔረሰቡ የሀብት ምንጭ ናቸው:: .. ዞኑ አሁን በአስር ወረደ ማለትም:- ምዕራብ አዘርነት:ምስራቅ አዘርነት፡አልቾውሪሮ:ዳሎቻ:ላንፎሮ:ሳንኩራ :ሁልባረግና ስልጢ×2 ወረዳዎች የተዋቀረ ነው::

" የስልጤ ህዝብና ለኢትዮጵያ የከፈለው መስዋዕትነት"
በአድዋ ጦርነት ወቅት ስልጤ ዞን ያሁኑን ቅርጽ ከመያዝዋና በሀድያ የስልጤ ህዝብና ለኢትዮጵያ የከፈለው መስዋዕትነት
በአድዋ ጦርነት ወቅት ስልጤ ዞን ያሁኑን ቅርጽ ከመያዝዋና በሀድያ ሱልጣኔት ስር በነበረችበት ወቅት ጦርነቱ ላይ ብዙ የስልጤ ጀግኖች ዘምተዋል።
ከነዚህም ውስጥ በህይወት ከተመለሱት አብዛኞቹ በ1928 ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ድጋሚ የአድዋን ሽንፈት ለመበቀል ተመልሳ መጥታ በወረረች ጊዜ ዛሬ ስልጤ ዞን በሚባለው አካባቢ በአድዋ ከዘመቱ ሰዎች ተጨማሪ ጀግኖችን በመያዝ በድጋሚ በማይጨው ጦርነት ዘምተዋል ስማቸውም ከታች ተዘርዝሯል።

👉ከምስራቅ አዘርነትና ከምዕራብ አዘርነት አካባቢ የዘመቱ
1) ግራዝማ ሹክራላ ሀምዱቴ
2) ግራዝማች ሙክታር ቡሽራ
3) ግራዝማች ኢብራሂም ኬሬቦ
4) ሀጂ ማመጫ ገ/ ማርያም
5) አቶ ኤርሞሎ ኢሳቦ
6) አቶ ባቾሬ ቂዶሬ
7) አበጋዝ ሀ/ገብሬ ጡረሞ
8) አቶ ጃቢር ሙዘይን
9) አቶ ሁሴን ላሌጎ
10) አቶ ሰይድ ዲባሞ
11) አቶ ባሙድ ጠቀሎ
12) አቶ ከማል ሀምዱቴ
13) ፊት አውራሪ ከበደ አሊ
14) አቶ ማሞ ሀይለማርያም
15) አቶ ኢላቶ ሚላቶ
16) አቶ ጊርጊቦ ወጋጎ
17) አቶ ሙዘይን ጡሬ
18) አቶ ሲራጅ ቡቃ
19) አቶ በዛብህ መቅረጽ
20) ሀጅ ሳሊያ ውልሲዶ
21) አቶ ኡስማን አለማር
22) አቶ ሻፊ ከበደ
23) አቶ መሀመድ ኦቼ
24) አበጋዝ ኑሪ ሲራጅ
25) አቶ መሀመድ ኑር ሲራጅ
26) አዝማች አሰና ጎልቤ
27) አቶ ቡሴር ጃቦሮ
28) አቶ መንጋ አለና
29) አቶ አልዬ ሞላሞ
30) አቶ ማሞ ሰይድ
👉ከስልጢና አሊቾ ውሪሮ ወረዳዎች አካባቢ የዘመቱ
1) አዝማች ኦርሞራ ጉና
2) ቀኝ አዝማች ሸረፋ በለቃ
3) ቀኝ አዝማች ሸረፋ አወል
4) አዝማች ሞሳ ዱካኖ
5) ግራዝማች አሰኖ ሞቼ
6) ፊት አውራሪ ወ/ መስፍን ኤግሳ
7) አዝማች ሁሴን ሳልያ
8)አቶ በቀለ ዘና
9) አቶ ጃቢር ጉና
10) አዝማች አጤሮ( ጤም ለዝቦ)
11) አቶ ኡመር ባሌ
12) ኢማም ቱሉሮ ጉላሮ
13) አበጋዝ ባሙድ
14) አቶ አሊማዳ ሀቢብ
15) አቶ ሁሴን ሀቢብ
16) አቶ ሸረፋ ኡመር
17) አቶ ሹኩሮ አብሮራ
18) አቶ የሱፍ ጄግሶ
19) አቶ ሁሴን ጄግሶ
20) አቶ ሁሴን አናቤ
21) አቶ አህመድ ሳሊያ
22) ወ/ሮ ላደሜ ሁሴን
23) አቶ ሽፈራ እመነው
24) አቶ እንግዳው አመነው
25) አቶ በዙ ሀብተየስ
26) አቶ ደምሴ ወ/ሰማያት
27) አቶ ካሳ ገ/ስላሴ
28) አቶ ዋበላ መኛታ
29) አቶ ያሲን ሚሬት
30) አቶ ሽፋ ላለንጎ
31) አቶ አ/ሰላም ሰላሞ
32) አቶ ሞሳ ኡገኜ
33) አቶ ኩምሳ ተሰማ
34) ግራዝማች ልዑልሰገድ ቅጣው
👉በሁልባረግ በሳንኩራና በዳሎቻ አካባቢ የዘመቱ
1) ግራዝማ ኡመር ረጀቦ
2) ግራዝማች ኤቼሞ ሞሊሶ
3) ግራዝማች ሰዒድ አብዶ
4) ቀኝ አዝማች ሀሰን ጡሞሶ
5) ባራባራስ አብደላ ኤረንጎ
6) አበጋዝ ሀይሌ ሁሴን
7) አቶ ከሊፋ ኢሊሞ
#ምንጭ -የስልጤ ባህልና ታሪክ ከተሰኘው መጽሐፍ እንዲሁም ከተለያዩ የታሪክ መዛግብት የተወሰደ
👉አዘጋጅ ሙጂብ ጁሀር

Silta waraba fc
24/12/2023

Silta waraba fc

Check out Mujib@jr's video.

ስልጤ ወራቤ እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ ፀጋዬ ወንድሙን የክለቡ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ  ሾማ!!የስልጤ ወራቤ እግር ኳስ ክለብ ሻሸመኔ ከነማን በ2015 ወደ ፕሪሚየርሊግ  ያሰገባውን አሰልጣኝ ...
21/12/2023

ስልጤ ወራቤ እግር ኳስ ክለብ አሰልጣኝ ፀጋዬ ወንድሙን የክለቡ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾማ!!

የስልጤ ወራቤ እግር ኳስ ክለብ ሻሸመኔ ከነማን በ2015 ወደ ፕሪሚየርሊግ ያሰገባውን አሰልጣኝ ፀጋዬ ወንድሙን የክለቡ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ ሾማ!!

ስፖርት ክለቡ የውጤት ቀውስ ውስጥ መግባቱን ተከትሎ ባለፈው ሳምንት ሶስቱንም የክለቡ አሰልጣኞች ማሰናበቱ ይታወቃል። በዚሁ መሠረትም በዛሬው እለት ቦርዱ ባደረገው ስብሰባ በ2015 የውድድር ዓመት ሻሸመኔ ከነማን ወደ ፕሪሚየርሊግ ያስገባውን እና የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ሆኖ ያገለገለውን አሰልጣኝ ፀጋዬ ወንድሙን የክለቡ ዋና አሰልጣኝ አድርጎ መድቧል።

አሰልጣኝ ጸጋዬ ወንድሙ የፊታችን ሰኞ ስልጤ ወራቤ ስፖርት ክለብ ከነቀምት አቻው ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ቡድኑን የሚመራ መሆኑ በቦርዱ በኩል ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

21/12/2023
የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሠረት በማድረግ በመካከለኛ እና በአነስተኛ ደረጃ የሰለጠነ ብቁ የሰው ሀይል በመፍራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵ...
12/12/2023

የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሠረት በማድረግ በመካከለኛ እና በአነስተኛ ደረጃ የሰለጠነ ብቁ የሰው ሀይል በመፍራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ ሀላፊ አቶ ይርጋ ሀንዲሶ ገለፁ ።
በስልጤ ዞን አሊቾ ውሪሮ ወረዳ የቃዋቆቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በአራት የተለያዩ የሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን አስመርቋል።

በምረቃ ፕሮግራም ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የቃውቆቶ ኢንዱስትሪያል እና ኮንስትራክሽን ኮሌጅ ዲን አቶ ሸምሴ አወል ሀገራት ዛሬ ኢኮኖሚያዊ እድገት ብቁና የሰለጠነ ፣በራሱ የሚተማመን ፣ስራ ፈጣሪ የሰው ኃይል ግንባታ ላይ ትኩረት ተሰጥተው በመስራታቸው መሆኑን ተናግራዋል ።
የቀውቀቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በበጀት አማቱ በመደበኛ መርሐ ግብር በ4 ዲፓርትመንቶች ከደረጃ 2 እስከ 4 ወንድ 15 ሴት 31 በድምሩ 46 ሰልጣኝ ተማሪዎችን ማስመረቅ መቻሉን ገልፀዋል ።

በምረቃ ፕሮግራም ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ቢሮ ሃላፊ አቶ ይርጋ ሀንዲሶ በመደበኛም ይሁን በአጫጭር ግዜ ፕሮግራሞች የሚሰጡ ስልጠናዎች ዋነኛ ግባቸው ዜጎች ስራ መስራት ብቻ ሰይሆን ስራ ፈጣሪ በመሆን ሀገራቸውን በብቃት መገልገል እንዲችሉ ለማድረግ መሆኑን ተነግረዋል ።

የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሠረት በማድረግ በመካከለኛ እና በአነስተኛ ደረጃ የሰለጠነ ብቁ የሰው ሀይል በመፍራት የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል ።

ሰልጠኞች በስልጠናው ሂደት የተለያዩ ችግሮችንና ውጣውረዶችን ተጋፍጠችሁ የተግባርና የንድፈ ሀሳብ ስልጠና በመውሰድ ለምረቃ በመብቃታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ ለይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሊ ከድር በሀገራችን የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ዘርፍ በተሰጠው ልዩ ተልእኮ በክህሎት የዳበረ ፣ስራ ፈጣሪ እና ገበያ ተኮር ስርዓትን በመከተል በዘርፉ የበቃ የሰው ሃይል ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል ፡፡

የቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ስልጠና ተቋማት የሚሰጡትን ስልጠና በማስፋት ከስልጠናው በተጨማሪ የስራ ፈጠራ ማእከል በማድረግና በተገቢው ተግባራዊ በማድረግ የማህበረሰባችንን የልማት እድገት ማፋጠን ይገባል ብለዋል፡፡

የአልቾ ውሪሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አማን ከድር በበኩላቸው ሀገራት ለስማዘገቡት ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እድገት ሚስጥር የተማረ በእውቀት የዳበረና የቴክኖሎጂ ክህሎት የለው ትውልድ ለመፍጠር ኢንቨስት በማድረግ መሆኑን ገልፀው ሰልጣኞች በኮሌጅ ቆይታቸው ወቅት የቀሰሙትን ክህሎት ወደ ተግባር በመቀየር የማህበረሰቡን ችግር ለመፍታት የበኩላቸውን ሀላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል ፡፡

የቀውቀቶ ኮንስትራክሽንና ኢንደስትሪያል ኮሌጅ ውጤታማ እንዲሆን እና የተቋሙ ተልእኮ እውን እንዲሆን ሁሉም አካላት በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ያሉት አቶ አማን ወጣቶች በተከፈቱ የስልጠና ዘርፎች ራሳቸውን በማብቃት የሙያ ባለቤት መሆን እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል።

ኮሌጁ በመጀመሪያው ዙር ምረቃ በአራት የተለያዩ የሙያ መስኮች ለመጀመሪያ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 15 ሴትና 31 ወንዶች በድምሩ 46 ሰልጣኞች አስመርቋል።

የዕለቱ ተማራቂ ተማሪዎች በበኩላቸው በተማረቁባት የሙያ ዘርፍ የማህበረሰቡን ችግር በሚቀርፉ የስራ ዘርፎች ለይ በመሰማራት የሚጠበቅባቸውን ለመወጣት መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል ።

በምረቃ ፕሮግራም ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ዋና ሀላፊ ክቡር አቶ ይርጋ ሀንዲሶ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ዋና ሀላፊው ክቡር አቶ ሽመልስ ዋንጎሮ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት የማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክቡር አቶ አብዱልዋሪስ ጀማል፣ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ክቡር አቶ አሊ ከድር፣ የስልጤ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ሀላፊ አቶ ቀድሩ አብደላና ሌሎች የክልልና የዞን ከፍተኛ አመራሮ፣ የሀይማኖት አባቶች ፣የሀገር ሽማግሌዎች ፣የተማረቂ ተማሪዎች ቤተሰቦችን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገለቸው እንግዶች ተገኝተዋል። via ሙጂብ ጁሀር

29/10/2023

የስልጤ ሕዝብ ከሚገባዉ በላይ አልጠየቀም!
••••••••••••••••••••••••••••••
❝የስልጤ ሕዝብ ከሚገባዉ በላይ አልጠየቀም። የስልጤ ሕዝብ የራሱን እንጂ የሌላ ስጡኝ አላለም። የስልጤ ሕዝብ የሚለዉ ዉክልናዬ ተነፍጓል፣ ማንነቴ ተረግጧል፤ ባህልና እምነቴ አልተከበረም••• እንጂ በልዩ ሁኔታ ከመብቱ ውጭ የማልቀስና የመጠየቅ ታሪክና ልምድ ፈጽሞ ኖሮት አያዉቅም።

በቀድሞ በ (54ቱ) በደቡብ ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ማንነቱ፣ እምነቱ፣ ባህልና እሴቱ በተሻለ ሁኔታ ተከብሮለት የነበረዉ ታላቁ የስልጤ ሕዝብ በሀገሪቱ ፖለቲከዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትጋት ዉስጥ ድርሻዉ ከፍ ያለ መሆኑን እሙን ነዉ።❞ Mujib Amino

የታላቁ የስልጤ ሕዝብ ዉክልና የት ሄዶ ነዉ?••••••••••••••••••••••••••••••Mujib Aminoማዕክላዊ ኢትዮጵያ ተብሎ በተሰየመዉ አዲሱ አወቃቀር ላይ የዚህን ስራ ወዳድ፣ ጠን...
13/10/2023

የታላቁ የስልጤ ሕዝብ ዉክልና የት ሄዶ ነዉ?
••••••••••••••••••••••••••••••
Mujib Amino

ማዕክላዊ ኢትዮጵያ ተብሎ በተሰየመዉ አዲሱ አወቃቀር ላይ የዚህን ስራ ወዳድ፣ ጠንካራ፣ ታጋይ ና ታማኝ፤ ለአገር ነጻነትና ሉዓላዊነት በተደረገ እንቅስቃሴ ከፊት ለፊት ለተሰለፈዉ ታላቁ የስልጤ ሕዝብ በሁሉም መመዘኛዎች ዉክልና ተነፍጓል።

ምናልባት ሰኔ 11/2012 የሲዳማ ክልል ስልጣንም በይፋ ሲረከብ ዉክልናዉ ወደዛ ሄዶ ይሆን?

ወይስ ህዳር 14፤ 2014 የደቡብ ምዕራብ ክልል ሲመሰረት የክልሉ ምክር ቤት አባላት ዉስጥ ሳናውቀዉ ስልጣንን አግኝተዉ ይሆን?

ዘንግተነዉ ከሆነ ደግሞ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አደረጃጀት ላይ ዉክልናችን ተቀምጦ ኖሯል?

ዉክልናችሁ ከላይ በተገለጹት በቀድሞ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል በነበሩ ዞኖች ዉስጥ አይደለም ብላችሁ ከሞግታችሁ የት ነዉ ያለነዉ? ግራ ቢገባን፣ ባህልና እሴታችንን ማንነታችንና እምነታቻንን ፈልገን ፍልገን ብናጣዉ ወዴት ይሆን ብለን መፈለጋችን ነዉ።

በመጨረሻ የተዋቀረዉ የማዕክላዊ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍለጋችንን ቀጥለናል። ከ 54 ብሔረሰቦች የሚልቁበት የነበረዉ በቀድሞ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ዉስጥ የማንነት፣ የባህልና እሴት ዉክልና የነበረዉ የስልጤ ታላቅ ሕዝብ በማዕክላዊ ኢትዮጵያ ክልል ዉስጥ ማንነቱና እምነቱን፣ ሕዝቡና ትጋቱን፣ አቅምና ጉልበቱን... በዜሮ አባዝተዉ ሕዝባችን የማይቀብለዉና ሊቀበለዉ ያልፈቀደዉን ኢ-ሕገ መንግስታዊ መዋቅር ይፋ አድርገዋል።

ለቀድሞ የደቡብ ክልል እድገትና ብልጽግና፣ መሰረተ ልማትና፣ ከፍታና ጥንካሬ፣ ...ወዘተረፈ ለበርካታ ማህበራዊና ፖለቲካዊ መዳበር ከፍተኛ ድርሻ የነበረዉ የስልጤ ማህበረሰብ እነሆ በማዕክላዊ ኢትዮጵያ ክልል 1ድም የወሳኝና የሰዉ ኀይል አደረጃጀት ላይ ዉክልና አጥቶ የበይ ተመልካች ሆኗል።

ይህ ታላቅ ሕዝብ፣ ዉክልና ያጣበት የትኛዉም መዋቅር ከእድገት የሰነፈ፣ ከልማት የራቀ፣ ከመራጋጋትና ከሰላም የላቀ በመሆን ጉዞዉን ቁልቁል ማድረጉ እሙን ለመሆኑ ከፊት ለፊታችን የሚመጡት ጊዜያት የሚያሳዩ ይሆናል።

በሀገር ዉስጥና ከሀገር ውጪ፣ በከተማና በገጠር፣ በንግድና በትምህርት፣ በስልጣንም ላይ ይሁን ተራዉ ማሕበረሰብ የማዕክላዊ ኢትዮጵያ ክልል አደረጃጀትን እዉቅና ነፍጓል።

እንደማህበረሰብ ያልተቀበልነዉ አደራጀጀት ከማስተክከልና ከመከለስ ውጪ አማራጭ የለዉም። ይህን አልቀብልም ያለ አካል በህዝብ/በማህበረሰብ ላይ በግዴታ የመጫን/የማስገደድ/...አምባገነንነትን ለመመለስ የሚደረግ ሙከራ በመሆኑ ዳግም አምባገንነትን የማስቆም ስራ እንሰራለን! ኢንሻ አሏህ

#አምቤዉ
#ሀርዴ
#እለዉፈርና
#ቡቹኩል

Address

Addis Ababa
Ababa
NO

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Silta Mass Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share