Amhara Media House አማራ ሚዲያ ሀውስ

Amhara Media House አማራ ሚዲያ ሀውስ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amhara Media House አማራ ሚዲያ ሀውስ, Media/News Company, Addis Ababa, Ababa.

የአርበኛ ዘመነ ካሴ የዓድዋ የእንኳን አደረሳችሁ መልክት ፦አድዋ  የቅኝ ግዛትን  ጨለማ  ድል ነስቶ  የበራ የእኩልነት እና የነጻነት አብሪ ኮኮብ ነው ።  አድዋ በአባቶቻችን  አጥንትና ደም...
02/03/2025

የአርበኛ ዘመነ ካሴ የዓድዋ የእንኳን አደረሳችሁ መልክት ፦

አድዋ የቅኝ ግዛትን ጨለማ ድል ነስቶ የበራ የእኩልነት እና የነጻነት አብሪ ኮኮብ ነው ። አድዋ በአባቶቻችን አጥንትና ደም የተሰራ ገዘፍ ያለ የእኩልነት ሃውልት እና ወደር ባልተገኘለት የዚያ ዘመን ትውልድ የሞራል ልዕልና የተበጀ ፍልስፍናም ነው። አድዋ የእነ አጤ ምኒልክ የእጅ ስራ ነው ። አባቶቻችን አድዋን የሰሩት ከአድዋ በበለጠ የአዕምሯቸው ምጥቀት ፣ የሀሳብ ርቅቀት ሲሆን በኢትዮጵያ ያልተቋረጠ የነጻነት ተጋድሎ ውስጥ አድዋ በአደራረጉም ይሁን በውጤቱ ህያው ምሳሌና መመሪያችን ነው።

አድዋን ስናከብር ፣ አባቶቻችን ስንዘክር ከነጻነት ራስጌው የነበርን እኛ ለፍጹም አምባገነን ስርዓት እና በህልውና አደጋ ውስጥ የተገኘነው ለምን እና እንዴት ነው ? የሚለውን ጥያቄ በመመርመር መሆን አለበት ። ለምንገኝበት ሁለንተናዊ ውድቀት ምክንያቱ ለአድዋ የሚመጥን ስርዓትና መዋቅር መገንባት ያለመቻላችን ነው ። ከአድዋ በሚቃረን አስተሳሰብ ላይ የቆመ ሁሉ የኢትዮጵያውያን ነጻነትና እኩልነት ሊቀበልና ሊያከብር አይቻለውም።

መላ ኢትዮጵያን ለመከራ የዳረገው ፣ የአማራን ህዝብ ደግሞ የማጥፋት ጦርነት የከፈተበት የአገዛዙ ገዥ አሰተሳሰብ ጸረ-አድዋ ፣ ጸረ-እኩልነት እና ፍጹም አረመኔ ነው ። ለኢትዮጵያውያን ባለው ንቀት እና የመግዣ ስልቱ በሆነው የማጭበርበር ዘዴው የተነሳ አድዋን በቃላት በማሽሞንሞን የአድዋ ወዳጅ ለማስመሰል ቢጥርም በግብሩ የአድዋን የነጻነት መንፈስ ለመረዳት የማይችል እቡይ መሆኑን አረጋግጧል ።

ትግላችን ለነጻነት ፣ ለእኩልነት ከሁሉም በላይ ደግሞ ለህልውና የምናደርገው ነው ። ትግላችን ከአድዋ አባቶቻችን በወረሰነው የላቀ የሞራል ልዕልና የሚመራ ነው ። ትግላችን በድል እንደምናጠናቅቅ የእጃችን መዳፍ ያህል እርግጠኞች ሆነን የምናውቀው ነጻነት እና እኩልነት በባርነት የሚረቱበት ፣ የሞራል ጥራትም በእቡይነት የሚመከትበት ታሪክም ሆነ ሳይንስ ስለሌለ ነው ።
በመሆኑም ትግላችን የተከፈተብንን የህልውና ጦርነት ድል አድርገን ለአድዋ የሚመጥን ስርዓትና መዋቅር በመገንባት የህዝባችን መብቶችና ጥቅሞች በቋሚነት በማስከበር ይሆናል ።

ከአድዋ አባቶቻችን የምንማረው አንዱ ቁም-ነገር በመካከላችን ያሉ ልዩነቶችን ሁሉ ወደ ጎን በመተውና ለጊዜው በማቆየት በዋናው ጠላታችን ላይ ማበር ያለብን መሆኑን ነው። ስለሆነም ከመቼውም ጊዜ በላይ ዛሬ በአንድነት እንድንሰለፍ ጥሪያችን እናቀርባለን።

እንኳን ለ 129ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ ።

አዲስ ትውልድ ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣ አዲስ ተስፋ !
አርበኛ ዘመነ ካሴ ባውቄ

ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ!ግንቦት 6 ቀን 1991 ዓ.ም የዛሬ 25 ዓመት ያረፉበት ቀን ነው። የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አፅመ እረፍት (የቀብር ቦታ)  ቀድሞ ከነበረበት ቅዱስ ባለወልድ ቤ...
14/05/2024

ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ!
ግንቦት 6 ቀን 1991 ዓ.ም የዛሬ 25 ዓመት ያረፉበት ቀን ነው። የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አፅመ እረፍት (የቀብር ቦታ) ቀድሞ ከነበረበት ቅዱስ ባለወልድ ቤተ ክርስትያን ተነስቶ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስትያን በደማቅ ሥነ ሥርዓት ሰኔ 18/2009 ዓ.ም በክብር አርፏል።

ፈጣሪ ነብሶዎን በአፀደ ገነት ያኑርልን!!

13/05/2024

አማራ ያሸንፋል።

13/05/2024
የድሮው ባለቀይ ቦኔት ኮማንዶ የአሁኑ ፋኖ   ባርነትን እምቢ ብለህ ከግፈኞች ጋር አንገት ለአንገት እየተናነቅህ በክብር ነው ያረፍከው። ስለከፈልክልን ዉድ ዋጋ እናመሰግናለን። በሰራኸው ጀግን...
07/11/2023

የድሮው ባለቀይ ቦኔት ኮማንዶ የአሁኑ ፋኖ ባርነትን እምቢ ብለህ ከግፈኞች ጋር አንገት ለአንገት እየተናነቅህ በክብር ነው ያረፍከው። ስለከፈልክልን ዉድ ዋጋ እናመሰግናለን። በሰራኸው ጀግንነት እናትህ ብቻ ሳትሆን መላው የአማራ ህዝብ ለዘላለም ሲኮራብህ ይኖራል። ስምህም ክብርህም ዘላለም እንደዋርካ ገዝፎ ይኖራል የኔ አንበሳ። ነብስህ በሰላም ትረፍ!

አማራነት ወንጀል አይደለም!   በሰላማዊ የነፃነት ታጋዮች ላይ እየደረሰ ያለው  የፍትሕ እጦት፣ የሰብዓዊ መብት ገፈፋ እና ያለ ጥፋታቸው መታሰራቸው የመብት ረገጣ መሆኑን በመግለጽ በአስቸኳይ...
31/10/2023

አማራነት ወንጀል አይደለም!
በሰላማዊ የነፃነት ታጋዮች ላይ እየደረሰ ያለው የፍትሕ እጦት፣ የሰብዓዊ መብት ገፈፋ እና ያለ ጥፋታቸው መታሰራቸው የመብት ረገጣ መሆኑን በመግለጽ በአስቸኳይ ከግፍ እስር እንዲለቀቁ " እኔም እጠይቃለሁ ፤ ለምን ?! " የበይነ መረብ ዘመቻው ዛሬ በይፋ ተጀምሯል ፣ይቀላቀሉ !

ለዘመቻው የተዘጋጀው ፕሮፋይል ይሄ ስለሆነ ፤ ፕሮፋይል ምስልዎን በመቀየር ፣ጽሁፎችን በመጻፍ፣ ምስሎችን በማጋራት ሃሳብዎን ያንፀባርቁ !!

የጎጃም ፋኖ ዕዝ የስራ አስፈፃሚ የመጀመሪያ ስብሰባ የአቋም መግለጫ:-እንደሚታወቀው የጎጃም ፋኖ እዝ ከተመሠረተ ጥቂት ቀናትን ብቻ ቢያሥቆጥርም በሥራዎቹ እና በፈፀማቸው ኦፕሬሺኖች ይበል የሚ...
30/10/2023

የጎጃም ፋኖ ዕዝ የስራ አስፈፃሚ የመጀመሪያ ስብሰባ የአቋም መግለጫ:-

እንደሚታወቀው የጎጃም ፋኖ እዝ ከተመሠረተ ጥቂት ቀናትን ብቻ ቢያሥቆጥርም በሥራዎቹ እና በፈፀማቸው ኦፕሬሺኖች ይበል የሚያሠኙ እና ስኬታማ ውጤቶችን በማሥመዝገብ ጠላትን በማሽመድመድ ወደፊት እየገሠገሠ ይገኛል ።

ዕዙ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥኬታማ የሆነ የሥራ አሥፈፃሚ ውይይት ካደረገ በኋላ ወቅታዊ ጉዳዮችን በሚገባ በማጤን የሚከተለውን ባለዘጠኝ ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል::

1ኛ.የዕዙን ሕገ ደንብ እና መመሪያ በተዋቀረው ኮሚቴ መሰረት የመጀመሪያው ረቂቅ የቀረበ ሲሆን ስራ አስፈጻሚው በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የማሻሻያ ነጥቦችን በጥንቃቄ በማንሳት መመሪያዋች ተስተካክለው በፍጥነት እንዲቀርቡ ወስኗል።

2.የዕዙ የገንዘብ አሰባሰብን በተመለከተ ከውጭ የሚገኝ የትኛውንም እርዳታ እንዲሁም በኬላዎች የሚገኝ የቀረጥ ገቢ በዕዙ ሎጀስቲክስ በኩል ብቻ እንዲገባ ወስኗል ። ተሽከርካሪዎችን በተመለከተ በጥልቀት ከተወያየ በኋላ የቀረጥ መጠን የወሰነ ሲሆን ህጋዊ በሆነ በእዙ ደረሰኝ ብቻ ክፍያ እንዲፈፀም ተወስኗል።

3ኛ. በዕዙ በአራተኛው ክፍለ ጦር ውስጥ አመራር ያልተመደበበትን ቦታ በተመለከተ ዕዙ በብርጌድ: በሻለቃና ሻምበል በፍጥነት እንዲደራጅ አቅጣጫ አስቀምጧል።

4ኛ. የዕዙ የሎጅስቲክ አሰባሰቡ ለህዝብና ለጦሩ ታአማኒነት ይኖረው ዘንድ ሰብሳቢ ፣ኦርዲናንስ እና መጋቢ ያለው በሶስት አካላት ተዋቅሮ እንዲሰበሰብ ወስኗል ።

5ኛ. የዕዙ የፖለቲካ ክንፍን (ሊቀመንበርና ም/ሊቀመንበር) በተመለከተ በተለያየ የፋኖ የፖለቲካ ክንፍ ውስጥ የነበሩ እና ያሉ የፋኖ የትግል ድርጅቶች በተለይም የአማራ ህዝባዊ ሃይልና የአማራ ህዝባዊ ግምባር ላይ የነበሩና ያሉ ከፍተኛ አመራሮች ወደ አንድነት መጥተው ለአማራ ህዝብ እንደሚታገሉ ከተስማሙ ዕዙ እንደሚቀበላቸው ዕዙ ሲመሰረት ባወጣው ባለ ሰባት/7/ ነጥብ የአቋም መግለጫ ማስታወቁ ይታወቃል።

በመሆኑም በተለያዩ የትግል አሰላለፎች እና አደረጃጀቶች የነበራችሁ የአማራ ህዝባዊ ሀይል እና ህዝባዊ ግንባር የፋኖ መሪዎች ከእዙ አመራር እና ስራ አስፈፃሚ ጋር በፍጥነት እንድትወያዩና ስራ አስፈፃሚውም ሆነ የዕዙ አመራር ለሚጠይቃችሁ ጥያቄዎች መልስ እንድትሰጡ እያሳሰብን ዕዙ በጠቀሰው ቀን እና ዕለት የማትገኙ ከሆነ ዕዙ የራሱን የፖለቲካ ክንፍ አመራር ምስረታ እንደገና ለማጤን ይገደዳል።

6ኛ. ዕዙ በየ አካባቢው የሚፈጠሩ ልዩነቶችን እንዴት መፍታት እንደሚቻል በጥልቀት ከተወያየ በኋላ ከየብርጌዱ በስነምግባር: በአካል እና በብቃት የታመነባቸው ፋኖዎች በዕዙ አመራር የሚመራ የዕዙ ልዩ ኮማንዶ ጦር እንዲመሠረት አቅጣጫ ሰጥቷል ።

7ኛ. የዕዙ አመራር ወጥነት ያለው እንዲሆን እና ተጠያቂነትን በማስፈን የሰው ሀይል አደረጃጀት እንዲሁም የጤና ዘርፍን በማዋቀር የስራ አቅጣጫ ሰጥቷል።

8ኛ. በቀን 16-02-2016ዓ.ም የአማራ ፋኖ ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ የተሰማንን ሃዘን እየገለፅን መግለጫው በጎጃም እዝ ከፍተኛ አመራሮችም ሆነ ስራ አስፈፃሚ እውቅና የሌለው መግለጫ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

የአማራ ፋኖ ምክርቤት ሲቋቋም 36 ወንበር ያሉት ወታደራዊ ክንፍ ሲኖረው ከዚህም ውስጥ 9ኙ ወንበር የጎጃም አማራ ፋኖ መቀመጫ እንዲሆን መወሰኑን ብንሰማም የምክርቤቱ የላይኛው አመራርም ሆነ የምክርቤቱ ስራ አስፈፃሚ ለጎጃም አማራ ፋኖ ክንፍ እውቅና ሲሰጥ አላስተዋልንም። ይልቁንም በጎጃም ምድር ውስጥ የአማራ ህዝብ እያደረገ ባለው ተጋድሎ የአማራ ፋኖ ምክርቤት አመራሮችን በግለሰብ ደረጃም ሆነ በስራ አስፈፃሚነት ደረጃ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራም አልተሳካም።

በተቃራኒው ደግሞ የሕዝብ መራር ትግል የወለዳቸው በርካታ ጀግና የፋኖ ወታደሮችና የፋኖ አመራሮች በጎጃም አማራ ውስጥ ተፈጥረዋል። በአንዲት ትንሽዬ የወረዳ ፋኖ አደረጃጀትም የጠላትን ሙሉ ክፍለጦር ሲደመሰስ ያየነው ለባሩድ ባልሸሹ ቆራጥ ልጆች ፊታውራሪነትና የሕዝባችን ተጋድሎ ነው።

ባልጠበቅነው ረድፍ በኩል ደግሞ ትግሉን ቤት ቁጭ ብለው ለመምራት በማሰብ የሳይበር ሚዲያውን ብቻ ለይተው የሚያስጮሁ አካላት ከትላንት ያልተማረ አካሄዳቸውን መጠቀማቸውን ቀጥለዋል። እነዚህ አካላትም ከመሰል ድርጊታቸው እንዲታቀቡ እናሳስባለን።

አሁን ባለው ተጨባጭና ነባራዊ ሁኔታ ህዝባችን የትግሉ ድል ባለቤት፣ የአማራ ፋኖ ደግሞ የትግሉ ዋና መሪ አካል መሆኑ እየታወቀ የህዝባችንን ስም የተሸከሙ ድርጅቶች ዳገቱን ባልጨረስንበት በዚህ ሰዓት የትግል ንጥቂያና ሽሚያ ውስጥ መግባታቸው እጅጉን ያሳስበናል።

አሁን ላይ የተጀመረው የአማራ ህዝብ ትግል ሕልውናን መሰረት ያደረገ ሲሆን ከትላንቱ የታሪካችን ስብራቶችም በብዙ የተማረ ነው። የአማራ ህዝብ ትግል ዋናዎቹን መጠበቅ፣ በዋናዎቹ መመራትና ዋናዎቹን ማክበር የአማራ ፋኖ ተቀዳሚ ተግባራችን ነው።

አስተሳሰባችን ከተቸንካሪነትና ቁሞቀርነት የተላቀቀ ሲሆን ከመጠላለፍና ሴራ የራቀ የፖለቲካ አሰላለፍ ለህዝባችን እንሻለን። ለዚህም ሲባል በሐገር ውስጥ ያሉ ውድ ወንድምና እህቶቻችን ያላቸውን ክፍተት በአስቸኳይ በመሙላት ህዝባችንን የሚመጥን አሰላለፍ ይዘው እንዲያሳውቁን እናሳስባለን።

የአማራን ህዝብ የሕልውና ጥያቄ አይክዱም፣ በትግላችንም ውስጥ ዋኖቻችን ናቸው ብለን የምናስባቸው ግለሰቦች ማለትም የአራስነት ቆይታዋን ሳትጨርስ በእስር ከምትማቅቀው መስከረም አበራ እስከ ጋዜጠኛና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች መዓዛ ሙሃመድ፣ ከአርበኛ ዘመነ ካሴ እስከ ታላቁ እስክንድር ነጋ፣ ከዶክተር ወንድወሰን እስከ ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቼው እንዲሁም ስማቸው ያልጠቀስናቸው አብሪ ኮከቦችና ዋናዎቻችን የአማራ ህዝብ እያደረገ ላለው ህዝባዊ ትግል የወሳኝነት ሚና አላቸው ብለን እናምናለን።

በውጭ ሐገር የሚገኙ የአማራም ሆነ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ድርጅቶች ለሕዝባዊ ትግሉ ያደረጋቹህትን አስተዋጽኦ እናደንቃለን። እነዚህ ማኅበራት የአማራን ህዝብ የሕልውና ትግል ለአለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማሳወቅ የምታደርጉትን መጠነ ሰፊ አይተኬ ሚናም እናመሰግናለን።

እኛ ለአማራ ህዝብ የትግል ቀይ መስመር ለመፍጠር ሲባል ከላይ ድሮን ከታች መድፍ እየዘነበብን አንድነትን እንደመሰረትን ሁሉ እናንተም አንድነትና ጥምረትን በመፍጠር በአንዳንድ ትንንሽ ጉዳዬች የምታደርጉትን የእርስ በእርስ ሽኩቻ ወደ ጎን በመተው ሙሉ ትኩረትና ድጋፋቹሁ ለህዝባዊ ትግሉ እንዲሆን ጥሪ እናስተላልፋለን።

በእኛ ግምገማ ከአለም አቀፍ የዲፕሎማት ማሕበረሰቡ ጋር የተሻለ ቅቡልነት አላቸው፣ በዚህም ሂደት የምዕራባውያን ትኩረትን ወደ አማራ ህዝብ መሳብ ችለዋል ብለን የምናስባቸው በርካታ የአማራ ማኅበራትና ግለሰቦች አሉ።

በአብይ አህመድና ግብረአበሮቹ በሚሰጥ ቀጭን ትዕዛዝ ከጀዊሽ አይሁዶች ያልተናነሰ እልቂት ህዝባችን ላይ እየተፈፀመ ባለበት በእዚህ ወቅት ይህንን እልቂት ለመቀልበስ የአማራ ፋኖ የግንባር ፍልሚያ እያደረገ ሲሆን በርካታ ስማቸውን ያልጠቀስናቸው የአማራ ምሑራንና ሐገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ይሔንን ትግል በስትራቴጂክም ሆነ ታክቲካል ሂደቶች ቀረፃ፣ የምክርና ሐሳብ ስራዎችን እየሰሩ ነው ብለንም እናምናለን።

የጣት መቀሳሰር ሂደትም የሕዝባችንን የድል መጥቢያ ዘመን ከማራዘም የዘለለ ሚና ይኖረናል ብለን አናምንም። ወዳጅን በእጅጉ ማፍራትና ጠላትን አብዝቶ መቀነስ ወቅታዊው የፖለቲካ አሰላለፍ የሚፈልጋቸው ግብኣቶች መሆናቸውን መዘንጋትም አይገባም። ይህም ማለት ግለሰቦችን ከማጠልሸትና ከመኮነን ይልቅ መዋቅራዊ ጥቃት እየደረሰበት ላለው ህዝባችን መዋቅራዊ አደረጃጀት መፍጠር ብቸኛ መዳኛው ነው ብለን እናምናለን።

በመሆኑም የአማራ ፋኖ ምክርቤት እንደ ቀጠና የጎጃምን እዝ ክንፍ ያላወያዬ መግለጫ ከማውጣቱም ባሻገር የሙሉ መግለጫውን ሐላፊነት የተሰጠው ቡድንም ሆነ ግለሰቦች ላይ እውቅና ስለሌለን በድጋሜ እንዲጤን እንጠይቃለን።

በሌላ በኩል ሚዲያ ከወታደራዊ ክንፉ ያልተናነሰ ጉልበት አለው። በዚህም በርካታ ሚዲያዎች የአማራን ህዝብ የሕልውና ትግል በማስተጋባት ደማቅ አሻራን እያሳረፉ ነው ። ሁሉም ትግሉን የሚደግፉ የሳተላይትና የዩቲዩብ ሚዲያዎች የጠላትን የፕሮፓጋንዳ ክንፍ በመስበርና ህዝባዊ የሆነውን የአማራ ፋኖ ተጋድሎ አጉልቶ በማውጣት ለትግሉ የቀጣይ አቅጣጫ አሰላለፍና ረድፈን አሳይተውናል።

በመሆኑም ለአማራ ህዝብና ምድር ለነኩ ሐቀኛ ታጋዬችና አደረጃጀቶች ማስተላለፍ የምንፈልገው መልዕክት ቢኖር የአማራን ህዝብ እሴት ያከበረ፣ ከመነቃቀፍ ይልቅ "ሳር ሲነባበር ዝናብ ይከላከላል" ብሂልን የተከተለ፣ አንድነትን የትግል መርሑና የማይደፈር ቀይ መስመር ያደረገ፣ 'እኔ' ከሚል መታበይ ይልቅ 'እኛ' የሚል ትህትናን ያዘለ ጉዞን እንድንከተል ስንል በጥብቅ እያሳሰብን የተገኙ ድሎች ሁሉ በህዝባዊ ተጋድሎው የተመዘገቡ የቡድን ስራ ውጤት መሆናቸው እንዲሰመርበት በአፅንኦት እንገልፃለን።

9ኛ.በመጨረሻም የጎጃም ዕዝ ሁሉም ማህበረሰብ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ለህልውና ዘመቻ እንዲዘጋጅ አቅጣጫ በማስቀመጥ የዕዙን የመጀመርያ ስብሰባ በስኬት አጠናቋል ።

ድል ለተገፋው የአማራ ህዝብ!

ቀን 18-02-2016 ዓ.ም
ጎጃም ደጋ ዳሞት
ፈረስ ቤት

30/10/2023

የአብይ አህመድ ሰራዊትን የተመለከቱ 2 መረጃዎችች:-

1. ጀኔራል መሀመድ ተሰማ በሌለበት "ወታደሩን አስጨረሰው" በሚል እየተገመገመ ነው። ከዚህ ቀደም የ6ኛ ዕዝ አዛዥ የነበረውና የጎጃም ቀጠና ኮማንድ ፖስት ጠርናፊው ሜ/ጀኔራል ተስፋዬ ወ/ማርያም ዕዙ ሲደመሰስ ሰውዬው በግምገማ ተባሯል። ጀኔራል መሀመድ ተሰማ ተመሳሳይ ዕጣ ፈንታ ሊገጥመው ይችላል።

2. ባለፈው በአንቶኖቭ ከባህርዳር እና ጎንደር የወጡት የኦሮሚያ ወታደሮች መሆናቸው ተረጋግጧል። ያኔ እንደቅጠል እየረገፉ ሲያሰግሯቸው ለተሃድሶ ስልጠና እና ተኩስ ልምምድ መልሰው አስወጥተዋቸው ነበር። አሁን የ1ወር ስልጠናቸውን ጨርሰው ወደአማራ ክልል ተመልሰው ሊገቡ ነው። በምን መንገድ ይግባ በሚለው ላይ የመከላከያ የሎጂስቲክስ መኮንኖች ስብሰባ ተቀምጠዋል።

ምስጋናው ዘ-ግዮን ምስጋናው ዘ-ግዮ

የማኀበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጥሪ(ጥቅምት 20 እና 21)1- "እኔም ዐማራ ነኝ!"2- "ስለ ፍትሕ እንጮኸለን!"በእነዚህ ሁለት ቀናት:- ከአዲስ አበባ እስከ ፌደራል ፖሊስ፣ ከመከላከያ ካምፕ እስከ...
30/10/2023

የማኀበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ጥሪ
(ጥቅምት 20 እና 21)

1- "እኔም ዐማራ ነኝ!"

2- "ስለ ፍትሕ እንጮኸለን!"
በእነዚህ ሁለት ቀናት:- ከአዲስ አበባ እስከ ፌደራል ፖሊስ፣ ከመከላከያ ካምፕ እስከ ማይታወቁ ማጎሪያዎች፣ ከቂሊንጦ እስከ ቃሊቲ፣ ከአዋሽ አርባ እስከ አፋር በረሃ፣ ከዐማራ ክልል እስከ መላው ኢትዮጵያ ድረስ በሚዘረዘሩ ቦታዎች ዐማራ በመሆናቸው ብቻ ተቆልፎባቸው እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖቻችን አንድም በአስቸኳይ እንዲፈቱ፤ ሁለትም ከጎናቸው እንዳለን ለማስታወስ ስንል የምናካሄደውን የማኀበራዊ ዘመቻ እንድትቀላቀሉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

ዘመቻው ሁሉንም የማኀበራዊ ድረ-ገፆችን ጨምሮ፣ የአገር ውስጥ እና የውጪ ሚዲያዎችን ያካትታል። በምስል፣ በድምጽ፣ በካርቶን ስእሎችና ቪዲዮዎች የተደገፈ ይሆናል። ማንም ሰው የዘመቻውን ዋና አላማ ከግብ የሚያደርስ የራሱን ፈጠራ ሊጠቀም ይችላል።

አስታውሱ ዘመቻው የፊታችን ማክሰኞ እና እሮብ የሚካሄድ ሲሆን፤

የመጀመሪያው ቀን ማክሰኞ ጥቅምት 20 መሪ ቃሉ:- "እኔም ዐማራ ነኝ" የሚል ነው።

የሁለተኛው ቀን ጥቅምት 21 መሪ ቃል ደግሞ "ስለ ፍትሕ እጮኸለው" የሚል ይሆናል።

ከነሐሴ 5/2015 ጀምሮ በግፍ እስር ላይ የምትገኘው የጄነራል ተፈራ ማሞ ባለቤት መነን ሀይሌ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች የነበሩት የሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ የልጅ ልጅ ከሆነችው ህይ...
29/10/2023

ከነሐሴ 5/2015 ጀምሮ በግፍ እስር ላይ የምትገኘው የጄነራል ተፈራ ማሞ ባለቤት መነን ሀይሌ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች የነበሩት የሊቀ ትጉሃን አስታጥቄ የልጅ ልጅ ከሆነችው ህይወት ጋር አርብ ሌሊት የጦር ካምፕ ወደ ሆነው አዋሽ አርባ መወሰዳቸው ታውቋል።
Natnael Ye

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለጥቅምት 10 ተቀጠረ በሌላኛው ችሎት ጋዜጠኛ ታዲዮስ ታንቱም ለጥቅምት 14 ተቀጥረዋል።የችሎቱን ሙሉ ዝርዝር በሮሃ ሚዲያያገኙታል።ምንጭ፦ ማዕዛ ሙሐመድ (Meaza M...
02/09/2022

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለጥቅምት 10 ተቀጠረ በሌላኛው ችሎት ጋዜጠኛ ታዲዮስ ታንቱም ለጥቅምት 14 ተቀጥረዋል።
የችሎቱን ሙሉ ዝርዝር በሮሃ ሚዲያያገኙታል።
ምንጭ፦ ማዕዛ ሙሐመድ (Meaza Mohammed)

የዚች ሀገር መሪዎች ከጦር ይልቅ ብዕር የሚፈሩት ነገር ይገርመኛል። ፍትህ የአሸናፊዎች ሎሌ ናት‼

የተጣለ ፈረስ(በእውቀቱ ስዩም)ደሞስ መች ይጠፋል? ካንቺም ከኔም መንደር የቀድሞ ወታደር፥ በጨነቀን ጊዜ ፥“በናት ሀገር ጥሪ “ የምናጣድፈው፥ በድል ቀን ከድግስ፥ የማናሳትፈውከነጣቂ መዳፍ ፥...
27/08/2022

የተጣለ ፈረስ
(በእውቀቱ ስዩም)

ደሞስ መች ይጠፋል? ካንቺም ከኔም መንደር
የቀድሞ ወታደር፥
በጨነቀን ጊዜ ፥“በናት ሀገር ጥሪ “
የምናጣድፈው፥
በድል ቀን ከድግስ፥ የማናሳትፈው
ከነጣቂ መዳፍ ፥ አገር የሚያስመልስ
በገዛ አገሩ ላይ፥
መብቱ ከወፍ አንሶ፤ ጎጆ የማይቀልስ፤

Address

Addis Ababa
Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Media House አማራ ሚዲያ ሀውስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share