Zoble Post

Zoble Post በሀገራዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተዓማኒ መረጃዎችን እና ጥልቅ ትንታኔዎችን የሚያቀርብ የዲጂታል መጽሔት!

በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ከሩሲያ ጎን ሆነው የሚዋጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከ”1,800″ ማለፉ ተነገረ።በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት አራተኛ ዓመ...
22/03/2026

በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት ከሩሲያ ጎን ሆነው የሚዋጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከ”1,800″ ማለፉ ተነገረ።

በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል የተቀሰቀሰው ጦርነት አራተኛ ዓመቱን የተሻገረ ሲሆን፣ ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከሩሲያ ጎን ሆነው በቅጥረኛ ተዋጊነት እየተሳተፉ እንደሚገኝ ዞብል ፖስት ያገኘው መረጃ ያሳያል።

ለሩሲያ በተዋጊነት የሚመለመሉ ኢትዮጵያውያን አብዛኛዎቹ ከአማራ እና ከትግራይ ክልሎች እንደሆነ መጽሔታችን ያገኘው መረጃ የሚያሳይ ሲሆን፣ ባለፉት አራት ዓመታት ከ1 ሺህ 8 መቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ከሩሲያ ጎን ሆነው በጦርነቱ መሳተፋቸው ተነግሯል።

አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ለሩሲያ ለመዋጋት የተፈራረመ ኢትዮጵያዊ ለዞብል ፖስት እንደገለፀው፣ ከትውልድ ቀየው ከአማራ ክልል ወደ ሩሲያ ለመጓዝ በቅድሚያ 800 ሺህ የሩሲያ ሩብል ወይም 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ገደማ እንደተከፈለው የገለፀ ሲሆን፣ በየወሩ ደግሞ 200 ሺህ የሩሲያ ሩብል ከሩሲያ መንግሥት እንደሚከፈለው አሳውቋል።

ግለሰቡ አክሎም ከሩሲያ ጎን ሆነው የሚዋጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥራቸው ከ1 ሺህ 8 መቶ በላይ መድረሱን የጠቆመ ሲሆን፣ ከትግራይ ክልል ውቅሮ አካባቢ፣ ከኦሮሚያ ክልል ባሌ ሮቤ አካባቢ፣ እንደዚሁም ከኢትዮጵያ መንግሥት ፀጥታ መዋቅር ከድተው ለቅጥረኛ ተዋጊነት ወደ ሩሲያ የሄዱ ኢትዮጵያውያንን እንደሚያውቅ አያይዞ ገልጿል።

ኢትዮጵያውያኑ ለቅጥረኛ ተዋጊነት የሚመለመሉት በራሳቸው ፈቃድ እና የሦስተኛ ወገን ተፅዕኖ ሳይኖርባቸው እንደሆነ የተነገረ ሲሆን፣ ሩሲያ ከዩክሬን ጋር በምታደርገው ጦርነት ሲሳተፉ ግን የሩሲያን ሕግ ሙሉ በሙሉ ለመተግበር እንደሚገደዱ ታውቋል።

ዝርዝሩን ለማንበብ! 👇

https://zobelepost.com/ethiopians-fighting-for-russia-in-the-war-with-ukraine/

ከስራ በተያያዘው ሊንክ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ!

https://t.me/zoblePost

ከሳዑዲ አረቢያ በባሕር አቋርጠው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በጀልባ መገልበጥ አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ። ዕቅዳቸው በኢትዮጵያ ሕጋዊ የጉዞ ሰነድ አሟልተው ወደ ሳዑዲ አ...
17/03/2026

ከሳዑዲ አረቢያ በባሕር አቋርጠው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በጀልባ መገልበጥ አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ተነገረ።

ዕቅዳቸው በኢትዮጵያ ሕጋዊ የጉዞ ሰነድ አሟልተው ወደ ሳዑዲ አረቢያ ለመመለስ ነበር ተብሏል።

ከየመን የባሕር ዳርቻ ተነስተው ወደ ጂቡቲ ሲጓዙ የነበሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን ይጓዙበት የነበረው ጀልባ ተገልብጦ መሞታቸውን በአደጋው ሰለባ የሆኑትን ቤተሰቦች እና የቅርብ ሰዎችን ዋቢ አድርጎ ተቀማጭነቱ በካናዳ የሆነው ሆርን ፍሪኩዌንሲ የተሰኘው የበይነ-መረብ ሚዲያ ዘግቧል።

በጀልባ መገልበጥ አደጋው ህይወታቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያን ነዋሪነታቸውን በሳዑዲ አረቢያ ያደረጉ እንደነበሩ የገለፀው ሆርን ፍሪኩዌንሲ፣ በባሕር አቋርጠው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ቀይ ባሕር ላይ ባጋጠማቸው የጀልባ አደጋ ህይወታቸው ማለፉን ዘግቧሎ።

የመገልበጥ አደጋ ያጋጠማት ጀልባ ኢትዮጵያንን ጨምሮ በግምት 150 ይሆናሉ የተባሉ የአፍሪካ ስደተኞችን ጭና ስትጓዝ እያለ በአደገኛ የባሕር ሞገድ ተመታ መገልበጧ ታውቋል።

በየመን ባሕር ዳርቻ አቅራቢያ በደረሰው የጀልባ መገልበጥ ቢያንስ 10 ኢትዮጵያውያን መሞታቸው ተገልጿል። በአደጋው ህይወታቸውን ካጡት ኢትዮጵያውያን መካከል የቅርብ ጓደኛዋ እንደሚገኝበት ሆርን ፍሪኩዌንሲ ነዋሪነቷን ሳዑዲ አረቢያ ካደረገች ወጣት አነጋግሮ ዘግቧል።

ወጣቷ እንደምትለው፣ በባሕር ሲጓዝ የሞተው ጓደኛዋ በሕገወጥ መንገድ ሳዑዲ አረቢያ ይኖር የነበረ ወጣት ሲሆን በባሕር ወደ ኢትዮጵያ እየተመለሰ የነበረውም ሳውዲ አረቢያ በሕጋዊ መንገድ መኖር የሚችልበትን ሂደት ለማስፈጸም እንደነበር ጠቁማለች።

ወጣቷ “የልቤ ሰው መካሪዬ ወረቀት ላውጣ ብሎ በባሕር ሄደ፣ ሆዴ እየፈራ በሰላም ተመልስ ብዬው፣ ይሄው ባሕር በላው” በማለት እንባ እየተናነቃት ሁኔታውን አስረድታለች።

ተጨማሪ ለማንበብ 👇 https://zobelepost.com/ethiopians-die-in-boat-capsize/

የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል 👇

https://t.me/zoblePost

እስራኤል በሶማሌላንድ የውሃ ጠረፍ ላይ የጦር ሰፈር ለመገንባት ዝግጅት እያደረገች ነው። እስራኤል በቅርቡ የሀገርነት እውቅና በሰጠቻት ሶማሌላንድ የውሃ ጠረፍ ላይ ስትራቴጂያዊ የጦር ሰፈር ለ...
12/03/2026

እስራኤል በሶማሌላንድ የውሃ ጠረፍ ላይ የጦር ሰፈር ለመገንባት ዝግጅት እያደረገች ነው።

እስራኤል በቅርቡ የሀገርነት እውቅና በሰጠቻት ሶማሌላንድ የውሃ ጠረፍ ላይ ስትራቴጂያዊ የጦር ሰፈር ለማቋቋም ዝግጅት እያደረገች እና የቦታ ልየታ ስራ እያከናወነች እንደምትገኝ ብሉምበርግ ዘግቧል።

ብሉምበርግ የሶማሌላንድ ባለሥልጣናትን አነጋግሮ ባሰፈረው ሰፊ ሀተታ፣ እስራኤል ለማቋቋም ያሰበችው የጦር ሰፈር ከሶማሌላንድ ወደ ቀይ ባሕር መውጫ በኩል ባለ አካባቢ መሆኑን ዘግቧል።

ይህ ዕቅድ ተግባራዊ እንዲሆን ያስቻለው እስራኤል በፈረንጆቹ የታኅሣሥ ወር 2025 ዓመተ-ምህረት ላይ “ታሪካዊ ውሳኔ” ስትል የጠራችውን የሶማሌላንድ የሀገርነት እውቅና ተከትሎ ነው።

እስራኤል ከበርበራ ወደብ በስተምዕራብ በኩል 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ከፍተኛ ቦታ ላይ የጦር ሰፈር እና የደህንነት ተቋም ለመገንባት ጥናት ስታደርግ መቆየቷም ተረጋግጧል።

የጦር ሰፈር ይገነባበታል የተባለው ስፍራ ከየመን የሁቲ አማፅያን ይዞታ በባሕር በኩል 260 ኪሎ ሜትር ብቻ የሚርቅ እንደሆነ የተነገረ ሲሆን፣ እስራኤል ከገዛ ድንበሯ ከ2 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ መጓዝ ሳያስፈልጋት የሁቲ አማፂያንን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠርም ሆነ በቡድኑ ይዞታዎች ላይ ጥቃት ለመፈፀም ያስችላታል ተብሏል።

ሃማስ እና ሂዝቦላህ በእስራኤል ከደረሰባቸው ጥቃት በኋላ የሁቲ አማፂያን ቡድን ለኢራን የቀራት ብቸኛ ጠንካራ አጋር ሲሆን፣ እስራኤል በሶማሊላንድ የምትገነባው የጦር ሰፈር የሁቲ ታጣቂዎችን በቅርብ ርቀት ለማጥቃት እና ለማዳከም ያመቻታል ተብሏል።

እስራኤል ለሶማሌላንድ የሰጠችውን እውቅና ተከትሎ ያደረገቻቸው ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ስምምነቶች በአፍሪካ ቀንድ የተፅዕኖ አድማሷን ለማስፋት እና በቀጠናው ወታደራዊ ቁመና እንዲኖራት ያስቻለ መሆኑን የቀጠናው ተንታኞች አስተያየታቸውን ሲሰጡ ይደመጣል።

ሊንኩን ተጭነው ተጨማሪ ያንብቡ!
https://zobelepost.com/israel-to-build-a-military-base-in-somaliland/

የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል ከስር በተያያዘው ሊንክ ይግቡ!

https://t.me/zoblePost

አጫጭር ዜናዎች!1ኛ)✓አቶ ጌታቸው ረዳ የምርጫ ቦርድ ውሳኔን ተቃውመው ለፍርድ ቤት ያስገቡትን ክስ በዛሬው ዕለት በፍቃዳቸው ማንሳታቸውን ለፍርድ ቤቱ አሳውቀዋል። ይሄንን ተከትሎ በ7ኛው ሀገ...
11/03/2026

አጫጭር ዜናዎች!

1ኛ)✓
አቶ ጌታቸው ረዳ የምርጫ ቦርድ ውሳኔን ተቃውመው ለፍርድ ቤት ያስገቡትን ክስ በዛሬው ዕለት በፍቃዳቸው ማንሳታቸውን ለፍርድ ቤቱ አሳውቀዋል። ይሄንን ተከትሎ በ7ኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ከትግራይ ክልል ውጭ ሆኖ በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲካሄድበት የፌደሬሽን ምክር ያሳለፈውን ውሳኔ የምርጫ ቦርድ ተፈፃሚ ያደርጋል ተብሏል።

2ኛ)✓
ህወሓት ግዳጃቸውን ፈፅመው በክብር የተሸኙ፣ በተለያዩ ምክንያቶች ከሠራዊት አባልነት አቋርጠው የተመለሱ፤ የአርሚ ማሰልጠኛ ቦታዎችን በተመለከተ መረጃ ሳይኖራቸው ቀርተው ወደ ቡድኑ ለመቀላቀል ያልቻሉ፣ እንደዚሁም የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩ እና በእስር ላይ የቆዩ የትግራይ ተወላጆች የህወሓትን ሰራዊት እንዲቀላቀሉ በትግራይ የተለያዩ ወረዳዎች በማስታወቂያ ጥሪ እያደረገ ነው ተብሏል።

3ኛ)✓
የመከላከያ የውጪ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ሜጄር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ "የአሰብ አፈጣጠር ለአባት ሀገሩ ኢትዮጵያ እንጅ ለኤርትራ አይደለም'' ሲሉ መናገራቸው ተሰምቷል። ጄኔራሉ ከዚህ ቀደም "የኢትዮጵያ ወጣት የአሰብ ወደብን ለማስመለስ ተዘጋጅ!" ሲሉ መናገራቸው አይዘነጋም።

4ኛ)✓
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን በትናንትናው ዕለት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በጋጮ ባባ ወረዳ ማዞ ዶይሳ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት ናዳ እስካሁን የ52 ሰዎች ሕይወት ማለፉንና 50 የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ የደረሱበት እንዳልታወቀ የጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።

5ኛ)✓
የመከላከያ ሠራዊቱ ከወለጋ አካባቢዎች መውጣቱን ተከትሎ "አካባቢያችሁን ከኦነግ ሸኔ መጠበቅ አለባችሁ" በሚል በምስራቅ ወለጋ፣ ምዕራብ ወለጋ፣ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ ዞኖች የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ለወጣቶች እና አርሶ አደሮች "አስገዳጅ" ወታደራዊ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተሰምቷል።

የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል 👇

https://t.me/zoblePost

ኤርትራ 12 ለሚጠጉ የሱዳን ታጣቂ ቡድኖች ወታደራዊ ስልጠና ትሰጣለች ተባለ። ከታጣቂ ቡድኖች ውስጥ አሜሪካ በሽብርተኝነት ከፈረጀችው "የሱዳን ሙስሊም ወንድማማቾች" ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያላ...
10/03/2026

ኤርትራ 12 ለሚጠጉ የሱዳን ታጣቂ ቡድኖች ወታደራዊ ስልጠና ትሰጣለች ተባለ።

ከታጣቂ ቡድኖች ውስጥ አሜሪካ በሽብርተኝነት ከፈረጀችው "የሱዳን ሙስሊም ወንድማማቾች" ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው እንደሚገኙበትም ተነግሯል።

ሊንኩን ተጭነው ዝርዝሩን ያንብቡ!

መጋቢት 1 2018 ዓ.ም-ዞብል ፖስት ዜና! ጄኔራል አል-ቡርሃን ከሚመራው የሱዳን ብሔራዊ ጦር ጎን ተሰልፈው በሱዳን የእርስ በርስ ጦርነት የሚሳተፉ ወደ 12 የሚጠጉ ታጣቂ ቡድኖች በኤርትራ መንግሥ...

የወልቃይት ጠገዴ "የአማራ የማንነት እና ወሰን ጥያቄ" አፋጣኝ ሕጋዊ እውቅና እንዲሰጠው ተጠየቀ።የወልቃይት ጉዳይ "የአማራ ፅኑ ማንነታችን እንጅ አወዛጋቢ የፖለቲካ ካርድ አይደለም” የሚል መ...
05/03/2026

የወልቃይት ጠገዴ "የአማራ የማንነት እና ወሰን ጥያቄ" አፋጣኝ ሕጋዊ እውቅና እንዲሰጠው ተጠየቀ።

የወልቃይት ጉዳይ "የአማራ ፅኑ ማንነታችን እንጅ አወዛጋቢ የፖለቲካ ካርድ አይደለም” የሚል መልዕክትም ተላልፏል!

የካቲት 26 2018 ዓ.ም --ዞብል ፖስት ዜና! የወልቃይት ጠገዴ የማንነት እና የወሰን ጥያቄ አፋጣኝ ሕጋዊ እውቅና እንዲሰጠው በዛሬው ዕለት በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተለያዩ አካባቢዎ....

አሜሪካ እና እስራኤል በጥምረት በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ተነገረ።ኢራን በበኩሏ "የከፋ አፀፋዊ እርምጃ እወስዳለሁ" ያለች ሲሆን፣ እስራኤል ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ካስነገረች በኋላ ...
28/02/2026

አሜሪካ እና እስራኤል በጥምረት በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸው ተነገረ።

ኢራን በበኩሏ "የከፋ አፀፋዊ እርምጃ እወስዳለሁ" ያለች ሲሆን፣ እስራኤል ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ካስነገረች በኋላ የአየር ክልሏን ዘግታለች።

ሊንኩን ተጭነው ተጨማሪ ያንብቡ!

የካቲት 21 2018 ዓ.ም ዞብል ፖስት ዜና! በዛሬው ዕለት እስራኤል እና አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት መክፈታቸውን በርካታ የመገናኛ ብዙሃን የሁለቱን ሀገራት ባለሥልጣናት ጠቅሰው በመዘገብ ላይ ይ...

አጫጭር ዜናዎች 1ኛ✓በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ በትግራይ እና በአማራ ክልላዊ መንግሥታት መካከል "አከራካሪ" በተባሉት የሑመራ፣ የአዲረመፅ፣ የኮረም አፍላ፣ የጠለምትና፣ የራያ አላማጣ ምርጫ ክል...
23/02/2026

አጫጭር ዜናዎች

1ኛ✓
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ በትግራይ እና በአማራ ክልላዊ መንግሥታት መካከል "አከራካሪ" በተባሉት የሑመራ፣ የአዲረመፅ፣ የኮረም አፍላ፣ የጠለምትና፣ የራያ አላማጣ ምርጫ ክልሎች ከትግራይ ክልላዊ መንግሥት ውጪ ሆነው ለብቻቸው በቀጥታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫ እንዲደረግ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በቁጥር ፌደም/አፈ/5/13138 ለቦርዱ በጻፈው ደብዳቤ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳውቋል።

ወሳኔውን ተከትሎ፣ በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ስምረት ፓርቲ "የሀገሪቱን ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት መሠረት የሚንድ፣ ተቋማዊ ነፃነትን የሚደፈጥጥ፣ ሥርዓት አልበኝነትን የሚያውጅ ነው" እንደዚሁም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር "የትግራይ ሕዝብ በከፈለው መስዋዕትነት የተገነባውን ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት በመጣስ፣ አደገኛ መዘዝ የሚያስከትል ውሳኔ ተላልፏል" ሲሉ ተመሳሳይ የተቃውሞ ድምጾችን አሰምተዋል።

2ኛ✓
የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ታጣቂዎች ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘልቀው በመግባት ቡለን እና ወንበራ ተብለው የሚጠሩ አካባቢዎችን መቆጣጠራቸው ተሰምቷል። ቡድኑ ሠራዊቱ ወደ ክልሉ እንዲገባ ከማድረጉ በፊት የፌደራል መንግሥቱ መከላከያ ሠራዊቱን ከአካባቢው ለቅቆ እንዲወጣ ማድረጉ ተሰምቷል።

3ኛ✓
የሳዑዲ አረቢያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ድኤታ ኢንጂነር ወሊድ አብደልከሪም አል-ኸሪጂን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ ጋር በወቅታዊ የአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ ውጥረት ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ተሰምቷል። ከአሥር ቀናት በፊት የሳዑዲው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፈርሃን አል-ሳዑድ ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በነገው ዕለት ደግሞ የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

4ኛ✓
የሶማሊላንድ መንግስት በእስራኤል ዋና ከተማ ቴል-አቪቭ የኤምባሲ ህንፃ ግንባታ እና የሰው ኃይል ማደራጀት ስራ ማጠናቀቁ ተሰምቷል። ባሳለፍነው የፈረንጆቹ 2025 ዓመት መገባደጃ ላይ እስራኤል ሶማሊላንድን እንደ ነጻ እና ሉዓላዊት ሀገር በይፋ እውቅና መስጠቷ ተከትሎ ነው ኤምባሲ የመክፈት ስራ የተጀመረው። የእስራኤሉ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ሰዓር ባለፈው ወር ሶማሌላንድን በጎበኙበት ወቅት ሀገራቸው በተመሳሳይ በሐርጌሳ ኤምባሲዋን እንደምትከፍት መናገራቸው ይታወሳል።

የቴሌግራም ቻናላችንን ለመቀላቀል 👇

https://t.me/zoblePost

አጫጫር ዜናዎች!1ኛ✓ ሦስት ከፍተኛ የህወሓት ወታደራዊ አመራሮች ከትግራይ አዲስ አበባ ገብተዋል። አመራሮቹ ከዚህ ቀደም የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩና በፌደራል መንግሥቱ እና በህወሓት መ...
19/02/2026

አጫጫር ዜናዎች!

1ኛ✓
ሦስት ከፍተኛ የህወሓት ወታደራዊ አመራሮች ከትግራይ አዲስ አበባ ገብተዋል። አመራሮቹ ከዚህ ቀደም የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበሩና በፌደራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል በተደረገው ጦርነት የህወሓት ታጣቂዎችን ሲመሩ እና ሲያዋጉ የነበሩ ናቸው።

በትናንትናው ዕለት አዲስ አበባ የገቡት የህወሓት ወታደራዊ አመራሮቹ ብርጋዲየር ጄኔራል ጉዕሸ ገብረ፣ ብርጋዴየር ጄኔራል ከበደ ፍቃዱ፣ እና ኮሎኔል ንጉሥ ወልደ ገብርኤል ናቸው። ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮቹ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ የገቡበት ምክንያት በግልፅ ባይነገርም "ከህወሓት አፈንግጠው ወጥተው" ሊሆን ይችላል ተብሏል።

2ኛ✓
የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አስቸኳይ ስብሰባ መቀመጡ ተነግሯል። ማዕከላዊ ኮሚቴው አስቸኳይ ስብሰባ የጠራው በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከርና ውሳኔ ለማሳለፍ መሆኑ የተሰማ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት እንደዚሁም በፌዴራል መንግሥቱ እና በህወሓት መካከል ያለው መካረር ዋነኛ የውይይት አጀንዳ ናቸው ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ፣ ለሦስት ዓመታት ያህል በእስር ላይ በሚገኙ የአማራ ተወላጅ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ እንደዚሁም የሕዝብ እንደራሴዎች ጉዳይ ላይ ለመወያየት አጀንዳ መያዙ ተነግሯል። በፖለቲካ እስረኞቹ ጉዳይ ውይይት ይደረጋል ቢባልም አጀንዳው እስረኞቹን ስለመፍታት ይሁን አይሁን የታወቀ ነገር የለም።

3ኛ✓
የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ በርካታ የመካከለኛው ምሥራቅ የሚዲያ አውታሮች ዘግበዋል። ፕሬዚዳንቱ በአዲስ አበባ ለአንድ ቀን የሚቆይ የስራ ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን፣ በቆይታቸው የሶማሌንድን እውቅና፣ እንደዚሁም እስራኤል "ቀጠናዊ ተገዳዳሪዎቼ" የምትላቸው ተርኪየና ጠቅላይ ሚንስትር ረሲብ ጣይብ ኤርዶጋን እና የሳዑዲ አረቢያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፈርሃን አል-ሳዑድ በቀናት ልዩነት በኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉብኝት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።

4ኛ✓
አንድ የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት ጋዜጠኛ ወደ ትግራይ ክልል እንዳይበር መከልከሉ ተነግሯል። "መቀመጫው በአዲስ አበባ የሆነና ሕጋዊ ፈቃድ ያለው ዘጋቢዬ ወደ ትግራይ ክልል ሽሬ ለመብረር ሲሞክር ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፈቃድ የለህም በሚል ከቦሌ አየር ማረፊያ እንዲመለስ ተደርጓል" ሲል የዜና አገልግሎቱ አስታውቋል። የድንበር የለሽ ጋዜጠኞች ቡድን (RSF) በበኩሉ "መረጃ የማግኘት መብት ጥሰት ነው” ሲል በጋዜጠኛው ላይ የተደረገውን ክልከላ ተቃውሟል።

የመጽሔታችንን የቴሌግራም ቻናል ለመቀላቀል ከስር የተያያዘውን ሊንክ ይጠቀሙ! 👇

https://t.me/zoblePost

በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት በማንኛውም ቅፅበት ሊፈነዳ የሚችል “የባሩድ በርሜል ሆኗል” ሲል “International Crisis Group” አስጠነቀቀ።በዚህ ዓመት በአፍሪካ ...
18/02/2026

በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት በማንኛውም ቅፅበት ሊፈነዳ የሚችል “የባሩድ በርሜል ሆኗል” ሲል “International Crisis Group” አስጠነቀቀ።

በዚህ ዓመት በአፍሪካ ሊከሰቱ ከሚችሉ 7 የፀጥታ ችግሮች አንዱ ነውም ተብሏል!

ሊንኩን ተጭነው ዝርዝሩን ያንብቡ!

የካቲት 11 2018 ዓ.ም-ዞብል ፖስት ዜና! ዋነኛ ትኩረቱን በሠላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ አድርጎ የሚሰራው International Crisis Group በዛሬው ዕለት ኢትዮጵያን እና ኤርትራን እንደዚሁም በትግራይ ክልል ....

ከደቡብ ሱዳን ወደ ጋምቤላ ክልል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ እየገባ እንደሚገኝ ተነገረ! "ፖቻላ" ተብሎ የሚጠራው አዋሳኝ ስፍራ ዋነኛ ማስተላለፊያ መስመር ነው ተብሏል።ሊንኩ...
07/02/2026

ከደቡብ ሱዳን ወደ ጋምቤላ ክልል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ እየገባ እንደሚገኝ ተነገረ!

"ፖቻላ" ተብሎ የሚጠራው አዋሳኝ ስፍራ ዋነኛ ማስተላለፊያ መስመር ነው ተብሏል።

ሊንኩን ተጭነው ዝርዝሩን ያንብቡ!

ጥር 30 2018 ዓ.ም ዞብል ፖስት ዜና! መነሻውን ከደቡብ ሱዳን ያደረገ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ድንበር ተሻግሮ ወደ ጋምቤላ ክልል እየገባ እንደሚገኝ ዞብል ፖስት ለጉዳዩ ቅር...

ገዱ አንዳርጋቸው ለጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ የምስክርነት ጥሪ ምላሽ ሰጡ።"ጠቅላይ ሚንስትሩ ስለ እኔ የተናገሩት ሀሰት ነው" ሲሉም ገልጸዋል! ሊንኩን ተጭነው ተጨማሪ ያንብቡ!
05/02/2026

ገዱ አንዳርጋቸው ለጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ የምስክርነት ጥሪ ምላሽ ሰጡ።

"ጠቅላይ ሚንስትሩ ስለ እኔ የተናገሩት ሀሰት ነው" ሲሉም ገልጸዋል!

ሊንኩን ተጭነው ተጨማሪ ያንብቡ!

ጥር 28 2018 ዓ.ም--ዞብል ፖስት ዜና! የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ገዱ አንዳርጋቸው ባሳለፍነው ማክሰኞ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፊት በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ስለተፈጠረው ፀብ አ.....

Address

Addis Ababa
Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zoble Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share