InfoHub

InfoHub Your daily source for what's happening now. The Pulse delivers breaking news and top stories to keep you informed. Stay ahead.
(1)

ጎበዟ ተማሪ 15,000 ብር መክፈል አቅቷት እራ-ሷን አጠ-ፋች የሚል ዜና መስማት እንዴት ያ-ማል? 😭ሂንሴኔ ተፈሪ ትባላለች፤ ነዋሪነቷ በነቀምቴ ከተማ ሲሆን፣ በ'ኒው ጀነሬሽን' ኮሌጅ የቢኤ...
18/05/2026

ጎበዟ ተማሪ 15,000 ብር መክፈል አቅቷት እራ-ሷን አጠ-ፋች የሚል ዜና መስማት እንዴት ያ-ማል? 😭

ሂንሴኔ ተፈሪ ትባላለች፤ ነዋሪነቷ በነቀምቴ ከተማ ሲሆን፣ በ'ኒው ጀነሬሽን' ኮሌጅ የቢኤስሲ ነርሲንግ (BSc Nursing) የ4ኛ ዓመት ተማሪ ነበረች።

በቅርብ የሚያውቋት ጓደኞቿና መምህራኖቿ እንደሚመሰክሩት፣ ሂንሴኔ በትምህርቷ እጅግ ጎበዝ፣ ታጋሽ እና በከፍተኛ ውጤቷ ሌሎች ጭምር የሚቀኑባት ድንቅ ተስፋ የነበረች ወጣት ነበረች።

ሆኖም ግን፣ ይህቺ በነገይቱ ሀገር ላይ ትልቅ እምነት ተጥሎባት የነበረች ባለ ብሩህ አእምሮ ተማሪ፣ ዛሬ በገጠማት ከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ ምክንያት ህይወቷን በገዛ እጇ እንድ-ታጠፋ ያደረጋት ልብ ሰ-ባሪ ታሪክ ተሰምቷል።

የዚህ አ-ሳዛኝ ጉዳይ መነሻ ደግሞ ለትምህርት ቤት መክፈል የነበረባት አስራ አምስት ሺህ (15,000) ብር ክፍያ በመቅረቱ ምክንያት ነው።

በወቅታዊው አሰራር መሰረት፣ የቀረባትን የትምህርት ክፍያ ካላጠናቀቀች ብሄራዊ የ'Exit Exam' ፈተናን መፈተን እንደማትችል ተነግሯት ነበር። ይህንን ተከትሎ፣ የረጅም ዓመታት ልፋቷ ከንቱ ሆኖ መቅረቱ እና አብረዋት የለፉ ጓደኞቿ ተፈትነው ወደ ስራ አለም ሲቀላቀሉ እሷ ግን በገንዘብ እጥረት ምክንያት ወደ ኋላ መቅረቷ፣ ውስጧን በከፍተኛ ተስፋ መቁረጥና በጭንቀት እንዲሞላው አድርጎታል። ይህ የማህበራዊና የስነ-ልቦና ጫናም
በመጨረሻ ለዚህ አስከፊ ውሳኔ እንድትደርስ አድርጓታል።

ይህም መንግስትም ሆነ ስለወጣቱ ግድ የሚለው ሁሉ ሊሰራበት የሚገባ ሁላችንም አጥብቀን ልንፀልይበት የሚገባ ጉዳይ ነው!

ለቤተሰቦቿ ለወዳጅ ዘመዶቿ መፅናናትን ተመኘሁ!

እኔ በጣም የምገርመኝ የሶዶ መናኻራያና የአርባምንጭ መናኻሪያ ልዩነት ነው ፤ ዛሬ ቅርብ ቦታ ለመሄድ አርባ ምንጭ መናኻሪያ ሄድኩኝ ሁሉም መክኖች  ከመናኻሪያ ከ50%እስከ 100 % የታሪፍ ጭ...
17/05/2026

እኔ በጣም የምገርመኝ የሶዶ መናኻራያና የአርባምንጭ መናኻሪያ ልዩነት ነው ፤ ዛሬ ቅርብ ቦታ ለመሄድ አርባ ምንጭ መናኻሪያ ሄድኩኝ ሁሉም መክኖች ከመናኻሪያ ከ50%እስከ 100 % የታሪፍ ጭማሪ አድርጎ ነው እየጫኔ ያሉት። የመንገድ ና ትራንስፖርት ሰዎች አልሰሙም ይሆናል ብዬ ቢሮ ገብቼ ታርጋ ቁጥሮችና ስንት አስከፍለው እየጫኑ መሆናቸውን መንገድ ላይ ትራፊክ ከጠየቀ ስንት ማለት አለባችሁ እያሉ እንደሆነ ነገርኳቸው ። ማንም ምንም ያላቸው የለም ፤ ሁሉም ባሉት ታርፍ አሳፍሮ እየወጡ ናቸው፡ አሁን ይሄ ምን ይባላል ፤ የመግስት ኃላፊዎች መናኻሪያ ሄደው ስላማይሳፌሩ ህዝቡ ምን ይሁን? ይንን tragedy የምሰማ መንግስት አለ? 100%imagine፤ አሁን ነገሮች ተስተካክሏል አልተባለም? እርባ ምንጭ ለምን የለም? ለምን አልተስተካከለም? እኛ ኢትዮጵያውያን አይደለንም? የሚመለከተው መላ ማለት ይጠበቅበታል። በጣም ነው የታዘብኩት ።🤣

ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን አሸነፈበእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐግብር ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢትሃድ በተደረገው ጨዋታ የ...
09/05/2026

ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን አሸነፈ
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሐግብር ማንቼስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ምሽት 1 ሰዓት ከ30 በኢትሃድ በተደረገው ጨዋታ የውሃ ሰማያዊዎቹን ግቦች ዶኩ፣ ሀላንድ እና ማርሙሽ በ2ኛው አጋማሽ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ነጥቡን 74 በማድረስ ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ማጥበብ ችሏል፡፡

ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ ከሰንድርላንድ 0 ለ 0፣ ሊቨርፑል ከቼልሲ 1 ለ 1 አቻ ሲለያዩ፥ ብራይተን ወልቭስን 3 ለ 0 እንዲሁም በርንማውዝ ፉልሃምን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡

09/05/2026

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ የአየር ኃይል ምልመላ ጥሪ ማስታወቂያ

‼️ According to reports,   and   have made enquiries over Endrick’s availability in recent weeks.However, Real Madrid ha...
04/05/2026

‼️ According to reports, and have made enquiries over Endrick’s availability in recent weeks.

However, Real Madrid have made it clear that Endrick is firmly part of their first-team plans for next season. 🔵

04/05/2026

Celebrating my 5th year on Facebook. Thank you for your continuing support. I could never have made it without you. 🙏🤗🎉

እነዚህ አፖች ስልካችሁ ላይ ካሉ  ያጥፏቸው !​ የግል መረጃዎቻችን በጨለማው ዓለም (Dark Web) እስከ $240 ሊሸጥ ይችላል። 📌 አስፈላጊ ያልሆነ የማይክሮፎን ፍቃድ የሚጠይቁ ፦ ለስራቸ...
01/05/2026

እነዚህ አፖች ስልካችሁ ላይ ካሉ ያጥፏቸው !


የግል መረጃዎቻችን በጨለማው ዓለም (Dark Web) እስከ $240 ሊሸጥ ይችላል።

📌 አስፈላጊ ያልሆነ የማይክሮፎን ፍቃድ የሚጠይቁ ፦ ለስራቸው የማይክሮፎን አገልግሎት ሳይፈልጉ ድምጽዎን ለመቅዳት ፍቃድ የሚጠይቁ።

📌 ነፃ የቪፒኤን (Free VPN) መተግበሪያዎች፦ አብዛኛዎቹ የእርስዎን ዳታ ለሶስተኛ ወገን በመሸጥ ገቢ ያገኛሉ።

📌 የባትሪ ብርሃን (Flashlight) መተግበሪያዎች፦ ከ20 በላይ ፍቃዶችን (Permissions) የሚጠይቁ ከሆነ መረጃዎን እየሰረቁ ነው።

📌 ካልታወቁ ድርጅቶች የተሰሩ ኪቦርዶች (Keyboards) ፦ የሚጽፉትን ማንኛውንም የይለፍ ቃል (Password) ሊሰርቁ ይችላሉ።

📌 ከ6 ወር በላይ ያልተጠቀሙባቸው አፕሊኬሽኖች፦ በስልክዎ ላይ ዝም ብለው ተቀምጠው መረጃዎን ሊሰበስቡ ስለሚችሉ ማጥፋቱ ይመረጣል ።

የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ሐገራቸው የኢራንና በቀጠናው ያሉ ሐገራትን ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚቻላትን ሁሉ ታደርጋለች» አሉየሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ሐገራቸው የኢራንና በቀጠ...
28/04/2026

የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ሐገራቸው የኢራንና በቀጠናው ያሉ ሐገራትን ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚቻላትን ሁሉ ታደርጋለች» አሉ

የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ሐገራቸው የኢራንና በቀጠናው ያሉ ሐገራትን ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚቻላትን ሁሉ ታደርጋለች» አሉ። ፑቲን ይህን ያሉት የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺን ዛሬ ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው ተብሏል።
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝንት ዛሬ ሩስያ ከገቡ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት አጭር መግለጫ የሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ አገልግሎት እንዳይሰጥ ዩናይትድ ስቴትስ እንቅፋት እየሆነች ነው ሲሉ ተናግሯል። በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ላይ ከዩናይትድስቴትስ ከስምምነት ላይ ያልተደረሰው አሜሪካ በድርድሩ በምታቀርባቸው የተጋነኑ የመደራደሪያ ጥቃያቄዎች ምክንያት ነው ሲሉም ተደምጠዋል። አራግቺ ስለጉብኝታቸው አስመልክተውም «በቅርቡ ስለተከሰተው ጦርነትና ስለወቅቱ ሁኔታ ከሩስያ ወዳጆቻችን ጋር ለመወያየትና ለመገምገም ይህ ጥሩ አጋጣሚ ነው» ብለዋል ሲል የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
ዘግየት ብለው የወጡ መረጃዎች እንዳመላከቱት ደግሞ አራግቺ ከሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተገናኝተው መክረዋል። ሁለቱም መሪዎች ስለተነጋገሩበት ጉዳይ በዝርዝር ባይገለጽም የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ለኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ «ሩስያ የኢራንና በቀጠናው ያሉ ሐገራትን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚቻላትን ሁሉ ታደርጋለች» ማለታቸውን ተዘግቧል። ፑቲን አክለውም የኢራን ሕዝብ በአስቸጋሪ ሁኔታ እንደሚገኝ ገልጸው «ሰላም ያሸንፋል» ማለታቸውን የሩስያ መገናኛ ብዙኃንን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግበዋል።
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከአሜሪካ የልዑካን ቡድንን ጋራ በፓኪስታን ይገናኛሉ ተብሎ ሲጠበቅ ቅዳሜ አመሻሽ ላይ ፓኪስታንን ጥለው መውጣታቸውን ይታወሳል። ይህን ተከትሎ የኢራን መንግስት ባወጣው መግለጫ አሜሪካ ከኢራን ወደቦች የሚወጡትንና የሚገቡ መርከቦችን ማገዷን ካላቆመች ከአሜሪካ ጋር የሚደረግ ቀጥታዊ ንግግር አይኖርም ብሏል።
በሌላ ዜና የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ስለኢራን ወቅታዊ ሁኔታ ለፎክስ ኒውስ የዜና ማሰራጫ በሰጡት ቃለ ምልልስ «ሁሉም የመጫወቻ ካርዶች በእጃችን ላይ ናቸው። መነጋገር ከፈለጉ ወደኛ መምጣት አለባቸው፤ ወይም ሊደውሉልን ይችላሉ» ሲሉ ተደምጠዋል።
የአሜሪካ የመካከለኛ ምስራቅ ማዕከላዊ ዕዝ ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ ደግሞ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ወደቦች የሚወጡም ሆነ የሚገቡ መርከቦች እንዲታገዱ መመሪያ ከሰጡበት ጊዜ ጀምሮ 38 መርከቦችን ከመንገድ ማገዱን አስታውቋል።

18/10/2025

🔥25,000 ብር ልንሸልምዎ መተናል 💸💵

🔥በተጠባቂው የእንግሊዝ ፕርሚየር Liverpool ከ Manchester united ይፋለማሉ

ይህን ተጠባቂ ጨዋታ ኮሜንት ሴክሽን ላይ በትክክል ለገመቱ 25 ቤተሰቦቻችን የ1000ብር ሽልማት እንሰጣለን 💵🎁

ተሻላሚ የሚሆኑት ከቴሌግራም እና ከፌስቡክ ተመርጠው ይሆናል👇

ማሳሰቢያ ፦ የኛን የቴሌግራም እና ፌስ ቡክ አካውንት የማይከተል ሰው መልሱን ቢያገኝ እንኳን እንደማይሸለም ከወዲሁ እናሳውቃለን!

መልካም እድል!

Address


1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when InfoHub posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to InfoHub:

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share