Sileshi Kubi

Sileshi Kubi ለሁሉም ጊዜ አለው!!!

ሀገር በልጆቹዋ ትደምቃለች!!
03/09/2026

ሀገር በልጆቹዋ ትደምቃለች!!

03/09/2026

ሀገርን ማገልገል!!

ከደም መስዋዕትነት ወደ ላብ ትሩፋት!!
03/09/2026

ከደም መስዋዕትነት ወደ ላብ ትሩፋት!!

03/09/2026

ለሀገርና ለወገን!!

02/09/2026

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችው!!

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎችጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”
02/09/2026

የጳጉሜን ወር አምስቱ ቀናት ስያሜዎች
ጳጉሜን 1 – “የእመርታ ቀን”
ጳጉሜን 2 – “የማንሰራራት ቀን”
ጳጉሜን 3 – “የጽናት ቀን”
ጳጉሜን 4 – “የኅብር ቀን”
ጳጉሜን 5 – “የነገ ቀን”

02/09/2026

ለሀብታሙ፣ ለደሃው፣ ለተማረው፣ ላልተማረው፣ ለወጣቱ፣ ለአዛውንቱ!!

01/09/2026

ዜና!!

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት 1ኛ ደረጃ ወጣ። ነሀሴ 26/2018፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲየከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት...
01/09/2026

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት 1ኛ ደረጃ ወጣ።
ነሀሴ 26/2018፣ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2018 በጀት ዓመት የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ዓመታዊ የትምህርት ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው ። ባለፋት ዓመታት በተጀመሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሪፎርም ስራዎች፣ በአጋር አካላት እርካታ፣ በመውጫ ፈተና፣ በድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የትምህርት ወጪ ፣በተመራቂ ተማሪዎች የመቀጠር ምጣኔ፣ እና መሰል የሪፎርም አጀንዳዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ የከፍተኛ ትምህርት ገባዔ ከነሐሴ 25 እስከ 27 /2018 ዓ/ም እየተካሄደ ሲሆን በጉባዔው የዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ ም/ ፕሬዝዳንቶች እና አጋር አካላት ተገኝተዋል።
በአረንጓዴ ግቢው፣ በፍፁም ሠላማዊነቱ እና በተመራጭ ፕሮግራሞቹ የሚታወቀው እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተካሄደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት (Students' satisfaction Survey) አንደኛ ደረጃ በመውጣት በተማሪዎች ተመራጭ እና ተወዳጅ መሆኑን አረጋግጧል ።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ደረጃ የወጣበት የተማሪዎች የእርካታ ጥናት በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎች የሚያቀርቧቸው የምኝታ እና የምግብ አገልግሎቶች ፣ የትምህርት ጥራትን፣ የአመራር እና የመምህራንን ተደራሽነት፣ የግቢውን ውበት እና ምቹነት ፣ የግቢውን ሠላም እና ደህነት መሠረት ያደረጉ መለኪያዎችን ባካተተ ጥናት ነው።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተ አጭር እድሜው ቢሆንም ባለፉት ዓመታት ግቢውን ለተማሪዎች እና ለሰራተኞች ማራኪ እና ምቹ ለማድረግ ባካሄዳቸው መጠነ-ሰፊ የግቢ ውበት ስራዎች እና ባስፋፋቸው የአካዳሚክ ፕሮግራሞች በተማሪዎች ግንባር ቀደም ተመራጭ እየሆነ የመጣ ዩኒቨርሲቲ መሆኑ ይታወቃል።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በሰባት ኮሌጆች ማለትም በህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ፣ በቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ፣ በምህንድስና እና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ፣ በተፈጥሮ እና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ፣ በትምህርት እና ስነ-ባህሪ ኮሌጅ፣ በማህበራዊ እና ሰባዊ ሳይንስ ኮሌጅ እና በግብርና ኮሌጅ እንዲሁም በህግ ትምህርት ስር በተደራጁ በ61 የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞች መደበኛ ተማሪዎችን ለመቀበል አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ያስታወቀው ዩኒቨርስቲው በ2018 የትምህርት ዘመን ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ያመጡ ተማሪዎች እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን የመጀመሪያ ምርጫቸው እንዲያደርጉት ጥሪውን አስተላልፏል።
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ቀጥሎ ኦዳቡልቱም እና ወልዲያ ዩኒቨርስቲዎች በተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ይዘዋል።

የወርሀ ሐምሌ እና ነሐሴ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት************የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር፦የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ስምንተኛ ዓመቱን በያዘበት በዚህ ዓ...
01/09/2026

የወርሀ ሐምሌ እና ነሐሴ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቁልፍ ተግባራት ቅኝት
************

የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር፦
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ስምንተኛ ዓመቱን በያዘበት በዚህ ዓመት፤ የኮፕ32 (COP32) ሰብሳቢ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና የኮፕ32 ብሔራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ዓመታዊውንና የአንድ ጀምበር ሀገር አቀፍ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብርን መርተዋል። ዘመቻው በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአንድ ቀን ውስጥ 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ታላቅ ግብን የሰነቀ ሲሆን በዚህም ከተቀመጠው እቅድ በላይ ማሳካት የቻለ ዘመቻ ነበር። ይህ ጥረት በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን የተከናወነ ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ተሳታፊዎች የታሪክ፣ የአንድነት እና የጽናት ድል ያስመዘገቡ መሆናቸውን በመግለጽ ለሁሉም ምስጋና አቅርበዋል።

ፕሮጀክቶች ጉብኝት እና ምረቃ፦
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በባሕር ዳር የሚገኘውን የደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አዲስ ተርሚናል መርቀው ከፍተዋል። ይህ ፕሮጀክት ለኢትዮጵያ ቁልፍ ከሆኑ መግቢያ በሮች አንዱ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ከተማዋ በቅርቡ ባጋጠሟት ፈተናዎች ሳትበገር የጽናት፣ የማገገም እና የቀጣይ ኢንቨስትመንት ማዕከልነት ማረጋገጫ መሆኑን አስገንዝበዋል። አዲሱ ተርሚናል ዘመናዊ የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ ልማቶችን፣ የተሻሻሉ የመዳረሻ መንገዶችን እና ሰፊ አገልግሎቶችን በማካተት የአውሮፕላን ማረፊያውን አቅም የሚያሰፋና የመንገደኞችን ምቾት የሚያሻሽል ሲሆን፤ ይህም ከከተማዋ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽን ጋር ተዳምሮ ባሕር ዳርን ለዓለም አቀፍ እና ለሀገር ውስጥ በረራዎች ማዕከል ያደርጋታል።
‎ማኅበራዊ ጉዳይ፦

በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ (OBN) ጋር ቃለ መጠይቅ ያደረጉ ሲሆን በቆይታቸውም ከሀገራዊ ጥቅም ይልቅ ግላዊ ጥቅምን ያስበለጡ በኦሮሚያ፣ በአማራ እና በትግራይ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች መንግሥትን ለብቻቸው ማሸነፍ እንደማይችሉ ከተገነዘቡ በኋላ ህብረት መፍጠራቸውን ገልጸዋል። በተጨማሪም ጊዜው ባለፈበት የፖለቲካ አስተሳሰብ እና የአመራር ዘይቤ እነዚህ ቡድኖች ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ለመበታተን ለሚፈልጉ ታሪካዊ የውጭ ጠላቶች እንደ መጠቀሚያ መሣሪያ እያገለገሉ የመሆናቸውን ታሪካዊ ግድፈት አብራርተዋል።

አክለውም እውነተኛ ዲሞክራሲ ከተራ የፖለቲካ ግልጽነት ባለፈ የሕግ የበላይነትን ወደሚያረጋግጥ እውነተኛ ብሔራዊ ውይይት መሸጋገር እንዳለበት አፅንዖት ሰጥተዋል።

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sileshi Kubi posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share