07/05/2025
14 ያለቀላቸውን ግቦች ያዳነው የኢንተሩ ግብ ጠባቂ ያን ሶመር ..
የኢንተር ሚላኑ ግብ ጠባቂ ያን ሶመር በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች የባርሴሎናን 14 ያለቀላቸውን የግብ ሙከራዎች አክሽፏል።
ሶመር ባለፉት 15 ዓመታት የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ላይ ሁለተኛው ብዙ ግብ ያዳነ ግብ ጠባቂ መሆን ችሏል።
ከዚህ በፊት እንዲህ ያለው አስደናቂ ስራን በመስራት ጂያንሉጂ ቡፎን 17 ኳሶችን ከግብ በማዳን ሪከርዱን ይዞ ይገኛል።
ያን ሶመር ባሳየው የምሽቱ ድንቅ ብቃት የኢንተር ሚላን እና ባርሴሎና ጨዋታ ኮከብ ተጫዋች ተብሎም ተመርጧል።
ኢንተር ሚላን የአሁን የማንችስተር ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናናን በ50 ሚሊዮን ዩሮ ሲሸጥ ያን ሶመርን ከባየር ሙኒክ በአውሮፓውያኑ 2023 በ6 ሚሊዮን ዩሮ ነበር ያስፈረመው።
ታዲያ ኢንተር 50 ሚሊየን ዩሮ በኦናና አትርፎ በ6 ሚሊየን ዩሮ የገዛው የ36 ዓመቱ ሶመር ከተጠበቀውም ከተከፈለውም ገንዘብ በላይ የኢንተር ሚላን ዋስትና ሆኖ ተገኝቷል