Soofam News TUBE

  • Home
  • Soofam News TUBE

Soofam News TUBE Information

14 ያለቀላቸውን ግቦች ያዳነው የኢንተሩ ግብ ጠባቂ ያን ሶመር ..የኢንተር ሚላኑ ግብ ጠባቂ ያን ሶመር በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች የባርሴሎናን 14 ያለቀ...
07/05/2025

14 ያለቀላቸውን ግቦች ያዳነው የኢንተሩ ግብ ጠባቂ ያን ሶመር ..
የኢንተር ሚላኑ ግብ ጠባቂ ያን ሶመር በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች የባርሴሎናን 14 ያለቀላቸውን የግብ ሙከራዎች አክሽፏል።

ሶመር ባለፉት 15 ዓመታት የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የግማሽ ፍጻሜ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ላይ ሁለተኛው ብዙ ግብ ያዳነ ግብ ጠባቂ መሆን ችሏል።

ከዚህ በፊት እንዲህ ያለው አስደናቂ ስራን በመስራት ጂያንሉጂ ቡፎን 17 ኳሶችን ከግብ በማዳን ሪከርዱን ይዞ ይገኛል።

ያን ሶመር ባሳየው የምሽቱ ድንቅ ብቃት የኢንተር ሚላን እና ባርሴሎና ጨዋታ ኮከብ ተጫዋች ተብሎም ተመርጧል።

ኢንተር ሚላን የአሁን የማንችስተር ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናናን በ50 ሚሊዮን ዩሮ ሲሸጥ ያን ሶመርን ከባየር ሙኒክ በአውሮፓውያኑ 2023 በ6 ሚሊዮን ዩሮ ነበር ያስፈረመው።

ታዲያ ኢንተር 50 ሚሊየን ዩሮ በኦናና አትርፎ በ6 ሚሊየን ዩሮ የገዛው የ36 ዓመቱ ሶመር ከተጠበቀውም ከተከፈለውም ገንዘብ በላይ የኢንተር ሚላን ዋስትና ሆኖ ተገኝቷል

የትራምፕ አስተዳደር በፈቃዳቸው ከአሜሪካ ለሚወጡ ሰነድ አልባ ስደተኞች 1ሺ ዶላር እንደሚሰጥ አሳወቀ‼️የትራምፕ አስተዳደር በፈቃዳቸው ከአሜሪካ ለቀው  ወደ  አገራቸው ለሚመለሱ ህገወጥ ስደተ...
07/05/2025

የትራምፕ አስተዳደር በፈቃዳቸው ከአሜሪካ ለሚወጡ ሰነድ አልባ ስደተኞች 1ሺ ዶላር እንደሚሰጥ አሳወቀ‼️

የትራምፕ አስተዳደር በፈቃዳቸው ከአሜሪካ ለቀው ወደ አገራቸው ለሚመለሱ ህገወጥ ስደተኞች በነፍስ ወከፍ የ1ሺ ዶላር አበል እንደሚሰጥ ትላንት ሰኞ አስታውቋል፡፡ የጉዞ ወጪያቸው እንደሚሸፈንም ታውቋል፡፡

የ1ሺ ዶላር አበሉ የሚከፈላቸው ወደ ትውልድ አገራቸው መመለሳቸው ከተረጋገጠ በኋላ እንደሆነ የአገር ውስጥ ደህንነት ዲፓርትመንት ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል፡፡

"እዚህ ያላችሁት በህገ ወጥ መንገድ ከሆነ በፈቃዳችሁ ወደ አገራችሁ መመለስ ተመራጩ፣ ወጪ ቆጣቢና ደህንነቱ የተጠበቀ መንገድ ነው" ሲሉ የአገር ውስጥ ደህንነት ሚኒስትር ክሪስቲ ኖም ተናግረዋል፡፡

በፈቃዳቸው አሜሪካን ለቀው ለሚወጡ ህገወጥ ስደተኞች የሚከፈለው የ1ሺ ዶላር አበልና የሚሸፈነው የአየር ትራንስፖርት ወጪ፣ በግዴታ ለማባረር ከሚወጣው ወጪ ጋር ሲነጻጸር በ70 ፐርሰንት ገደማ እንደሚቀንስ ያመለከተው ዲፓርትመንቱ፤ ህጋዊ ሰነድ የሌለውን ሰው በቁጥጥር ስር የማዋልና ከአገር የማስወጣት አማካይ ወጪ 17ሺ ዶላር እንደሆነ ጠቁሟል፡፡

"ይህን ኬንያዊ🇰🇪 ሯጭ አስታውስ ከመጨረሻው መስመር ጥቂት ጫማ ርቀት ላይ የነበረ ነገር ግን በምልክቱ ግራ ተጋብቶ ውድድሩን እንዳጠናቀቀ በማሰብ ቆመ። ስፔናዊው ሯጭ ኢቫን ፈርናንዴዝ ከኋላው...
07/05/2025

"ይህን ኬንያዊ🇰🇪 ሯጭ አስታውስ ከመጨረሻው መስመር ጥቂት ጫማ ርቀት ላይ የነበረ ነገር ግን በምልክቱ ግራ ተጋብቶ ውድድሩን እንዳጠናቀቀ በማሰብ ቆመ። ስፔናዊው ሯጭ ኢቫን ፈርናንዴዝ ከኋላው ሆኖ ነበር እና ምን እየተፈጠረ እንዳለ ስላወቀ ውድድሩን እንዲቀጥል ኬንያዊውን መጮህ ጀመረ። አንድ ጋዜጠኛ ኢቫንን "ለምን እንዲህ አደረግክ?" ኢቫን እንዲህ ሲል መለሰ:- "የእኔ ህልም አንድ ቀን የምንገፋፋበት እና የምንረዳዳበት አይነት የማህበረሰብ ህይወት እንዲኖረን ነው" ጋዜጠኛው "ግን ለምን ኬንያዊውን እንዲያሸንፍ ፈቀድክለት?" ኢቫን እንዲህ ሲል መለሰ: - " እንዲያሸንፍ አልፈቀድኩም, ሊያሸንፍ ነበር, ውድድሩ የእሱ ነበር." ጋዜጠኛው እንደገና "ግን ማሸነፍ ይቻል ነበር!" ኢቫን ወደ እሱ ተመልክቶ "ግን የእኔ ድል ምን ሊሆን ይችላል? በዚያ ሜዳሊያ ውስጥ ያለው ክብር ምን ይሆን? እናቴ ስለዚያ ምን ታስባለች?" እሴቶች ከትውልድ ወደ ትውልድ ይተላለፋሉ. ልጆቻችንን ምን ዓይነት እሴቶችን እያስተማርን ነው? ልጆቻችንን የማሸነፍ ዘዴዎችን እና የተሳሳቱ መንገዶችን አናስተምር። ይልቁንም የእርዳታ እጅን ውበት እና ሰብአዊነት እናስተላልፍ. ምክንያቱም ታማኝነት እና ስነምግባር እያሸነፉ ነው!"

እስራኤል በዋና አየር ማረፊያዋ የደረሰባትን የሚሳኤል ጥቃት ተከትሎ በየመን ሁቲዎች ላይ የአፀፋ እርምጃ እንደምትወስድ ገለጸች‼️የእስራኤል ጦር ከየመን የተተኮሰ ሚሳኤልን ለመጥለፍ መሞከሩን ...
07/05/2025

እስራኤል በዋና አየር ማረፊያዋ የደረሰባትን የሚሳኤል ጥቃት ተከትሎ በየመን ሁቲዎች ላይ የአፀፋ እርምጃ እንደምትወስድ ገለጸች‼️

የእስራኤል ጦር ከየመን የተተኮሰ ሚሳኤልን ለመጥለፍ መሞከሩን ማስታወቁን ተከትሎ የሀገሪቱ ፖሊስ በሀገሪቱ ዋና አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ "ተፅእኖ" ያለው አደጋ መድረሱን አስታውቋል።

ከየመን የሁቲ አማጽያን የተሰነዘረ ነው የተባለው ጥቃት በእስራኤል ዋና አየር ማረፊያ ላይ ጉዳት ባያደርስም በአካባቢ ግን ለስደስት ሰዎች መጎዳት እና ለበረራ መስተጓጎል ምክንያት ሆኗል።

ይህን ተከትሎ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ለጥቃቱ "ሁለገብ ምላሽ" እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

በቴል-አቪቭ ቤን ጉሪዮን አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ ያረፈው የሚሳኤል ጥቃት ከየመን የተተኮሰ መሆኑን የእስራኤል ጦር ማረጋገጡን ገልጾ ሚሳኤሉን ለመጥለፍ ሙከራ ማድረጉን አስታውቋል።

ቀደም ሲል በጦርነት ውስጥ በነበረችው ጋዛ ለፍልስጤማውያን ድጋፍ እናደርጋለን የሚሉት ሁቲዎች በእስራኤል ለደረሰው ጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስደዋል።

አማፅያኑ ሃይፐርሶኒክ ባሊስቲክ ሚሳኤል በመጠቀም የእስራኤል ዋና ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሆነው ቤን ጉሪዮን ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ኦፕሬሽን እንደነበር ገልጸዋል።

ይህንን ተከትሎ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ዝርዝር ማብራሪያ ባይሰጡም አጸፋዊ ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

Address


1000

Telephone

+251922045038

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Soofam News TUBE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Soofam News TUBE:

Shortcuts

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share