31/07/2026
የልብ ብርሃን ማለት የሀገርን ከፍታ አስቀድሞ የማየት፣ በፈተናዎች ውስጥ እንኳ የተስፋን ጎህ አሙቆ የመጠበቅ፣ እንዲሁም የትናንትናውን ክብር ከነገው ታላቅነት ጋር የሚያገናኝ የመንፈስ ጥንካሬ ነው።
የብርሃናማ ልብ ባለቤቶች ሀገራቸውን ሲመለከቱ ድክመቷንና ቁስሏን ብቻ ሳይሆን፣ ጥበቧን፣ ጽናቷንና እምቅ አቅሟን ያያሉ።
ልበ ብርሃኖች የታሪክ ባለዕዳ ሳይሆኑ የታሪክ ባለቤቶች ናቸው። ምክንያቱም፣ የትናንትናውን የተከበረ ታሪክ እያሰቡ፣ የዛሬውን ፈተና በጽናት እየተጋፈጡ፣ ነገን በብሩህ ተስፋ የሚገነቡ አርቆ አሳቢዎች ናቸውና!
እኛም ልባችንን አጥርተንና በፍቅር ሞልተን፣ የሀገራችንን ሉዓላዊነትና ጥቅሟን አስቀድመን የኢትዮጵያን ከፍታ በጋራ እናረጋግጣለን!