ኢትዮጵያ Ethiopia

ኢትዮጵያ Ethiopia ትኩስ ዜናዎችን አስተማሪና አዝናኝ መረጃዎችን እናደርሳለን ! (Ethiopia )

‎አስተማሪ ታሪክ!‎‎ከማጣት በስተጀርባ ያለው በረከት!‎‎አንድ ሰው ነበር በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ በማዕበል ተመታና መርከቡ ተሰባብሮ በባህሩ ውስጥ ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱ...
22/07/2025

‎አስተማሪ ታሪክ!

‎ከማጣት በስተጀርባ ያለው በረከት!

‎አንድ ሰው ነበር በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ በማዕበል ተመታና መርከቡ ተሰባብሮ በባህሩ ውስጥ ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፍና አንድ ጎጆ ቤት ውስጥ ለቀናት ለብቻው እዛች ደሴት ላይ ይኖራል።ዓሳ እያጠመደ እየተመገበ ብዙ ቆየ።

‎አንድ ቀን ዓሳ ሊያጠምድ ወደ ባህሩ እየሄደ በመሀል እዛች ባህር ላይ ጭስ ይሸተዋል ዞር ብሎ ሲመለከት ያቺ ጎጆው እየነደደች ነው ... እየሮጠ ቢመለስም ጎጆውን ሊያድናት አልቻለም ለካ ዓሳ ለማብሰል ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ ጎጆውን አንድዶታል አለቀሰ ፈጣሪውን ወቀሰ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ጥለኃኝ ከቤተሰቦቼ ነጠልከኝ ስታበቃ በስንት ልፋት የሰራኋትን ጎጆ ታቃጥልብኝለህ ብሎ አለቀሰ አማረረ ...

‎ከደቂቃዎች በኃላ አንድ ድምፅ ሰማ ወደ ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ አየ ተደሰተ... የመርከቡ ሶዎችም መጥተው ጭነው ወሰዱት ከዚያም ለመርከቡ ሰዎች ጠየቃቸው።
‎እንዴት አገኛቹኝ እዚህ አከባቢ እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት መጣቹ አላቸው ...

‎መርከበኞቹም እኛም በዛኛው በኩል ዙረን እየሄድን ነበር ከዚያ በኩል ጭስ አየን እና እዚ ሰው ይኖራል ብለን መጣን አንተን አገኘን አሉት ።
‎አቤት አምላኬ ለካ ከዚ መከራ ልታወጣኝ ፈልገህ ነው ትንሽዋ ጎጆዬን ያፈረስከው ወደ ትልቁ ቤት ልትወስደኝ ነው አለ።

‎አንዳንዴ የሆነ ነገር ስናጣ ሲበላሽብን ፈጣሪንም ሰውንም ስናማርር እንኖራለን ግን ካጣነው ነገር ከጎደለብን ነገር ጀርባ ብዙ ጥሩ ነገር ልናገኝ እንደምንችል እንዘነጋለን በችግራችን ግዜ መጠጋት ያለብንን አምላካችንን እንረሳልን ከዝያም አልፈን የሁሉ ነገር ፈጣሪውን እንኮንነዋለን።

‎ያጣነውን የሰጠን ፈጣሪ አእምሯችን ከሚያስበው በላይ ሊሰጠን እንደሚችል ማመን አለብን!


በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ‎‎ፍቅር እና ገንዘብ‎‎“መለያየት እፈልጋለሁ፡፡ ፍታኝ?” አልኩት በመኪናው መስኮት አሻግሬ ዓይኖቹን እየሸሸሁ፡፡‎‎“እሺ!!” ነበር መልሱ:: ቢያንስ ‘ለምን?...
22/07/2025

በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ

‎ፍቅር እና ገንዘብ

‎“መለያየት እፈልጋለሁ፡፡ ፍታኝ?” አልኩት በመኪናው መስኮት አሻግሬ ዓይኖቹን እየሸሸሁ፡፡

‎“እሺ!!” ነበር መልሱ:: ቢያንስ ‘ለምን?’ ብሎ እንዴት አይጠይቀኝም?

‎“መች ነው እንዲሆን የምትፈልጊው? አሁን? ነገ? ከሳምንት በኋላ? መቼ?” ቀለል አድርጎ ቀጠለ፡፡ ቀጥዬ የምለው ጠፋኝ፡፡ ለራሴ ምክንያት መስጠት እፈልጋለሁ፡፡ ተናዶ እንዲናገረኝ እሱ ላይ እንከን ማግኘት አጥብቄ እፈልጋለሁ፡፡’ፈታችው’ ከመባል ሌላ ቅጥያ ተጨምሮበት ‘ስላናደዳት ፈታችው’፣ ‘ስለመታት ፈታችው’……… ብቻ ምክንያቱ ከሱ ቢመጣ ደስ ይለኛል፡፡

‎“ካለቀልን ዛሬም ብንፋታ ደስ ይለኛል፡፡”

‎“ከዛሬ በኋላ ተፋተናል፡፡ የግድ በህግ መፋታት የለብንም፡፡ እኔን መፍታት አይደል የፈለግሽው? ስለወደድኩሽ እንጂ ማንም ስለፈረመ እና ምስክር ስለተጠራ አላገባሁሽም፡፡” ብሎኝ ከመኪናው ወረደ እና የኔን በር ከፈተልኝ፡፡ ቤታችን ደጅ ደርሰን ነበር፡፡ ተናደድኩ፡፡

‎“የንብረት ክፍፍሉ……..” አላስጨረሰኝም፡፡

‎“የትኛውን ንብረት ነው የምትፈልጊው?” የአጥሩን በር ከፍቶ በእጁ እንድገባ አሳየኝ፡፡

‎“ድርሻዬን::”

‎“ህምምምም…….. ቅር ካላለሽ ትንሿን መኪና ልውሰዳት ሌላውን ንብረት አልፈልገውም፡፡ ከዛሬ በኋላ ባልሽ አይደለሁም፡፡ ምንም ንብረትም የለኝም፡፡” ብሎኝ ‘ትንሿ’ ያላት መኪናው ውስጥ ገብቶ ተመልሶ ሄደ፡፡

‎ምን እንደምፈልግ ግራ ገባኝ፡፡ ካሳሁንን ሳላገባው በፊት ነበር የማፈቅረው ቀን የሚናፍቀኝ፡፡ ሳላገባው ፈትቼዋለሁ፡፡ እሱ ያገባኝ የመሰለው ቀን እኔ አግብቼም ፈትቼዋለሁ፡፡ታዲያ ለምን አገባሁት? እሱን አላገባሁትም፡፡ ገንዘቡን እንጂ። ወንዶች ‘ሴት ልጅ ገንዘብ ያለው ወንድ ትወዳለች’ ሲሉ ሳቄ ያመልጠኛል፡፡ ወይ ሰውየው ማርኳታል ወይ ገንዘቡ ማርኳታል፡፡ ለአንዳቸው ቅድሚያ ትሰጣለች፡፡ለገንዘቡ ብላ ከሆነ ገንዘቡን እንጂ እሱን አትወደውም። ገንዘቡ እስካለ ወይም የምትፈልገውን እስክታገኝ ድረስ አለች፡፡ እነሱ ግን ራሳቸውን ሳይሆን ገንዘባቸውን ያቀርቡላታል፡፡ ምክንያቱም የቁስን ያህል ራሳቸውን አያምኑትም፡፡ ስለዚህ ከቁሳቸው ይልቅ ራሳቸውን ተወዳጅ አድርገው ማቅረብ ሲሳናቸው ለገንዘቤ ብላ ነው የወደደችኝ ይላሉ እንጂ ገንዘቤን ነው የወደደችው አይሉም፡፡ ሰውየውን ከወደደችው ለገንዘቡ ብላ፣ ለቁመናው ብላ፣ ለወዙ ብላ…. የሚሉት ቀልድ አይጥመኝም፡፡ በቃ ሰውየውን ነው የወደደችው፡፡

‎የዛን ቀን ምሽት አልመጣም፡፡ ጠበቅኩት፡፡ እውነቱን እንደሆነ ገባኝ፡፡ ካሳሁን ፈቶኛል፡፡ ሁለተኛው ቀን መሸ ።አልመጣም፡፡ አልደወለም፡፡ ሶስተኛ ቀን ሆነ……… አራተኛ ቀን መጣ… … አስር ቀን ሞላው። አልመጣምም። አልደወለምም። የገባኝ ግን ቢመጣ ደስ እንደሚለኝ ነው፡፡እሱን መፍታት ያስደስተኛል ብዬ ያሰብኩትን ያህል አልነበረም የደስታዬ መጠን፡፡

‎“አልወደውም፡፡ ከሀብቱ እንጂ ከእርሱ ጉዳይ የለኝም።” ለራሴ ብቻዬን አነበነብኩ። ስልኬን እልፍ ጊዜ ልደውልለት አነሳሁ። እልፍ ጊዜ ተውኩት፡፡ በአስራአንደኛው ቀን ስልኬ ጠራ። እሱ ነበረ። ለምን ደስ አለኝ? አብሬው መኖር የማልፈልገው ሰው ድምፁን መስማቴ እንዴት አስደሰተኝ?

‎“ደህና አደርሽ ሰብሊ? …… ላግኝሽ?”

‎“እሺ:: የት እንገናኝ?”

‎“ስራ ቦታ:: አራት ሰዓት ላይ መጥቼ ወስድሻለሁ፡፡”

‎ስራ የመግባት ፍላጎት አልነበረኝም፡፡ቁምሳጥኑን ከፍቼ ሊያቆነጀኝ ይችላል ብዬ ያሰብኩትን ሁሉ ልብስ ሞከርኩ፡፡ ላማልለው? ወይስ ከሱ በመለየቴ አለመከፋቴን ለማሳየት? ለራሴ የምሰጠው ምክንያት ባይኖረኝም

ኡፍፍፍፍ ይህንን ፁሁፍ ሳነበው...አንብቡት እስኪ ምክንያቱ ባይገባኝም ክፍሉን መኝታቤት አድርጎታል።እየመጣ ይተኛል።ገና የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ሆኖ፤አባቱ በመኪና አንቀባሮ እያመጣው፤እኔ መምህ...
21/07/2025

ኡፍፍፍፍ ይህንን ፁሁፍ ሳነበው...አንብቡት እስኪ
ምክንያቱ ባይገባኝም ክፍሉን መኝታቤት አድርጎታል።እየመጣ ይተኛል።ገና የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ሆኖ፤አባቱ በመኪና አንቀባሮ እያመጣው፤እኔ መምህሯ እንኳ በልቼ ማላቀውን በየቀኑ እየበላ ሲያንቀላፋ ደሜ ይፈላል!!ክፍል ውስጥ ስገባ ከተማሪ ሁሉ ሳየው ተስፋ ቆርጣለሁ።እኮሳተርበታለሁ።ባይፈቀድልኝም ሰበብ እየፈለኩ አጮለዋለሁ።እሱ እቴ...

እንኳን ትምህርቱ ማስተምረው ምን ሰብጀክት መሆኑን አያቅም።አስተማሪ ሁሉ ነገሩ ሰልችቶታል።ካልተማረ ባያመጡት የሚልም አልጠፋም።ግን ደሞ ዳይሬክተሩ እሱን የነካ በእንጀራው መጣ የምትል ቀጭን ትእዛዝ አስተላልፏል።በዚህ ምክንያት እሱም ሲተኛ እኛ ስናስተምር አመቱ ተጠናቆ የመጨረሻው ቀን ደርሷል

አንተ ባሮክ ባሮክ ባሮክ....(የመጨረሻው ሟን ክፍለ ጊዜው ተደውሎ ክፍል ውስጥ ብቻውን ተኝቷል

አቤት...|ፍንጥር ብሎ እየተነሳ

ቆይ ማታ ማታ አትተኛም??ለምንድነው በትክክል ማትማረው?? ቆይ ምን ጎድሎብካል???

ምንም

አትፍራ ንገረኝ ለሊት ጌም ትጫወታለክ አደለ??

አረ አልጫወትም

እና

እማ እና አባባ ሁሌ ይደባደባሉ ሁሌ አባቴ እየመጣ ይደበድባታል።እናቴ በሱ ድብደባ ልትሞትብኝ ነው።እሷ እንዳትሞትብኝ ለሊት ቁጭ ብዬ እጠብቃታለሁ።ትንሽ እንቅልፍ ሚወስደኝ እዚህ ስመጣ ነው።

አይኑ ውስጥ እንባ ሞልቶ ሲያወራኝ አንጀቴ ይንሰፈሰፍ ጀመረ።አላስተዋልነው እንጂ ከለቅሶ ብዛት አይኑ ቀልቷል።ሰአቱን ጠብቆ የሚመጣው አባቱ በማርፈዱ ምክንያት ደጅ ቁጭብሎ ምሳ እቃውን ላመጣለት ስሮጥ ሄድኩ።ምሳቃው ይከብዳል ውስጡ ያለውን ምግብ እንዳልበላው ያስታውቃል።አጠገቡ እንደደረስኩ መሳሳት በሞላው ድምፅ

ባሮኬ ምሳክን አልበላክም እንዴ አልኩት

እናቴኮ ተደብድባ ታማ ተኝታለች።እሳ ምግብ ከበላች ቆየች።እኔ ያለ እናቴ ምግብ አልበላም (ሲል አይኑ ላይ የቆረዘዘውን እንባ ዘረገፈው።ብዙ ማልቀስ ብዙ ማውራት ብዙ መጮኽ እንደማይችል ያስታውቃል።ልጅነቱ ተቀምቶ የልጅ ሽማግሌ ሆኗል።መሳቅ መጫወት ማውራት መሯሯጥ ለሱ ብርቅ ነው።ከደቂቃወች በኋላ አባቱ የሚያሽከረክራት መኪና በር ላይ ደርሳ ስትቆም አየሁና እንባውን ጠራርጌ ይዤው ሔድኩ።መኪና ውስጥ ግን ሁሌ ሚመጣው አባቱ አልነበረም የሆነ ጢማም ሰው ከመኪና ወርዶ ሲጣደፍ መጣና

ይቅርታ አስጠበቅኳችሁ ብሎ ጎትቶኝ ትንሽ ከባሮክ ካራቀኝ በኋላ ድምፁን ቀንሶ ያወራ ጀመረ

የባሮክ አጎት ነኝ ማለቴ የእናቱ ወንድም።የባሮኬ እናት ዛሬ አርፋለች አባቱ ደሞ ታስሯል።የመጣሁት ባሮኬን ልወስድ ነው።ምናልባት በቶሎ ከተመለሠ አመጣዋለሁ እናንተም.....(ሰውየው ከእንባው ጋ እየታገለ አውርቶኝ ባሮክን አቅፎት መኪና ውስጥ ገባ።ባሮክ ግን ሁሉን ያወቀ ይመስላል።በመስኮት አሻግሮ እያየኝ እንባው እየፈሰሰ ከአይኔ ተሰወረ

ባሮክ ከዛች ቀን ወዲህ ተመልሶ አልመጣም።ከባሮክ ጋ የመጨረሻዋ ቀን አስተዋውቃ ለያየችን

"ባጭር ቀረን" ስንል - እድሜ ላበደሩንቀርፀው ላሳመሩንለኩሰው ላበሩንቺርስ!!።።።።ፊታችንን ዐይተው እንደተቸገርን - ካይናችን ላወቁስለማርያም ብለን እስክንለምናቸው - ቆመው ላልጠበቁቺርስ!...
21/07/2025

"ባጭር ቀረን" ስንል - እድሜ ላበደሩን
ቀርፀው ላሳመሩን
ለኩሰው ላበሩን
ቺርስ!!
።።።።
ፊታችንን ዐይተው
እንደተቸገርን - ካይናችን ላወቁ
ስለማርያም ብለን
እስክንለምናቸው - ቆመው ላልጠበቁ
ቺርስ!!!
።።።።
ወድቀው ለማይጥሉ -ነግሰው ለሚያነግሱ
ነውራችንን ዐይተው
ልክ እንደ ድመት ኩስ ፣ ለሚያለባብሱ
ብድር አበድረው ፣ ፈጥነው ለሚረሱ😉
ቺርስ!!!!
።።።።።።
ላባ ላረጉልን ፣ የመከራ ሸክሙን
ቀልደው ላሳቁን ፣ ተጫውተው ላከሙን
በቸከ ዘመን ላይ...
ስጋ ለበስ ትንግርት -ሆነው ላስደመሙን
ቺርስ!!!!!
።።።።።።።።።።።
(✍️ Bewketu Seyoum )

"ለምንድነው ድንገት የተውከኝ ?"አለቺኝ "እኔ'ንጃ ምን አልባት ፈርቼሽ ይሆናል"።በዓይኗ እየተቅለሰለሰች  "ምኔ አስፈራህ ትባ'ላለች አሉህ ወይ "ጥቁረቷ የዐይኗን ውበት ጨምሮታል  ጥቁረቷ ...
21/07/2025

"ለምንድነው ድንገት የተውከኝ ?"አለቺኝ

"እኔ'ንጃ ምን አልባት ፈርቼሽ ይሆናል"።

በዓይኗ እየተቅለሰለሰች "ምኔ አስፈራህ ትባ'ላለች አሉህ ወይ "

ጥቁረቷ የዐይኗን ውበት ጨምሮታል ጥቁረቷ ጥርሷን ጥርሰ በረዶ ናት እንድትባል ያደረጋት ይመስለኛል።

ስታምር !

ትክ ብዬ እያየኋት

"የመወደድ ርኃብ ያለብሽ ይመስላል "አልኳት

ምን ማለት ነው ??

"የሚወደኝ አጥቼ ማለት ነው? " ሳቀች አሳሳቋ ፌዝ አዝሏል

አይምሰልሽ...
የአንዳንድ ርሃብ ምንጭ እኮ የአቅርቦት እጥረት አይደለም የአስተዳደግ ጠባሳም ሊሆን ይችላል።

ቀጠሮ ኖርበት የክት ልብሱን አጥቦ ፀሃይን እንደሚጠብቅ ሰው ነው ቀልብሽ ቆሌሽ ሁሉ ነገርሽ መወደድሽን የሚጠብቀው ....

እመኚኝ ቲጂ...

ማስከተል ለምደሻል ...

ፍላጎት አምጠሽ ፣አስወልደሽ ፣አሳድገሽ እንዳላወቀ ድንግጥ ብለሽ እንዴት እንደዚህ ሊሰማ ቻለ !? ብለሽ መካድ ለምደሻል !

ለመወደድ ምቹ ሆኖ ጠዋት ማታ ከለፉ በኃላ በዚህ መንገድ አላሰብኩም ብለው ከሚያለግጡት ውስጥ ነሽ

ከልብ ያሆነ ፈገግታ ፊቷ ላይ ብርት ብሎ ጠፋ ..."ያንተ ጠላት አንተ ነህ መታገስ ሲያቅትህ ለመሸሽ የሰጠህኸው ሰበብ ነው ግርማ እመነኝ የማጣት ፍርሃት አለብህ ..."

አይ ቲጂ..

እኔ የማቃጥለው ትርፍ ግዜ የለኝም !!
የመታኝን ዓይነት እንቅፋት እንዳየሁት ነው የማውቀው ከነ ሕመሙ ነው የማስታውሰው

እኔ የሰው trauma ማከም አቅም ላይ አይደለሁም ...!

አሁን ባላሁበት ሁኔታ አልችልሽም...

ያሸሸኝ የአቅም ጉዳይ ነው ...
መንገድሽን ዞር ብለሽ እይው ሲርቁሽ የምትከትየው እና ሲቀርቡሽ የምትርቂው ርቀት ተመሳሳይ ይመስለኛል

ፈራሁሽ !!

እንዳንቺ ዓይነት ሰዎች እንደተወደዱ ካረጋገጡ በኋላ ቀስስ ብለው ከሪትሙ ይወጣሉ ለመወደድ ያደረጉት የከፈቱትን ሁሉ ዝግትግት ያደርጋሉ ...

Look ...

መጀመርያ ሰሞን እምቶኝልኝ ነገር ሁሉ እንደእጮኛሽ ነው ፣ የመጀመርያ ሰሞን የምታወሪበት ድምፅት እንኳን የለም ። እንክብካቤሽ፣ መንገድ ስንሄድ ሽጉጥ የምትይብኝ ፣መውድድሽ በየምክንያቱ ማክበርሽን በየስበቡ የምታሳይኝ ነገር ሁሉ ራሱን አጥፍቷል።

የመንገደኛን ኮቴ መከተል አልችለም ትኩረቴን የሚሻ ህልም አለኝ የኔን ግዜ የሚፈልግ ሌላ ትግል አለኝ።

"በኔ አታሳብ ግርምሽ
ቶሎ መወደድ ለምደህ ነው!! ሳጠይቅ ማግኘት አበላሽቶህ ነው!!
ሳትበረታ ላጣኸው ሁሉ ያንተ ጥፋት እንዳልሆነ ለጭንቅላትህ መንገር ለምደህ ነው ።ድክመቱን ሁሉ የሰው ችግር አድርጎ እንደሚተነትን የሚያሳዝነኝ የለም ።"

ቲጂዬ
እውነትሽን ነው አቅም ስለሌለኝ ነው የሸሸሁት።

ከማልችለው ጋ ምን አታገለኝ ብዬ ነው !! አንቺ ደሞ ሁኔታሽ ሁሉ እንደወፍ ነው ሲከተሉሽ ትበርያለሽ ስረጋጋ ስቆም መጥተሽ አናቴ ላይ ትወጫለሽ ደስታ ሊያስደንሰኝ ሲጀምር ትበርያለሽ ...

እንደቅድሙ አልሳቀችም ....

"ዳንስ መቼ ትችል እና ...ይልቅ ግርምሽ
ሪስክ የማይወስድ ሰው አልወድም ፣
የተበላሸ ነገር ለመስራት የማያቅድ ወንድ ፤ የተሰራ ነገር የሚያሳድድ ሰው ያሳዝነኛል በተለይ ወንድ ...."

ካንቺ ባላቅም ....!

ጀግና የሚያተርፈውን ሳያሰላ አይታገልም ። ጀግና ሁኔታን እና ዋጋን አስልቶም ይሸሻል
እስከማውቀው .... አለም ላይ የመወደድ ርሃብ ካለበት ሰው ጋ እንደተጣበሰ ፣ እንደተጋባ የሚያሳዝነኝ የለም ...

ጠዋት ማታ ሥራ አለበት፥ ማባበል አለበት፥ ውድድር አለበት ኑሮ ሁሉ ሪሲሊንግ በይው...።እስኪ እናንተ ብትሆኑ ምን ታደርጋላችሁ መሸሽ ወይንስ ያልተሰራን መስራት???

‎"ስለ አንዳች ነገር መረዳቱ ይኖርህ ዘንድ ጅማሬና ዕድገቱን አጥብቀህ መርምረው።"‎‎"ብዙ ጊዜ ሰዎችን የጠላሁበት ገጠመኝ ራሴን ለመከላከል ብዬ ነው፤ጠንካራ ብሆን ኖሮ ፈፅሞ ያንን መሳሪያ ...
21/07/2025

‎"ስለ አንዳች ነገር መረዳቱ ይኖርህ ዘንድ ጅማሬና ዕድገቱን አጥብቀህ መርምረው።"

‎"ብዙ ጊዜ ሰዎችን የጠላሁበት ገጠመኝ ራሴን ለመከላከል ብዬ ነው፤ጠንካራ ብሆን ኖሮ ፈፅሞ ያንን መሳሪያ አልጠቀምም ነበር።

‎"በቅንነት ስህተትህን የሚገልፁልህን እንጂ፤ቃልህንና ተግባርህን በሙሉ የሚያወድሱትን ታማኝ አድርገህ እንዳታስብ።"

‎"ደካማ ጎንህን ማንም እንዲያውቅ አታድርግ፤ሰዎች የሚይዙህ አንተው ባሳየሃቸው ወጥመድ ነው።"

‎"ከሰዎች ጋር ሩጠህ ያልደረስክበት ነገር ካለ፤ወደ ተነሳህበት ተመልሰህ ከፈጣሪህ ጋር መሮጥ ጀምር ያኔ ካሰብክበት ሳይሆን ካሰበልህ ትደርሳለህ።"

‎"የሰው ልጅ ከደስታው ይልቅ የሃዘኑን ቀናት መቁጠር ይወዳል።"

‎"ሰው ከጊዜና ከማጣት ብዙ ይማራል።"

‎"መጀመሪያ ለራስህ ራስህ መሆን ስትጀምር፤ለማን ምን መሆን እንዳለብህ ትገነዘባለህ።"

‎"በፍፁም በሌሎች ሰዎች ስሜት ላይ አትጫወት፤ምክንያቱም ጨዋታውን ብታሸንፍ እንኳን ሰዎቹን ግን እስከወዲያኛው ታጣቸዋለህ።"

‎‼ የማትናደፍ ንብ ከፈለክ ከዝንብ ጋር ተጋባ "‎‼ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው ። ለማሩ ስንል ንድፊያውን መታገሥ ፡፡ ቆይተህ ደግሞ ንድፊያውን መልመድ ፡፡ ገበሬ ቀፎ ሰቅሎ ንብ ሲያንብ ...
21/07/2025

‎‼ የማትናደፍ ንብ ከፈለክ ከዝንብ ጋር ተጋባ "
‎‼ ትዳር ከንብ ጋር መኖር ነው ። ለማሩ ስንል ንድፊያውን መታገሥ ፡፡ ቆይተህ ደግሞ ንድፊያውን መልመድ ፡፡ ገበሬ ቀፎ ሰቅሎ ንብ ሲያንብ ፣ ንብ እንደምትናደፍ ሳያውቅ ቀርቶ አይደለም ፡፡ የማትናደፍ ንብ ከፈለገ በየደጁ ቆሻሻ ፍለጋ የምትጓዘው ዝንብ ነበረችለት ፡፡ ዝንብ ምን ጠባይዋ ሸጋ ቢሆን ፤ ጠብ የሚላት ግን ሌላ ነገር ነው ፡፡

‎‼ ይህን ያውቃል ገበሬው ፡፡ እያወቀም ንብ ያንባል ፡፡ ማነብ ብቻ ሳይሆን ከንብ ጋር እንዴት መኖር እንደሚቻልም ያውቃል ፡፡ ንብ ትናደፋለች ፤ ግን እንዳትናደፍ ማድረግም ይችላል ፡፡ የምትወደውና የማትወደው ሽታ አለ ፡፡ ስትቀርብህ ምን ማድረግና ምን አለማድረግ እንዳለብህ ገበሬው ያውቃል ፡፡

‎‼ በሀገራችን ንብ አትገደልም ፡፡ ነውር ነው ፡፡ ብትነድፍም አትገደልም ፡፡ የንቧን ማር ለመውሰድም ንቧን ገድሎ ፣ አጥፍቶ ፣ ጎድቶ ወይም አሰቃይቶ ሳይሆን በጭስ ራሱን እየተከላከለ ፣ ፊቱን በጨርቅ ሸፍኖ ፣ ወደ ንቧ ቀፎ ገብቶ ነው ማሩን የሚቆርጠው ፡፡ ንቧም ሳትጎዳ ፣ማሩም ሳይጠፋ ፣ እርሷም ሳትናደፍ ፡፡

‎‼ ትዳርም እንዲህ ነው ፡፡ አኗኗሩን ነው ማወቅ ፤ የንቧን ንድፊያ የመቀነሻውን መንገድ ነው ማወቅ ፣ የማሩን አቆራረጥ መንገድ ነው ማወቅ ፡፡ ደግሞም‘ኮ አስገራሚው ገበሬው የሚከባከበው ይህቺኑ የምትናደፈውን ንብ መሆኑ ነው ፡፡ የምትቀስመው አበባ ትፈልጋለች ፣ ንጹሕ አካባቢ ትፈልጋለች ፣ ከጉንዳንና ከአውሬ ነጻ የሆነ ቀፎ ትፈልጋለች ፡፡ ግን ትናደፋለች ፡፡ ደግሞም ማር ትሰጣለች ፡፡

‎‼ ትዳር አስደሳች ነገር ብቻ ሳይሆን አስመራሪ ፣ አስጠሊታ ፣ ጨጓራ አንዳጅ ፣ ልብ አቃጣይም ክፍል አለው ፡፡ ይናደፋል ፡፡ ግን ደግሞ ክብካቤም ይፈልጋል ፡፡ ንጹሕ ልብ ፣ ታማኝ ኅሊና ፣ ቻይ አንጀት ፣ ታጋሽ ሆድ ፣ ጠቢብ አእምሮ ፣ አሳላፊ ልቡና ይፈልጋል ። ለምን ቢሉ ? ማር ይሰጣልና ታገሱ ።

‎!l ፌስቡክን ለመታወቅ ሳይሆን ያወቅነውን ለማሳወቅ እንጠቀም ፡፡ ማወቅ መልካም ነው ያወቁትን ማሳወቅ ደግሞ ፍፁም በጎነት ነው ፡፡ በምድር ላይ የምናደርጋቸው ነገሮች ሁሉ በሰማይ ላይ የዘላለም ደመወዝ ሆነው ይከፈሉናል ፡፡ ሁሌም ቢሆን ከክፋት ይልቅ በጎ በጎውን ነገር እናስብ መልካምነት ለራስ ነውና ፡፡

‎‼ ስለዚህ አንተም ይህ አሁን ያነበብከው መጣጥፍ ትምህርት ሰጪ ሆኖ ካገኘሀው የእርስዎ ዘመዶችህ እንዲያነቡትና ትምህርት እንዲወስዱ ዘንድ ሼር ያድርጉላቸው።


‎ #ገራሚ ታሪክ ‎አንድ ባል አለ እና በየቀኑ ማታ ማታ ከስራ ሲመለስ ሚስቱን ይደበድባታል። ይሄ ድብደባ ምርር ያላት ሚስት ወንድሟን ስለጉዳዩ ነገረችው። ወንድሟም፦ “ጓሮ ካለው ምንጭ ውሃ ...
20/07/2025

‎ #ገራሚ ታሪክ
‎አንድ ባል አለ እና በየቀኑ ማታ ማታ ከስራ ሲመለስ ሚስቱን ይደበድባታል። ይሄ ድብደባ ምርር ያላት ሚስት ወንድሟን ስለጉዳዩ ነገረችው። ወንድሟም፦ “ጓሮ ካለው ምንጭ ውሃ በጠርሙስ ቀድተሽ አምጪልኝ” አላት። እሷም ቀድታ ይዛለት መጣች። ወንድሟም ለጥቂት ደቂቃ ውሃውን አተኩሮ አየና እንዲህ አላት፡- “ባልሽ ከስራ በገባ ቁጥር ከዚህ ጠርሙስ ትንሽ ጠጪ ነገር ግን ውሃውን ፈጽሞ እንዳትውጪው።”

‎እሷም እንደተባለችው አደረገች። ባሏም እንደልማዱ ሳይመታት ቡናውን ጠጥቶ አልጋው ላይ እንደ ህፃን ልጅ ጥቅልል ብሎ ተኛ። ሚስት በዚህ በጣም ተገረመች። አንድ ወር ሙሉ በጊዜ ወደቤቱ ይገባል። አይመታት አይጨቃጨቃትም። በሰላም አውርቷት እራቱን በልቶ ይተኛል። ነገር ግን ባሏ በገባ ቁጥር በየቀኑ አፏ ላይ የምትይዘው ውሃ ከጠርሙሱ አለቀ። ይሄኔ ወደ ወንድሟ ጋር ተመልሳ፦“ሌላ የውሃ ጠርሙስ እፈልጋለሁ። እና ደግሞ እባክህ በእናትችን ይዥሃለሁ ንገረኝ፤ ከምንጭ የቀዳውት ውሃ ምን አይነት መለኮታዊ ምስጥር ነው ያለው?”

‎የእህቱን አመል የሚያውቀው ወንድም ተረጋግቶ መለሰላት፦“ምንም የመለኮት ሆነ የመተት ሚስጥር የለውም። ባልሽ ደክሞት ከስራ ወደቤት ሲገባ ቢያንስ ዝም በማለት አፍሽን ጠብቂ!” 🤲🏼 🤐

‎ሴት ልጅ በምታፈቅረው ወንድ ላይ እምነት ስታጣ መጀመሪያ ልቧን ትዘጋለች። ‎‎አታፈቅረውም ወይም ፍቅሯ ያልቃል ማለት አይደለም። ‎‎ልቧ ሲዘጋ የምታቆመው ማፍቀሯን ማሳየትን ነው። ፈልጋ የም...
20/07/2025

‎ሴት ልጅ በምታፈቅረው ወንድ ላይ እምነት ስታጣ መጀመሪያ ልቧን ትዘጋለች።

‎አታፈቅረውም ወይም ፍቅሯ ያልቃል ማለት አይደለም።

‎ልቧ ሲዘጋ የምታቆመው ማፍቀሯን ማሳየትን ነው። ፈልጋ የምታደርገው ነገር አይደለም .... አቅም አጥታ የምትተወው ነው።

‎ያን ጊዜ ወንዱ ፍቅሯ ያለቀ ወይንም ሌላ ሰው ያፈቀረች እና በሆነው ባልሆነው ነጭናጫ እና ጨቅጫቃ እየሆነች የመጣች ይመስለዋል።

‎መታመሟን እያሳየችው፣ መጎዳቷን እየነገረችው መሆኑን አይረዳም።

‎ልቧን በጣም ከምታፈቅረው ሰው እየተከላከለችው መሆኑን አያስተውልም።

‎መልካም ሴት ስታፈቅርህ ፥ በፍቅሯ ውስጥ ንፅህና፣ የዋህነት እና እውነት አለ።

‎በልብህ እና በልቧ መካከል የሚኖረው ድልድይ መሰረቱ ከእምነት የተገነባ ነው።

‎ይሄንን ድልድይ ያፈረስከው ጊዜ ወለል ብሎ ተከፍቶ እንደፈለክ ትመላለስበት የነበረው፣ አለገደብ ያፈቅርህ የነበረው ልቧ በሩን ይዘጋል።

‎እምነት እና መተማመን በሌለበት የልብ ለልብ መገናኘት የለም። ልብ እና ልብ ባልተዋሀደበት ደግሞ የፍቅር ግንኙነት የለም።

‎ሴትን ልጅ ማሸነፍ እና የዘላለም የፍቅርህ ምርኮኛ ማድረግ ከፈለክ ታማኝነትህ ላይ ስራ።

‎ቃል ከገባህላት ፦

‎ቃልህን ጠብቅ፤

‎አታየውም፣

‎አትሰማም፣

‎አይገባትም፣

‎አትረዳውም፣

‎አትደርስበትም ፣ የምትለው ምንም ነገር አይኑርህ።

‎ሴትን ልጅ ከነገርካት በላይ ያልነገርካት፣ ካሳየሀት በላይ የደበቅካት ነገር ቀድሞ ይታያታል።

‎የሴትን ልጅ ልብ ማስከፈት ከባድ ነው።

‎ቢሆንም አንዴ ካመነችህ ሁለ ነገሯ ያንተ ነው።

‎እምነቷን ቀልደህበት የዘጋችውን ልቧን ግን እንኳን አንተ እሷም ብትፈልግ መልሳ መክፈት አትችልም።

‎ምናልባት ሌላ ወንድ በስንት ጥረት እና ድካም ካስከፈተው እንጂ ለአንድ ወንድ እድሉ አንዴ ነው !!

‎~ ... ብቻ ነገሩ ውስብስብ ነው !! ~

‎✨ ባሻ ዘብሔረ ጠቅላይ ግምጃ ቤት ✨

‎★★★ ኦሮማይ ★★★ 🧘

‎ አንድ በጣም በሚስቱ የተማረረ ባል ሳይኮሎጅስት ጋር ይሄዳል…‎‎ #ሳይኮሎጅስቱ፦ እሺ ጌታው ለመኖር ምንድነው ምትሰራው ?‎ #ባል፦ በአንድ ባንክ ቤት ውስጥ ማናጀር ነኝ‎ #ሳይኮሎጅስቱ፦ ...
19/07/2025

‎ አንድ በጣም በሚስቱ የተማረረ ባል ሳይኮሎጅስት ጋር ይሄዳል…

‎ #ሳይኮሎጅስቱ፦ እሺ ጌታው ለመኖር ምንድነው ምትሰራው ?
‎ #ባል፦ በአንድ ባንክ ቤት ውስጥ ማናጀር ነኝ
‎ #ሳይኮሎጅስቱ፦ እሺ ባለቤትህስ ምንድነው ምትሰራው ?
‎ #ባል፦ እሷ ባክህ ምንም አትሰራም የቤት እመቤት ነች #ሳይኮሎጅስት፦ ጠዋት ለቤተሰቡ ቁርስ ሚሰራው ማነው ?
‎ #ባል፦ ሚስቴ ነቻ ምክንያቱም ምንም ስራ የለባትም…
‎ #ሳይኮሎጅስት፦ ሚስትህ ጠዋት ከእንቅልፏ ስንት ሰአት ነው የምትነሳው ?

‎ #ባል፦ ለሊት 11:00 ሰአት አከባቢ ነው ምትነሳው
‎ቁርስ ከመስራቷ በፊት ቤት ስለምታፀዳ ቀደም ብላ ነው ምትነሳው……
‎ #ሳይኮሎጅስት፦ ልጆችህ ትምህርት ቤት ሚሄዱት እንዴት ነው ?
‎ #ባል፦ ሚስቴ ስራ ስለሌላት እሷ ነች የምትወስዳቸው
‎ #ሳይኮሎጅስት፦ ልጆችህ ትምርት ቤት ከወሰደች በሃላ ምን ትሰራለች ?

‎ #ባል፦ ከወሰደቻቸው በሃላ ያው ስራ ስለሌለባት ወደ ገበያ ሄዳ ምሳ የሚሰራበትን ነገር ትገዛዛና ምሳ ከሰራች በሃላ ልብስ ታጣጥብና እረፍት ታረጋለች በቃ ምንም የምትሰራው ስራ የላትም

‎ #ሳይኮሎጅስት፦ አንተ ማታ ከስራ ስትመለስ ምን ታደርጋለህ ?
‎ #ባል፦ እኔ ስራ ደክሜ ስለምገባ በቃ ሻወር እወስድና ረጋ ብዬ ከልጆቼ ጋር እቀመጣለው
‎ #ሳይኮሎጅስት፦ የዛኔ ሚስትህ ምን ትሰራለች ?
‎ #ባል፦ ለቤተሰቡ እራት ታቀርብና እቃ ታጣጥብና ልጆቹ አስተኝታ ወደ እንቅልፍ ትሄዳለች

‎ #ሳይኮሎጅስት፦ እሺ ከአንተና ከሚስትህ ማን በጣም የሚሰራ ይመስለሃል የሚስትህ ውሎ ከንጋቱ 11 ሰአት የጀመረ እስከ ማታ ድረስ የሚቀጥል ነው። ታድያ ይሄንን ነው ስራ ስለሌለባት የምትለው!!!! አዎ በርግጥ የቤት እመቤት ለመሆን ትምርት ቤት ገብቶ ሰርተፍኬት መቀበል ላያስፈልገው ይችላል ግን በህይወታችን ውስጥ የነሱ የነሱ አስተዋፅኦ በጣም አስፈላጊ ነው።

‎💠 …

‎✅ ፀጥ ስትል ብዙ ሚሊዮን የሚሆኑ ሃሳቦችን እያሰበች እያብሰለሰለች መሆኑን ይግባህ።
‎✅ አፍጣ ስታይህ ለምን እንደዚ እንደምትወድህ እና ይህን ሁሉ መስዋእትነት እንደምትከፍልልህ እያሰበች ነው።
‎✅ አብሬህ እቆማለው ስትል ማዕበል እንካን ቢመጣ አልንቀሳቀስም ማለቷ ነው።
‎✅ አትጉዳት ወይም በተሳሳተ መንገድ አታስባት … አንተ ስትራብ ተርባ ስትቸገር ተቸግራ ስትራቆት ተራቁታ ገበናህን ሸፍና የምትኖረው
‎ሚስትህ የልጆችህ እናት ሚስትህ ናት። አረ እውነታውን ልንገርህ ሚስትህ ማለት የቤትህ ብርሃን ናት ስለዚ አክብራት ውደዳት ፍቅር ስጣት።

‎የተመቻችሁ ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ

‎ #ኢትዮጵያ |ህይወትህን ብኩን የሚያደርጉ ነገሮች‎++++++++++++++++++++++++++++++‎• ምርጥ ሃሳቦች በአእምሮህ ዉስጥ እየመጡ በተግባር ካላዋልካቸዉ‎•  እራስህን ከሌሎች ጋ...
19/07/2025

‎ #ኢትዮጵያ |ህይወትህን ብኩን የሚያደርጉ ነገሮች
‎++++++++++++++++++++++++++++++
‎• ምርጥ ሃሳቦች በአእምሮህ ዉስጥ እየመጡ በተግባር ካላዋልካቸዉ
‎• እራስህን ከሌሎች ጋር የምታነጻጽር ከሆነ
‎• የሚጠቅምህ ነገር ላይ ሳይሆን የማይጠቅምህ ላይ ጊዜህን ካቃጠልክ
‎• ሰዎች ስለኔ ምን ያስቡ ይሆን ብለህ መጨነቅ ከጀመርክ
‎• ትላንት ስላሳለፍከዉ ህይወት ሁሌ የሚቆጭህ ከሆነ
‎• ነገ ምን እሆናለሁ ብለህ የምትጨነቅ ከሆነ
‎• እቅድህ በጣም ከበዛ
‎• ሰዉን ለመለወጥ ሁሌ የምትሞክር ከሆነ
‎• ምንም የማይጠቅም ክርክር ዉስጥ እራስህን ካገኘህ
‎• ለምትሰራዉ ነገር ደንታ ቢስ ከሆንክ ህይወትህን በጣም እያባከንከዉ ነዉና ንቃ!

 #ኢትዮጵያ| ‎‎1) "ክፉ ሰዎች ስህተትህን በሰዎች ፊት ይነግሩሃል፤መልካም ሰዎች ግን በስውር ያስተምሩሃል።"‎‎2) "ከዘመኑ ጋር ራሳቸውን ያላሻሻሉ ሰዎች ትውልድን ሲጎትቱ ይኖራሉ።"‎‎3...
19/07/2025

#ኢትዮጵያ| ‎‎1) "ክፉ ሰዎች ስህተትህን በሰዎች ፊት ይነግሩሃል፤መልካም ሰዎች ግን በስውር ያስተምሩሃል።"

‎2) "ከዘመኑ ጋር ራሳቸውን ያላሻሻሉ ሰዎች ትውልድን ሲጎትቱ ይኖራሉ።"

‎3) "የሰው ልጅ የተመኘውን በሙሉ ቢያገኝ እንኳን አንድ ቀን ያገኘውን ሁሉ ያጣዋል።"

‎4) "ተስፋን ማጣት ህይወትን ማጣት ነው፤የሚያኖረን ተስፋችን ነውና።"

‎5) "ብርቱ ሰው በሰው ወሬ መንገዱን አይስትም፤ለአሉባልተኞችም ጊዜ የለውም።"

‎6) "መሄድንና መተውን የሚያስተምሩን አብረውን እንዲቆዩ ብዙ የታገስናቸው ሰዎች ናቸው"

‎7) "የሚጎዱ ነገሮች ሁሉ ያስተምራሉ"

‎8) "ሰዎችን ማሸነፍ ቀላል ሊሆን ይችላል፤ማንነታቸውን ማሸነፍ ግን እጅግ ከባድ ነው።"

‎9) "ወደ ክብር የሚወስደው አቋራጩ መንገድ፤የምትመኘውን ለመሆን መጣር ነው።"

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢትዮጵያ Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share