07/01/2026
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል (ገና) በሰላም አደረሳችሁ እያልን፤ በዓሉ በሰላም፣ በጤና እና በደስታ እንዲጠናቀቅ ላደረጉ ለክልላችን ሕዝብና ለባለድርሻ አካላት በሙሉ ቢሯችን ምስጋናውን ያቀርባል።
የዘንድሮው የገና በዓል በክልላችን በሰላም መጠናቀቁ ለልማት ሥራዎቻችን ትልቅ ስንቅ ነው። በበዓሉ ወቅት ማህበረሰቡ የእንስሳት ተዋጽኦዎችን (ሥጋ፣ ወተት፣ ቅቤና እንቁላል) በአግባቡና በጤናማ ሁኔታ እንዲጠቀም የግንዛቤ ማስጨበጥ እና የክትትል ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።
በበዓሉ የታየውን ከፍተኛ የፍላጎት መጠን ለማሟላት አርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ የእንስሳት ምርታማነትን እንዲያሳድጉ ድጋፋችንን አጠናክረን እንቀጥላለን።
በበዓላት ወቅት የሚታየውን የፍጆታ ፍላጎት ተከትሎ በሽታዎች እንዳይስፋፉ የክትባትና የቁጥጥር ሥራዎችን በስፋት እያከናወንን።
አምራቾች ምርታቸውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለተጠቃሚው ማድረስ የሚችሉበትን ዘመናዊ የገበያ ትስስር በመፍጠር። የተገኘው ሰላም ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የክልላችንን የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ሁላችሁም የድርሻችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
መልካም የሥራ ዘመን ይሁንልን!
ጋሻው መጨ( ዶር)
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ