Ethio Press

Ethio Press Official FaceBook page of Ethio Press

ሐሰተኛ መረጃበአማራ ክልል የሚልሻ አባላትን ትጥቅ ማስፈታት ይመለከታል በሚል ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ ነው  ሰሞኑን በአማራ ክልል ‘የሚልሻ አባላትን ትጥቅ ማስፈታትን ይመለከታል’ በሚል ሐሰ...
24/04/2024

ሐሰተኛ መረጃ

በአማራ ክልል የሚልሻ አባላትን ትጥቅ ማስፈታት ይመለከታል በሚል ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ ነው

ሰሞኑን በአማራ ክልል ‘የሚልሻ አባላትን ትጥቅ ማስፈታትን ይመለከታል’ በሚል ሐሰተኛ መረጃ እየተሰራጨ እንደሚገኝ ተጠቆመ።

ለሁሉም ዞንና ከተማ አስተዳደሮች በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ደብዳቤ የተጻፈ በማስመሰል የወጣው መረጃ ፍጹም ሐሰት መሆኑን ክልሉ አረጋግጧል።
ድርጊቱ የተፈጸመው በክልሉ የተፈጠረውን አንጻራዊ ሰላም ዘላቂ ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ለማደናቀፍ ያለመ እንደሆነም ተነግሯል።

በዚህም በክልሉ ያሉ የጸጥታ ኃይሎች ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጋር ተቀናጅተው እያመጡት ያለው ውጤት ኪሳራ ያደረሰባቸው ኃይሎች በሚልሻውና ህብረተሰቡ ውስጥ መደናገርን ለመፍጠር አልመው የፈጸሙት እኩይ ድርጊት መሆኑ ተገልጿል።

 #ትዝብት"ረሃብን በሪሞት- አዲሱ ፈጠራ!?" 🤔ረሃብን ከፖለቲካ ፍጆታነት አልፎ  #በሪሞት መቆጣጠር የተቻለበትን ፈጠራ ከሰሞኑ ከወደ ትግራይ እያየን ነዉ፡፡ ከወራት በፊት የክልሉ ጊዜያዊ አ...
17/04/2024

#ትዝብት
"ረሃብን በሪሞት- አዲሱ ፈጠራ!?" 🤔

ረሃብን ከፖለቲካ ፍጆታነት አልፎ #በሪሞት መቆጣጠር የተቻለበትን ፈጠራ ከሰሞኑ ከወደ ትግራይ እያየን ነዉ፡፡

ከወራት በፊት የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕ/ንት ጨምሮ በርካታ ወሬ አቀባይ አፎቻቸው በትግራይ ክልል ከ 1977ዓ.ም የከፋ #ረሃብ እንዳለ ለአለም ሚዲያዎች መረጃ ሲያቀባብሉ አስተዉለናል።

በሚባለዉ ደረጃ ረሃብ ስለመኖሩ ምንም ማስረጃ በሌለበት ከፍተኛ ዘመቻ የተካሄደ ቢሆንም ነገሩ ብዙም ሳይቆይ ከረሃብ ጩሀት ወደ ጥይት ጩሀት ተቀይሯል፡፡
እንግዲህ... ከወደ ህወሃት መንደር ረሃብ ሲፈለግ የሚመጣ ሳይፈለግ በቀላሉ በሪሞት የሚጠፋ ነው ማለት ነው?
ሪሞቱም በህወሃት እጅ ነው ያለው ብለን እንድንጠረጥር አድርጎናል።
ህወሃት ይቺን የርሃብ ሪሞት በአእምሮ ንብረት ፈጠራ ስራ አስመዝግቧት ይሆን?! 😂

#ትዝብት 🤔
ህዝቤ ረሃብ ዉስጥ ነው ያለ ክልል ገንዘብ አውጥቶ መግዛት ያለበት ስንዴ ወይስ ጥይት?

ህወሓት አሁንም የትግራይን ህዝብ መከራ ለማስቀጠል የፕሪቶሪያ ስምምነትን የሚያፈርሱ ትንኮሳዎችን እያደረገች ነው።

የፕሪቶሪያዉ ስምምነት አከራካሪ ቦታዎችን በሚመለከት
# የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ #ቀያቸው መመለስ እና አካባቢዎቹን በመከላከያ ሰራዊት ስር ማስገባት
# ለተፈናቃዮች ከትራንስፖርት እስከ ስንቅ ድረስ እንዲሁም ወደ መደበኛ ኑሮ #የሚመለሱበት ሁኔታን ማመቻቸት
# ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸዉ ከተመለሱና መደበኛ ህይወታቸዉን መምራት ከጀመሩ በኋላ በማካሄድ እራሳቸዉን የሚያስተዳድሩበትን ሁኔታ መፍጠር የሚሉት የሚጠቀሱ ናቸዉ ፡፡

ነገር ግን ከወደ ትግራይ የምንሰማዉ ነገር ለትግራይ ተወላጅ እና ህዝብ እጅግ አስጊ ነገር ነዉ፡፡

የህወሃት ስብስብ ይህንን ሁሉ የሰላም አማራጭ ረግጦ "ጠብ ያለሽ በዳቦ" የሚያስብለው የጦርነት ሱስ እንጂ ሌላ ምን ይባላል?

በትግራይ የሚነፍሰዉን የሰላም አየር አደፍርሶ ከጎረቤት ክልሎች ጋር የሚያናክሰውን ይህንን የጦርነት አዙሪት የተጠናወተውን ስብስብ ከጫንቃው ላይ ካላወረደ የትግራይ ህዝብ የሰላም እንቅልፍ እንደራቀው ይቀራል!

ድህነት የተጫነው ሕዝብ ይዘን በላዩ ላይ ጦርነት ከጨመርንበት የክፍለ ዘመኑ ማሰብ የተሳነን ሰዎች ሆነናል ማለት ነው። ትልቁ ማሰላሰል የሚገባን ቁምነገር ከርሃብ እንዴት መውጣት አለብን የሚለ...
13/04/2024

ድህነት የተጫነው ሕዝብ ይዘን በላዩ ላይ ጦርነት ከጨመርንበት የክፍለ ዘመኑ ማሰብ የተሳነን ሰዎች ሆነናል ማለት ነው።

ትልቁ ማሰላሰል የሚገባን ቁምነገር ከርሃብ እንዴት መውጣት አለብን የሚለው ጉዳይ ላይ ነበር። እኛ ግን በተቃራኒው ርሃብን ሊያባብስ፤ ድህነትን ሊያስፋፋ የሚችለውን ጦርነት መርጠናል።

ከቦታ ቦታ ተዘዋውረን ባለመነገዳችን፤ አርሰን ባለማዝመራችን፤ መማር ባለብን ጊዜ በግጭት ውስጥ በመሆናችን፤ ... ድህነት እየተስፋፋብን ይገኛል።

ስለሆነም ከርሃብ፣ ከድህነትና ጉስቁልና ለመውጣት የሚያስፈልገን ዘላቂ ሰላም ነው። ሰላም ያስፈልገናል።

ሰላም ለሕዝባችን❗️

ቢሊዮኖችን ለመመገብ የሚችል የሚታረስ መሬት አለን። ሁኖም ግን ለምናርሰው መሬት የተቀየረ አስተሳሰብና አስተሳሰቡን መሬት ላይ የሚያወርድ የተለወጠ የሰው ሃይል ያስፈልገናል።በዚህ ጊዜ የአማራ...
13/04/2024

ቢሊዮኖችን ለመመገብ የሚችል የሚታረስ መሬት አለን። ሁኖም ግን ለምናርሰው መሬት የተቀየረ አስተሳሰብና አስተሳሰቡን መሬት ላይ የሚያወርድ የተለወጠ የሰው ሃይል ያስፈልገናል።

በዚህ ጊዜ የአማራ ክልል አርሦ አደር ለዓመት ቀለቡ ሳይሆን፤ ለገበያ፣ ለፋብሪካዎችና ለኤክስፖርት ማምረት መቻል ይኖርበታል። ይህንን ለማድረግ ደግሞ ለግብርናችን ብቻ ሳይሆን ለሕዝባችን ጥያቄዎች ያለን እይታም መለወጥ አለበት።

የሃገራችን አርሦ አደር ግብአት በሃገሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት አለበት። ምርጥ ዘር በተሟላ ሁኔታ ማግኘት አለበት። አሲዳማው አፈር ምርቱን ስለሚቀንስበት መሬቱን ለማከም የሚያስችል በቂ የኖራ ግብአት ያስፈልገዋል። የአማራ አርሦ አደር ለብዙ ሺ ዓመታት ያረሰበትን ማረሻ ጥሎ የምርት ጥራትና መጠንን የሚያሳድጉ ጊዜ ቆጣቢ ቴክኖሎጂዎችን የሚያስታጥቁትን ልጆቹን ይሻል።

ሕዝባችን በየአካባቢው የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ያስፈልጉታል። የሚመረቱ ጥሬ እቃዎችንም ሆነ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶችን ለሃገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ገበያ የሚያደርስበት የተሟላ የየብስ፣ የአየርና የኢንተርኔት መሰረተ ልማት እንዲሁም የሃይል አቅርቦት ከምንጊዜውም በላይ ዛሬ እጃችን ላይ ሊገቡ ይገባል።

ይህ ሲሆን የፍትሐዊ የልማት ተጠቃሚነት ጥያቄያችን መልስ ማግኘቱ ብቻ ሳይሆን የሥራ እድልና የሥራ ፈጠራ ያድጋል። ሥራ አጥነት ይቀንሳል። ባለን አቅም ልክ ኢኮኖሚ እናመነጫለን። ባመነጨነው ኢኮኖሚ ልክ ለመንግሥት የሚፈለገውን ገቢ እናስገኛለን። ባስገኘነው ገቢ ልክ ደግሞ የማኅበራዊና መሰረተ ልማት በማያቋርጥ መስፋፋትና እድገት ውስጥ እንዲገቡ እናደርጋለን።

ሕዝባችን በዚህ ጊዜ የሚሻው ጀግንነት ይህ አይነቱን ጀግንነት ነው። አርሶ አደራችን "ለምን ከብልጽግና ማዳበሪያ ተቀብለህ መጣህ" ብለህ በማሰቃየት በአንዱ ሰኔ እንዳያርስ አድርገህ ሰባት ሰኔ እየነቀልከው አንተን የሚፈልግ ይመስልሃል። ይህ ሁኔታ አሠራሩ ባልተቀየረ ግብርና ውስጥ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነው።

አሁን ሕዝባችን የሚፈልገው ክላሽ ወይም የስናይፐር ጥይት አይደለም። ከሰባት ሰኔ እየነቀልክ ከርታታ ልታደርገው እየሠራህ "እጠቅመዋለሁ ፤ ጥያቄውንም እመልስለታለሁ" ማለትም አትችልም። በመጽሐፍ “... ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ ድንጋይን የሚሰጠው ከእናንተ ማን ሰው ነው?” እንደተባለው ዳቦ ለሚጠይቀን ወገናችን ጥይት መስጠት ዘለዓለምህን ዳቦ ሲያምርህ ኑር ማለት እንጂ የዳቦ ጥያቄውን መፍታት የሚያስችል ስልት ሊሆን አይችልም። Atleast በአሁኗ ኢትዮጵያ ጦርነት የዳቦ ጥያቄን መፍቻ ዘዴ ሊሆን አንችልም።

ስለዚህ ጀግንነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገማሸር ሳይሆን ሠርቶ መለወጥ መሆኑ ሊገባን ይገባል። እንደ አማራ ሕዝብ በመሰረታዊነት ሠርተን ከምንለወጥባቸው ጉዳዮች አንዱ ደግሞ አሁን በእጃችን ላይ ያሉት በቂ የሚታረስ መሬት፣ ለዘርፋ የሚሆን የሰው ሃይል እና ትንሽ ሠርተንና ወጪ አድርገንበት ልናሳካው የምንችለው የግብርና ቴክኖሎጂ ባለቤት መሆናችን ነው።

ሰላም ለሕዝባችን❗️

ማሸነፍ የውዴታ ግዴታችን ነው❗️******ትምህርት የለውጦች ሁሉ መሰረት ነው። ሁኖም ግን "አንድ ሰኔ የነቀለውን ሰባት ሰኔ አይተካውም" እንዲሉ አበው ትምህርትም እንደዛው ነው። አንድ ዓመት...
12/04/2024

ማሸነፍ የውዴታ ግዴታችን ነው❗️
******
ትምህርት የለውጦች ሁሉ መሰረት ነው። ሁኖም ግን "አንድ ሰኔ የነቀለውን ሰባት ሰኔ አይተካውም" እንዲሉ አበው ትምህርትም እንደዛው ነው። አንድ ዓመት ትምህርት ያለፈው ሰው በብዙ ማኅበራዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ውስጥ በማለፍ ከእነአካቴው ከትምህርት ገበታ ውጭ የሚሆንበት እድል ብዙ ነው።

በዛው ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ በአንድና ሁለት ትውልድ የሚለካ የተወዳዳሪነት ችግር ይፈጥራል። በአጭሩ በምንም መመዘኛ የተወዳዳሪነት መንፈስ ውስጥ የማይገባ ትውልድ ይፈጠራል። በትምህርት መበደል ደግሞ ከሌሎች ሁሉ በደሎች የከፋና ከዘር ማጥፋት ወንጀል የሚስተካከል ነው ማለት ይቻላል።

"ፍለጠው፣ ቁረጠው ... ትንሽ ቀርቶናል ..." ወዘተ እያለ የሚጃጃለው ሃይል በአዲሱ ትውልድ መጻኢ እድል ላይ አደጋ መደቀኑና በየትኛውም መመዘኛ በሃገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ ወጣቶች ጋር ተወዳዳሪ ያልሆነ ልፍስፍስ አልያም ተጣሞ የበቀለ ትውልድ መፍጠሩ የማይቀር ነው።

ስለሆነም ይህንን ሃይል የምንታገለው ዛሬ ላለንበት ሁኔታ መረጋጋትን ለመፍጠርና የሕዝባችንን ስቃይና እንግልት ለማስቆም ብቻ ሳይሆን ነጋችን ላይ የተጋረጠውን አደጋ ለመመከት ጭምር መሆኑ ታውቆ ትግላችን አሁንም በጽናት በማስቀጠል ልናሸንፍ ይገባል። ማሸነፍ የውዴታ ግዴታችን ነው።

ከንሥሮቹ ዓይን ለመሰወር ጫካ ለጫካ እየተሹለከለከ የመጥፊያው ንጋት ላይ የሚገኘው ቡድን በያዛቸው ቀበሌዎች ላይ መሬት እደለድላለሁ ማለቱን ሰማን።አላዋቂነት ቤት ሲሠራብህ እንዲህ ትሆናለህ። ...
11/04/2024

ከንሥሮቹ ዓይን ለመሰወር ጫካ ለጫካ እየተሹለከለከ የመጥፊያው ንጋት ላይ የሚገኘው ቡድን በያዛቸው ቀበሌዎች ላይ መሬት እደለድላለሁ ማለቱን ሰማን።

አላዋቂነት ቤት ሲሠራብህ እንዲህ ትሆናለህ። የአማራን ሕዝብ መሬት ነጥቆ ለአማራ መስጠት የሚኖረው ፋይዳ ምንድን ነው ብትሉ ሕዝቡ እርስበርስ በጠላትነት እንዲተያይ ማድረግ ብቻ ነው።

ከጊዜ ጊዜ አቅሙ እየተዳከመና የያዛትን ትንሽየ ቀበሌ እንኳን መሻገር ያቃተው ቡድን አሁን ደግሞ እውር ድንብሱን የድንጋጤ ዘፈን እየዘፈነና በሌለው አቅም እንደ እንቁራሪቷ እየጮኸ ይገኛል።

አመንንም አላመንም ወጣቱ ሠርቶ መለወጥ ይፈልጋል። እንደ ባርያ ሠርቶ እንደ ንጉሥ የሚዝናናው የዘመኔ ወጣት ለአንጋቹ ቡድን አልተመቸውም። ምክንያቱም ይህ ቡድን የአማራን ሕዝብ ጥያቄ ለመፍታት ስልቱም፣ አቅሙም፣ እውቀቱም የለውም። ይህንን ሕዝባችን ጥርት አድርጎ ካወቀ ቆይቷል።

እነ ጋሸ ፋኖ ተብየ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ላይ ፣ በመዝናኛ ቦታዎች፣ በዩኒቨርሲቲዎች፣ ...ወዘተ ቦንብ ቢያፈነዱና ሕጻናትን ጭምር በመግደል ሕዝቡን ለማስፈራራት ቢሞክሩም አልሆነም።

እንዲያውም እንዲህ አይነቱ ተግባር ከመፈጠራቸው መጥፋታቸው የሚያስብል ደረጃ ላይ እንዲደርሱ አግዟል።

ሕዝቡ ማንነታቸውን በትክክል እንዲረዳና ወደ ለየለት የሽብር ሥራ ውስጥ በመግባታቸው አንቅሮ እንዲተፋቸውም ሁኗል።

ስለሆነም ዝሆኑ ሕዝባችን እንቁራሪቶችን ሊሰማ የሚችልበት እድል የለም። እንቁራሪቶች ጩኸታቸው ይረብሽ ይሆናል እንጂ አንዳች ነገር የሚፈጥሩበት አቅም የለም።

በሕዝብ ድምጽ የተመረጠውን መንግሥት በአፈሙዝ ለመግልበጥ ማኅበራዊ መሰረት ያላገኘው ቡድን እታገልለታለሁ የሚለውን ሕዝብ መልሶ ማጥቃት ከጀመረ ውሎ አድሯል።በዛሬው ዕለት በምዕራብ ጎጃም ፍኖተ...
04/04/2024

በሕዝብ ድምጽ የተመረጠውን መንግሥት በአፈሙዝ ለመግልበጥ ማኅበራዊ መሰረት ያላገኘው ቡድን እታገልለታለሁ የሚለውን ሕዝብ መልሶ ማጥቃት ከጀመረ ውሎ አድሯል።

በዛሬው ዕለት በምዕራብ ጎጃም ፍኖተ ሰላም ከተማ በአንጋፋው ዳሞት ቁጥር 1 መሰናዶ ትምህርት ቤት ላይ ተማሪዎች በሚማሩበት ክፍል ውስጥ ተማሪዎች ፈተና ላይ እንዳሉ የቦንብ ጥቃት በመፈጸም ሩጠው ባልጠገቡ ታዳጊዎች ላይ አሰቃቂ ጉዳት አድርሷል። የሕዝብ ጠላት መሆኑንም አሳይቷል።

እንዲህ አይነቱ የሽብር ሥራ የዚህን ቡድን "ሳይበቅሉ መርገፍ" እያሳየን ይገኛል። ከመፈጠሩ አርጅቶ መሞቱንም እያስተዋልን ነው።

ታጣቂ ሆይ ሕዝብ ካልደገፈህ አልደገፍህም አለቀ። ሕዝብ ባለመደገፍ ስህተትህን እያሳየህ ... እንደገና በሕዝብ ላይ ሌላ ስህተት የምትሠራ ከሆነ እየተንሰራፋህ ሳይሆን እየጠፋህ መሆኑን እወቅ።

" ከመንግሥት ጋር ተቀናጅተን በወረዳችን ዘላቂ እና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን እንሠራለን" -የሰከላ ወረዳ ነዋሪዎች ይህ የሰከላ ወረዳ ሕዝብ አቋም የሁሉም የአማራ ክልል ሕዝብ እምነትና ስ...
04/04/2024

" ከመንግሥት ጋር ተቀናጅተን በወረዳችን ዘላቂ እና አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን እንሠራለን" -የሰከላ ወረዳ ነዋሪዎች

ይህ የሰከላ ወረዳ ሕዝብ አቋም የሁሉም የአማራ ክልል ሕዝብ እምነትና ስሜት ነው። የአማራን ሕዝብ ጥያቄዎች መንግሥትን በሃይል አፍርሰን እንመልሳለን ያሉ ሃይሎች ለሃገሬ ገበሬ የአፈር ማዳበሪያ አያቀርቡለትም። ምርጥ ዘር አይሰጡትም፤ የመስኖ ልማቱን አይደግፉለትም። የመሰረተ ልማት ጥያቄውን አይፈቱለትም። ከህመሙ ማገገሚያ መድኀኒት አያቀርቡለትም።

እነዚህን ሰዎች አበጥረው የሚያውቋቸው ዘመዶቼ ሁልጊዜም የተሻለውን ስለሚያውቁ ከጎናቸው አይቆሙም። የአማራን ሕዝብ ጥያቄ እንፈታለን ብለው የተሰባሰቡት ሰዎች ማኅበራዊ ሃላፊነት የሚባለው ደረጃ ቀርቶ ኪስ በማውለቅ፣ ማጅራት በመምታት፣ ትግልን በመክዳት፣ ታላላቆችን በመናቅ፣ ሥራ በመፍጠር ሳይሆን የፈጠሩትን በመዝረፍ የሚታወቁ መሆናቸውን አበጥሮ የሚያውቀው ሕዝባችን ፈጽሞ አይከተላቸውም። የሆነውና እየሆነ ያለውም ይኸው ነው።

ይህ ሕዝብ ትናንትም፣ ዛሬም ነገም የሚፈልገው (የሚጠይቀው) ዘላቂ ሰላም፣ ፍትሃዊ ልማት እና ማንነቱ ተከብሮ መሥራትና መለወጥን ነው።

🕊ሰላም ለሕዝባችን❗️

ውሾቹ ይጮኻሉ፤ ግመሎቹ ጉዟቸውን ቀጥለዋል🇪🇹በ   ከተማ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞ የሚገነባው ዘመናዊ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ላንድፊልድ ፕሮጀክት በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው።ዘመና...
03/04/2024

ውሾቹ ይጮኻሉ፤ ግመሎቹ ጉዟቸውን ቀጥለዋል🇪🇹
በ ከተማ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞ የሚገነባው ዘመናዊ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ላንድፊልድ ፕሮጀክት በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው።

ዘመናዊ የደረቅ ቆሻሻ ማስወገጃ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለከተማው አገልግሎት መስጠት ሲጀምር የከተማውን የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት በማዘመን ደብረ ብርሃንን ለነዋሪዎች ምቹ ከተማ ከማድረጉ በተጨማሪ ቀላል የማይባል የሥራ ዕድልም ይፈጥራል።

"አማራ ክልል በርካታ የልማት ጥያቄዎች የሚነሳበት ክልል ነው። ይህንን የሕዝብ ጥያቄ ለመመለስ ደግሞ  ኢኮኖሚያችን በሚያመነጨው ልክ  ተመጣጣኝ ገቢ  መሰብሰብ ይጠበቅብናል። የአማራ ክልል በ...
02/04/2024

"አማራ ክልል በርካታ የልማት ጥያቄዎች የሚነሳበት ክልል ነው። ይህንን የሕዝብ ጥያቄ ለመመለስ ደግሞ ኢኮኖሚያችን በሚያመነጨው ልክ ተመጣጣኝ ገቢ መሰብሰብ ይጠበቅብናል።

የአማራ ክልል በቆዳ ስፋትም ሆነ በሕዝብ ብዛት ታላቅ የሚባል ብቻ ሳይሆን ለሃገራችን ኢኮኖሚ የሚያበረክተው አስተዋጽኦም በእጅጉ ሰፊ ነው። ሁኖም ግን ክልሉ በሚያመነጨዉ ሃብት ልክ ገቢ በአግባቡ እየተሰበሰበ አለመሆኑ የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት እያቀጨጨው ይገኛል።

ስለሆነም ከላይ እስከ ታች ያለው የክልሉ አመራር ለበጀት ምደባ የሚጓጓውን ያክል ገቢን በአግባቡ በመሰብሰብና ገቢን በማስተዳደር የሕዝብን የመልማት ጥያቄ ለመፍታት መሥራት ይጠበቅበታል።

ከደሃ ሕዝብ የመልማት ጥያቄ ላይ ቁመው ግብር የሚሰውሩ፣ ግብር ለሚሰውሩ ወገኖች የሚተባበሩ፣ ግብር ከፋዮችን ዘመናዊ በሆነ ጥራት ያለው አገልግሎት የማያስተናግዱ አካላት እየሠሩት ያለው ሥራ የሕዝብ ጠላትነት መሆኑ መታወቅ አለበት። ይህንን አይነት ሕገወጥነት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማረም የግብር አሰባሰብ ሥርዓቱን ማዘመን ከሁላችንም ይጠበቃል።

በክልላችን ውስጥ የሚገኙ የውሃ፣ የትምህርት ቤት፣ የመድኀኒት አቅርቦት፣ የመስኖ፣ የመንገድና ሌሎች መሰረተ ልማቶች ሁሉ ከግብር ከፋዩ ሕዝብ በሚሰበሰብ ገንዘብ የሚሠሩ መሆናቸውን የማይረዳ የክልላችን ነዋሪ ይኖራል ተብሎ አይጠበቅም።

ስለሆነም ይህንን እያወቁ የሕዝብን ሃብት የሚመዘብሩ ሙሰኞች፣ ግብር የሚሰውሩ የሕዝብ ጠላቶችም ሆነ ሃቀኛውን ግብር ከፋይ ምቹና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዳያገኝ የሚያደርጉ አሠራሮች ሁሉ ተያይዘን እንድንወድቅ የሚያደርጉ በመሆናቸው መስተካከል የሚገባቸው ናቸው።

በዚህ ወቅት ከሕዝብ ጎን በመቆም ከድሃ ሕዝብ ላይ ግብር በመሰወር አንከብርም፤ ታማኝነታችን በሰላምና በደስታ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በመከራ ጊዜም ሕያው ነው ነብላችሁ በሃቀኝነት የጸናችሁ ታማኝ ግብር ከፋዮች ክብር ይገባችኋል።"

ክቡር አቶ አረጋ ከበደ
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር

የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ "ግብር ለሀገር ክብር" በሚል መሪ መልእክት ምስጉን ግብር ከፋዮችንና ታታሪ ሠራተኞችን ለማበረታታት ባዘጋጀው የንቅናቄ መድረክ ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደz

ከጠላት ጋር የሚወግን ሁሉ ጠላት ነው❗️ግርማ ካሳ የተሰኝ የጽንፈኛው ቡድን አፈቀላጤ ከሰሞኑ ህወሃት በራያና በዋግ ኽምራ ሕዝብ ላይ የጀመረችውን ትንኮሳ መነሻ በማድረግ የራያና የአገው ሕዝብ...
02/04/2024

ከጠላት ጋር የሚወግን ሁሉ ጠላት ነው❗️

ግርማ ካሳ የተሰኝ የጽንፈኛው ቡድን አፈቀላጤ ከሰሞኑ ህወሃት በራያና በዋግ ኽምራ ሕዝብ ላይ የጀመረችውን ትንኮሳ መነሻ በማድረግ የራያና የአገው ሕዝብ ለምን ሰላማዊ ሰልፍ አደረገ ብሎ "ለራያ ወገኖች ትኩረቱ መቀሌ ሳይሆን አራት ኪሎ ይሁን" ብሎ ጽፏል።

ስለዚህ እንዲህ ከሆነ የአማራ ሕዝብ ተቆርቋሪዎች ነን የሚሉት ፋኖ ተብየ ጽንፈኞቹ ከህወሃት ጋር ምን አስተሳሰራቸው የሚለው ጥያቄ የወቅቱ ዐቢይ ጉዳይ ነው።

የትኛውም አንባቢ እንደሚረዳው ህወሃትን ጠላት ለማለት የተገደድነው ህወሃት በአማራ ሕዝብ ፍትሃዊ ፍላጎቶችና መብቶች ላይ የጭቆና ቀንበርን ጭኖ የኖረና ለሠራው ግፍም ይቅርታ ያልጠየቀ እንዲሁም የአማራን ሕዝብ ሃብቱንና መሬቱን ዘርፎ የኖረ፣ ማንነቱን የቀማ፣ የአማራ ሕዝብ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠላት ተደርጎ እንዲታይ በፖሊሲ፣ በሕግና በተቋማት ግንባታ ውስጥ አካቶ የሠራ፣ የዘር ማጥፋት ወንጀል የፈጸመ ድርጅት በመሆኑ ነው።

ይህም ብቻ ሳይሆን ዛሬም ከዚህ ስህተት ሳይመለስ የፌዴራል መንግሥቱ ለዘላቂ ሰላም በሚበጅና የሕዝብን ድምጽ መሰረት ባደረገ አሠራር ችግሩን ለመፍታት እየሄደበት ያለውን መንገድ ለማደናቀፍ የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመና ትንኮሳውንም እያደረገ ያለ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ይህንን ሃይል ነው እንግዲህ እነ ግርማ ካሳ " እጃችሁን አጣጥፋችሁ ዝም ብላችሁ ተወረሩ።ለምን ወደ መቀሌ ትጮሃላችሁ። ትክክለኛው ጠላታችሁ እኮ ህወሃት ሳይሆን ብልጽግና ነው" እያሉ ያሉት።

በዚህ ስሌት እነሱ ብልጦች እኛ ጅሎች መሆናችን ነው። ብልጽግና የአማራና የትግራይ ሕዝብ ጦርነት ውስጥ በመግባታቸው የሚያተርፍ ድርጅት አይደለም። መሪ ድርጅት እንደመሆኑ መንግሥቱን አጽንቶ፣ በአቻ መንግሥታት ሁሉ ተከብሮ፣ የኢኮኖሚ እድገት አስመዝግቦ፣ ...የተሻለ ተወዳጅና የለውጥ መንግሥት ሁኖ መኖርና ለቀጣይ ምርጫ በሕዝብ ዘንድ ተመራጭ ሁኖ የሚቀጥለው ሃገር ሰላም ሲሆን ብቻ ነው። ይህ ስብከት ጅሎችን ለማነቃነቅ የሚጠቅም የጅል ዘፈን ብቻ ነው።

ሌላው ሃቅ ግን የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑን አካሄድ ለማደናቀፍ የሚሠራው ፤ ሕዝበ ውሳኔ አንቀበልም ያለው፤ የራያ፣ የዋግ ኽምራ፣ የወልቃይት ጠገዴና ጠለምትን በሃይል ወርሬ እይዛለሁ እያለ የሚዝተውና የጦርነት ነጋሪት እየጎሰመና ግጭትም እየጀመረ ያለው ሃይል በምን መስፈርት የአማራ ሕዝብ በጥተኛ ጠላተሰ እንደማይሆን እነ ግርማ ሊያስረዱን አልቻሉም።

በዚህ እውነተኛ መነጽር ስንመለከተው ለዘላቂ መፍትሔ እየሠራ ያለው ብልጽግና ፤ የአማራን ሕዝብ ጥያቄ ለማዳፈንና ማንነቱንና መልክዐ ምድሩን ለማዘረፍ ሽፋን እየሰጠ ያለው ደግሞ ጽንፈኛው ቡድን ነው።

ስለሆነም የአማራ ሕዝብ እውነቱን ይረዳዋልና ከወሮበላው ቡድን ጋር አይቆምም። ባለመቆሙም የተበሳጩት እነ ግርማ የራያ ሕዝብ ለምን ኮከብ ያለው ባንዲራ ይዞ ሰላማዊ ሰልፍ ወጣ ብለው በሕዝባችን ላይ የስድብ አፋቸውን አንስተዋል፤ ተበሳጭተዋልም😂

ጽንፈኞች ሆይ ስንት ጥያቄ ነው ያላችሁ ... ብሔራዊ ተቀባይነት የሌለው፣ ዓለም አቀፋዊ እውቅና የሌለው፣ ኮከብ ባለመኖሩ ዳቦ የማይሆንና ፖለቲካዊ ፋይዳ የሌለው የባንዲራ ጥያቄ ደግሞ ምንድን ነው?? በስንቱ እንሳቅ😂

ጉዳዩ ሲጠቃለል ከጠላት ጋር የሚወግን ሁሉ ጠላት መሆኑ ይታወቅ። የራያና የአገው ሕዝብ የሕዝባችን ጥያቄ በዘላቂነት ይፈታ ዘንድ የክልሉም ሆነ የፌዴራል መንግሥቱ እየሄደበት ያለው ከደም አፋሳሽና ከጠላትነትን ነጻ የሚያደርግ እንዲሁም የሕዝብን ድምጽ የሚያከብር ዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዳይደናቀፍ በሰለጠነ መንገድ ያቀረበው ጥያቄ የሚበረታታ ነው።

ሰላም ለሕዝባችን ❗️

የተከበሩ አቶ አደም ፋራህ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማእርግ የዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ ሆነው በመሾምዎ የ Ethio Press ዝግጅት ክፍል እንኳን ደስ አለዎት እ...
01/04/2024

የተከበሩ አቶ አደም ፋራህ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማእርግ የዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ ሆነው በመሾምዎ የ Ethio Press ዝግጅት ክፍል እንኳን ደስ አለዎት እያለ መልካም የሥራ ጊዜ ይሁንልዎት ዘንድ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share