Ethio Press

Ethio Press Official FaceBook page of Ethio Press

13/08/2026
"ሰራዊቱ በሰራው ህግ የማስከበር ሥራ የታሪካዊ ጠላቶቻችንን ዕቅድ ማክሸፍ ተችሏል" - ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማየምሥራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማ ከምዕራብ ጎጃም ዞን...
30/07/2026

"ሰራዊቱ በሰራው ህግ የማስከበር ሥራ የታሪካዊ ጠላቶቻችንን ዕቅድ ማክሸፍ ተችሏል" - ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማ

የምሥራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል መሐመድ ተሰማ ከምዕራብ ጎጃም ዞን አስተዳደር የስራ ኀላፊዎች ጋር ዞኑ ባከናወናቸው የህግ ማስከበር ሥራዎች ላይ ውይይት አካሂደዋል።

በውይይቱ ወቅት በቀጣይ በጋራ በሚከናወኑ ሥራዎች ላይ የሚያግዙ አቅጣጫዎችም ተቀምጠዋል።

በመድረኩ የ302ኛ ኮር ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል መላኩ ገላነህን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦር መኮንኖችና የፖለቲካ አመራሮችም ተገኝተዋል።

የምሥራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል መሐመድ ተሰማ ክልሉ በ2015 ዓ.ም ገጥሞት ከነበረው የሰላም እጦት ችግር ተላቆ ሰላምን በአስተማማኝ ደረጃ ላይ እያጸና መሆኑን ገልጸዋል።

የፌዴራል ተቋማትና የክልሉ የጸጥታ ኃይሎች በቅንጅት በሰሩት የህግ ማስከበር ሥራ የታሪካዊ ጠላቶቻችን፣ የባዕዳንና የባንዳ ዕቅድ መክሸፉን ገልጸዋል።

እንደ ዋና አዛዡ ገለጻ፣ የጸጥታ መዋቅሩ የጽንፈኛውን ኃይል አከርካሪ በመስበርና እግር በእግር ተከትሎ በመምታት የክልሉን ህዝብ ሰላም ለማረጋገጥ እየሰራ ነው። ጥምር የጸጥታ ኃይሉ በከፈለው ዋጋም ክልሉ በሁለት እግሩ ቆሞ ከክልል እስከ ወረዳ ድረስ መዋቅር መዘርጋቱን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከክልሉ ህዝብና ከጸጥታ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት የጀመረው የህግ ማስከበር ተልዕኮ አስተማማኝ ሰላም እስኪረጋገጥ ድረስ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዕድሜዓለም አንተነህ በበኩላቸው፣ ጥምር የጸጥታ ኃይሉ የዞኑን ሰላም በአስተማማኝ ደረጃ ለማጽናት ሰፊ ሥራ መሥራቱን ገልጸዋል።

የዞኑ ህዝብ ለሰላምና ለልማት ያለው ፍላጎት ከፍተኛ መሆኑን የገለጹት አቶ ዕድሜዓለም፣ አስተዳደሩ አስተማማኝ ሰላም በማጽናት፤ ልማትንና መልካም አስተዳደርን በማስፈን የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

21/07/2026
ምን ይላል? ተርጉምልኝማ!
20/07/2026

ምን ይላል? ተርጉምልኝማ!

13/07/2026
06/07/2026

ሰላም ለሀገራችንም ሆነ ለክልላችን ሁለንተናዊ ልማትና ህልውና መሠረት ነው!

ሰላም ለሰው ልጆች ሁሉ እንደ እስትንፋስ እጅግ አስፈላጊ ተፈጥሯዊ ፀጋ ነው። ሰላም በሌለበት ሁኔታ ወልዶ መሳም፣ ዘርቶ መቃም፣ ሰርቶ መክበርና ማደግ ከቶውንም አይታሰብም።

በክልላችን ባለፉት ሶስት ዓመታት በተከሰተው የሰላም እጦት ምክንያት በህዝባችን ላይ ከፍተኛና ዘርፈ-ብዙ ሁለንተናዊ ጫና ደርሷል። በዚህም ሳቢያ የውድ ዜጎቻችን ህይወት በከንቱ ጠፍቷል፤ የህዝብ መጠቀሚያ የሆኑ ታላላቅ መሰረተ-ልማቶች ወድመዋል፤ ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ህፃናት ልጆቻችን ከትምህርት ገበታቸው ተለይተው እንዲቀሩ ሆኗል፤ ትርፍ አምራች የሆነው አርሶ አደራችን ምርቱን በነፃነት ወደ ገበያ እንዳያቀርብ እንቅፋት ሆኖታል፤ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት በማስተጓጎል፣ ለአርሶ አደሩ የሚቀርበውን ሰው ሰራሽ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በወቅቱ ማድረስ እጅግ ፈታኝ ሆኖ አልፏል።

የዚህ ሁሉ ውድመት፣ ግጭትና የህዝብ ሰቆቃ መሪ ተዋናይና ጠንሳሽ የሆነው ፅንፈኛው ተላላኪ ቡድን ነው። ይህ ቡድን ይሄንን ሁሉ ግፍና በደል በህዝባችን ላይ የፈፀመው "ስልጣን በህጋዊ ምርጫ ከህዝብ የሚመነጭ መሆኑ እየታወቀ በአፈሙዝ የመንግስትን ኃላፊነት እይዛለሁ" በሚል ቅዠት ሲሆን፣ ከ21ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የሰለጠነ አስተሳሰብ ጋር ፍፁም በተጋጨ የኋላቀርነት አባዜ ተገፋፍቶ መሆኑ ግልፅ ነው።

የክልላችንን ህዝብ ከዚህ እኩይና ጽንፈኛ ቡድን ሰለባነት ለመታደግና የተሟላ ሰላም ለማስፈን በተወሰደው የተቀናጀ የህግ ማስከበር እርምጃ፤ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የክልላችን የፀጥታ አካላት በጥምረት ውድ ህይወታቸውን በመገበር ባከናወኑት ስኬታማ ህግ የማስከበር ስራ በህዝባችን ላይ ተደቅኖ የነበረው ከፍተኛ አደጋ ተቀልብሷል። በዚህም አሁን የሚታየው አንፃራዊ ሰላም ሊሰፍን ችሏል።

መንግስት የዜጎችን ደህንነትና የህግ የበላይነትን የሚረጋገጠው በሃይል አማራጭ ብቻ ነው ብሎ አያምንም። በመሆኑም በተሳሳተ መንገድ ተደናግረው ጫካ ለገቡ ኃይሎች በሙሉ እይታና በቅን ልቦና በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪ አቅርቧል። በዚህም ምክንያት የሰላም ጥሪውን መነሻ በማድረግ በሺዎች የሚቆጠሩ ታጥቀው በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጣቂዎች ጥሪውን በመቀበል ወደ መንግስት በመግባት ማህበረሰባቸውን ተቀላቅለዋል። ታጣቂዎቹ ወደ ሰላም አማራጭ ለመመለስ በወሰዱት ጠንካራ ውሳኔም የህዝባቸውን ሰላም ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን ራሳቸውንም ከተሳሳተ አጥፊ መንገድና ከተላላኪነት ነፃ አውጥተዋል፡፡

በአንፃሩ፤ የመንግስትን የሰላም ጥሪና ትዕግስት እንደ ፍርሃት በመቁጠር፤ አሁንም ድረስ በህዝባችን ላይ ዝርፊያ፣ እገታ እና አላስፈላጊ ትርምስ ለመፍጠር ሌትና ቀን የሚሰሩ ኃይሎች አሉ። እነዚህ ፅንፈኛ ቡድኖች ከህዝባችን ታሪካዊ ጠላቶች በተለይም ከአጥፊው ቡድን ህወሐት ጋር በመተባበር የአማራን መሰረታዊ ጥያቄና በደምና በአጥንት ያስመለሳቸውንና ቀሪ ህጋዊ ጉዳዮችን ለማስጨረስ ከሃገሪቱ ህዝቦች ጋር በመመካከር ላይ የምንገኘውን የወሰንና ማንነት ጉዳዮች አሳልፎ በመስጠት ለአማራ ህዝብ እታገላለሁ በሚል ሽፋን እኩይ ድርጊቱን በመቀጠል ላይ ይገኛል።

መንግስት የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅና የህግ የበላይነትን የማስከበር ቀዳሚና ታሪካዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በእነዚህ ግትርና ተላላኪ ፅንፈኛ ቡድን ላይ ቀጣይነት ያለው የህግ ማስከበር እርምጃ ይወስዳል፤ እየተወሰደም ይገኛል። ከህግ ማስከበር ስራችን ጎን ለጎንም የሰላም አማራጭን ለሚቀበሉ ታጣቂዎችም መንግስት ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ የመፍታት ጥሪና በሩ ሁሌም ክፍት ነው፡፡

የዜጎችን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ በሚደረገው መጠነ-ሰፊ ርብርብ እና አሁን የተገኘው አንፃራዊ ሰላም ወደ ዘላቂ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መላው የክልላችን ህዝብ የተለመደውን ድጋፍና ንቁ ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ
ባህር ዳር

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share