በሌ አዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/Bele awasa town prosperity party office

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • በሌ አዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/Bele awasa town prosperity party office

በሌ አዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/Bele awasa town prosperity party office Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from በሌ አዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/Bele awasa town prosperity party office, በሌ አዋሳ, Addis Ababa.

በወላይታ ዞን የከፍተኛ ቀዶ ጥገና አገልግሎት የሚሰጡ 4 ጤና ጣቢያ ሥራ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ ህዳር 15 2017 የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ሀ...
24/11/2024

በወላይታ ዞን የከፍተኛ ቀዶ ጥገና አገልግሎት የሚሰጡ 4 ጤና ጣቢያ ሥራ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ

ህዳር 15 2017 የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ በአቶ ፀጋዬ ኤካ የተመራው የባለሙያዎች ቡድን በዳሞት ፑላሳ እና ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ከወረዳ ከፍተኛ አመራሮች እና ከጤናው ዘርፍ አመራሮች ጋር በአጭር ጊዜ ውስጥ የቀዶ ህክምና ብሎኮችን ሥራ ማስጀመሪያ ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

በዞኑ የከፍተኛ ቀዶ ጥገና አገልግሎት የሚሰጡ 4 ጤና ጣቢያ ሥራ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን የወላይታ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ ፀጋዬ ኤካ አስታውቀዋል።

የዞኑ ጤና መምሪያ የጤና አገልግሎት ጥራት እና ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እየተገበራቸው ካሉት በርካታ ስራዎች አየተሰሩ መሆኑንና የዚሁ ግብ አንድ አካል የሆነው በቀዶ ህክምና የማዋለድ አገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ሞትን መከላከል ትኩረት የተሰጠው ተግባር እንደሆነ አቶ ፀጋዬ ተናግረዋል፡፡

የቀዶ ህክምናን ተደራሽነት ለማሻሻል እስካሁን 8 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሎች በገጠር ወረዳዎች እና ከተማ አስተዳደር አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን የገለጹት ሀላፊው የቀዶ ህክምና ብሎኮች በሚገኙ በአዴ ሻንቶ፣ ጋራ ጎዶ፣ ጉኑኖ እና ሆብቻ ጤና ጣቢያዎች አገልግሎት ለማስጀመር የሚያስችል ግብአትና የሰለጠነ የሰው ሃይል ተሟልተው አገልግሎት እንዲጀመሩ ከዞን አስተዳደር እና አክሲስ ከተሰኘ አጋር ድርጅት ጋር በጥምረት ክትትል እና ድጋፍ ሥራዎች እየተሰራ መሆኑን ነው የመምሪያ ሀላፊ የተናገሩት።

ከጤና ጣቢያዎቹ 5 ጠቅላላ ሀኪሞች በቀዶ ህክምና እንዲያዋልዱ የሚስችል የክህሎት ስልጠና በማጠናቀቅ ላይ መሆናቸውን በመግለጽ ከዞን አስተዳደር፣ ወረዳ አስተዳደር፣ ከተማ አስተዳደር እንድሁም ከሆስፒታሎች እና ጤና ጣቢያዎች ጋር ትስስር በመፍጠር ግብአት የማሰባሰቡ ሥራ በማጠናቀቅ በቀጣይ አንድ ወራት ውስጥ ሥራ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ መሆኑን የመምሪያ ሀላፊ ገልጸዋል።

በወላይታ ዞን በተለያዩ ወንጀል ድርጊት የተጠረጠሩ አምስት አመራሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ      በሌ አዋሳ፤ጥቅምት 15/2017 በወላይታ ዞን በተለያዩ ወንጀል ድርጊት የተጠረጠሩ አምስት አመራ...
25/10/2024

በወላይታ ዞን በተለያዩ ወንጀል ድርጊት የተጠረጠሩ አምስት አመራሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በሌ አዋሳ፤ጥቅምት 15/2017 በወላይታ ዞን በተለያዩ ወንጀል ድርጊት የተጠረጠሩ አምስት አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ተጠሪጣሪዎች የመንግሥትንና የህዝብን አደራና ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው በሙስና እና በተለያዩ ወንጀል ድርጊቶች ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ነው ፖሊስ የገለጸው።

በቁጥጥር ስር የዋሉት፦

1ኛ. አቶ ተመስገን አለማየሁ የቀድሞ የወላይታ ዞን የመንግስት ረዳት ተጠሪ እና የፖለቲካና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ እንዲሁም የቀድሞ የወላይታ ሶዶ ከተማ ከንቲባ የነበሩ

2ኛ. አቶ መስፍን ዳዊት የቀድሞ የወላይታ ዞን የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም የአረካ ከተማ ከንቲባ የነበሩ

3ኛ. አቶ ማዕረጉ አስራት የቀድሞ የሆብቻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የነበሩ

4ኛ. ወ/ሮ ተዋበች ተረጬ የቀድሞ የአረካ ከተማ የመንግስት ረዳት ተጠሪ እና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ

5ኛ. አቶ ከበደ ካንፌሶ የቀድሞ የቦሎሶ ሶሬ ወረዳ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ መሆናቸውን ፖሊስ አስታውቋል።

አመራሮቹ በቁጥጥር ሥር ዉለዉ በህግ እንዲጠየቁ ምርመራ መጀመሩን ፖሊስ ገልጿል።

በመጨረሻም ህብረተሰቡ በሌሎች አካባቢዎችም በህገ ወጥ ወንጀል ድርጊቶች የሚሳተፉ ተጠርጣሪዎችን መረጃ በመስጠት የተለመደዉን ትብብርና እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ፦የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ

በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር ክልል አቀፍ ብሔራዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ  ቀንን በማስመለከት  በነገው ዕለት የአካል ብቃት እቅስቃሴ እንደሚካሄድ ተገለጸ።በሌ አዋሳ፦ ታህሳስ 23/2016 ...
02/01/2024

በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር ክልል አቀፍ ብሔራዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ቀንን በማስመለከት በነገው ዕለት የአካል ብቃት እቅስቃሴ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

በሌ አዋሳ፦ ታህሳስ 23/2016 ዓ/ም በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር ክልል አቀፍ ብሔራዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ቀንን በማስመለከት በነገው ዕለት እንደሚካሄድ ተገልጿል።

ዓላማው የስፖርት እንቅስቃሴን በማስፋፋት ህብረተሰቡ በሚኖርበት፣ በሚሰራበትና በሚዝናናበት አካባቢ ተሳታፊ ሆኖ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን እንዲከላከልና ጤናውን እንዲጠብቅ የሚረዳ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማህበረሰባዊ ግንኙነትን ከማጠናከሩም ባሻገር ወንድማማችነትና እህትማማችነት አንድነታችንን ይበልጥ ያጠናክራል ተብሏል።

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ ከማለዳው ልክ 12፡00 ሰዓት ላይ በከተማ አስተዳደር ፍትለፍት ባለዉ አደባባይ ሁሉም ህብረተሰብ ክፍሎች እንዲገኙ ጥሪ ተላልፏል፡፡

በዚህ ታሪካዊ የማህበረሰብ ስፖርት ላይ ሁሉም አካላት ወጣቶች፣ ሴቶች ፣ መንግስት ሠራተኛዉ፣ አጠቃላይ የከተማዉ ማህብረሰብ በነቂስ ወጥቶ እንዲሳተፉም ጥሪ ቀርቧል፡፡

በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የ2014 የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈጻጸም ግምገማና የ2015 ዓ.ም የፈጻሚ ማዘጋጃ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ነውበሌ አዋሳ፤ ነሐሴ 25/2014 ዓ.ም በ...
31/08/2022

በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የ2014 የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈጻጸም ግምገማና የ2015 ዓ.ም የፈጻሚ ማዘጋጃ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ነው

በሌ አዋሳ፤ ነሐሴ 25/2014 ዓ.ም በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የ2014 የፓርቲና የመንግስት ስራዎች አፈጻጸም ግምገማና የ2015 የፈጻሚ ማዘጋጃ የአመራር ግምገማ መድረክ መካሄድ ተጀምሯል።

አጠቃላይ አመራር በተገኘበት"ለብልፅግና ጉዞ ስኬት በተደራጀ መንገድ እንረባረባለን" በሚል መሪ ቃል የከተማ ዓቀፍ የአመራር መድረክ እየተካሄደ ነው።

የ2014 አፈፃፀም በጥልቀት የሚገመገም ሲሆን ድክመቶችን በመቅረፍ በቀጣይ በጀት ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ለማምጣት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ይመክራሉ

በ2014 በጀት ዓመት የነበሩ ጥንካሬዎችን በማጽናትና በማስፋት ጉድለቶችን በማረም አመራሩ ለቀጣይ ተልዕኮ ራሱን ዝግጁ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ተነስተዋል::

"የፈተናዎች መብዛት ከብልጽግና ጉዙአችን አያስቆመንም "በሚል መሪ ቃል እና በሌሎች በተለያዩ አጃንዳዎች ዙሪያ የዉይይት መድረክ በበሌ አዋሳ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።በሌ አዋሳ፤ መጋቢት 14/2...
23/03/2022

"የፈተናዎች መብዛት ከብልጽግና ጉዙአችን አያስቆመንም "በሚል መሪ ቃል እና በሌሎች በተለያዩ አጃንዳዎች ዙሪያ የዉይይት መድረክ በበሌ አዋሳ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

በሌ አዋሳ፤ መጋቢት 14/2014 በብልጽግና ፓርቲ አንደኛ ጉባኤ የተላለፉ ውሳኔዎችና የተቀመጡ ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ በበሌ አዋሳ ከተማ ከተለያዩ ከከተማ ህብረተሰብ የተወጣጡ ነዋሪዎች ጋር ሕዝባዊ ውይይት መካሄድ ጀምሯል።

በመድረኩም የዎላይታ ዞን አከባቢ ጥበቃና ደን ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ዋዱ ዳና ፣የዎላይታ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምርያ ምክትል ኃላፊ አቶ እንግዳወርቅ ገነቱ እና በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የበሌ አዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ስምኦን ሳፓ እና አጠቃላይ የከተማ አመራሮችና ከበሌ አዋሳ ከተማ የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የህዝብ ውይይቱ ዋና አላማው በጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎች ከህብረተሰቡ ወቅታዊ እና ዘላቂ ፍላጎቶች ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን ማረጋገጥ፤

በየደረጃው ካለው የህብረተሰብ ክፍል ጋር ችግሮችን በጋራ ለመፍታት የሚያስችል የጋራ መግባባት መፍጠር እና ሕዝቡን የመፍትሄ አካልና የውጤቱም ተጠቃሚ ማድረግ ነው።

መዋቅር ተለዉጦ በመለወጥ በምል መሪ ቃል በአንድ ወራት የሚተገበር የፀጥታ መዋቅር የንቅናቄ ዕቅድ ዙሪያ የዉይይት መድረክ ተካሄደ።በሌ አዋሳ ፣ የካቲት 26/2014 ዓ.ም በበሌ አዋሳ ከተማ ...
05/03/2022

መዋቅር ተለዉጦ በመለወጥ በምል መሪ ቃል በአንድ ወራት የሚተገበር የፀጥታ መዋቅር የንቅናቄ ዕቅድ ዙሪያ የዉይይት መድረክ ተካሄደ።

በሌ አዋሳ ፣ የካቲት 26/2014 ዓ.ም በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር መዋቅር ተለውጦ በመለወጥ በምል መሪ ቃል በአንድ ወራት የሚተገበር የፀጥታ መዋቅር የንቅናቄ ዕቅድ ዙሪያ ከሠላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ጋር የዉይይት መድረክ ተካሄደ።

የበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፋ ዶ/ር አባይነህ አጫ እንደተናገሩት በከተማችን የለውጡ ጉዞ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ የህብረተሰቡን ሠላምና ደህንነት ለማስጠበቅ፣ የህግ በላይነትን ለማስከበር እና ለዉጡ ተጠናክሮ እንድቀጥል ከማድረግ አንጻር ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ተሰርተዋል ብለዋል።

አክለዉም ዶ/ር አባይነህ አጫ በከተማችን አሁናዊ የሚታዩ የፀጥታ ችግሮችን በዘላቂነት ለማስወገድ በከተማችን የህግ የበላይነት በማረጋገጥ ዘጎች ከማንኛዉም የፀጥታ ስጋት ነፃ ሆነዉ በልማትና በለዉጡ ስራዎች ላይ ብቻ ትኩረት እንድያደርጉ የፀጥታ መዋቅሩ ከመቸዉም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥተዉ ከህዝቡ ጋር መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

የበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ተመስገን ፎላ አሁን ያለውን አንጻራዊ ሰላም ሁሉንም ህብረተሰብ ክፍል እና አመራር ከፀጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀት ዘላቂና አስተማማኝ ሰላምን ለማምጣት መዋቅራችንን በማጥራት ለላቀ ቁመና መዘጋጀት አለብን ብለዋል።

በተለያዩ አከባቢዎች የሚታዩ የተለያዩ ስርቆቶች ዝርፍያዎች ተበራክተዉ እየታዩ ነው ያሉት በበሌ አዋሳ ከተማ ከስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ዋና ሳጅን በደቀ በርገነ ህዝቡ ያለ ማንም ቀስቃሽ ለአከባቢ ሰላም በመቆም ከፀጥታ አካል ጎን መሰለፍ እጅጉን አስፈላጊ ነዉ ብለዋል።

።።የጠራ እሳቤ፣ የተግባር አንድነት፤ለአድስ ድል ጉዞ ምዕራፍ።።

02/03/2022

"አድዋን ስናከብር የአባቶቻችንን እልህና ወኔ ተላብሰን ለአንድ ዓላማ በጋራ መቆም አለብን"~አቶ ዮሐንስ በየነ

እንኳን ለጥቁር ህዝቦች ኩራት ለሆነዉ ለታላቁ የአድዋ ድል 126ኛ ዓመት የመታሰቢያ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

የአድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ተርፎ ለአፍሪካና ለዓለም ጥቁር ህዝቦች መመኪያና መኩሪያ የሆነ ታላቅ ድል በዓል ነው፡፡

ይህ ታላቅ ድል ለ126ኛ ጊዜ ስናከብርና ስንዘክር አንድነታችንን በማጠናከር ለመጪው ትውልድ የይቻላልና የአሸናፊነትን መንፈስን ማጎናጸፍ ይገባናል፡፡

የአድዋ ድል በዓል ኢትዮጵያውያን በማንኛውም ወቅት በሀገር ሉዓላዊነት፣ በህዝብ መብትና ነፃነት ላይ የማይደራደሩ ቆራጥ ህዝቦች መሆናቸውን ያሳዩበት የክብር በዓል ነው፡፡

ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች ወራሪውን የጣልያን ፋሽስት ጦር በአንድነት በመዝመት ያሰመዘገቡትን አኩሪ ድል በማስታወስና በመዘከር የአሁኑ ትውልድ በሀገራዊ አንድነትና ልማቱ ላይ በርትቶ መስራት እንዳለባቸው በዚሁ አጋጣሚ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

ከተባበርን የማይቻሉ የሚመስሉ ፈተናዎች እንደሚታለፉ አድዋ ምስክራችን ብቻ ሳይሆን በእኛ በኢትዮጵያዊያን የተፈፀመ ጀብዱ መሆኑን የዓለም ህዝብ በታሪክ መዝገብ ላይ ሲዘክረው ይኖራል፡፡

በነጮች የበላይነት በጥቁሮች ላይ ተጭኖ የነበረው የብዝበዛና አፈና ቀንበር በኢትዮጵያውያን ታላቅ ተጋድሎ ከጥቁሮች ጫንቃ ላይ የወረደበት፣ የመላ ዓለም ተፈጥሯዊ ግብርና ሰብዓዊ ክብር የተመለሰበት፣ በእውነትና በፍትህ ህልውና ላይ ተደቅኖ የነበረው ቀስት የተሰበረበት ታላቅ በዓል ነው።

አሁን ላይ ከድህነት የባርነት ጭቆና ለመላቀቅ የለውጥ ምህዋር ውስጥ ገብተን በተባበረ የኢትዮጵያውያን ተጋድሎ ጉዞ ጀምረናል፡፡

ሁላችንም የየግል ኃላፊነታችንን ከተወጣን ድህነትም ድል የሚሆንበትና ብልፅግናችንን የምናረጋግጥበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡

በመሆኑም የሀገራችንን ነጻነት በደም እና በአጥንታቸው ጠብቀዉ ለዛሬ ያበቁን የጀግኖች አባቶቻችንን ገድል በመከተል የአድዋን የመደመር እሳቤ ይዘን የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ማረጋገጥ ይኖርብናል።

የአሁኑ ትውልድ የአባቶቻችንን እልህና ወኔ በመላበስ በየትኛውም አቅጣጫ የሀገርን ክብር የሚዳፈር ጥቃት ሲፈፀም ልዩነቱን ወደ ጎን በመተው በአንድነት ወደ ድል አድራጊነት መምጣትን ከአባቶቻችን ሊወርስ ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

አቶ ዮሐንስ በየነ
የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ
የካቲት፤2014 ዓ.ም

02/03/2022

"አድዋ የመላው ኢትዮጵያዊያን የጀግነነት፣ የአልገዛም ባይነት ምልክትና የጥቁር ህዝቦች አለኝታ ነው" አቶ አክሊሉ ለማ

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳደር አቶ አክልሉ ለማ 126ኛውን የአድዋ ድል በዓልን በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዘንድሮ ለ126ጊዜ በልዩ ሁኔታ አድዋን ስናከብር እኛም እንደ ቀደምት አባቶቻችን ታላቅ ሀገርና ህዝብ ለመመስረት ቃል በመግባት ሊሆን ይገባል!

ከዛሬ 126 ዓመት በፊት በአድዋ ተራሮች የፈሰሰ ደም፣የተከሰከሱ አጥንቶች ለሀገር ክብርና ሉኣላዊነት መሆኑን ማንም የሚዘነጋው አይደለም። የሀገር ነጻነት፣የህዝቦች አልገዛም ባይነት ትልቅ ማሳያ ነው።

የቅኝ ገዥዎችን እብሪት የሰበረ፣በተቃራኒው የቅኝ ተገዥዎችን የነጻነት ትግል ከጫፍ እስከ ጫፍ ያነቃነቀ የእኛ ኢትዮጵያዊያን የኩራት ምንጭ ነው።

እንደ ያኔዎቹ ቅኝ ገዢዎች ሁሉ አሁንም ኢትዮጵያ ሀገራችንን ለማፍረስ፣ህዝቧን ለእርስ በርስ እልቂት ለመዳረግ የሚታትሩ የውጭና የውስጥ ጠላቶቻችን በርካቶች ናቸው።
ባለፉት ጥቂት አመታት ያየናቸው ፈተናዎች ይህን ሀቅ በግልጽ የሚያሳዩ ናቸው።

ጥንትም ሆነ የአሁኑ ትውልድ የሀገሩን ሉኣላዊነት መደፈር ከሚያይ ሞቱን ይመርጣል።

ጀግኖች አባቶቻችን ያቆዩትን ሀገር አሁን ላለው ትውልድ ለማስተላለፍ የደምና የአጥነንት መስዋዕትነት ከፍለዋል።
ይህ መስዋዕትነት በቀላሉ የሚታይ አይደለም ከአድዋ ድል የአልሸነፍ ባይነት ጥልቅ የሀገር ፍቅር ጎልቶ ይታያል ።

ጀግኖች አባቶቻችን በክብር ያቆዩልንን ሀገር በቀላሉ ለማፍረስ የሚጥሩ አካላት ምናልባትም የአድዋን ድል ምንነት ያልተገነዘቡ ናቸው።

የአድዋ ድል ከኢትዮጵያ አልፎ ለፓን አፍሪካኒዝም ንቅናቄ መመስረት መሠረት የሆነ የመላው ጥቁር ሕዝቦች ኩራት የሆነ ታላቅ ታሪካዊ ድል ነው፡፡

ዛሬ በልበ ሙሉነት ሀገር አለን ብለን መናገር እንድንችል ላደረጉን ጀግኖች አባቶቻችን ክብር ይገባቸዋል።
የአሁኑ ትውልድም የአባቶቹን አደራ ተረክቦ ይህችን ሀገር ለማስቀጠል የደም እና የአጥንት መስዋዕትነት እየከፈለ ነው።

ጠላት የከፈተብንን ወረራ መክተን ፊታችንን ወደ ልማት አዙረናል፣ ፈተናዎቻችንን ፊት ለፊት እየተጋፈጥን በሁሉም ዘርፍ ድል በመጎናጸፍ ላይ እንገኛለን። ያጋጠሙን ፈተናዎች ይበልጥ ጥንካሬ ሰጡን እንጂ እንድንሸነፍ አላደረጉንም።
መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ድምጽ ሆ ብለው በመነሳት የጠላትን ሴራ በማክሸፍ ደማቅ ታሪክ አስመዝግበዋል።

አሁንም የጠላትን ፍላጎት እየገታን ወዳለምነው የብልጽግና ጉዞ እንሻገራለን። ባልተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ ሆነን እንኳ ልማታችንን እያስቀጠልን ነው።

እኛ ከተባበርን እና አንድነታችንን ካጠናከርን የሀገራችንን ስምና ክብር ከፍ በማድረግ ድህነታችንን ታሪክ ማድረጋችን አይቀርም።

ለመላው የሀገራችን እና የዞናችን ህዝቦች በድጋሚ እንኳን ለአድዋ የድል በአል በሰላም አደረሰን ለማለት እወዳለሁ።

በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያውን የብልጽግና ፓርቲ ኮንፈረንስ ለማካሄድ ደማቅ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛልበሌ አዋሳ፣ የካቲት 20/2014 ዓ.ም በወላይታ ዞን በበሌ አዋሳ ከተማ አስ...
27/02/2022

በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያውን የብልጽግና ፓርቲ ኮንፈረንስ ለማካሄድ ደማቅ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል

በሌ አዋሳ፣ የካቲት 20/2014 ዓ.ም በወላይታ ዞን በበሌ አዋሳ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያውን የብልጽግና ፓርቲ ኮንፈረንስ ለማካሄድ ደማቅ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል ።

ታርካዊዉን የብልጽግና ፓርቲ ኮንፈረንስ ለማካሄድ በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።

ሁሉም መሠረታዊ ፓርቲዎች የነገዉን ኮንፈረንስ ለማካሄድ በየዘርፋቸዉ ደማቅ ዝግጅት እያካሄዱ ይገኛሉ ።

የመድረክ ዝግጅቶችን ጨምሮ የባነር ፣ ስትከር ፣ እና የተለያዩ ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛሉ ።

እንኳን ለመጀመሪያውን የብልጽግና ፓርቲ ኮንፈረንስ በሰላም አደረሳችሁ !

Address

በሌ አዋሳ
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when በሌ አዋሳ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት/Bele awasa town prosperity party office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share