Factify Ethiopia

Factify Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Factify Ethiopia, Media/News Company, Addis Ababa.

Factify Ethiopia is a machine learning based factchecking service with the sole purpose of becoming independent empirical repository and analytics base about the disinformation campaign in the Ethiopian Social Media Landscape.

የኢትዮጵያ መንግስት ከሀገራት ጋር ባለው የተለያዩ ግንኙነቶች ላይ ጫና የማሳደር የትዊተር ዘመቻዎችJune 16, 2022ትዊተር በኢትዮጵያ በዋነኝነት በአንድ በኩል መንግስትን ኢላማ ላደረጉእና...
16/06/2022

የኢትዮጵያ መንግስት ከሀገራት ጋር ባለው የተለያዩ ግንኙነቶች ላይ ጫና የማሳደር የትዊተር ዘመቻዎች
June 16, 2022

ትዊተር በኢትዮጵያ በዋነኝነት በአንድ በኩል መንግስትን ኢላማ ላደረጉእናበሌላ በኩል መንግስትን ለወገኑ ፖለቲካዊ ዘመቻ ፉክክሮች መድረክ ሆኖ ይገኛል። ዘመቻዎቹ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ጫናዎች ለማሳደር የሚካሄዱ ናቸው። ይህንንም ጫና ለመፍጠር ከመንግስት እስከ የሚዲያ አካላት፣ ከበይነ መንግስታት እስከ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አመራሮች እና ተቋማት ላይ የተለያዩ ዘመቻዎቹ ሲካሄዱ ቆይተዋል። በዚህ ሪፖርት የሚዳሰሰው በተለያዩ ሀገራት በመንግስት አካላት ላይ ትኩረት አድረገው የተካሄዱ የትዊተር ዘመቻዎች ሲሆኑ አጠቃላይ ዘመቻዎቹ ኢላማ ካደረጓቸው አካላት መካከል የመንግስት አካላት የአንበሳውን ድርሻ ሸፍነው ተገኝተዋል።

በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እውነታዎች ላይ መንግስትን ኢላማ በማድረግ እና መንግስትን በመወገን ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሄዱ ከ261 ሺህ በላይ የትዊተር ዘመቻ ትዊቶች ላይ በጥናቱ ዳሰሳ ተደርጓል። መንግስትን ኢላማ ያደረጉ ዘመቻዎቹ ከዘመቻ ትዊቶቹ መካከል 210 ሺህ (80%) የሚጠጋ የሚሸፍኑ ሲሆን መንግስትን የሚወግኑት 51 ሺህ (20%) ያህሉን የዘመቻ ትዊቶች አሰተራጭተዋል። መንግስትን ኢላማ ያደረጉ ዘመቻዎቹ 3,900 በሚሆኑ የትዊተር አካውንቶች ትዊት ሲደረጉ መንግስትን የወገኑት በ2,300 ያህል አካውንቶች ተሰራጭተዋል። መንግስትን ኢላማ ያደረጉ ዘመቻ ያካሄዱት የትዊተር ተጠቃሚዎች ካላቸው የአካውንት የቁጥር ብልጫ በተጨማሪ በዘመቻዎቹ የተሳትፎ ቁርጠኝነት አሳይተዋል። ከዚህም አንጻር መንግስትን ኢላማ ያደረጉ ዘመቻ ተሳታፊዎች በአማካይ በአንድ አካውንት 54 ትዊቶች ሲያሰራጩ መንግስትን የሚወግኑ ዘመቻ አካውንቶቹ በአንድ አካውንት በእጅጉ ያነሳ በአማካይ 22 ትዊቶች ብቻ ትዊት አድርግዋል።

ትዊተር በኢትዮጵያ በዋነኝነት በአንድ በኩል መንግስትን ኢላማ ላደረጉእናበሌላ በኩል መንግስትን ለወገኑ ፖለቲካዊ ዘመቻ ፉክክሮች መድረክ ሆኖ ይገኛል። ዘመቻዎቹ በኢትዮጵያ መንግስ.....

በኢትዮጵያ የትዊተር ተጠቃሚዎች እና አጠቃቀም ባለፉት ሁለት አመታት በተለይ ከፖለቲካዊ የትዊተር ዘመቻዎች ጋር በተያያዘ ከፍተኛ እድገት እና ለውጥ አስተናግዷል። የትዊተር ዘመቻዎቹ በመንግስት...
01/06/2022

በኢትዮጵያ የትዊተር ተጠቃሚዎች እና አጠቃቀም ባለፉት ሁለት አመታት በተለይ ከፖለቲካዊ የትዊተር ዘመቻዎች ጋር በተያያዘ ከፍተኛ እድገት እና ለውጥ አስተናግዷል። የትዊተር ዘመቻዎቹ በመንግስት ላይ ፖለቲካዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ጫናዎች የማሳደር “መንግስትን ኢላማ ያደረጉ ዘመቻዎች” እና “መንግስትን የሚወግኑ ዘመቻዎች” ናቸው። ዘመቻዎቹ ኢላማ ካደረጓቸው የዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ አካላት መካከል የሚዲያ ተቋማት እና ጋዜጠኞች ይገኙበታል። በዚህም ረገድ የሚዲያ አካላት የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ እውነታ የሚመለከቱበትን መነጽር በመቅረጽ እና የሚዘግቡትን አጀንዳ በማስያዝ በአጠቃላይ ትርክቶች (Narrative) ላይ ጫና ለመፍጠር በሁለቱም ጎራ በርካታ ቅስቀሳዎች ተካሂደዋል። በሚዲያ ሽፋን የሚገኝ የበላይነት የሚዲያዎቹን ትርክት መቆጣጠር ከመቻል ባሻገር የውሳኔ ሰጪ አካላት ጨምሮ የሚዲያ ታዳሚዎች ለጉዳዩ የሚይዙትን ምልከታ መቆጣጠር ያስችላል።
ሙሉ ሪፖርቱን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ

በኢትዮጵያ የትዊተር ተጠቃሚዎች እና አጠቃቀም ባለፉት ሁለት አመታት በተለይ ከፖለቲካዊ የትዊተር ዘመቻዎች ጋር በተያያዘ ከፍተኛ እድገት እና ለውጥ አስተናግዷል። የትዊተር ዘመቻዎቹ ...

የመሬት ባለቤትነት ውዝግቦች (territorial disputes) መልከ-ብዙ የሆነ አላማ ያነገቡ የፖለቲካ አካላት (entities) በተለያዩ አካባቢ እና ክልሎች ዙሪያ ባሉ መሬቶች ዙሪያ የይ...
17/05/2022

የመሬት ባለቤትነት ውዝግቦች (territorial disputes) መልከ-ብዙ የሆነ አላማ ያነገቡ የፖለቲካ አካላት (entities) በተለያዩ አካባቢ እና ክልሎች ዙሪያ ባሉ መሬቶች ዙሪያ የይገባኛል ወይም የባለቤትነት ጥያቄ እንዲሁም የድንበር ወሰን ውዝግቦች የሚያነሱባቸውን ግጭቶች ናቸው። የመሬት ውዝግቦች ለተለያዩ ጦርነቶች መቀስቀስ እና ሽብርተኝነት መነሳት ዋንኛ ምክንያቶች እንደሆኑ በተለያየ የታሪክ አጋጣሚዎች ላይ ታይቷል። የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያሳዩትም ለመሬት ውዝግቦች በዋነኝነት እንደ መንስኤ የሚታየው የተፈጥሮ ሀብት ባለቤትነት ጥያቄ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ባህል-ተኮር፣ ሀይማኖት-ተኮር እና ማንነት-ተኮር ምክንያቶች መንስኤ ሊሆኑ ይችላሉ። በአለም አቀፍ ደረጃ በአሁኑ ወቅት ከ150 በላይ መሬትን ማዕከል ያደረጉ ውዝግቦች (Territorial disputes) አሉ። አብዛኞቹ ውዝግቦች በአፍሪካ፣ ኤዢያ፣ ምስራቅ አውሮፓ እና በፓስፊክ አካባቢ ባሉ አካባቢዎች ያሉ ሲሆን ብዙ ጊዜ የመሬት ውዝግቦቹ በሀገራት መካከል የሚቀሰቀስ ነው። ለዚህም ኢትዮጵያ ከኤርትራ እና ከሱዳን ጋር የነበራትን እና ያላትን የመሬት ውዝግቦች እንደ ምሳሌ ማንሳት ይቸላል። ነገር ግን እንደ ኢትዮጵያ ባሉ የፌድራል አዋቀቀርን በሚከተሉ ሀገሮች የፌዴሬሽኑ አባላት እርስ በእርስ በሚወሳኑባቸው አካባቢዎች ላይ የመሬት ባለቤትነት ጥያቄዎችን ሲያነሱ ማየት ይችላል።
ሙሉ ሪፖርቱን ለማንበብ የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ ..

መግቢያ የመሬት ባለቤትነት ውዝግቦች (territorial disputes) መልከ-ብዙ የሆነ አላማ ያነገቡ የፖለቲካ አካላት (entities) በተለያዩ አካባቢ እና ክልሎች ዙሪያ ባሉ መሬቶች ዙሪያ የይገባኛል ወይም የባ.....

ኣብ መንጎ መንግስታትን መንግስታዊ ዘይኮኑ ኣካላትን ኣብ ዝተኻየዱ ኲናታት ሓበሬታ ማእኸል ዝገበሩ ቐጥታዊ ዘይኮኑ ናይ ኲናት መዋጋእቲ መንገድታት (Information warfare) ኣብ ዝተፈ...
16/05/2022

ኣብ መንጎ መንግስታትን መንግስታዊ ዘይኮኑ ኣካላትን ኣብ ዝተኻየዱ ኲናታት ሓበሬታ ማእኸል ዝገበሩ ቐጥታዊ ዘይኮኑ ናይ ኲናት መዋጋእቲ መንገድታት (Information warfare) ኣብ ዝተፈላለየ እዋናት ኣብ ዝነበሩ ብዓለም ደረጃ፣ ኣህጉራውን ሃገራውን ኲናታት ኣብ ኣገልግሎት ክውዕሉ ብተደጋጋሚ ተራእዩ ኢዩ። ቀንዲ ሽቶ ናይ ኲናት ሓበሬታ ነቲ ኣብ ኲናት ዘሎ ሓሳባትን ዋሕዚ ሓበሬታታትን (Information space) ብዝተፈላለየ መንገዲ ብምቁፅፃር ኣብ ልዕሊ ተፃባእቲ ሓይልታት ናይ ሓበሬታ ፀብለልታ ምርካብ እዩ ። እዚ ንምትግባር ዘገልግሉ ዝተፈላለዩ ሜላታትን ናውትን ኣብ ጥቕሚ ብምውዓል ዝፍፀም እዩ ።ብፍላይ ናይ ማሕበራዊ መራኸቢ ምስፍሕፋሕ ተኸቲሉ እዞም መራኸብቲ መድረኻት ከም ዋና መሳርሒ ኲናት ሓበሬታ ኾይኖም እዮም። ብ 2013 ዓ.ም ኣብ ሃገርና ኣብ ሰሜን ኢትዮጵያ ኣብ ዝነበረ ኲናት እውን ብተመሳሳሊ ናይ ኲናት ሓበሬታ ሓደ ናይቲ ኲናት ኣካል ኮይኑ ኣብ ጥቕሚ ክውዕል ተራእዩ እዮ። ብፍላይ ኣብ ማሕበራዊ ሚዲያታት ዝዝርግሑ ናይ ሓሶት ሓበሬታታት ብዝለዓለ ደረጃ ዝወሰኹሉ እዋን ነይሩ። ብተወሳኺ ዝተፈላለዩ ኣሉታዊ ትሕዝቶ ዘለዎም ዛንታታትን(narration) ሓበሬታታትን ኣብ ማሕበራዊ መራኸቢ ብምዝርጋሕ ኣብቲ ኲናት ዝተሳተፉ ኣካላት ናይ ባዕሎም ወገናት ድጋፍ ንምርካብ ፃዕርታት እንትገብሩ ምስትውዓል ተኻኢሉ እዩ።

ኣብ መንጎ መንግስታትን መንግስታዊ ዘይኮኑ ኣካላትን ኣብ ዝተኻየዱ ኲናታት ሓበሬታ ማእኸል ዝገበሩ ቐጥታዊ ዘይኮኑ ናይ ኲናት መዋጋእቲ መንገድታት (Information warfare) ኣብ ዝተፈላለየ እዋናት...

Odeeffannoowwan Sobaa Miidiyaalee Adda Addaa Wabeeffachuun Tamsa’anMiidiyaalee hawaasaa Itiyoophiyaa keessatti odeeffann...
06/05/2022

Odeeffannoowwan Sobaa Miidiyaalee Adda Addaa Wabeeffachuun Tamsa’an

Miidiyaalee hawaasaa Itiyoophiyaa keessatti odeeffannoowwan qabiyyee sobaa of keessaa qaban amanamummaa issaanii dabaluun tamsaasuf maxxansoota miidiyaalee fi angawoota bebbeekamoo akka maddaa odeeffannootti ka’aniin yokaan ibsaniin kan guutame dha. Namoonni baay’een odeeffannoowwan miidiyaa bebbeekamoon barreeffaman haala salphaatti waan amananiif gabaasa miidiyaalee kanaa akka wabiitti fudhachuuf gara fuula miidiyaalee kanaa waan deemaniif miidhaan kara kanaan uumamu akka salphaatti kan ilaalamu miti. Xinxalli kuniis tamsaasi fi dhibaa barreeffamoonni akka kanaa miidiyaalee hawaasaa Itiyoophiyaa irratti uumaa jiran irratti kan xiyyeeffate dha. Qo’annoo kanaaf odeeffannoowwan qabiyyee sobaa of keesaa qaban 332, akkaawuntoota feesbuukii 237 ta’aniin ji’oota kudhan keessatti maxxanfaman akka eddattootti kan fudhataman yoo ta’u, 95% kan ta’an odeeffannoowwan qabiyyee sobaa of keessaa qaban, 10% kan ta,an ammoo odeeffannoowwan qabiyyee jibbaa of keessaa qaban, akkasumas kan hafan 6% kan ta’an waliiti bu’insi fi jeequmsi akka ummamu barreeffamoota kakaasan kan of keessaa qabanidha.

Miidiyaalee hawaasaa Itiyoophiyaa keessatti odeeffannoowwan qabiyyee sobaa of keessaa qaban amanamummaa issaanii dabaluun tamsaasuf maxxansoota miidiyaalee fi angawoota bebbeekamoo akka maddaa odeeffannootti ka’aniin yokaan ibsaniin kan guutame dha. Namoonni baay’een odeeffannoowwan miidiyaa beb...

በተደጋጋሚ አሉታዊ መረጃዎችን የሚያሳራጩ አካውንቶችበኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ላይ በስፋት አሉታዊ መረጃዎችን የሚያሰራጩ አካውንቶች በብዛት ያሉ ሲሆን እነዚህ አካውንቶች ያለምንም ደ...
06/05/2022

በተደጋጋሚ አሉታዊ መረጃዎችን የሚያሳራጩ አካውንቶች

በኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ላይ በስፋት አሉታዊ መረጃዎችን የሚያሰራጩ አካውንቶች በብዛት ያሉ ሲሆን እነዚህ አካውንቶች ያለምንም ደንብ እና መመሪያ የማህበራዊ ሚዲያውን ለተለያዩ አሉታዊ አላማዎች ሲጠቀሙበት በተደጋጋሚ ተስተውሏል። እነዚህ አካውንቶች የማህበራዊ ሚዲያ መተግበሪያውን ደንቦች በየጊዜው ሲጥሱ የሚታይ ቢሆንም ድርጅቱ በቀጣይነት እርምጃ ሲወስድ አይታይም። በዚህ ጥናትም ላይ ከእነዚህ አካውንቶች ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ አሉታዊ መረጃን የሚያሰራጩ 100 አካውንቶችን በመምረጥ ያላቸውን ተደራሽነት፣ ተሳትፎ እንዲሁም አጠቃላይ ባህሪ እና በሚያሰራጩት አሉታዊ መረጃ ላይ ይዘታዊ ትንተና ለመስራት ተሞክሯል።

በተደጋጋሚ አሉታዊ መረጃን ያሰራጩትን 100 አካውንቶች ከሚያሰራጩት አሉታዊ መረጃ ይዘት አንፃር ስናያቸው በአጠቃላይ 2461 አሳሳች መረጃዎችን ያሰራጩ ሲሆን ይህም እነዚህ አካውንቶች ከ2019 እስከ 2021 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ከተሰበሰበው መረጃ ውስጥ 25 በመቶ ያህል የሚሆነውን መረጃ አሰራጭተዋል ማለት ነው። በአጠቃላይ እነዚህ አካውንቶች 17 እና ከዚያ በላይ ጊዜ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ አሳሳች መረጃዎችን አሰራጭተዋል። አካውንቶች ካሰራጩት 2461 አሳሳች መረጃዎች ውስጥ 1723 ሀሰተኛ መረጃዎች፣ 431 ግጭት ቀስቃሽ ይዘት ያላቸው እና 307 የጥላቻ ንግግር ይዘት ያላቸው መረጃዎችን ሆነው ተገኘተዋል።

መግቢያ ፌስቡክ ወይም ሜታ በ2021 ሶስተኛው ሩብ አመት ውስጥ ብቻ የማህበራዊ ሚዲያውን የማህበረሰብ ደንብና ፖሊሲን የጣሱ ከ1.8 ቢሊዮን በላይ የሆኑ አካውንቶችን ከመተግበሪያው ላይ እንደአ...

በኢትዮጵያ ማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ተጠቃሚዎች ዘንድ ፌስቡክ የአንበሳውን ድርሻ ይዞ የሚገኝ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የትዊተር ተጠቃሚዎች ቁጥር ከፍተኛ እድገት እያሳየ ይገኛል። ትዊትር ...
27/04/2022

በኢትዮጵያ ማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ተጠቃሚዎች ዘንድ ፌስቡክ የአንበሳውን ድርሻ ይዞ የሚገኝ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የትዊተር ተጠቃሚዎች ቁጥር ከፍተኛ እድገት እያሳየ ይገኛል። ትዊትር አጀንዳ እና ሀሳብን በተደራጀ መንገድ እና ለተፈለገ አካል ተደራሽ የማድረግ አገልግሎቱ በተለይ የተቀናጁ ፖለቲካዊ ዘመቻዎች በሚያደርጉ ተጠቃሚዎች ዘንድ ተመራጭ እየሆነ መጥቷል። በዚህም ረገድ በኢትዮጵያ የትዊተር ተጠቃሚዎች እና አቃቀም ከሀገሪቱ የፖለቲካ ሁናቴ ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት የሚስተዋልበት ሲሆን በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ትዊተር በቀደምትነት በመንግስት ላይ አሉታዊ ጫና ለመፍጠር እና መንግስትን በመደገፍ ለሚካሄዱ የፖለቲካዊ ዘመቻዎች መድረክ ሆኖ ይገኛል። ሙሉ ሪፖርቱን ለማንበብ ሊንኩን ይከተሉ

በኢትዮጵያ ማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ተጠቃሚዎች ዘንድ ፌስቡክ የአንበሳውን ድርሻ ይዞ የሚገኝ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የትዊተር ተጠቃሚዎች ቁጥር ከፍተኛ እድገት እያሳየ ይገኛል።...

የትጥቅ ትግል (Armed struggles or insurgency) እንደ አንድ የፖለቲካ ስልጣን ማግኛ ወይም የፖለቲካ ግብ ማሳኪያ በመጠቀም የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በተለያዩ የአለም ሀገራት በ...
20/04/2022

የትጥቅ ትግል (Armed struggles or insurgency) እንደ አንድ የፖለቲካ ስልጣን ማግኛ ወይም የፖለቲካ ግብ ማሳኪያ በመጠቀም የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በተለያዩ የአለም ሀገራት በተደጋጋሚ ሲፈጠሩ ይታያል። የትጥቅ ትግል በተፈጠሮው ቀውስ-ፈጣሪ (Disruptive) እና ኢ-ደንባዊ (Irregular) ጦርነት ሲሆን ከቀጥተኛ ጦርነት በተለየ ከማዕከላዊ መንግስት ጋር ከተለያዩ ገጠራማ ወይም ራቅ ካሉ ቦታዎች በመነሳት በአነስተኛ የሰው ሀይል የሚደረጉ የሽምቅ ውጊያዎችን (Guerrilla warfare) በዋነኝነት ያካታትል። የትጥቅ ትግል ብዙ መንስኤዎች ሊኖሩት ይችላል፤ ነገር ግን የመጨረሻ ግቡ በሀይል የፖለቲካ ስልጣን መያዝ ነው። ከዚህ በፊት በአለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴዎች መንስኤ በዋነኝነት ስናያቸው ኢኮኖሚያዊ (የኢኮኖሚ ምንጮችን መቆጣጠር)፤ ራስን በራስ ለማስተዳደር ወይም ሀገር ለመሆን (self-determination/secessionist)፤ ርዕዮተ አለማዊ (Ideological) እና ማንነት (Identity) መሠረት ያደረጉ ናቸው።
ሙሉ ሪፖርቱን ለማንበብ ሊንኩን ይከተሉ

መግቢያ የትጥቅ ትግል (Armed struggles or insurgency) እንደ አንድ የፖለቲካ ስልጣን ማግኛ ወይም የፖለቲካ ግብ ማሳኪያ በመጠቀም የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በተለያዩ የአለም ሀገራት በተደጋጋሚ ሲፈጠ...

Persistent set of false narratives that act like a template has been fabricated over the years in the social media lands...
13/04/2022

Persistent set of false narratives that act like a template has been fabricated over the years in the social media landscape here. These templates, usually associated with a single umbrella wording/label, has enabled offenders to adjust the narrative as they see fit and inject them into the information environment to distort facts and sow division as a result.

Over the years, Ethiopian elites has not been able to agree about the country’s political history, and even future. This disagreement has manifested itself in the country’s social media space, where it has provided an opportunity for a disinformation and propaganda ecosystem to actively create division between various political elites and people with differing ethnic background. And one target of this disinformation campaign on the social media has been the Amhara political elite.
Click on the link to read the full report.

Persistent set of false narratives that act like a template has been fabricated over the years in the social media landscape here. These templates, usually associated with a single umbrella wording/label, has enabled offenders to adjust the narrative as they see fit and inject them into the informat...

የሀሰተኛ መረጃዎች መፈጠር፣ መሰራጨት እና መስፋፋት በማህበረሰቡ ዘነድ የመረጃ ክፈተቶች የሚፈጥሩ አዳዲስ ክስተቶች እና ሰበር ዜናዎች በሚኖሩባቸው ጊዜያት በስፋት ይጨምራል። በተለይም ክስተቶ...
13/04/2022

የሀሰተኛ መረጃዎች መፈጠር፣ መሰራጨት እና መስፋፋት በማህበረሰቡ ዘነድ የመረጃ ክፈተቶች የሚፈጥሩ አዳዲስ ክስተቶች እና ሰበር ዜናዎች በሚኖሩባቸው ጊዜያት በስፋት ይጨምራል። በተለይም ክስተቶቹ ፖለቲካዊ አንድምታ እና ትስስር ያላቸው በሚሆኑባቸው አጋጣሚዎች የሚፈጠሩት ሀሰተኛ መረጃዎች በሴራዊ ትርክቶች እና ማብራሪያዎች የሚሞሉ ከመሆናቸው አንጻር የህብረተሰቡን ምክንያታዊ አስተሳሰብ የመገዳደር ተጽዕኖዋቸው ከፍተኛ ይሆናል። በ2013 ዓ.ም የበጋ ወራት በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች በሚገኙ ደኖች ላይ ተፈጥረው የነበሩ የሰደድ እሳቶች እንደ አንድ ክስተት ለበርከታ ሴራ ላይ ለተመሰረቱ ሀሰተኛ መረጃዎች መፈጠር ምክንያት ሆነው አልፈዋል።
ሙሉን ሪፓርት ለማንበብ ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ

የሀሰተኛ መረጃዎች መፈጠር፣ መሰራጨት እና መስፋፋት በማህበረሰቡ ዘነድ የመረጃ ክፈተቶች የሚፈጥሩ አዳዲስ ክስተቶች እና ሰበር ዜናዎች በሚኖሩባቸው ጊዜያት በስፋት ይጨምራል። በተለ....

Dhalattoonni saba Oromoo fi Amaaraa akka walitti bu’aniif duula yookiin sochiilee gaggeeffamaa turanMidiyaaleen hawassa ...
06/04/2022

Dhalattoonni saba Oromoo fi Amaaraa akka walitti bu’aniif duula yookiin sochiilee gaggeeffamaa turan

Midiyaaleen hawassa kannen akkaa feesbuuki hatattaman dhaqabamuu, dangaa mallessa ta’uu fi fayyadamtootaf haguuga kennaaniiraan kan ka’e, yaddooleen hawaasa kessatti jibbaa fi walitti bu’insa uuman, daraan akka babal’atanifi yaaddoo tokko malee akka faca’an isaan dandeessissera. Namootni bakka garagaraatti argamaniifi yaddoota walfakkaataa qaban fageenyii walliraa qaban osoo isaan hin dhorkiin ololaa jibbaaf waliiti bu’insa uuman wixinuun midiyaalee hawassa kaneen irratti facaasanii yaada fayyadamtoota midiyalee kanaa irratti dhibaa uumun gara jibbaafi walliti bu’insatti yeroo galchan ni mul’ata.

Midiyaaleen hawassa kannen akkaa feesbuuki hatattaman dhaqabamuu, dangaa mallessa ta’uu fi fayyadamtootaf haguuga kennaaniiraan kan ka’e, yaddooleen hawaasa kessatti jibbaa fi walitti bu’insa uuman, daraan akka babal’atanifi yaaddoo tokko malee akka faca’an isaan dandeessissera. Namootni b...

በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ ስለታየው የጥላቻ ንግግር ስርጭት እና መገለጫዎቹበኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ውስጥ ሀሰተኛ፣ ግጭት ቀስቃሽ እንዲሁ...
04/04/2022

በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ ስለታየው የጥላቻ ንግግር ስርጭት እና መገለጫዎቹ

በኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ምህዳር ውስጥ ሀሰተኛ፣ ግጭት ቀስቃሽ እንዲሁም የጥላቻ ይዘት ያላቸው አሉታዊ መረጃዎች በከፍተኛ ደረጃ እንደሚሰራጩ የተለያዩ ሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ተቋማት በተለያየ ጊዜ ይጠቁማሉ። በተለይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያለው የአሉታዊ መረጃዎች ስርጭት በየአመቱ በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መጥቷል። በሰሜኑ ኢትዮጵያ ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኋላ ይህ አዝማሚያ ከሌላው ጊዜ በተለየ ጨምሮ ታይቷል። በተለይም የጥላቻ መልዕክቶች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ያለምንም ገደብ ሲሰራጩ ተስተውሏል።የትግራይ ጦርነቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ የነበረውን የጥላቻ ይዘት ያላቸው መረጃዎች ስርጭት ጦርነቱ ከመቀሰቅሱ በፊት ከነበረው ስርጭት ጋር ስናነፃፅረው ፈጣን የሆነ አዝማሚያ (Exponential trend) አሳይቷል።

https://factifyethiopia.com/?p=998

በመንግስታት እና መንግስት ባልሆኑ አካላት መካከል በሚደረጉ ጦርነቶች ላይ መረጃን ማዕከል ያደረጉ ቀጥተኛ ያልሆኑ የጦርነት መዋጊያ መንገዶች (Information warfare) በተለያየ ወቅት በተነሱ አለ...

Disinformation Campaign and Conspiracy Theory targeting the ‘Oromuma’ Political NarrativeConspiracy theories exist in ev...
04/04/2022

Disinformation Campaign and Conspiracy Theory targeting the ‘Oromuma’ Political Narrative

Conspiracy theories exist in every political space. They involve consistent political narrative that aims to affect influence on people. Due to this, conspiracy theories can be easily weaponized by disinformation campaigns.

One consistent political narrative (conspiracy theory) in the social media platform here in Ethiopia is a narrative that posits various Oromo political influencers in the ruling party ODP/ Prosperity party, including and mainly, the Prime Minister, as having a hidden agenda of setting up an Oromo dominated Ethiopian politics ‘Oroomumaa’ at the cost of the country, and in particular the Amhara people and the regional State. And to some extent, there is flip side to this narrative in which there’s a widespread claim that the PM and some ODP members are working with Amhara Prosperity Party and other Amhara nationalist party to bring back the old unitary type of state machinery.

As conspiracy theory is a belief that one set of groups is aiming to harm the interest of another group, when the Ataye clashes erupted in March and April of last year, these consistent narratives escalated in the social media platform as weaponized tool of a disinformation campaign.

https://factifyethiopia.com/?p=985

Conspiracy theories exist in every political space. They involve consistent political narrative that aims to affect influence on people. Due to this, conspiracy theories can be easily weaponized by disinformation campaigns.   One consistent political narrative (conspiracy theory) in the social medi...

የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የተጠቃሚዎችን የአጠቃቀም ባህሪን ለመረዳት ተደራሽነት እና ተሳትፎን እንደ ዋና የትንታኔ መለኪያ ይጠቀማሉ። ተደራሽነት ሲባል አንድ ተጠቃሚ የለጠፈውን መረ...
30/03/2022

የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የተጠቃሚዎችን የአጠቃቀም ባህሪን ለመረዳት ተደራሽነት እና ተሳትፎን እንደ ዋና የትንታኔ መለኪያ ይጠቀማሉ። ተደራሽነት ሲባል አንድ ተጠቃሚ የለጠፈውን መረጃ ምን ያህል ልዩ የሆነ የሱ ጓደኛ፣ ተከታይ ወይም ወዳጅ የሆነ ተጠቃሚ ጋር ደርሷል (Organic reach) ወይም አይተውታል የሚለውን ቁጥር የሚጠቁን የትንታኔ መለኪያ ነው። አብዛኛው የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚ አይቶ ወይም አንብቦ አላፊ (window shopper) ስለሆነ እንዲሁ በአጠቃላይ ሊፈጥሩ ይችላሉ የሚባለውን አንደምታን (Impression) ከመገመት አንፃር የተደራሽነት ቁጥሩ የሚጠቁመን ወይም የሚያሳያን አዝማሚያ ይኖራል።
ሙሉን ሪፓርት ለማንበብ ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ https://factifyethiopia.com/?p=989

የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የተጠቃሚዎችን የአጠቃቀም ባህሪን ለመረዳት ተደራሽነት እና ተሳትፎን እንደ ዋና የትንታኔ መለኪያ ይጠቀማሉ። ተደራሽነት ሲባል አንድ ተጠቃሚ የለ....

የሃሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች ተደራሽነት እንዲሁም ተአማኒነት በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም። በተለያዩ የሃሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች ላይ ለመረዳት እንደተቻለው በዘመቻዎቹ ኢላማ ከተደረገው የህብረተሰ...
22/03/2022

የሃሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች ተደራሽነት እንዲሁም ተአማኒነት በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም። በተለያዩ የሃሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች ላይ ለመረዳት እንደተቻለው በዘመቻዎቹ ኢላማ ከተደረገው የህብረተሰብ ክፍል ውስጥ ቀላል የማይባል ቁጥር ያለው ሰው የሚደርሰውን ሃሳተኛ መረጃ በቀላሉ አምኖ የመቀበል እድሉ ከፍ ያለ ነው። የተዓማኒ መረጃ ምንጮች ማነስ እንዲሁም ወቅታዊ ብዥታን የሚያጠራ መረጃን ለህብረተሰቡ ተደራሽ አለማድረግ ይበልጥ ችግሩን ያባባሰው ሲሆን ይህም ማህበረሰቡ የሚደርሱትን አሉታዊ መረጃዎች በቀላሉ አምኖ እንዲቀበል እያደረገው ይገኛል። ይህ ሪፖርት በተለያዩ ጊዜያት በኦሮሚኛ ቋንቋ በፌስቡክ ምህዳሩ የተለያዩ ምክንያቶችን በማቅረብ “በአሁን ሰዓት ሃገሪቱን እየመራ ያለው መንግስት የፌደራል ስርዓቱን ለማጥፋት እና በአሃዳዊ ወይም የነፍጠኛ ስርዓት ለመተካት እየሰራ ነው” በሚል ሃሳብ ዙርያ የተሰራጩ ሃሰተኛ መረጃዎችን በተመለከተ ጥቅል ምልከታዎችን ያቀርባል። ሙሉ ሪፖርቱን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ። https://factifyethiopia.com/?p=971

የሃሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች ተደራሽነት እንዲሁም ተአማኒነት በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም። በተለያዩ የሃሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች ላይ ለመረዳት እንደተቻለው በዘመቻዎቹ ኢላማ ከተደረገ.....

በተደጋጋሚ ግጭት በሚፈጠርባቸው አካባቢዎች ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ስነ-ልቦናዊ ቀውሶች በማባባስ የማህበራዊ ሚዲያው ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን ጥናቶች ይጠቁማሉ። በተለይም በማህበ...
22/03/2022

በተደጋጋሚ ግጭት በሚፈጠርባቸው አካባቢዎች ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ስነ-ልቦናዊ ቀውሶች በማባባስ የማህበራዊ ሚዲያው ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን ጥናቶች ይጠቁማሉ። በተለይም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተመሳሳይ ፋላጎት፣ እሴት እና ባህል ባላቸው ተጠቃሚዎች መካከል በሚፈጠር መስተጋብር ምክንያት የሚመሰረቱ ዝግ የመረጃ መድረኮች (Echo-chamber) አማካኝነት በጉዳዮች ወይም በክስተቶች ላይ ፍጹም የሚቃረን የመረጃ ትርጓሜ እና አረዳድ በመፍጠር ለልዩነት እና ግጭት በሰፊው አስተዋጽኦ ያደርጋሉ። በተለያየ ወቅት በሀገራችን የሚከሰቱ የተለያዩ ክስተቶችን ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ የአሉታዊ መረጃዎች ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ ይጨምራል። ከዚሁ ጋር ተያይዞም በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች መካከል ባለው ኢኮ-ቻምበሮች አመካኝነት በተመሳሳይ ጉዳይ ሁለት አይነት የተለያዩ ሲልም ፍጹም የሚቃረኑ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያው ላይ ሲሰራጩ ይስተዋላል። በተለይም በአማራ፣ ኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ክልሎች ውስጥ በተለያየ ወቅት የሚከሰቱ የተለያዩ ግጭትና ጥቃቶችን ተከትሎ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አውታሮች ላይ በሚኖረው የመረጃ ፍሰት ላይ ይህ እውነታ ጎልቶ ይወጣል።
ሙሉ ሪፖርቱን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ። https://factifyethiopia.com/?p=974

በተደጋጋሚ ግጭት በሚፈጠርባቸው አካባቢዎች ሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ስነ-ልቦናዊ ቀውሶች በማባባስ የማህበራዊ ሚዲያው ከፍተኛ ሚና ያለው መሆኑን ጥናቶች ይጠቁማሉ። በተለ....

Damaging Disinformation targeting the National Peace DialogueSocial media can be used as a tool to undermine peace talks...
16/03/2022

Damaging Disinformation targeting the National Peace Dialogue

Social media can be used as a tool to undermine peace talks. It has happened elsewhere, and now it has happened here as well. In an effort to put an end to the various political problems of the country, the Ethiopia government has initiated an effort to start talks. Nevertheless, various fake contents have already targeted it with the view of undermining the initiative before it even get started.

Since the issue of peace and national dialogue first hit the social media space and the country’s political sphere over four months ago, there have been various fake contents that were spread. This report has garnered 116 fake and violence inciting contents to assess the damaging disinformation that was peddled with the aim of undermining the process, and the various reactions it elicited in a time-theme series analysis.

To Read the Full article click the link https://factifyethiopia.com/?p=955

Social media can be used as a tool to undermine peace talks. It has happened elsewhere, and now it has happened here as well. In an effort to put an end to the various political problems of the country, the Ethiopia government has initiated an effort to start talks. Nevertheless, various fake conten...

በፌስቡክ ከፍተኛ ተሳትፎ ያገኙ በአፋን ኦሮሞ የተሰራጩ የአሉታዊ መረጃ (Disinformation) መልዕክቶችየሀሰተኛ መረጃ፣ የግጭት ቀስቃሽ እና የጥላቻ ንግግር (አሉታዊ መረጃ | Disinf...
16/03/2022

በፌስቡክ ከፍተኛ ተሳትፎ ያገኙ በአፋን ኦሮሞ የተሰራጩ የአሉታዊ መረጃ (Disinformation) መልዕክቶች

የሀሰተኛ መረጃ፣ የግጭት ቀስቃሽ እና የጥላቻ ንግግር (አሉታዊ መረጃ | Disinformation) ጹሁፎች ከትክክለኛ ዜናዎች እና መደበኛ ጹሁፎች በተለየ ፍጥነት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እንደሚሰራጩ ጥናቶች ያሳያሉ። ፌስቡክ ልጥፎች ለተጠቃሚዎች የሚደርሱበትን መጠን “ትርጉም ያለው ማህበራዊ መስተጋብር (Meaningful Social Interactions – MSI)” የሚለውን ልጥፎች ለሚያገኙት ሼር እና ኮሜንት ቅድሚያ የሚሰጥ ተሳትፎ ላይ የተመሰረተ ቀመር (Algorithm) ይጠቀማል። በፌስቡክ ላይ ተጠቃሚን ስሜታዊ የሚያደርጉ የአሉታዊ መረጃ ልጥፎች ከመደበኛ ልጥፎች በተለየ ሼር እና ኮሜንት እንደሚያገኙ ጥናቶች የሚያሳዩ ሲሆን ይህም ከፌስቡክ አሰራር ጋር ተደማምሮ ተጠቃሚን ስሜታዊ በማድርግ ሼርና ኮሜንት ማግኘት የሚችሉ አሉታዊ መረጃ ልጥፎች ለብዙ ተጠቃሚ መድረስ እየቻሉ ይገኛሉ።

በዚህም ሪፖርት ባለፉት ሁለት ዓመታት (ከእ.አ.አ 2020 ጀምሮ) በ506 የፌስቡክ አካውንቶች በተሰራጩ 2ሺህ የኦሮምኛ ቋንቋ አሉታዊ መረጃ ልጥፎች (Disinformation Campaign) ላይ ጥናት ተደርጓል። ልጥፎቹ ከ924 ሺህ በላይ (በአማካይ 461) የፌስቡክ ተጠቃሚ በሼር፣ ኮሜንት እና ሪአክሽን የተሳተፈባቸው ሲሆን ተሳትፎው በእነዚሁ አካውንቶች የተሰራጩ መደበኛ የፌስቡክ ልጥፎች ካገኙት ተሳትፎ በሁለት ሶስተኛ የሚበልጥ ነው።

ሙሉ ሪፖርቱን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ። https://factifyethiopia.com/?p=959

የሀሰተኛ መረጃ፣ የግጭት ቀስቃሽ እና የጥላቻ ንግግር (አሉታዊ መረጃ | Disinformation) ጹሁፎች ከትክክለኛ ዜናዎች እና መደበኛ ጹሁፎች በተለየ ፍጥነት በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እንደሚሰራጩ .....

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 23:00
Tuesday 08:30 - 23:00
Wednesday 08:30 - 23:00
Thursday 08:30 - 23:00
Friday 08:30 - 23:00
Saturday 08:30 - 23:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Factify Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share