ብሩክ ፈለቀ በድሬዳዋ የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ብሩክ ፈለቀ በድሬዳዋ የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

ብሩክ ፈለቀ በድሬዳዋ የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እለታዊና ትኩስ መረጃዎችን ያግኙ

06/09/2023

በጳጉሜን ቀናት የተሰየሙት መሠረታዊ ሃሳቦች የድሬዳዋ መገለጫ እና መትጊያ ሆነው ያገለግላሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር ገለጹ።
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
በአስተዳደሩ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የሚደረጉ ጥረቶች በጳጉሜን ቀናት ለማጠናከር በተደራጀ አግባብ በትኩረት እንደሚሰራም ክቡር ከንቲባው አክለዋል።
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
ክቡር ከንቲባው ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ፤ በኢትዮጵያ ደረጃ በጳጉሜን ቀናት የተሰየሙት መሠረታዊ ሃሳቦች የድሬዳዋ መገለጫ እና መትጊያ በመሆን ያገለግላሉ ብለዋል።
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
በአገልግሎት፣ በመስዋዕትነት፣ በበጎነት፣ በአምራችነት፣ በትውልድ እና በአብሮነት የተሰየሙት የዘንድሮ የጳጉሜን ቀናት በድሬዳዋ የህዝብን መሠረታዊ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በተቀናጀ መንገድ ለመመለስ የሚደረጉ ጥረቶችን ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራበት ተናግረዋል።

ዛሬ በሁሉም ተቋማት የተሻለና የተቀናጀ የአገልጋይነት ቀን ተደርጎ ለህዝብ ነፃ አገልግሎቶች እንደሚሰጡ አመልክተው፤ በትራንስፖርት ዘርፍ ለዜጎች ነፃ አገልግሎት ይሰጣል ብለዋል።

ለሀገር ሉአላዊነትና ለዜጎች ነፃነት ታላቅ መስዋዕትነት የከፈሉትን ጨምሮ በየመስኩ ታላቅ ስራ ያከናወኑ ሰዎችን በማስታወስ ይከበራል ሲሉ ገልጸዋል።

የበጎነት ቀን በጎነት በማህበረሰቡ ውስጥ እንዲሰርፅ በሚያግዝ መንገድ ይከበራል ብለዋል።

እንደ ክቡር ከንቲባ ከድር ገለፃ፤ ድሬዳዋ የንግድና የኢንዱስትሪ መናኸሪያ፤ የነፃ የንግድ ቀጣና መሆኗን በትክክል በሚያንፀባርቁ ሁነቶች የአምራችነት ቀን እንደሚከበርም ገልጸዋል።

በተለይ የአብሮነት ቀን የድሬዳዋ ልዩ ሃብት የሆነው የአብሮነትና የአንድነት መገለጫን በትውልድ ውስጥ እንዲሰርጽ በሚያስችሉ ልዩ ልዩ ክዋኔዎች እንደሚከበር አብራርተዋል።
Dire Dawa Mayor Office & Management

06/09/2023
06/09/2023
ተቋማት ወጥነት ያለውና የተናበበ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ሊኖራቸው እንደሚገባ ተገለፀ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ለሴክተርና ለወረዳዎች እንዲሁም ከፌደራል ተቋ...
24/08/2023

ተቋማት ወጥነት ያለውና የተናበበ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ሊኖራቸው እንደሚገባ ተገለፀ

የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ለሴክተርና ለወረዳዎች እንዲሁም ከፌደራል ተቋማት ለተውጣጡ የኮሙዩኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ባለድርሻ አካላት በኮሙዩኒኬሽን ፅንሰ ሀሳብና አተገባበር እና በሚዲያ አጠቃቀም ላይ የሚያተኩር የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ።

በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ ተቋማት ወጥነት ያለውና የተናበበ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ሊኖራቸው እንደሚገባ ተናግረዋል።

በተመሳሳይም እቅዶች ሲታቀዱ የእናት መስሪያ ቤት እቅድ መሰረት በማድረግ ሊሆን እንደሚገባና ይሄም ደግሞ ወጥነት ያለው ስራን ለመስራት እንደሚያስችል ጠቁመዋል።

የኮሙዩኒኬሽንን ስራ በተቀላጠፈ መልኩ ለማከናወን ብሎም ከተደራሽነትና ከፍጥነት አንፃር አሁን ላይ ተቋማት ቲክቶክን በመጠቀም ስራዎቻቸውን ለማህበረሰቡ ማድረስ እንደሚገባቸውም አቶ ብሩክ ገልፀዋል።

በመድረኩ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የፕላንና ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ ዳንኤል ሲሳይ የተቋሙ የ2015 ዓ.ም ሪፖርትና የ2016 ዓ.ም እቅድ የቀረበ ሲሆን፤ የለውጥ ስራዎችና የመልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በሆኑት መስከረም ተ/ኃይማኖት ደግሞ የመልካም አስተዳደር እቅድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።

ስልጠናው እስከ ነገ የሚቀጥል ሲሆን በሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ላይ፣ የኮምኒኬሽን ፅንሰ ሀሳብና አተገባበር ላይ እንዲሁም በኮሙዩኒኬሽንና ግሎባላይዜሽን ዙሪያ ስልጠናዎች ይሰጣሉ።

በኤደን ሳሙኤል
ፎቶ፦ሰላም አበበ

ተጠርጣሪው ተያዘ   |  በወይዘሪት ፀጋ በላቸው የጠለፋ ወንጀል ተጠርጥሮ በፖሊስ ሲፈለግ የነበረው ተጠርጣሪ የጸጥታ ሀይሉ ባደረገው ክትትል በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10፡40 ሰዓት ላይ  በሀገረ...
07/06/2023

ተጠርጣሪው ተያዘ

| በወይዘሪት ፀጋ በላቸው የጠለፋ ወንጀል ተጠርጥሮ በፖሊስ ሲፈለግ የነበረው ተጠርጣሪ የጸጥታ ሀይሉ ባደረገው ክትትል በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10፡40 ሰዓት ላይ በሀገረ ሰላም ወረዳ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቲዮስ በወይዘሪት ጸጋ በላቸው የጠለፋ ወንጀል ተጠርጥሮ በተደረገው ከፍተኛ ክትትል ተበዳይዋን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን ቀደም ሲል ማስጣል መቻሉን አስታውሰዋል።

ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ከፀጥታ ሀይል ለማምለጥ ሲል በሻፋሞ ጫካ ለጫካ ሲዘዋወር እንደነበረ አስታውሰው ማንም ከህግ በላይ አይደለምና የፀጥታ ሀይሉ በተቀናጀ መንገድ ከበባ ውስጥ በማስገባት ክትትል ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል።

ተጠርጣሪው አከባቢ በመቀየር ፍለጋውን አስቸጋሪ ቢያደርግም ማህበረሰቡን በማሳተፍ በተደረገው አሰሳ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ላይ በሀገረ ሰላም ወረዳ በቁጥጥር ስር መዋሉን አረጋግጠዋል።

ተጠርጣሪው ግለሰብ ወንጀሉን ለመፈጸም ሲጠቀምባቸው ከነበሩ አንድ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያና ሽጉጥ ጋር መያዙንም አክለዋል።

ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል መላው የክልሉ የጸጥታ ሀይል የብሄራዊ መረጃ ደህንነትና ፌዴራል ፖሊስን ጨምሮ የተሳተፉበት መሆኑን ገልፀጸው ላበረከቱት ትጋት ምስጋና አቅርበዋል።

በቀጣይ በደሉ የደረሰባትን ወይዘሪት ፀጋ በላቸውን በፍትህ ስርዓቱ የመካስና ተጠርጣሪው እና ግብረአበሮቹ ተገቢውን የህግ ቅጣት እንዲያገኙ የማድረጉን ስራ ክልሉ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ወይዘሪት ፀጋ በላቸው ግንቦት 15 ቀን 2015 ዓ.ም ከስራ ቦታዋ ወደ ቤት ስታቀና መጠለፏ ይታወሳል።

21/04/2023

#ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ
እንኳን ለ 1444 ኢድ አል ፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፤ የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልቤ እመኛለሁ።🙏🙏🙏🙏🙏🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በዓሉን ስናከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማሰብ ካለን በማካፈል፤ ፍፁም በሆነ መተሳሰብ እንድናሳልፍ በአክብሮት እጠይቃለው፡፡
የአስተዳደሩ ነዋሪዎች በሙሉ በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁላችንም የዜግነት ግዴታችንን እንወጣ ።

በመጨረሻም በዓሉን ስናከብር በምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ሁሉ ቅድመ ጥንቃቄ እንዳይለየን አካባቢያችሁን በንቃት እንድንጠብቅ አደራ እላለሁ፡፡

Hordoftoota amanta Islaamaa hundaa baga ayyaana Eid Alfexir 1444 tiin isin gahe.


Ciid mubarak kulo camo ita belqeyr dhaman umada muslimita mel kasto dunida ka jogtan cid wngsn

መልካም ኢድDire Dawa Mayor Office & Managementfice & Managementyor Office & Management 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

አቶ ገበየሁ ጥላሁን የከንቲባው ጽ/ቤት እና የካቢኔ ጉዳዩች ኋላፊ

🇪🇹🇪🇹 🇪🇹 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

13/04/2023

ለመላው የአስተዳደራችን የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት እና የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ በዓሉ የሰላም፤ የደስታ የቸርነትና የልግስና እንዲሆንላችሁ ከልቤ እየተመኘሁ በዓሉን ስናከብር ቃለ ወንጌሉን በተግባር በማሳየት የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማሰብ ካለን በማካፈል፤ በህመም ምክንያት በየሆስፒታል የተኙትን እና በህግ ጥላ ስር ያሉ ወገኖቻችንን በመጠየቅ ፍፁም በሆነ መተሳሰብ እንድናሳልፍ በአክብሮት እጠይቃለው፡፡

ሌላው አደራ ማለት የምፈልገው መላው የአስተዳደሩ አመራርና የፀጥታ አካላት በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁላችንም የዜግነት ግዴታችንን በመወጣት በአሉን በመተራስ በአንዳድ ስግብግብ ነጋዴ የሚፈጠረውን የዋጋ ጭምሪበጋራ እንከላከል።

በመጨረሻም ሁሉም የበዓሉ አክባሪ ነዋሪዎቻችን ለግብይት ስትንቀሳቀሱ እራሳችሁን ከትራፊክ አደጋ፤ ለበዓሉ ስትዘጋጁ በቤት ውስጥ ከሚደርስ የእሳት አደጋ እራሳችሁን እና አካባቢያችሁን እንድትጠብቁ እንዲሁም ቅባት የበዛባቸው ምግቦችን በመመገብ ከሚፈጠር ህመም ቅድመ ጥንቃቄ እንዳይለያችሁ አደራ እላለሁ፡፡

ድሬዳዋ መገለጫዋ ወደሆነው ነዋሪዎቿ በሀይማኖት ተከባብሮና ተዋዶ በፍርቅ፤ በሰላምና በመቻቻል የመኖር ክብሯ ከፍ እንድትል ሁላችንም የድርሻችንን እንወጣ…፤

በዓሉ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁላችንም የዜግነት ግዴታችንን እንወጣ መልካም የፋሲካ በዓል ይሁንላችሁ

አቶ ገበየው ጥላሁን

የከንቲባ ፅ/ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ሀላፊ
መልካም የፋሲካ በዓል ይሁንልን

ለተሻለ ለውጥ እንትጋ
06/12/2022

ለተሻለ ለውጥ እንትጋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተለያየ የትምህርትና ስልጠና መስክ ያሰለጠናቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎችን  አስመረቀ። በምረቃ ስነስርዓቱም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ...
01/10/2022

በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተለያየ የትምህርትና ስልጠና መስክ ያሰለጠናቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎችን አስመረቀ።

በምረቃ ስነስርዓቱም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር፣ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባና ንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሀርቢ ቡህ እና የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዲሁም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ተገኝተው ለተመራቂ ሰልጣኝ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልክት አስተላልፈዋል።

ኮሌጁ ከተቋቋመ ከ2001 እስከ 2015 ዓ.ም በ9 ዲፓርትመንቶች ማለትም በአውቶቲቭ፣ በአሌክትሪክ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በአይ.ሲ.ቲ፣ በኮንስትራክሽን፣ በሆቴል፣ በሰርቬይ፣ በፈርኒቸር እና በቢዝነስ ከደረጃ 1 እስከ ደረጃ 5 አጠቃላይ በመደበኛ ስልጠና 16,461 አንዲሁም በአጫጭር ስልጠና ሙያ መስኮች ከ20,000 በላይ ሰልጣኞች አሰልጥኗል፤ በተጨማሪም በሳተላይት ዲግሪ መርሃ-ግብር ከ300 በላይ ሰልጣኞች በመደበኛና በኤክስቴንሽን መርሃ ግብር ተቀብሎ እንያሰለጠ ይገኛል፡፡

በዛሬው ዕለት የተመረቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች ብዛት ወንድ-246 እና ሴት-297 በድምሩ 543 ሲሆኑ የዘንድሮ ምረቃ ስነስርዓት ልዩ የሚያደርገው ጉዳይ በዘርፍ አዲሱ ፖሊሲ መሰረት ከፍተኛ አካዳሚክ ውጤት ያላቸው ሰልጣኝ ተማሪዎች ተሸላሚ መሆናቸው ነው፡፡

የድሬዳዋ መንግሰት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች  ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ  ለመስቀል በአል የመልካም ምኞት መልዕክት።  ! መስቀል የፍቅር፣ የሰላምና የአብሮነት በዓል በመሆኑ የመስቀል ደመራ በዓ...
27/09/2022

የድሬዳዋ መንግሰት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ ለመስቀል በአል የመልካም ምኞት መልዕክት።

!

መስቀል የፍቅር፣ የሰላምና የአብሮነት በዓል በመሆኑ የመስቀል ደመራ በዓል የጨለማው በብርሃን መሸነፍ ማሳያ በመሆኑ ይህንን በዓል በፍቅር፣ እርስበእርስ በመተሳሰብ ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ በመስራት፣ ጀግኖችን በማክበር፣ ደጀንነትን የበለጠ በማረጋገጥ፣ አንድነትን በማጽናት እንደ ደመራው ደምቀን ጨለማ በሆነብን ሁሉ ላይ እያበራን በአሸናፊነት እንቀጥል ሲሉም መልዕክተ አስተላልፈዋል።

የመስቀል በዓል አከባበር ልዩ የሚያደርገው መስቀል የሰላም፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ፣ የመደጋገፍ፣ የመከባበር ከመሆኑም ባሻገር የድሬዳዋ እሴታችን ደምቆ የሚታይበት በዓል ነው ብለዋል፡፡

ህብረተሰቡ የተለመደ የመተዛዘንና የመረዳዳት ባህሉንም በመተግበር በዓሉን ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር እንዲያከብርም ጥሪ አቅርበዋል።

የተጀመረው የእድገት እና የብልጽግና ጉዞ እውን እንዲሆን በየአካባቢያችን ሰላማችንን አጽንተን ያሉንን ጸጋዎች በመጠቀም ሙሉ አቅማችንን እና ትኩረታችንን በልማት ላይ ልናደርግ ይገባል ብለዋል።

በድጋሚ እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን።

የድሬዳዋ መንግሰት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ

የድሬዳዋ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ በ650 ሚሊዮን ብር ወጪ ማሻሻያ እና እድሳት ተደርጎለት በዛሬው እለት ተመርቆ ስራ ጀመረ።በፋብሪካው ውስጥ በ5.4 ቢሊዮን ብር የሚቋቋም አዲስ የጋርመንት ፋብሪካ...
17/09/2022

የድሬዳዋ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ በ650 ሚሊዮን ብር ወጪ ማሻሻያ እና እድሳት ተደርጎለት በዛሬው እለት ተመርቆ ስራ ጀመረ።

በፋብሪካው ውስጥ በ5.4 ቢሊዮን ብር የሚቋቋም አዲስ የጋርመንት ፋብሪካ የመሰረት ድንጋይም በክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር ተቀምጧል

08/09/2022

Test

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀበከተማም በገጠርም እየተሰሩ ያሉ የመንገድ የልማት ስራዎች ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በሰፊው እየተሰሩ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደ...
12/06/2022

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑ ተገለፀ

በከተማም በገጠርም እየተሰሩ ያሉ የመንገድ የልማት ስራዎች ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በሰፊው እየተሰሩ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ሀላፊ አቶ ብሩክ ወርቅነህ ተናገሩ፡፡

እንደ አቶ ብሩክ ገለፃ ለበርካታ ጊዜያት በህዝብ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን አስተዳደሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ተጀምረው የነበሩ ፕሮጀክቶችን በአፋጠኝ የመጨረስ እና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በዘጠና ቀን እቅድ ውስጥ በማካተት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡

በመንገዶች ባለስልጣን የተያዙ ነባር ፕሮጀክቶች የ4.2 ኪ.ሜ የድሮ ኬላ የመንገድ ስራ፣ የ5.4 የገንደ ተስፋ የመንገድ ስራ፣ የቦረን እና የሲስታ መንገድ የከፈታ ስራዎች የዘገዩ ቢሆኑም ከካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች ሊጓተቱ መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡

በዘጠና ቀን እቅዳችን ውስጥ ይጠናቀቃሉ ብለን የያዝናቸው የህዝብ እሮሮ የሆኑ መንገዶችን የማስተካከል፣ አራት ነባር ድልድዮችን የማስዋብና የመጠገን፣ ድልድይ ስር ያሉ የጎርፍ መከላከያ መውረጃዎችን የማጠናከር ስራ ተሰርተው መገባደጃ ላይ መሆናቸውን አቶ ብሩክ ገልፀዋል፡፡ የሶላር መብራቶችም በዋና ዋና የከተማው ቦታዎች ላይ መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡

በየቦታው በከተማው ውስጥ ተቆፋፍሮ የሚታየው ከተማዋን በሁሉም መንገድ የማልማት እና የመቀየር ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ከነዚህ ስራዎች ውስጥ የእግረኛ መንገድ በሰፊው ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሚገኝ የመንገዶች ባለስልጣን ሀላፊው የተናገሩት፡፡

ከሀይስኩል ትምህርት ቤት እስከ ዲፖ ገበያ የእግረኛ መንገድ የሸክላ ንጣፍ የተሰራ ሲሆን፣ ከለንበርዋን ፍርድቤት ፋይናንስን አልፎ እስከ መብራቱ ድረስ የሚሰራው የሸክላ ንጣፍ የእግረኛ መንገድ በአንድ ወር ውስጥ እንደሚጠናቀቅ አቶ ብሩክ ገልፀዋል፡፡

በቀጣይ ወደ ማህል ከተማ ውስጥ በመግባት በሳቢያን፣ በገንደቆሬ በመሳሰሉ አካባቢዎች ላይ የእግረኛ መንገዶችን የማስዋብ እና የሸክላ ንጣፍ ስራዎችን ለማከናወን በእቅድ ይዘናል ብለዋል፡፡

ሌላው የትራፊክ ምልክቶችን አስቸጋሪ የሆኑ ቦታዎች ላይ በማስቀመጥ የፍጥነት መቀነሻ ብርሃን ሰጪ የሆኑንት አስር የተመረጡ ቦታዎች ላይ አስተክለናል ብለዋል፡፡ በተመሳሳይ የትራፊክ ምልክቶች በትምህርት ቤት አካባቢ፣ በሆስፒታሎች መዳረሻ ላይ ምልክቶቹ መተከላቸውን አቶ ብሩክ ተናግረዋል፡፡
ከኮብል እስቶን እጣፍ ጋር በተያያዘ ሰፊ ስራዎች መስራታቸውን የጠቀሱት አቶ ብሩክ በሁሉም ቀበሌዎች ስልሳ ዘጠኝ ማህበራትን የስራ እድል ማመቻቸታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ከማህበራቱ ጋር ቀደም ብለው የስራ ውል የተፈራረሙ ሲሆን ስራዎችን የሚያጓትቱ እና የጥራት ደረጃው የወረደ ስራ የሚሰሩ ማህበራት ላይ በባለሙያ አስገምግመን ክፍያ የማንፈፅም መሆኑን ቀድመን ለማህበራቱ አሳውቀናል ብለዋል፡፡

በከተማ ደረጃ ሰፊ መነቃቃትን የፈጠረ ውጤት እያመጣን ያለንበት የመንገድ ልማት ስራዎች ቀጣይነት ያላቸው ተግባሮች ናቸው ብለዋል አቶ ብሩክ፡፡ በህዝብ ዘንድ ትልቅ እሮሮ የነበሩ የዘመናት ጥያቄ የሆኑ በዚህ ዘጠና ቀናት ውስጥ እየተሰሩ እንዳለና አሁንም ቀሪ ስራዎች መኖራቸውን የተገለጸ ሲሆን በበጀት መደገፍ ስላለባቸው በቀጣይ የምንሰራቸው ይሆናሉ ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ በገጠር በእቅድ ደረጃ 80 ኪ.ሜ የመንገድ ከፈታ እና የጥርጊያ ስራ ለመስራት ታቅዶ መጀመሩን የመንገዶች ባለስልጣን ሀላፊ አቶ ብሩክ የተናገሩ ሲሆን በዚህ ዓመት 15 ኪ.ሜ የመንገድ ከፈታ እና የጥርጊያ ስራ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል፡፡

አሁን ላይ በዋናነት ሶስት የገጠር ቀበሌዎችን ይዘን እየሰራን ሲሆን ዋሂል፣ ኮርቱ፣ ጀሎ በሊና ላይ ቦታዎችን የማስተካከል ስራዎች እየሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡
በ በድሉ ሃይሌ
ፎቶ :- አብይ ሽመሊስ

በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚቀጥሉት 5 ወራት የመኖሪያ ቤት አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪም ሆነ ከቤት የማስለቀቅ ተግባር እንዳያደርጉ ውሳኔ ተላለፈ ።       የድሬዳዋ...
11/06/2022

በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚቀጥሉት 5 ወራት የመኖሪያ ቤት አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪም ሆነ ከቤት የማስለቀቅ ተግባር እንዳያደርጉ ውሳኔ ተላለፈ ።

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ሰኔ 2 \ 2014 ዓ.ም ባደረገው መደበኛ ስብሰባ ላይ ሁለት ውሳኔዎችን ያስተላለፈ ሲሆን እነዚህንም ውሳኔዎች አስመልክቶ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ብሩክ ፈለቀ በዛሬው እለት ለሚዲያ አባላት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል ።

በድሬዳዋ አስተዳደር የዝናብ ወቅት መራዘምን ተከትሎ በገጠር ቀበሌዎች ላይ የከፋ ድርቅ እንዳይከሰት ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የቴክኒክ ኮሚቴ በማቋቋም የዳሰሳ ጥናት የተካሄደ ሲሆን ይህም የዳሰሳ ጥናት ውጤት እንደሚያሳየው በተለያዩ የግብርናው ዘርፍ የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት የእንስሳት መኖ እጥረት እንዲሁም በጤናና ትምህርት ዘርፍ ከድርቁ ጋር ተያይዞ ችግሮች እንዳሉ ለማወቅ እንደተቻለና እነዚህም ችግሮች እንዳይባባሱ የአስተዳደሩ ካቢኔ የተለያዩ ውሳኔዎች መወሰናቸውን አቶ ብሩክ ፈለቀ ተናግረዋል ።

እነዚህም ውሳኔዎች አርሶ አደሩ በጊዜ የመሬት ዝግጅቱን በማዘጋጀት ዘር የዘራ ቢሆንም ዝናብ ባለመኖሩ ምክንያት የተዘራው አዝመራም ያልበቀለበት ቦታ በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚደርሱ ዘሮች እንዲገዙና ለአርሶ አደሩ እንዲውሉ ውሳኔ ከመወሰኑም በዘለለ ለእንስሳት የመኖና የመድሀኒት አቅርቦት በፍጥነት እንዲቀርብ የአስተዳደሩ ካቢኔ መወሰኑን ነው አቶ ብሩክ ፈለቀ በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ የገለፁት።

በተለይም የንፁህ መጠጥ ውሀ አቅርቦት ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች ተጨማሪ የውሀ ቦቴዎች በመጠቀም ውሀ እንዲደርስላቸውና በተፈጠረው ችግር ምክንያት ዜጎች እንዳይጎዱ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያገኙ እንዲደረግ የአስተዳደሩ ካቢኔ መወሰኑን አቶ ብሩክ ገልፀው ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተል የአብይ ኮሚቴ በማቋቋም ለችግሩ ምላሽ እንዲሰጥ 10 ሚሊዮን ብር በጀት ፀድቆ መመደቡን ገልፀዋል።

ሌላው በድሬዳዋ አስተዳደር የሚኖሩ የቤት አከራዮችን በተመለከተ የአስተዳደሩ ካቢኔ ውሳኔ ያስተላለፈ ሲሆን ውሳኔውም በድሬዳዋ ላይ ያሉ የመኖሪያ ቤት አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ አላግባብ የሆነ የዋጋ ጭማሪ ማድረግና ጭማሪውንም መክፈል የማይችሉትን አካላት ከቤት የማስወጣት ተግባር ሲሆን ይህም ችግር በከተዋማ ላይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በስፋት ከመስተዋሉ ጋር ተያይዞ ዜጎች ለከፍተኛ እንግልት እየተጋለጡ እንደሆነና ይህንንም ችግር ለመፍታት ይቻል ዘንድ በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚቀጥሉት 5 ወራት የመኖሪያ ቤት አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪም ሆነ ከቤት የማስለቀቅ ተግባር እንዳያደርጉ ውሳኔ መተላለፍን የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ብሩክ ፈለቀ በዛሬው እለት ለሚዲያ አባላት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስታውቀዋል

Address

Followed By 38, 970 People
Addis Ababa

Telephone

+251948304022

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ብሩክ ፈለቀ በድሬዳዋ የመንግስት ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share