7 killo ፯ ኪሎ

7 killo ፯ ኪሎ 7 killo | ፯ ኪሎ

በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊ ?

የኢትዮጵያ ስደተኞች በሳውዲ አረቢያ  በግልጽ ላልታወቁ ወራት በሳውዲ እስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በረሃብ፣ በወረርሽኝ እና በፍትህ እጦት እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡ በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ ...
29/03/2022

የኢትዮጵያ ስደተኞች በሳውዲ አረቢያ

በግልጽ ላልታወቁ ወራት በሳውዲ እስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በረሃብ፣ በወረርሽኝ እና በፍትህ እጦት እየተሰቃዩ ይገኛሉ፡፡ በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ መንግስት እርምጃ እንዲወስድ በዜጎች ጥያቄዎች ቢቀርቡም ምላሽ ሲሰጥ አልተስተዋለም፡፡

በትናንትናው ዕለት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሰጠው መግለጫ በሳውዲ ወህይኒ ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በነገው ዕለት አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ከ7 እስከ 11 ወራት ከ100 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሐገራቸው እንደሚገቡ ተነግሯል፡፡

7 killo | ፯ ኪሎ ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣የኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ እና የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር የዩቱዩብ ፕሮግራም ነው።

ኢትዮጵያ በአሰቃቂ ረሐብ ጫፍ ላይ ነች የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት ሰብዓዊ ኪሳራ እያደረሰ ያለው በምስራቅ አውሮፓ ብቻ ሳይሆን፣ በመላው ዓለም ላይ ነው፡፡ በምስራቅ አፍሪካ የተከሰተው ታላ...
29/03/2022

ኢትዮጵያ በአሰቃቂ ረሐብ ጫፍ ላይ ነች

የሩሲያ እና የዩክሬን ጦርነት ሰብዓዊ ኪሳራ እያደረሰ ያለው በምስራቅ አውሮፓ ብቻ ሳይሆን፣ በመላው ዓለም ላይ ነው፡፡ በምስራቅ አፍሪካ የተከሰተው ታላቅ ድርቅ በቀጠናው የሚገኙ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ለአደጋ አጋልጧል፡፡ በተለይም የቀጠናው ማዕከል የሆነችው ኢትዮጵያ ዜጎቿ በድርቅ፣ በረሐብ እና በጦርነት እየታመሱ ይገኛሉ፡፡

በምስራቅ ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተከሰተው ረሀብ ድምጽ አልባ እልቂት ፈጥሯል፡፡ አከባቢው ዝናብ ካገኘ ሁለት ዓመታት ያለፉት ሲሆን፣ በክልሉ የሚገኙ ሴቶች ውሃ ለማግኘት በየዕለቱ ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት በእግራቸው ይጓዛሉ፡፡ ያላቸው ሌላ አማራጭ ከመኖሪያ አከባቢያቸው 70 ኪሎ ሜትር የሚርቅ ወንዝ ነው፡፡

ነዋሪዎቹ እንደሚናገሩት በአከባቢያቸው ከዚህ በፊት ታይቶ የማያውቅ ድርቅ ተከስቷል፡፡ በቀድሞው ግዜ በሚከሰተው ድርቅ ቢያንስ ከብቶቻቸው ለአደጋ እንደማይጋለጡ ይናገራሉ፡፡ በዘንድሮው ድርቅ ግን ከብቶቻቸው እየረገፉ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ የሚሞቱት ከብቶች ከመብዛታቸው የተነሳ የሚኖሩበት አከባቢ በመጥፎ ጠረን ተበክሏል፡፡ አሸር መሃዲ የተባለ ነዋሪ እንደሚገልጸው ከ260 ፍየሎች በህይወት የቀሩት 12 ብቻ መሆናቸውን በሐዘን ይናገራል፡፡ የቀሩትም በህይወት ብዙ እንደማይቆዩ ያምናል፡፡

በጎዴ ሆስፒታል በወር እስከ 10 የሚጠጉ በምግብ እጦት የተጎዱ ህጻናት ይመጡ ነበር፡፡ አሁን ከ25 እስከ 30 ከዛም በላይ ህጻናት በድርቁ ምክንያት በወር ውስጥ ከዛ በላይ ህጻናት እየመጡ ነው፡፡ እነዚሁ ሴቶች ለልጆቻቸው የህክምና እርዳታ ለማግኘት ከ100 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት ይጓዛሉ፡፡ ሴቶቹም የተጎዱ ስለሆኑ ለህጻናቱ የጡት ወተት ለመስጠት ይቸገራሉ፡፡

የፌደራሉ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ በተቀሰቀሰው ግጭት ምክንያት ትኩረቱ ወደ ግጭቱ ስለሆነ፣ በሐገሪቱ ውስጥ የሚከሰቱ ሰብዓዊ ቀውሶች ትኩረት አጥተዋል፡፡ ተመሳሳይ አይነት የድርቅ አደጋ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች መከሰታቸው አይዘነጋም፡፡ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል የዜጎች መፈናቀል አደገኛ በሆነ መልኩ ትኩረት ያጣ ብሔራዊ ክስተት ነው፡፡ በአማራ፣ በትግራይ፣ በአፋር ክልል የሚታየው ሰብዓዊ ቀውስ ሲደማመር ኢትዮጵያ ከፊቷ አደገኛ ሐገራዊ ስጋት እንደሚያጋጥማት ማሳያ ነው፡፡

7 killo | ፯ ኪሎ ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣የኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ እና የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር የዩቱዩብ ፕሮግራም ነው።

"ኢትዮጵያ በአሰቃቂ ረሐብ ጫፍ ላይ ነች"  ተባለ
29/03/2022

"ኢትዮጵያ በአሰቃቂ ረሐብ ጫፍ ላይ ነች" ተባለ

7 Killo | ፯ ኪሎ ከዚህም ከዚያም ናይሮቢ በደረሰ የመኪና አደጋ አንድ ሰው ሲሞት፣ አምስት ኢትዮጵያውያን ቆሰሉበናይሮቢ ደቡብ ሁለተኛ መንገድ ላይ በደረሰ የመኪና አደጋ አንድ ኢትዮጵያዊ...
28/03/2022

7 Killo | ፯ ኪሎ ከዚህም ከዚያም

ናይሮቢ በደረሰ የመኪና አደጋ አንድ ሰው ሲሞት፣ አምስት ኢትዮጵያውያን ቆሰሉ

በናይሮቢ ደቡብ ሁለተኛ መንገድ ላይ በደረሰ የመኪና አደጋ አንድ ኢትዮጵያዊ ሲሞት፣ አምስት ቆስለዋል፡፡ አደጋው የደረሰው እሁድ ጠዋት ሲሆን፣ ጉዳት የደረሰባቸው ኢትዮጵያውያን በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሱዳን የገቡ መሆናቸውን የናይሮቢ ባለስልጣናት ተናግረዋል፡፡

አደጋው እንደደረሰ ከአደጋው ቦታ ወደ ኬንያታ ሆስፒታል የተወሰደው ስደተኛ በህክምና ቦታው ሲደርስ ህይወቱ አልፏል፡፡ የናይሮቢ ፖሊስ አዛዥ ጀምስ ሙጌራ አደጋው ከደረሰ በኃላ የተጎዱት ወደ ሆስፒታል ሲደርሱ፣ ሌሎች ቀሪዎቹ ስምንቱ ወደ ህግ ቦታ ተወስደዋል ብለዋል፡፡ ፖሊስ ሰኞ ስደተኞቹን ፍርድ ቤት አቅርቦ ጉዳያቸውን ከተመለከተ በኃላ ወደ ሐገራቸው እንደሚመለሱ ገልጿል፡፡

ፖሊስ እንደገለጸው ከኢትዮጵያውያን ጋር በሲዋሂሊም ሆነ በእንግሊዘኛ መግባባት አስቸጋሪ መሆኑን ይናገራል፡፡ ስደተኞችንም የሚያሸጋግሩት ደላሎችም በብዛት አሁንም እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

በህወሓት እና በፌደራል መንግስት መካከል ዳግም ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ተሰግቷል

በህወሓት እና በፌደራል መንግስቱ መካከል የነገሰው ውጥረት ዛሬም አልረገበም፡፡ ሁለቱን ኃይሎች ለማደራደር የተለያዩ አካላት ሙከራ ቢያደርጉም ስኬት ማግኘት ግን አልቻሉም፡፡ ሰሞኑን ግን የፌደራል መንግስቱ ለሰብዓዊ እርዳታ እንዲረዳው የተናጥል ተኩስ አቁም እንዳደረገ ሲገልጽ፣ የህወሓት ኃይሎችም የተኩስ አቁሙን እንደተቀበሉ አሳውቀዋል፡፡

ከሁለቱ መግለጫ በኃላ እየወጡ ያሉ መረጃዎች የሚያሳዩት ሶስቱ ኃይሎች፣ ማለትም ህወሓት፣ የኤርትራ ሰራዊት፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ኃይል እንዲሁም የአፋር ልዩ ኃይል ጦራቸውን ወደ ግጭቱ አከባቢዎች እያስጠጉ ነው፡፡ በተለይም በወልቃይት አከባቢ ከፍተኛ የሆነ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለተወሰኑ ወራት እንደተስተዋለ ተመልክቷል፡፡ ይህ እየሆነ ያለው ሁለቱ ኃይሎች ለድርድር በራቸውን ከፍተዋል የሚሉ ዘገባዎች እየወጡ ባለበት ወቅት ነው፡፡

በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ አባላት መካከል ግጭት ተፈጠረ

በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱን የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቡላ ኡቦንግ አስታወቋል።

በአሁኑ ሰዓት የአካባቢውን ሠላም ወደነበረበት ከመመለስ ባሻገር ግጭት ፈጥረዋል የተባሉ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢው ማጣራት እየተካሄደ መሆኑንም ተገልጿል።

ፖሊስ የግጭቱን መንስኤ እያጣራ እንደሆነ የገለጹት ኮሚሽነሩ በአሁኑ ሰዓት ሰላማዊ እንቅስቃሴ መኖሩን አመልክተዋል።

ከተማዋ ሰላም መሆኗን እና ህብረተሰቡም ወደ ተለመደው የሰላም ሁኔታ መመለሱን ኮሚሽነር አቡላ ተናግረዋል።

ችግሩ በተፈጠረባቸው አካባቢዎች ተገቢው ፀጥታን የማረጋገጥና ሰላምን የማስፈን ስራ መሠራቱን ጠቁመዋል።

መላው ህብረተሰብ ወደ ግጭት ሁከትና መረበሽ ሰዎችን እንዲያመሩ ከሚያደርጉ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችና ያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሱን እንዲጠብቅ ማሳሰባቸውን አሻም ከጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት የማሕበርዊ ትስስር ገጽ ተመልክታለች።

#የውጭ ዜና

መድረክ መሪው በዊል ስሚዝ ጥፊ ላሰ
ትናንት በተካሄደው የኦስካር ሽልማት ላይ አስደማሚ ክስተት ተስተውሏል፡፡ ትናንት በተካሄደው 94ኛው ዝግጅት ላይ መድረክ መሪ የነበረው ኮሜዲያን ክሪስ ሮክ፣ በዊል ስሚዝ ሚስት ላይ በቀለደው ቀልድ የተበሳጨው ዊል ስሚዝ በአዋራጅ መልኩ በጥፊ መቶታል፡፡

የዊል ስሚዝ ባለቤት ጄዳ ፒንኬት ስሚዝ ከ2018 አንስቶ አሎፒሺያ በተባለ በሽታ የምትሰቃይ ሲሆን፣ ህመሙ በተለያዩ አካሎች ላይ ጉዳት ያደርሳል፡፡ እንዲሁም የራስ ጸጉርን ያራግፋል፡፡ ጄዳም በተደጋጋሚ ስለህመሟ በሚዲያ ስትገልጽ ቆይታለች፡፡ ክሪስ ሮክም ሊቀልድ የሞከረው በዚሁ በጄዳ የተመለጠ ጸጉር ነበር፡፡

በዚህ ቀልድ የተከፋችው ጄዳ ፊቷ ላይ በግልጽ ቢታይም፣ በወቅቱ ዊል ስሚዝ በቀልዱ ሲስቅ ታይቷል፡፡ ከወንበሩ ተነስቶ ክሪስን የመታው የጄዳ ፊት መከፋት ከተመለከተ በኃላ ነው፡፡ በድርጊቱ ለግዜው መድረኩ ቢቀዛቀዝም፣ ክሪስ በራሱ ላይ በመቀለድ የነበረው ጭንቀት ማርገብ ችሏል፡፡ ጄዳ ቀደም ባሉት ዓመታት በዊል ስሚዝ ላይ እንደማገጠች ይታወቃል፡፡ በማህበራዊ ሚዲያ ላይም ዊል ስሚዝ "የሚናደደው ሚስቱ ስትማግጥ ሳይሆን ሲቀለድባት ነው" የሚል ቀልድ ሲዘዋወር ውሏል፡፡

በዕለቱ ዊል ስሚዝ ኪንግ ሪቻርድ ፊልም ላይ ባሰየው ብቃት በምርጥ አክተር ዘርፍ ሽልማቱን አንስቷል፡፡

በዮቲዬብ ቻናላችንም ይከታተሉን

7 killo | ፯ ኪሎ ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣የኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ እና የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር የዩቱዩብ ፕሮግራም ነው።

በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ አባላት በተፈጠረ ግጭት  የሰው ህይወት አለፈ።በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የአ...
28/03/2022

በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ አባላት በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አለፈ።

በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በክልል ፖሊስ እና በፌደራል ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ በአንድ ሰው ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱን የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቡላ ኡቦንግ አስታወቋል።

በአሁኑ ሰዓት የአካባቢውን ሠላም ወደነበረበት ከመመለስ ባሻገር ግጭት ፈጥረዋል የተባሉ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢው ማጣራት እየተካሄደ መሆኑንም ተገልጿል።

ፖሊስ የግጭቱን መንስኤ እያጣራ እንደሆነ የገለጹት ኮሚሽነሩ በአሁኑ ሰዓት ሰላማዊ እንቅስቃሴ መኖሩን አመልክተዋል።

ከተማዋ ሰላም መሆኗን እና ህብረተሰቡም ወደ ተለመደው የሰላም ሁኔታ መመለሱን ኮሚሽነር አቡላ ተናግረዋል።

ችግሩ በተፈጠረባቸው አካባቢዎች ተገቢው ፀጥታን የማረጋገጥና ሰላምን የማስፈን ስራ መሠራቱን ጠቁመዋል።

መላው ህብረተሰብ ወደ ግጭት ሁከትና መረበሽ ሰዎችን እንዲያመሩ ከሚያደርጉ አንዳንድ ማህበራዊ የሚዲያ ገፆችና ያልተረጋገጠ መረጃ ከሚሰጡ ዘገባዎች እራሱን እንዲጠብቅ ማሳሰባቸውን አሻም ከጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት የማሕበርዊ ትስስር ገጽ ተመልክታለች።

ምንጭ:- አሻም ቲቪ

ሰበር እስከ ምሽት 2 ሰአት ድረስ ሲካሄድ በቆየው የኦፌኮ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ፕ/ር መረራ ጉዲና የኦፌኮ ሊቀመንበር ሆነው እንዲቀጥሉ የተመረጡ ሲሆን ኦቦ በቀለ ገርባ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበ...
26/03/2022

ሰበር

እስከ ምሽት 2 ሰአት ድረስ ሲካሄድ በቆየው የኦፌኮ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ፕ/ር መረራ ጉዲና የኦፌኮ ሊቀመንበር ሆነው እንዲቀጥሉ የተመረጡ ሲሆን ኦቦ በቀለ ገርባ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው እንዲቀጥሉ ተመርጠዋል።

ኦዳ ፓርቲ ኦፌኮን ሙሉ በሙሉ ተቀላቅሏል። 623 አባላት በጠቅላላ ጉባኤው ላይ መገኘታቸው ታውቋል።
26/03/2022

ኦዳ ፓርቲ ኦፌኮን ሙሉ በሙሉ ተቀላቅሏል። 623 አባላት በጠቅላላ ጉባኤው ላይ መገኘታቸው ታውቋል።

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ጠቅላላ ጉባኤውን በዋቢ ሸበሌ ሆቴል በማካሄድ ላይ ይገኛል።
26/03/2022

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ ጠቅላላ ጉባኤውን በዋቢ ሸበሌ ሆቴል በማካሄድ ላይ ይገኛል።

የሩሲያ ወረራ ከተጀመረ ዛሬ አንድ ወር ያስቆጠረ ሲሆን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በአውሮፓ ትልቁ ጦርነት ተብሏል። የሩስያ ጦር ሃይሎች በዩክሩን ዋና ከተማ ኪየቭ ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት...
26/03/2022

የሩሲያ ወረራ ከተጀመረ ዛሬ አንድ ወር ያስቆጠረ ሲሆን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በአውሮፓ ትልቁ ጦርነት ተብሏል።

የሩስያ ጦር ሃይሎች በዩክሩን ዋና ከተማ ኪየቭ ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት ቢሰነዝሩም ከተማዋን ቀለበት ዉስጥ ማስገባት ያልቻሉ ሲሆን ዩክሬን 15,800 የሩስያ ወታደሮችን መግደሏን እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ታንኮችን፣ የጦር ተሽከርካሪዎችን፣ መድፍ እና አውሮፕላኖችን ማውደሟን ስትገልፅ፤ በሩሲያ ላይ የተጣለዉ የኢኮኖሚ ማዕቀብ 1.5 ትሪሊዮን ዶላር ሲደርስ የሞስኮን ኢኮኖሚ ወደ ከፍተኛ ውድቀት እንዳስገባቸው ይታመናል፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ከኔቶ ያልተገደበ ወታደራዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጥሪ ሲያቀርቡ የኔቶ ዋና ስራ አስፈጻሚ ስቶልተንበርግ እንደተናገሩት ለሩሲያ ወረራ ምላሽ ለመስጠት 40,000 ወታደሮችን ወደ ምስራቃዊ አዉሮፓ ለማስፈር እና መከላከያውን ለማጠናከር መስማማታቸውን ተናግረዋል።

የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ቻርለስ ሚሼል በበኩላቸው የኔቶ መሪዎች በተገናኙበት በብራስልስ ስብሰባ ፑቲን የግድ መሸነፍ አለባቸው፤ ይህ እንዲሆን ዩክሬንን መደገፍ አለብን ተጨማሪ ማዕቀብን ተግባራዊ ማድረግን አለብን ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል ።

በዮቲዬብ ቻናላችንም ይከታተሉን

7 killo | ፯ ኪሎ ፣ በኢትዮጵያ የፖለቲካ፣የኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ እና የዲፕሎማሲ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር የዩቱዩብ ፕሮግራም ነው።

25/03/2022

ሕወሓት እና መንግስት ለሰላም እጃቸውን ዘረጉ !

የትግራይ ታጣቂዎች ከኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት ጋር የገቡበትን የኃይል ትግል ለግዜው እንደሚያቆሙ አስታወቁ፡፡

በትናንትናው ዕለት የፌደራል መንግስቱ ለሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽነት ሲባል የተናጥል ተኩስ አቁም ባወጀ ቅጽበት የህወሓት ኃይሎች ለሰላም ዝግጁ መሆናቸው ተሰምቷል፡፡

የህወሓት ኃይሎች የመንግስትን መግለጫ ተከትሎ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በላኩት ማስታወሻ "ጠላትነቱ ተወግዶ ወደ ሰላም ለመምጣት መፍጠን አለብን" እንዲሁም የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላሙ ቅድሚያ ሰጥቶ፣ በክልሉ ላጋጠመው ረሃብ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ አሳስበዋል፡፡

ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ጥቅምት 24 አንስቶ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሞተዋል፣ በሚሊየን የሚገመቱ ሰዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል፡፡ እንዲሁም ግጭቱ ወደ አጎራባች ክልሎች አፋርና አማራ ተስፋፍቷል፡፡

ሐሙስ ዕለት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ መንግስት ያልተጠበቀ የተናጥል የተኩስ አቁም አዉጇል፡፡ በተኩስ አቁም አዋጁ ውስጥም ፈጣን የሆነ የሰብዓዊ እርዳታ ወደትግራይ ክልል ማድረስ እንደሚቻል ተስፋ እንዳለው ጠቁሟል፡፡ በተጨማሪም በክልሉ የተከሰተውን ቀውስ ለመፍታት መንገድ እንደሚጠረግ እምነቱን ገልጿል፡፡

እንደተባበሩት መንግስታት ግምት በትግራይ ከ400ሺ በላይ ነዋሪዎች ቀያቸውን ለቀው ተሰደዋል፡፡ ድርጅቱ እንደሚለው ክልሉ ከሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ሙሉ ለሙሉ ተቆራርጧል፡፡ የአሜሪካ መንግስት ለዚህ የፌደራሉን መንግስት ተጠያቂ ሲያደርግ፣ መንግስት በበኩሉ ህወሓትን ለችግሩ ተጠያቂ ያደርጋል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ ባለፈው ሳምንት የኢኮኖሚስት ጋዜጠኛ ቶም ጋርድነር በቲዊተር ገጹ፣ የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል እና ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ለመጀመሪያ ግዜ በስልክ ተወያዩ የሚል መልዕክት በመለጠፉ ምክንያት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የሐገሪቱን ደህንነት ስጋት ላይ ጥልሃል በሚል የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ መጻፉ አይዘነጋም፡፡

22/03/2022
22/03/2022

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when 7 killo ፯ ኪሎ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share