H_Ethiopia

H_Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from H_Ethiopia, Media/News Company, Addis Ababa.

እንዲዚህ ፅፌላቹ ነበርተመልከቱ
19/12/2024

እንዲዚህ ፅፌላቹ ነበር

ተመልከቱ

08/12/2024

ከቤተ መግስት ወደብሔራዊ ወርቅ ባንክ ገባ የተባለዉን 400 ኬሎ ግራም ወርቃችንን አስቀምጠዉ መኮብለል ይችላሉ።😂😂

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምድረ ቻይና የመጀመሪያውን ደብር በመሰየም፣ ሥርዓተ ቅዳሴ አከናወነች! ኅዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)ባሳለፍነው ሳምንት...
08/12/2024

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በምድረ ቻይና የመጀመሪያውን ደብር በመሰየም፣ ሥርዓተ ቅዳሴ አከናወነች!

ኅዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

ባሳለፍነው ሳምንት ሐሙስ ለሁለተኛ ምዕራፍ ሐዋርያዊ አገልግሎት ቻይና የገቡት ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በዕለቱ ከተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል በማስከተል የአስተዳደር ሥራዎችን ሲያከናውኑ ከቆዩ በኋላ፤ በዕለተ እሑድ በቻይና ምድር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጀመርያ የሆነውን ቤተ ክርስቲያን "ደብረ ምሕረት መድኃኔዓለም" ብለው በመሰየም ሥርዓተ ቅዳሴ በመፈፀም ምዕምናንን አቁርበዋል።

በዕለቱም አንድ ኢ-አማኒ የነበረች ግለሰብ እና ሕፃን በማጥመቅ የሥላሴን ልጅነት እንዲያገኙ ያደረጉ ሲሆን የመጀመሪያውን አንድ ኢትዮጵያዊ ዲያቆንም ሹመት አከናውነዋል።

በዕለቱም ከቻይና የተለያዩ ክፍላተ ግዛት የተሰባሰቡ ምዕመናን፣ ቻይናውያን እና ትውልደ ቻይናውያን በሥርዓተ ቅዳሴው የተሳተፉ ሲሆን መጋቤ ሐዲስ ለይኩን ብርሃኑ "ሔዶም ታጠበና እያየም ተመለሰ" በሚል ርዕስ አስተምረዋል። ከሥርዓተ ቅዳሴው በኋላ ብፁዕነታቸው ለቀጣይ አገልግሎት ወደ ቤይጂንግ ከተማ አቅንተዋል።

መረጃውን ያደረሰን የብፁዕነታቸው ጽ/ቤት ነው

08/12/2024

በአዲስ አበባ የሚሰማው ተኩስ ምንድን ነው?

- በተኩሱ አንድ ሴት መገናኛ አካባቢ ተመትታ ህይወቷ አልፏል

- በአምቦ ከተማም በተመሳሳይ በተባራሪ ጥይት ተመትተው ሁለት ሰዎች ሞተዋል

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ እንደ ገርጂ፣ ጃክሮድ፣ ሾላ፣ 6 ኪሎ፣ መነን፣ ጎሮ ወዘተ ያሉ አካባቢዎች ከፍተኛ ድምፅ ያለው ተኩስ ሲሰማ ነበር።

በርካታ ነዋሪዎች በድምፁ ተደናግጠዋል፣ መረጃ የሰጠ የመንግስት አካልም የለም።

መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ ባደረገው ማጣራት ተኩሱ ከሰሞኑ ከመንግስት ጋር እርቅ ፈፀሙ በተባሉት የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት የተተኮሰ ነው።

መገናኛ አካባቢ አንዲት ሴት በተኩሱ ምክንያት በጥይት ተመትታ ህይወቷ ማለፉም ታውቋል። በተመሳሳይ ባለፉት ጥቂት ቀናት በአምቦ ከተማ በታጣቂዎቹ በተተኮሰ ጥይት ሁለት ሰዎች በተባራሪ ተመትተው እንደሞቱ ታውቋል።

ታጣቂዎቹ የኦነግን ባንዲራ በመያዝ ከሸገር ከተማ በመነሳት ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ወደ ሰማይ እየተኮሱ እንደገቡ የደረሰን መረጃ ያሳያል።

"ታጣቂዎቹ በቅጥቅጥ አና በሃይሉክስ መኪና ተጭነው ሾላ ፖሊስ ጣቢያ አካባቢ ሲደርሱ ወደ ሰማይ ተኩስ አየተኮሱ እየተጓዙ ነበር" ያለን አንድ የአይን ምስክር በሁኔታው በርካቶች እንደተደናገጡ ገልጿል።

ህዝብ በሚንቀሳቀስበት ጎዳና ላይ ድርጊቱ መፈፀሙ እንዳሳዘናቸው የገለፁት ነዋሪዎች ህዝብን በዚህ ሁኔታ፣ በተለይ ቀድሞ ባልተገለፀበት ሁኔታ ማሸበር አግባብ እንዳልሆነ ተናግረዋል።

ሾላ ፖሊሲ ጣቢያ ከሚገኙ አንድ የፖሊስ አባል ድርጊቱን ያረጋገጠ ሲሆን አንዳንዶች ከተኮሱ ቦታ በድንጋጤ ሲሸሹ ይታይ እንደነበር ገልፀዋል።

ተጠባቂው የአርሰናል እና ማንቺስተር ዩናይትድ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይደረጋል በ14ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት 5 ሰዓት ከ15 ላይ አርሰናል ከማንቺስተር ዩናይትድ ጋር የሚያደር...
04/12/2024

ተጠባቂው የአርሰናል እና ማንቺስተር ዩናይትድ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይደረጋል

በ14ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ምሽት 5 ሰዓት ከ15 ላይ አርሰናል ከማንቺስተር ዩናይትድ ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡

በሩበን አሞሪም አሰልጣኝነት የውጤት መሻሻል ያሳየው ማንቺስተር ዩናይትድ ከፕሪሚየር ሊጉ መሪ ሊቨርፑል ላለመራቅ ጨዋታውን የማሸነፍ ግዴታ ውስጥ ገብቶ የሚጫወተውን አርሰናልን በኤሜሬትስ ስታዲየም ይገጥማል።

ሁለቱ ቡድኖች ከዚህ በፊት ባደረጓቸው 241 የእርስ በእርስ ግጥሚያዎች ማንቺስተር ዩናይትድ 99 ጨዋታዎችን በድል ተወጥቷል፡፡

አርሰናል በበኩሉ 89 ጊዜ በድል ሲያጠናቅቅ፤ በቀሪዎቹ 53 ግጥሚያዎች ደግሞ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

በፕሪሚየር ሊጉ ዛሬ በሚደረጉ ሌሎች ተጠባቂ ጨዋታዎች ማንቺስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት፣ ኒውካስል ዩናይትድ ከሊቨርፑል እንዲሁም ሳውዝሃምፕተን ከቼልሲ ምሽት 4፡30 የሚጫወቱ ይሆናል፡፡

04/12/2024

አድማስ ዲጅታል ሎተሪ 29ኛ ዙር ዕጣ ዛሬ ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በእድል አዳራሽ በህዝብ ፊት የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮችም ከዚህ ጋር ተያይዟል

03/12/2024

ከተላኩልኝ መልዕክቶች አንዱ እንዲህ ይላል:- ይላል ፋሲል የኔ አለም
👇👇👇👇👇
“ ሰላም ፋሲሌ እንዴት ነህ?
ያው ቲቪያችን እየሰራ አደለም ። እናንተ ለመሥማት እድሉ ሰሞኑ የለኝም ።

አንድ ነገር ገርሞኝ ላካፍልህ ወደድኩኝ ። አሰሪዬ ቅርብ ጊዜ ሕንፃ ሰርቶ ጨርሶ 1ኛ ፎቅ ላይ አከራየና ለባንክ ካገኘው ግብር ሊከፍል ወደ ገቢዎች ይሄዳል። ያከራየህበትን ብር ምን አደረከው? ብለው ይጠይቁታል ። አጠፋሁት በላሁበት ይላቸዋል ። እነሱም አትችልም ይሉታል ። እንዴት ብሎ ይጠይቃል። መብት የለህም፣ አሸባሪ ረድተህበትስ ቢሆን ይሉታል ። ኧረ በፍፁም እንደሱ አይነት ሰው አደለሁም ይላቸዋል ። አይ አንቀበልም አሉትና ሌላ አተካራ ውስጥ ገብተው ፣ ለማንኛውም እኔ ለመጠይቅህ ብር ዝግጁ ከሆንክ ደህና ፣ አሊያ ደግሞ ዘብጥያም ልትወርድ ትችላለህ ብሎት እርፍ ።

ግራ ሲገባው እሱ ከሚያገኘው በላይ ለመኖር ሲል በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ብር ተሸከርካሪ ወንበር ላይ ለተቀመጠው ሰው አስረክቦ ወጣ ። የአብይ ብልፅግና ተብዬዎች እየገረሙኝ ነው። ግንባታ ፍቃድ ልትጠይቅ ብትሔድ ችግር ፣ ሰለ
ስንቱ ችግር ላውራልህ ። አሁን መርካቶ ውስጥ ያለውን ጣጣ ብታይ ፣ በቃ በዚህ ሀገር ተስፋ ትቆርጣለህ። ያሳዝናል በጣም።”

መረጃዉ የፋሲል የኔአለም ነዉ

የአቶ ታዬ ደንደዓ የዋስትና መብት መፈቀድ አስደሳች ቢሆንም ሁለት ጉዳዮችን ላንሳ:- አንደኛው አቶ ታዬ የተፈታው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተከሳሽ ምስክርነት ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ ለማድረግ ነው።...
02/12/2024

የአቶ ታዬ ደንደዓ የዋስትና መብት መፈቀድ አስደሳች ቢሆንም ሁለት ጉዳዮችን ላንሳ:- አንደኛው አቶ ታዬ የተፈታው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተከሳሽ ምስክርነት ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ ለማድረግ ነው። ከህግ በላይ መሆናቸውን ያስመሰከሩበት አጋጣሚ ነው። ታዬ ጠቅላይ ሚኒስትሩን በምስክርነት መቁጠሩ፣ ጥሩ ፖለቲካዊ ጨዋታ መጫወቱን ያሳያል።

ሁለተኛው አቶ ታዬ ከእስር ሲፈታ የአቶ በቲ ኡርጌሳ እጣ ፋንታ እንደማያጋጥመው ዋስትና የለውም። ከመፈታቱ ጋር ተያይዞ ብዙ አደጋዎች ከፊቱ እንዳሉ አይዘንጋ።

የፌደራል መንግሥት ኤርትራ ጦሯን ከኢትዮጵያ ግዛት እንድታስወጣ ይፋዊ ጥያቄ መቅረብ አለበት ተባለሕዳር 23/2017 ኤርትራ በኢትዮጵያ ይዛቸዉ ካለችዉ አካባቢዎች መዉጣት ይኖርባታል ሲሉ ዲፕሎ...
02/12/2024

የፌደራል መንግሥት ኤርትራ ጦሯን ከኢትዮጵያ ግዛት እንድታስወጣ ይፋዊ ጥያቄ መቅረብ አለበት ተባለ

ሕዳር 23/2017 ኤርትራ በኢትዮጵያ ይዛቸዉ ካለችዉ አካባቢዎች መዉጣት ይኖርባታል ሲሉ ዲፕሎማቶች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተናግረዋል።

"በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ዘላቂ ሰላም ማምጣት የሚቻለዉ ሕዝቡም ከስቃይ መዳን የሚችለዉ ኤርትራ ጧሯን ከኢትዮጵያ ማስወጣት ስትችል ነው" ሲሉ የተናገሩት፤ የኢሮብ አኒና ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት የቦርድ አባል የሆኑት አቶ ተስፋዬ አዉዓላ ናቸዉ።

"ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የፌደራል መንግሥት ኤርትራ ጧሯን ከኢትዮጵያ ግዛት ለቃ እንድትወጣ ይፋዊ የሆነ ጥሪ ማድረግ ሲችል ነው" ብለዋል፡፡

የድንበር ኮሚሽን ውሳኔንም በተመለከተ በሁለቱ ሀገራት መንግሥታት እንዲሁም በድንበር አካባቢ ያሉ የማህበረሰብ ክፍሎች በውይይት መፍታት እንዳለባቸውም አቶ ተስፋዬ አሳስበዋል።

"ነገር ግን ማንኛዉም ዉይይት ከመደረጉ ቀድሞ የኤርትራ ሰራዊት ከኢትዮጵያ ግዛት መዉጣት አለበት" ሲሉ አክለዋል።

"ከሰሜኑ ጦርነት ወዲህ የኤርትራ ሰራዊት ግማሽ ወረዳ ያህሉን የኢሮብ አካባቢን ጨምሮ ይዞ ይገኛል። በአልጀርሱ ስምምነት መሠረት የድንበር አካላይ ኮሚሽን በአየር ላይ ማስመሩ አሳውቆ ነበር" የሚሉት ደግሞ የቀድሞው ዲፕሎማት ዳያሞ ዳሌ ናቸዉ።

"ይህንን ለብዙ ጊዜ ሲንከባለል የመጣዉን ችግር መፍታት ወሳኝ ነው" ያሉት የቀድሞ ዲፕሎማቱ፤ "መሬት ላይ ድንበር ማካለል ባልተደረገበት የራስ አድርጎ መዉሰድ ተገቢ አይደለም" ብለዋል፡፡

የኤርትራ ሠራዊት 6ዐ በመቶ የሚሆነዉን የኢሮብ ማህበረሰብ መቆጣጠሩን የኢሮብ አኒና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ገልጿል።

01/12/2024



1 የመከላከያ አባል #እናትኔና #ልጅ ሲደፍር በህዝቡ ብርቱ ክትትል ተይዞ #ተረሽኗል የተረሸነዉ እዛዉ በአባሎቹ ነዉ #ይገባዋል አሰዳቢ

መንግስ በአማራ ክልል ህግ ከማስከበር ጎንለጎን #የአንዳድ ጋጠወጥ የመከላከያ አባል ላይ ህጋዊ እርምጃ ሊወስድ ይገባል ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምዕራብ ጎንደር ሀገረ ስብከት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤውን አጠናቀቀ፡፡(  ኅዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም)በዕለቱ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳ...
29/11/2024

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምዕራብ ጎንደር ሀገረ ስብከት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤውን አጠናቀቀ፡፡
( ኅዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም)
በዕለቱ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሰላማ፣ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አእላፍ አባ ኃይለ ማርያም፣ የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኀላፊዎች፣ የማኅበረ ሥላሴ አንድነት ገዳም አበምኔት፣ የወረዳ ቤተ ክህነት ሊቃነ ካህናት ሠራተኞች፣ የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም የማኀበረ ቅዱሳንና የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡

6ኛ ዓመት አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው ከኅዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጅምሮ ዛሬ ኅዳር 19 ቀን 2017 ዓ .ም የተጠናቀቀ ሲሆን በጉባኤው የሀገረ ስብከቱ እና የሁሉም ወረዳ ቤተ ክህነት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ተብሏል፡፡

በጉባኤው በካህናት ተልዕኮ እና መንፈሳዊ አገልግሎት፣ በመሪ ዕቅድ አተገባበር እንዲሁም በመረጃ አያያዝና እና አዘገጃጀት ዙሪያ ሥልጠና መሰጠቱ ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም በዚሁ ዕለት በሀገረ ስብከቱ ርእሰ ከተማ በ300 ካሬ ላይ ያረፈ ሁለገብ ባለ ሰባት ወለል ሕንፃ ለመገንባት ታስቦ በብፁዕ አቡነ ሰላማ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጧል::
ዘገባው የምዕራብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ነው።

የአማራ ገበሬ አሁናዊ ገጽታ!
27/11/2024

የአማራ ገበሬ አሁናዊ ገጽታ!

27/11/2024

ሩሲያ በዩክሬን ላይ የከፈተችው ወረራ ሦስተኛ ዓመቱ እየተቃረበ ነው። ሰሞኑን ባለፉት ሁለት ዓመታት ያልተጠቀመችባቸውን አዳዲስ መሣሪያዎችን ጥቅም ላይ አውላላች።

አዳዲሶቹ ሚሳዔሎች ፍጥነታቸው እና የሚጓዙት ርቀት እስከ ዛሬ ከተጠቀመቻቸው ጋር ሲነጻጸሩ በከፍተኛ እጥፍ ከፍ ያለ ነው።

ሩሲያ በዓለም ላይ ከፍተኛ መጠን ያለው የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እና ሚሳዔሎች ከታጠቁ አገራት መካከል በቀዳሚነት የምትጠቀስ ናት። ለመሆኑ ሩሲያን እንድትፈራ ያደረጓት እና በይዞታዋ የሚገኙ ምን ያህል የኒውክሌር አረሮች ታጥቃለች?

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ወቅታዊ መግለጫ*******የአማራ ክልል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ጽንፈኛ ኃይሎች በፈጠሩት ቀውስ የሰላም እጦት ገጥሞት የቆየ መሆኑ ይ...
24/11/2024

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ወቅታዊ መግለጫ
*******

የአማራ ክልል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች ጽንፈኛ ኃይሎች በፈጠሩት ቀውስ የሰላም እጦት ገጥሞት የቆየ መሆኑ ይታወቃል። በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሰው ጽንፈኛ ቡድን፣ በሕዝብ ስም እየማለ እታገልለታለሁ የሚለውን የአማራ ሕዝብ ለከፋ ጉዳት እና አሰቃቂ ችግሮች እየዳረገው ይገኛል።

ጽንፈኛው ቡድን የሰዎች እና የምርት እንቅስቃሴ በክልሉ ውስጥ እንዳይኖር መሰናክል ፈጥሯል፤ ሰው እያገተ የድኻ ገንዘብ ዘርፏል፤ ሕፃናትን በማገት የቤተሰብ ጥሪት ከማሟጠጥ ጀምሮ ያገታቸውን ሕፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሏል፤ አካባቢያቸው ሰላም እንዲሆን የጠየቁ የሀገር ሽማግሌዎችን አግቶ ገንዘባቸውን ከመዝረፍ በተጨማሪ በእንብርክክ አስኪዶ ገድሏቸዋል፤ አዳጊ ሕፃናትን ከትምህርት ገበታቸው እንዲነጠሉ አድርጓል፤ የሞያ ሥነ ምግባራቸውን እና ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት በትምህርት ገበታ ላይ የተገኙ መምህራንን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሏቸዋል፤ በመማሪያ ክፍሎች ውስጥ ቦንብ በማፈንዳት በተማሪዎች ላይ አካላዊ እና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት አድርሷል። ከዚህም በላይ የሆኑ፣ የሰሚን ጆሮ ጭው የሚያደርጉ ዘግናኝ ወንጀሎችን ፈጽሟል።

ይህ በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የሚንቀሳቀስ ጽንፈኛ ኃይል፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን እና የሕዝብ አብሮነትን የማይቀበል ኋላ ቀር ኃይል ነው። ይልቁኑም መቃቃርን የሚፈጥር፤ የኅብረተሰቡን ዕሴት በመሸርሸር እና አሰቃቂ ጥፋቶችን በመፈጸም የተጠመደ አረመኔያዊ ቡድን ነው።

በተመሳሳይ መልኩ በኦሮሚያ ክልል የሚንቀሳቀሰው ሽብርተኛው የሸኔ ቡድንም እታገልለታለሁ የሚለውን የኦሮሞ ሕዝብ እጅግ መራር እና አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ ግድያ፤ እገታ፤ ዝርፊያ፤ አፈና እየፈጸመበት ይገኛል። ሁለቱም ጽንፈኛ ኃይሎች ለአንድ አሰቃቂ ዓላማ ሁለት ቦታ የተሰለፉ ዕኩይ ቡድኖች ናቸው። እየፈጸሙት የሚገኙት እኩይ ተግባር በጦር ሜዳ የደረሰባቸውን ኪሳራ ለማስቀየሻ የሚፈጽሙት ነው። መቃብራቸው የሚቆፈረው በሕዝቦች ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ላይ በመሆኑ፣ ሕዝብን እርስ በርስ ማጋጨት እና ንጹሐንን መጨፍጨፍ የትግል ስልታቸው ነው።

እነዚህ መቃብራቸው የተማሰ፣ ልጣቸው የተራሰ ጽንፈኛ እና ሽብርተኛ ቡድኖች፤ ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን፣ ደራ ወረዳ ያደረሱትን ዘግናኝ እና አሰቃቂ ድርጊት የአማራ ክልል መንግሥት እና ሕዝብ በጽኑ ያወግዛሉ። ይህ ወንጀል ሰው የሆነ ፍጡር የማይፈጽመው የአውሬነት ተግባር ነው።

እነዚህ በጣዕረ ሞት ላይ የሚገኙ ጽንፈኛ ኃይሎች፣ ለዘመናት ማንም በማይበጥሰው የወንድማማች እና እኅትማማች ገመድ የተሣሠሩትን የአማራ እና የኦሮሞ ሕዝቦች ለመነጣጠል እና ወደ ግጭት ለማስገባት የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። ነገር ግን ሰላም ወዳዱ እና አርቆ አሳቢው ሕዝባችን ነገሮችን በጥንቃቄ እና በአስተውሎት በማየት፣ ድርጊታቸውን እና ዓላማቸውን ቀድሞ በመረዳት፣ የጽንፈኞችን እና የሤረኞችን እኩይ እና አጸያፊ ተግባር በንቃት እየመከተ ይገኛል።

የአማራ ሕዝብና የአማራ ክልል መንግሥት ከኦሮሞ ሕዝብና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት እንዲሁም ከፌዴራል መንግሥት ጋር በመሆን እነዚህ ዘግናኝ ተግባር የፈጸሙ ጽንፈኛ እና አሸባሪ ቡድኖች ለሕግ ቀርበው አስፈላጊውን ቅጣት እንዲያገኙ አበክረን እየሠራን መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።

የአማራ ክልላዊ መንግሥት ከውጭና ከውስጥ ጠላቶቻችን ጋር በጋራ የሚሠሩ፣ እንዲሁም እርስ በርሳቸው የሚናበቡ ጽንፈኛ ኃይሎች፤ በንጹሐን ዜጎች ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ በመፈጸም በሕዝቦች መካከል ግጭት ለመፍጠር ነዉ

በ2017 ዓ/ም አንደኛ ዙር የክለቦች ሻምፒዮና ተሳታፊ የሆነው የአዲስ አበባ ፖሊስ የቦክስ ቡድን በሴቶች አንደኛ እና በወንዶች ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ፡፡ *** አስራ ሁለት ክለቦች...
19/11/2024

በ2017 ዓ/ም አንደኛ ዙር የክለቦች ሻምፒዮና ተሳታፊ የሆነው የአዲስ አበባ ፖሊስ የቦክስ ቡድን በሴቶች አንደኛ እና በወንዶች ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ፡፡
***
አስራ ሁለት ክለቦችን ተሳታፊ ያደረገውና በኢትዮጵያ ቦክስ ፌደሬሽን በተዘጋጀው የ2017 ዓ/ም የአንደኛ ዙር የቦክስ የክለቦች ሻምፒዮና ተሳታፊ የሆነው የአዲስ አበባ ፖሊስ የቦክስ ቡድን በሴቶች ምድብ እና አራት ክለቦችን ተሳታፊ ባደረገው የአንደኛ ዙር ውድድር በሴቶች 2 ወርቅ፣ አንድ ብርና ሁለት ነሀስ ሜዳሊያዎችን በማምጣት የዙሩን ውድድር በአንደኝነት ማጠናቀቅ ችሏል፡፡

የሴቶች የቦክስ ቡድኑ በተለይም በ54 ኪ/ግ ሮማን አሰፋን ከኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ቡጢኛ ያገናኘ ሲሆን ተፋላሚዋን በመርታት አሸናፊነቷን ስታበስር፤ በ57 ኪ.ግ የተሳተፈችው ገነት ጸጋዬ እንደ ቡድን አጋሯ ሁሉ የኢትዮጵያ ወጣቶች አካዳሚ ተወዳዳሪን በመርታት ለክለቧ የወርቅ ሜዳሊያን ማምጣት ችላለች፡፡ ሌላዋ በውድድሩ ብቸኛውን የብር ሜዳሊያ በ50 ኪ.ግ ተወዳዳሪዋ ትዝታ ደመላሽ ማስመዝገብ የተቻለ ሲሆን በ48 ኪ.ግ እና በ52 ኪ.ግ ተሳታፊ የሆኑት ነፃነት ታምሩና ፅዮን ማሙሽ ከፍተኛ ተጋድሎን በማድረግ ለክለባቸው የነሀስ ሜዳሊያን ማጥለቅ ችለዋል፡፡

ሌላው ስምንት ክለቦችን ተሳታፊ ባደረገው በወንዶች ምድብ 3 የወርቅ፣ 4 የብር እና 3 የነሀስ ሜዳሊያ በማምጣት የዙሩን ውድድር በሁለተኛነት ማጠናቀቅም ተችሏል፡፡ የ48ኪ.ግ ተወዳዳሪው አቤል አባትዬ የኦሜድላ ተጋጣሚው ሲረታ፣ በ54 ኪ/ግ ደግሞ ደሳለኝ ሲሳይ የድሬዳዋ ከነማን ቡጠኛ እንዲሁም የ57 ኪ.ግ ተወዳዳሪው ሀይማኖት ደሳለኝ እርሱም በተመሳሳይ የድሬዳዋ ከነማውን ተፋላሚ በመርታት የወርቅ ሜዳሊያን ማምጣት ችለዋል፡፡

ብርቱ ፉክክር በታዩባቸው በ51 ኪ.ግ፣ በ57 ኪ.ግ፣ በ71 ኪ.ግ እና በ80 ኪ.ግ ውድድሮች ላይ የተሳተፉት ውጤታማዎቹ የአዲስ አበባ ፖሊስ ቡጢኞች ኢብራሒም አስራር፣ ተመስን ተስፋዬ፣ መስፍን ብሩና በረከት አድራሮ ተፋላሚዎቻቸውን በማሸነፍ የብር ሜዳሊያን ማጥለቅ ችለዋል፡፡
በ54 ኪ.ግ የተወዳደረው ኢዮብ ብሩ፣ በ48 ኪ.ግ ኪሊዮን ፍሬዘርና የ63.5 ኪ.ግ ተወዳዳሪው ዘርዓይ ድረስ እያንዳንዳቸው ለክለባቸው የነሀስ ሜዳሊያን ማስመዝገብ የቻሉ ሲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስ የቦክስ ቡድን በአንደኛ ዙር የቦክስ ክለቦች ሻምፒዮን ውድድር በአጠቃላይ 15 ሜዳሊያዎችን ማስመዝገብም ችሏል

አንድ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ባለስልጣናት ከግድያ ሙከራ መትረፋቸውን ገለፁ። በትግራይ ክልል የማእከላዊ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን መኣሾ ባለፈው እሁድ ለስራ ከአክሱም ከተማ ወደ መቐለ...
19/11/2024

አንድ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ባለስልጣናት ከግድያ ሙከራ መትረፋቸውን ገለፁ።

በትግራይ ክልል የማእከላዊ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን መኣሾ ባለፈው እሁድ ለስራ ከአክሱም ከተማ ወደ መቐለ በጉዞ ላይ እያሉ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች የግድያ ሙከራ እንደተደረገባቸው ተናግረዋል።

በዚህ የግድያ ሙከራ ባዠበእሳቸውም ይሁን በጠባቂያቸውና በመኪናቸው አሽከርካሪ ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን ገልፀዋል።

መኪናቸው አራት ቦታ በጥይት መመታቱን ተናግረው፣ የግድያ ሙከራው ማይቅነጠል በተባለ አካባቢ ላይ እንደተሞከረባቸው ገልፀዋል።

የፌደራል መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ ፀደቀየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል መንግስት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል፡፡6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር...
19/11/2024

የፌደራል መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ ፀደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል መንግስት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ስብሰባ ተካሂዷል።

ረቅቅ አዋጁ የመንግስት ሰራተኛ የሰው ሀይል ምልመላ ግልጸኝነት ባለው ውድድርና ብቃት ላይ እንዲመሰረት፣ የመንግስት መስሪያቤቶች የተሰጣቸውን ሀላፊነት በብቃት እንዲወጡ፣ ቀልጣፋ የመንግስት አገልግሎት ለመስጠት የሚስችል ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚረዳ ተገልጿል፡፡

የመንግስት ሰራተኞች አደራጀጀት ፍትሀዊና ቀልጣፋ በማድረግ የማህበረሰብን ፍላጎት የሚያሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል፡፡

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when H_Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share