Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ

Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ በማህበራዊ: በባህልና ኪነጥበብ ጉዳዬች ላይ የሚያተኩር ገፅ

መጻሕፍት እንዴት ይነበቡ?  ክፍል  ፩=======================* ኑ ! ስለ ንባብ ሐሳብ ተካፈሉ፤ ሐሳብ አካፍሉ!ዋልያ መፃሕፍት ነገረ ንባብ በየዕውቀት ዘርፉ - መጻሕፍት እንዴት...
09/10/2025

መጻሕፍት እንዴት ይነበቡ? ክፍል ፩
=======================

* ኑ ! ስለ ንባብ ሐሳብ ተካፈሉ፤ ሐሳብ አካፍሉ!

ዋልያ መፃሕፍት ነገረ ንባብ በየዕውቀት ዘርፉ - መጻሕፍት እንዴት ይነበቡ? በሚል ርዕስ ክፍል አንድ ፕሮግራም አሰናድተናል። በዚህ የዉይይት ፕሮግራም በሙያቸው የታወቁ የሥነ ጽሑፍ፣ የፍልስፍና፣ የፖለቲካ ሳይንስ እና የታሪክ ተመራማሪዎች የመጻሕፍት ንባብ በየሙያው እንዴት እንደሚለዋወጥ እና መጻሕፍት ሁሉ በአንድ መንገድ ብቻ እንደማይነበቡ ይተነትኑልናል፡፡

ስለ አነባበብ ጥበብ ባዘጋጀነው ልዩ የፓነል ውይይት ከእኛ ጋር ያሳልፉ!

አቅራቢዎች:
=========
ኃይሉ ሀብቱ (ተባባሪ ፕርፌሰር)
ደራሲ አለማየሁ ገላጋይ
ዳኛቸው አሰፋ ዶ/ር
አሞን በቀለ ዶ/ር
መሐመድ እድሪስ ዶ/ር

አወያይ
====
ቴዎድሮስ አጥላው

ቀን :-ቅዳሜ ጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓም

ሰዓት : - ከሰዓት 8:00 ጀምሮ

ቦታ: 4ኪሎ ኢክላስ ህንፃ ዋልያ መፃሕፍት አዳራሽ

ኑ ! ስለ ንባብ ሐሳብ ተካፈሉ፤ ሐሳብ አካፍሉ!

የመንሱር እና ብስራት ሬዲዮ ውዝግብ ========================የእግር ኳስ ስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ውዝግብ ውስጥ እንደገባ አስታወቀ።ጋዜጠኛ መንሱር...
09/10/2025

የመንሱር እና ብስራት ሬዲዮ ውዝግብ
========================

የእግር ኳስ ስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ውዝግብ ውስጥ እንደገባ አስታወቀ።

ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ ከሬድዮ ጣቢያው ጋር ስለተፈጠረው ውዝግብ ተከታዩን ብሏል"የብስራት ኤፍ ኤም 101.1 ፓርትነር በመሆን ከጣቢያው ጋር በትብብር ''ብስራት-ስፖርት" የተሰኘውን ፕሮግራም ለ12 ዓመታት ሳቀርብ መቆየቴ ይታወቃል።

ይሁንና በእነዚህ ሁለት ቀናት (ረቡዕ እና ሐሙስ መስከረም 28 እና 29) ከእኔ የስራ ትጋት ጋርባልተያያዘ (በግሌ ልፈታው በማልችለው ምክንያት) ከጣቢያው ጋር ያልተግባባንባቸው ጉዳዮች ተፈጥረዋል።

እነዚህ ልዩነቶች መፍትሔ እስኪያገኙ ድረስ (ዛሬ በማለዳ ያስተዋወቅኳችሁን ፕሮግራም ጨምሮ) "ብስራት-ስፖርት" ከሬድዮ አየር ላይ እንደወረደ ስገልጽላችሁ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ነው" ሲል ተናግሯል።

ሠዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ የጥበብ ስራዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኒሶታ እያሳየ ነዉ============================ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ ስነ-ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት በ1...
05/10/2025

ሠዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ የጥበብ ስራዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኒሶታ እያሳየ ነዉ
============================

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ ስነ-ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት በ1990 ዓ.ም. የተመረቀውና በልዩ የታሪክ አሳሳሉ የሚታወቀው ሰዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ፣ ሥራዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኒሶታ ለሚገኙ የጥበብ አፍቃሪዎች እያሳየ መሆኑን አስታወቀ።

ሠዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ ከ27 ጊዜ በላይ በግል እንዲሁም ከ47 ጊዜ በላይ በቡድን በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶችና የአውሮፓ ሀገራት ሥራዎቹን በማቅረብ ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈ ሲሆን፣ በሚኒሶታ እያደረገ ያለው ይህ የመጀመሪያ ኤግዚቢሽኑ ተመልካቾቹን ቀልብ ለመሳብ ችሏል።። ሥራዎቹን ካሳየባቸው ታዋቂ ቦታዎች መካከል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም፣ በአሊያንስ ኢትዮ-ፍራንሴዝ፣ በኒውዮርክ እና በአትላንታ በሚገኙ ጋለሪዎች እንዲሁም በቤልጂየም ብራሰልስ ይገኙበታል።

በሠዓሊነት ባሳለፈባቸው ከ28 ዓመታት በላይ፣ በተለይ በዓድዋ ጦርነትና ሌሎች ሀገራዊ ስሜትን በሚቀሰቅሱ (patriotism) ርዕሶች ላይ በሰራቸው ሥራዎቹና በመስመር አጠቃቀሙ ይታወቃል።

ከ25 በላይ የዘይትና የአክሪሊክ ቀለም ሥዕሎችን የያዘው ይህ የሥዕል ትርዒት፣ ላለፉት 2 ቀናት ሲታይ ቆይቶ ዛሬ ምሽት እንደሚጠናቀቅ የገለፀ ሲሆን፣ ህጻናትና አዋቂዎች ሳይለዩ ሁሉም የማህበረሰቡ አባላት እንዲጎበኙት ሰዓሊው የአክብሮት ጥሪውን አቅርቧል።

ቦታ: HILLTOP EVENT CENTER
421 Marie Ave, South Saint Paul, MN 55075

የሚቆይበት ጊዜ: ዛሬ የመጨረሻው ነው።

ይህ ኤግዚቢሽን በሚኒሶታ ለሚኖሩ የጥበብ አፍቃሪዎችና የማህበረሰቡ አባላት፣ የሰዓሊውን የረጅም ጊዜ ልምድና የፈጠራ ችሎታ በአካል ለመመልከት ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሯል።ሲል ዘ-ሐበሻ በፌስቡክ ገፁ ዘግቧል።

30/09/2025
30/09/2025
30/09/2025
የአቡዬው አገልጋይ የመጽሀፍ ምረቃ ግብዣ============================በገረገራ ኩሪሳ ኪዳነ ምሕረት የተጀመረው የክህነት አገልግሎት ጎንደር ዘልቆ እፍታ የጥበብ መረቁን ለሀገሬው...
29/09/2025

የአቡዬው አገልጋይ የመጽሀፍ ምረቃ ግብዣ
============================

በገረገራ ኩሪሳ ኪዳነ ምሕረት የተጀመረው የክህነት አገልግሎት ጎንደር ዘልቆ እፍታ የጥበብ መረቁን ለሀገሬው አቃምሰው ለዘመናት የማይደበዝዝ አሻራ አትመው ቀሪውን ለአዲስአበባ በማለት ከብዙ በጥቂቱ በቀበና አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ፣ በማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ፣ በቅዱስ ዑራኤል ፣በደብረ አሚን አቡነ ተ/ሐይማኖት፣በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ዋና አስተዳዳሪ በመሆን ያገለገሉባቸው አብያተ ቤተክርስቲያናት ናቸው !
እንደ ፍም እሳት እየጋመ የመጣው ታታሪው የወንጌል ገበሬ አቅም ደቀ-መዛሙሩቱን ለማብዛት ወደ ቅድስት ስላሤ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ በመሠየም አያሌ ሊቃውንትን ለማፍራት ችለዋል።
መልአከ ገነት አባ ምናሴ ዘለቀ ባህር ተሻግረውም በሰሜን አሜሪካ የሚጠበቅባቸውን የአባትነት ፋና ወጊነትም የበኩላቸውን ተወጥተው ለአዲሱ ትውልድ አስተላልፈው ወደሚወዷት ሀገራቸው በክብርና በሽልማት ለመሸኘት በቅተዋል።
በዘጠና አምስተኛው የዕድሜ ዘመናቸው ላይ የሚገኙት መልአከ ገነት አባ ምናሴ ዘለቀ ጠቅለል ያለው የሕይወት ታሪካቸው ጥንቅቅ ባለ መልኩ ተሰንዶ እነሆ መጽሐፉ የፊታችን እሑድ በ 25/01/18 ዓ.ም በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ስላሤ ካቴድራል አዳራሽ ከቀኑ 7፡30 ላይ ይመረቃል !!

ዶ/ር ደረጀ ዘለቀ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ እና የህፃና ት/ቤት በቤተ ጉራጌ በይፋ ተመርቆ ተከፈተ============================(ይትባረክ ዋለልኘ)* የኢትዮጽያዊያን የመፅሐፍ እና...
29/09/2025

ዶ/ር ደረጀ ዘለቀ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ እና የህፃና ት/ቤት በቤተ ጉራጌ በይፋ ተመርቆ ተከፈተ
============================

(ይትባረክ ዋለልኘ)

* የኢትዮጽያዊያን የመፅሐፍ እና የማስተማሪያ ቁሳቁሶች ድጋፍ እንዲያደርግላቸዉ ጠይቀዋል

የአንጋፋው ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶ/ር ደረጄ ዘለቀ በህይወት በነበረበት ወቅት ለሐገርና ለሕዝብ ይጠቅማል ከሚላቸዉ መሰረታዊ ጉዳዮች መካከል ትምህርት እና ለንባብ እንደሆነ የራሱን የህይወት ልምድ ጠቅሶ ይናገር ነበር። በመሆኑም ይህን ምሁር በስራዎቹ ለማሰብና ለማስታወስ ይረዳ ዘንድ የዶ/ር ደረጀ ዘለቀ ጓደኞቹ በሁሉም የሐገሪቱ ክልሎች ለሚገኙ የገጠር ቀበሌዎች በስሙ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ በመገንባትና በማደራጀት ለህዝብ አገልግሎት እንዲዉል ለማድረግ ዶ/ር ደረጀ ዘለቀ ከዚህ ዓለም የተለየበትን አንደኛ አመት ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የመታሰቢያ ስራዎች ሲሰሩ ሲቆይተዋል ።

የዚህ የመታሰቢያ ፕሮግራም አንዱ አካል የሆነዉ በማዕከላዊ ኢትዬጽያ ክልል ጉራጌ ዞን ቸሀ ወረዳ የፈረዝየ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ልዩ ቦታ አንዛናባጥ የዶ/ር ደረጄ ዘለቀ የቅርብ ጓደኛ በሆነዉ በአቶ ሚኪያስ ተሬሳ የተገነባዉ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ እና የህፃና ት/ቤት መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም የአካባቢዉ ህብረተሰብ በተገኙበት ለህፃናት የመማሪያ ቁሳቁሶችን እና ለቤተመፅሐፍቱ በርካታ መፅሐፍትን በስጦታ በማበርከት በይፋ ተመርቋል። በዚህ የምርቃት ፕሮግራም ላይ የእምድብር የፈረዝየ ቀበሌ ገበሬ ማህበር የአካባቢ የሐገር ሽማግሌዎች ወጣቶች የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል::ነዋሪዎችም በአካባቢያቸው ይህን አይነት ለትውልዱ የሚተርፍ ታላቅ ስራ በመሰራቱ እጅግ መደሰታቸውን የገለፁ ሶሆን ይህን ታላቅ ስራ ለፈፀሙ ኢትዮጽያዊያን በአካባቢው ባህል መሰረት በሶስት የሐገር ሾማግሌዎች ምርቃት አድርገዋል።

የመጀመሪያዉን “የዶ/ር ደረጄ ዘለቀ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ እና የቅድመ መደበኛ የህፃና ት/ቤት”ን የምርቃት ፕሮግራም ላይ ግንባታዉን ያደረገዉ አቶ ሚኪያስ ተሬሳ ጨሞሮ የዶ/ር ደረጀ ዘለቀ የመታሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጆች የሆኑት አቶ በፍቃዱ ቸርነት፣ ሠዓሊና ገጣሚ ቸርነት ወ/ገብርኤል፣አቶ ሲሳይ ተፈራ፣እና እኔ ይትባረክ ዋለልኘ በቦታዉ ተገኘተን የዶ/ር ደረጀ ዘለቀ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ እና የህፃና ት/ቤትን መርቀን አስከፍተናል።እንዲሁም የዶ/ር ደረጀ ዘለቀ ቤተሰቦችን ጨምሮ ከተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶ በስጦታ የሰበሰብናቸዉን ለህፃናቱ መማሪያ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን ( ጥቂት የህጻናት ወንበሮች፣4 ካርቶን ደብተር፣በመቶዎች የሚቇጠሩ እርሳስ፣ላዺስ እና እስክርቢቶዎች) እና ለቤተመፅሐፍቱ የሚሆኑ መፅሐፍትን በስጦታ አበርክተናል።በተጨማሪም ቤተመፅሐፍቱን እና ት/ቤቱን በኃላፊነት የሚያስተዳድሩ ስድስት በአካባቢው ነዋሪዎች የተመረጡ አንድ ኮሚቴ በመመስረት ሙሉ ንብረቶቹን ለእነዚሁ ኮሚቴዎች እንዲረከቡ እና እንዲያስተዳድሩ አድርገናል።

ይህን የዶ/ር ደረጄ ዘለቀ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ እና የቅድመ መደበኛ የህፃና ት/ቤት”ን እውን ለማድረግ ግንባታዉን በኃላፊነት ተከታትሎ ያሰራልን የአካባቢዉ ነዋሪዉን አቶ ጀማል ስባኒ ንስራነ እና የመፀሐፍ እና የቁሳቁስ ድጋፍ ያደረጋችሁትን ሁሉ በጣም እናመሰግናለን። በተለይ ከምርቃቱ አንድ ሳምንት በፊት እቦታዉ ድረስ በመሄድ የመፅሐፍ ድጋፍ ያደረገዉ ከቤት እስከ ከተማ ፕሮግራም አዘጋጁ ማህደር። እንዲሁም ዋሊያ ቡክ፣እነሆ መፅሐፍ፣ጃፋር መፅሐፍ፣ሀሁ መፅሐፍ እና የሐብከ ብርሃኔን ከልብ እናመሰግናለን።

ይህ የመታሰቢያ ቤተመፅሐፍ እና የቅድመ መደበኛ የህፃና ት/ቤትም በተሟላ መልኩ በሙሉ አቅም ለተጠቃሚዎች አገልግሎት ይሰጥ ዘንድ አሁንም ለህፃናቱ የመሚሪያና የማስተማሪያ ቁሳቁሶች ለቤተመፅሐፉ ሼልፎች በእጅጉ ያስፈልጋቸዋል::
በመሆኑም የዶ/ር ደረጄ ዘለቀ ወዳጆች ተማሪዎች አድናቂዎች እና ለንባብ ለህፃናት ትምህርት ግድ የሚላችሁ ኢትዮጽያዊያን ግለሰቦችና ድርጅቶች ሁሉ አንድም ሁለትም ሳትሉ አቅማችሁ በፈቀደዉ መጠን የመፅሐፍ ድጋፍ እንድታደርጉ በማክበር እንጠይቃለን።

በቀጣይነት በቅርቡ በሚመሰረተዉ”በዶ/ር ደረጀ ዘለቀ ፋዉንዴሸን” አማካኘነት ደግሞ በአማራ፣ በኦሮሚያ፣ በትግራይ እና በሁሉም ክልሎች የገጠር ቀበሌዎች ላይ ቤተመፅሐፍና የቅድመ መደበኛ የህፃና ት/ቤት በየአመቱ እንደሚከፈት የፋዉንዴሸኑ ጊዜያዊ ኮሚቴዎች እና ጓደኞቹ በዚህ ፕሮግራም ላይ ገልፀዋል።

ድጋፍ ማድረግ የምትሹ በዚህ ስልክ በመደወል እና በፁሑፍ [email protected] ኢሜይል መልዕክት በመላክ ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ።

+251 91 163 2945
+251910102299

( ጓደኞቹ)

20/09/2025

"ለዶ/ር ደረጀ ዘለቀ መታሰቢያ ቤተ መጸሐፍ” ማደራጃ የመፅሐፍ ድጋፍ ጥሪ

ይትባረክ ዋለልኘ

| የአንጋፋው ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶ/ር ደረጀ ዘለቀ ከዚህ ዓለም የተለየበትን አንደኛ አመት ምክንያት በማድረግ ከነሐሴ 17 ዓ ም ጀምሮ የተለያዩ የመታሰቢያ ዝግጅቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል ።

ዶ/ር ደረጀ ዘለቀን የተለያዩ የህይወት ገፅታዎችንና ምዕራፎች ከሚያስታዉሱ የመታሰቢያ ዝግጅቶች መካከል “ዶ/ር ደረጄ ዘለቀ መታሰቢያ ቤተመፅሐፍ” በሁሉም የሐገሪቱ ክፍል መክፈት አንዱ ነዉ።

ዶ/ር ደረጄ ዘለቀ በህይወት በነበረበት ወቅት ለሐገርና ለሕዝብ ይጠቅማል ከሚላቸዉ መሰረታዊ ጉዳዮች መካከል ትምህርት እና ለንባብ ናቸዉ ይል ነበር።

በመሆኑም ይህን ታላቅ ምሁር ዘወትር በስራዎቹ ለማሰብና ለማስታወስ ይረዳ ዘንድ በኢትዮጽያ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ገጠሮች ዉስጥ ጓደኞቹ በስሙ “የዶ/ር ደረጄ ዘለቀ መታሰቢያ ቤተመፅሐፍ” በሚል ገንብተዉና አደራጅተዉ ለህዝብ አገልግሎት እንዲዉል ማድረግ ነዉ።

የዚህ አመት የመታሰቢያ ዝግጅት አንዱ አካል የሆነዉ በቤተ ጉራጌ የተገነባዉ “ዶ/ር ደረጄ ዘለቀ መታሰቢያ ቤተመፅሐፍ”አንዱ ነዉ።

ይህ በቤተ ጉራጌ ገጠር ዉስጥ የተገነባዉ የመጀመሪያዉ “ ዶ/ር ደረጄ ዘለቀ መታሰቢያ ቤተመፅሐፍ” መስከረም 17 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ተመርቆ ለህዝብ አገልግሎት ይዉላል። ይህ ቤተመፅሐፍ በተሟላ መልኩ ለተጠቃሚዎች አገልግሎት ይሰጥ ዘንድ ለሶስት ቀን የሚቆይ የመፅሐፍ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል።

በመሆኑም ይህን ቤተመፅሐፍ በተለያዩ መፅሐፍት ይደራጅ ዘንድ የዶ/ር ደረጄ ዘለቀ ወዳጆች ተማሪዎች አድናቂዎች እና ለንባብ ግድ የሚላችሁ ግለሰቦችና ድርጅቶች ሁሉ አንድም ሁለትም ሳትሉ አቅማችሁ በፈቀደዉ መጠን እስከ መስከረም 13 ቀን ድረስ የመፅሐፍ ድጋፍ እንድታደርጉ በማክበር እንጠይቃለን።

ድጋፍ ማድረግ አራት ኪሎ ግንፍሌ ድልድይ ስር በሚገኝው አዲሱ “አማራጭ የማሰቢያ ስፋራ” አዳራሽ ድረስ በመምጣት ድጋፍ ማድረግ ትችላላችሁ !! ወይም በዚህ ስልክ በመደወል መረጃ ማግኝት ትችላላችሁ።
+251 91 163 2945

( ጓደኞቹ)

የፋና ላምሮት  አሸናፊው  የ200 ካሬ ሜትር  ቦታ ተሸለመ================================የመጪው ዘመን የሙዚቃ ንጉስ እንደሚሆን ያስመሰከረው ከደቡብ ጎንደር ዞን ጋይንት ...
20/09/2025

የፋና ላምሮት አሸናፊው የ200 ካሬ ሜትር ቦታ ተሸለመ
================================

የመጪው ዘመን የሙዚቃ ንጉስ እንደሚሆን ያስመሰከረው ከደቡብ ጎንደር ዞን ጋይንት ንፋስ መውጫ የተገኘው ጴጥሮስ ማስረሻ፣ በፋና ላምሮት የፍጻሜ ውድድር አንደኛ መውጣቱን ተከትሎ፣ የንፋስ መውጫ ከተማ አስተዳደር የ200 ካሬ ሜትር የቤት መስሪያ ቦታ ሸልሞታል።

ጴጥሮስ ማስረሻ 1.5 ሚሊዮን ብርና ዋንጫ መሸለሙ ይታወቃል፡፡

Address

Addis Ababa

Telephone

+251910102299

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ:

Share