Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ

Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ በማህበራዊ: በባህልና ኪነጥበብ ጉዳዬች ላይ የሚያተኩር ገፅ

27/10/2025
የማይረቡ ነገሮች ላይ ውደቁ ብሎ የፈረደብን ማን ይሆን ? ደጋግሜ የምላችሁ  ሰይፉ ፋንታሁን ይህ ነው ።==================================(ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ) ትናንት ...
27/10/2025

የማይረቡ ነገሮች ላይ ውደቁ ብሎ የፈረደብን ማን ይሆን ? ደጋግሜ የምላችሁ ሰይፉ ፋንታሁን ይህ ነው ።
==================================

(ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ)


ትናንት በሰይፉ በኢቢኤስ ከቀረቡ ፕሮግራሞች የእነዚህ ሁለት ልበ ብርሀን ህጻናትና ከሰውና ከብረት ተቀላቅላ የተሰራችው እናታቸው ጉዳይ ትኩረቴን ስቦታል ። በጣም ተገረምኩ ። የተገረምኩት ግን ለእነዚህ ልጆችና ለእናታቸው በተደረገው አይደለም ። ከእሱ በላይ እኛ ትኩረት የምንሰጥበት ርዕሰ ጉዳይ ልዩነት ይገርማል ። ትልቁን ጉዳይ ቸል ብለን ረብ የለሹ ላይ መንጠላጠላችን " ምን ሆነን ነው ? " ያስብላል ። ሰይፉ ፋንታሁን እነዚህን ልጆች ወደ ሚዲያው ከማምጣት ጀምሮ በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ተሰብስቦ የዓይናቸው ህክምና ጉዳይ ተጀምሮ ህክምናውን ቢያገኙም ውጤቱ ሳይሳካ ቀርቷል ። ሰይፉና አድናቂዎቹ ፣ የፕሮግራሙ ቤተሰቦችና በሰይፉ በኢቢኤስ መልዕክቱ የደሰረሳቸው ሁሉ የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል ።

ወዳጃችን ሰይፉ ፋንታሁን የእነ ሶሊያናን ጉዳይ እንዲሁ የአንድ ፕሮግራም አየር መሙያ አድርጎ አልተወውም ። ብረቷ ሴት በችግር እንዳይፈታ " ከፕሮግራሙ ተከታታዮች " ጋር ተባብሮ የመኖሪያ ቤት ኪራይ እንዳያስቸግራት ቪላ ቤት ፣ ልጆቿን ከቤት ት/ቤት ወይም አስፈላጊ ቦታ መውሰጃና መመለሻ እንዳይቸግራት ዘመናዊ መኪና ፣ ቤትና መኪና ቢኖራትም እሱ ብቻውን መተዳደሪያ ስለማይሆን ኬክ ቤት ከፍተው ሰጧት ። አንድ ጉርሻ እና 1,000.00 ብር የሰጠ ሁሉ በቴሌቪዥን እየቀረጹ ተረጂዎቹን መከራ በሚያሳዩበት በዚህ ጊዜ ሰይፉ ፋንታሁን ቢደመር ከ10,000,000.00 ብር በላይ የሚያወጣን ስጦታ በቀልድና በጨዋታ አዋዝቶ ትልቁን ጉዳይ እንደ ቀልድ ነው ያለፈው ። ሰይፉ ፋንታሁ አይናገረውም እንጂ " አንዳንድ የፕሮግራሜ ተመልካቾች " እያለ ለተቸገሩ ከሚሰጠው ጥቂት የማይባለውን ራሱ ሰይፉ ፋንታሁን ከኪሱ እያወጣ የሚያደርገው ነው ። እዚህ የቤት ፣ የመኪናና የኬክ ቤት ስጦታ ላይ ሰይፉ ፋንታሁን ቀላል በማይባል ደረጃ እንደሚኖርበት አምናለሁ ።

አስባችሁታል ለእነዚህ ቤተሰቦች እንደ ቀላል የተሰጣቸው ቤት ፣ መኪና እና ኬክ ቤት ነው ። የሰውን ሕይወት የሚያነሳው አንድ አምላክ ቢሆንም ሰይፉ ፋንታሁን ስድስት ሆነው አንድ ክፍል ውስጥ ተደራርበው ይተኙ የነበሩ ሰዎችን ነው የየራሳቸው ክፍል እንዲኖራቸው ያደረገው ። ሦስት ታማሚ ልጆቿን ባልተመቻቸ ሁኔታ ታንቀሳቅስ የነበረች ሴት ናት ድንገት የራሷ መኪና የኖራት ። ምንም አይነት መተዳደሪያ ያልነበራት፣ ምናልባትም ልጆቿን ኬክ መጋበዝ የሚቸግራት ሴት ናት ድንገት ኬክ ቤት የኖራት ። ይህ ተዐምር ሆኖ ሳለ ፣ ካሁን ቀደም በየትኛውም የሚዲያ ተቋም ያልተደረገ ሆኖ ሳለ የፌስቡኩ ቤተሰብ ምንም ሳይለው ( ምናልባት ጥቂቶች አንስተውት ቢሆን እንጂ ) ያለፈው ። ከእሱ ይልቅ የእነዚያ አታካች ጥንዶች ወሬ ትኩረት ተሰጥቶታል ። ራሱ ሰይፉ እነዚህን ጥንዶች ከዚህ ታላቅ ተግባር ጋር ደብሎ ማቅረቡ ልክ አልነበረም ።

የማህበራዊ ሚዲያው ቤተሰብ ምን ትኩረቱን እንደሚስበው ይታወቃል ። ዩቱዩብ ላይ ተመልካች ለማግኘት ካልሆነ እነሱን ማቅረብ ቢያንስ የትናንቱን ሰይፉ በኢቢኤስን አይመጥንም ። እኔ በግሌ ምንም ቢሉ ላያቸው ፈቃደኛ አይደለሁም ። እውነት ግን እንደ ህብረተሰብ ምንድነው የነካን ? የማይረቡ ነገሮች ላይ ውደቁ ብሎ የፈረደብን ማን ይሆን ? እንዴት ከወራት በፊት ማህበራዊ ሚዲያውን በትኩረት የወጠረው ሙሉ ቤተሰብ ሕይወት በአንድ ፕሮግራም ምክንያት ፈርሶ የመሰራት ያህል ሲለወጥ እንዴት ምንም ሳይመስለን ቀረ ? በመካካድ አጀንዳ መሆን የሚፈልጉን ተመሳሳይ ጠባይ ያላቸው ጥንዶች እንዴት እነሱ ትኩረታችንን ሳቡት ?

እንዴት ሰይፉ ፋንታሁንን ከልባችን አላመሰገነውም ? ይህ እኮ አንድ ፕሮግራም ሳይሆን ዓይናችን እያየ የተሰራ ተዐምር ነው ። ኮሚቴ ተዋቅሮና የወራት ሩጫን ጠይቆ ፣ ሚዲያውን አጭሶ በትልቅ መርሐ ግብር የሚደረገውን ስጦታ እኮ ነው ሰይፉ ፋንታሁን እንደዋዛ ሰጥቶ ዞር ያለው ። እንዴት እሱ በባለውለተኛነት ባይጮህ እኛ " እናመሰግንሀለን " አንለውም ። ይገርማልም ፣ ያሳዝናልም ። ወንድም ዓለም ሰይፉ ፋንታሁ ፋንታሁን በቃላት ላመሰግንህ አልችልም ። እግዚአብሔር ስራህን ይየው ። በራስህ ብቻም ሳይሆን በትዳርህና በልጆችህ ይከፈልህ ።

  ኮሜዲ ቲያትር በኬንያ - ናይሮቢ************************************የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 15 ቀን 2015 ዓ/ም ኬኒያ ናይሮቢ በታላቁ ኬ.አይ.ሲ.ሲ. አዳራሽ ። K...
22/10/2025

ኮሜዲ ቲያትር በኬንያ - ናይሮቢ
************************************
የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 15 ቀን 2015 ዓ/ም ኬኒያ ናይሮቢ በታላቁ ኬ.አይ.ሲ.ሲ. አዳራሽ ።
Kenya, Nairobi
KICC Hall
Saturday October 25/2025 G.C
5:00 pm

በኬኒያ ናይሮቢ እና አካበቢው ያለችሁ ኢትዮዽያውያን በፍጹም መጠራጠር የሌለባችሁ " ወደ ማዶ " በድርሰት ፣ በዝግጅት ፣ በትወና ሙሉ ሆኖ ተሰናድቶ ይመጣላችኋል ። ተጀምሮ እስኪያልቅ ሳቅ ከእናንንተ ጋር ይሆናል ። ቁምነገሩም ሙሉ ነው ። ከሁሉም በላይ የሀገር ቤት እና የባህር ማዶ እውነታዎችን ፣ ራሳችሁንና በእናንተና ሀገር ቤት ባለው ቤተሰባችሁ ፣ ፍቅረኛችሁ መሐል ያለውን እውነታ ታዩበታላችሁ ። አትጠራጠሩ ግን ዘና እያላችሁ ቁምነገር ትገበዩበታላችሁ ።

የመግቢያ ትኬቶች ፦

👉 በሀበሻ ምግብ ቤት (Tolcha)
👉 አልማዝ Shop (ፒንኪ Lady)
👉 ሃብታሙ Shop (ፒንኪ Lady)
👉 ሰሎሜ (ኦልምፒያ Caffe ፓናጋኒ)
👉 Abebaw (Jamhuri) ይገኛል

ኑና አብረን ፈታ እያልን በሳቅ እናምሽ

Nairobi News

የእኛ እና የትያትር ወዳጆች ይህን መልዕክት በማድረግ ወዳጅነታችሁን አሳዩን ።

ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በጂቡቲ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ                                                            ============================...
14/10/2025

ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በጂቡቲ አምባሳደር ሆነው ተሾሙ
================================

የቀድሞው የኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በጂቡቲ ሪፐብሊክ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው መሾማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

አምባሳደር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ዛሬ ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም. ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ፊት ቀርበው የሹመት ደብዳቤያቸውን በመቀበል ቃለ መሐላ መፈጸማቸውን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ገልጿል።
ከፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤያቸውን የተቀበሉት አምባሳደር ለገሰ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ቴዎድሮስ ምህረት ፊት ቀርበው ቃለ መሐላ ፈጽመዋል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዎን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር ብርሃኑ ፀጋዬ መገኘታቸው ተገልጿል።
ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) አምባሳደር ሆነው ከመሾማቸው በፊት ለአራት ዓመታት ያህል የፌደራል መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ሆነው ሠርተዋል።
አምባሳደር ለገሰ ቱሉ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ተደርገው መሾማቸው የተገለጸው ባለፈው ዓመት ማብቂያ ላይ ነበር።
የቀድሞው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበሩት አምባሳደር ለገሰ፤ የኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትር ሆነው ከመሾማቸው በፊት መስከረም 2011 ዓ.ም. በትምህርት ምክንያት ከፓርቲ ኃላፊነት ተሰናብተው ነበር።
የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን አጠናቅቀው ከተመለሱ በኋላ የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ሆነው የተሾሙ ሲሆን ለአራት ዓመታት ያህል ካገለገሉ በኋላ አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል።ሲል ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።

ምስል- የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

የቤተ ክርስቲያኗ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ዓለም አቀፍ መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ===============================     * ጉባኤው ለቀጣዮቹ 5 ቀናት ይቀጥላልየኢትዮጵያ ኦር...
14/10/2025

የቤተ ክርስቲያኗ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ዓለም
አቀፍ መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀመረ

===============================

* ጉባኤው ለቀጣዮቹ 5 ቀናት ይቀጥላል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ 44ኛው ዓለም አቀፍ መደበኛ ስብሰባ መካሄድ ጀምሯል፡፡

በጉባኤው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስን ጨምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ አህጉረ ስብከት ተወካዮች እየተሳተፉ ሲሆን ፓትርያርኩ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በጥበብ በመምራት፣ ለመጭው ትውልድ ማሻገር እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል፡፡

በጉባኤው ላይ በቤተ ክርስቲያንና ገዳማት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮች ቀርበው የመፍትሔ ሐሳቦች ይሰጥባቸዋል የተባለ ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያኗ ያከናወነቻቸው ተግባራት ቀርበው ውይይት እንደሚደረግባቸውም ተጠቁሟል፡፡


በየዓመቱ በጥቅምት ወር በሚካሔደው በዚህ ጉባኤ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚጠቅሙ፣ ለመንፈሳዊ አስተዳደሯም የሚበጁ መሠረታዊ ጉዳዮች ይቀርባሉ። በሚቀርቡት ሪፖርቶች ላይም ውይይትና የልምድ ልውውጥ ተደርጎ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ይሸለማሉ፤ ዝቅተኛ አገልግሎት ይዘው የመጡ ደግሞ ከጉባኤው ልምድ ቀስመው አገልግሎታቸውን እንዲያሻሽሉ ይመከራሉ ተብሏል።

መደበኛ ስብሰባው ከዛሬ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ቀናት እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡

መጻሕፍት እንዴት ይነበቡ?  ክፍል  ፩=======================* ኑ ! ስለ ንባብ ሐሳብ ተካፈሉ፤ ሐሳብ አካፍሉ!ዋልያ መፃሕፍት ነገረ ንባብ በየዕውቀት ዘርፉ - መጻሕፍት እንዴት...
09/10/2025

መጻሕፍት እንዴት ይነበቡ? ክፍል ፩
=======================

* ኑ ! ስለ ንባብ ሐሳብ ተካፈሉ፤ ሐሳብ አካፍሉ!

ዋልያ መፃሕፍት ነገረ ንባብ በየዕውቀት ዘርፉ - መጻሕፍት እንዴት ይነበቡ? በሚል ርዕስ ክፍል አንድ ፕሮግራም አሰናድተናል። በዚህ የዉይይት ፕሮግራም በሙያቸው የታወቁ የሥነ ጽሑፍ፣ የፍልስፍና፣ የፖለቲካ ሳይንስ እና የታሪክ ተመራማሪዎች የመጻሕፍት ንባብ በየሙያው እንዴት እንደሚለዋወጥ እና መጻሕፍት ሁሉ በአንድ መንገድ ብቻ እንደማይነበቡ ይተነትኑልናል፡፡

ስለ አነባበብ ጥበብ ባዘጋጀነው ልዩ የፓነል ውይይት ከእኛ ጋር ያሳልፉ!

አቅራቢዎች:
=========
ኃይሉ ሀብቱ (ተባባሪ ፕርፌሰር)
ደራሲ አለማየሁ ገላጋይ
ዳኛቸው አሰፋ ዶ/ር
አሞን በቀለ ዶ/ር
መሐመድ እድሪስ ዶ/ር

አወያይ
====
ቴዎድሮስ አጥላው

ቀን :-ቅዳሜ ጥቅምት 1 ቀን 2018 ዓም

ሰዓት : - ከሰዓት 8:00 ጀምሮ

ቦታ: 4ኪሎ ኢክላስ ህንፃ ዋልያ መፃሕፍት አዳራሽ

ኑ ! ስለ ንባብ ሐሳብ ተካፈሉ፤ ሐሳብ አካፍሉ!

የመንሱር እና ብስራት ሬዲዮ ውዝግብ ========================የእግር ኳስ ስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ውዝግብ ውስጥ እንደገባ አስታወቀ።ጋዜጠኛ መንሱር...
09/10/2025

የመንሱር እና ብስራት ሬዲዮ ውዝግብ
========================

የእግር ኳስ ስፖርት ተንታኙ መንሱር አብዱልቀኒ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ውዝግብ ውስጥ እንደገባ አስታወቀ።

ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ ከሬድዮ ጣቢያው ጋር ስለተፈጠረው ውዝግብ ተከታዩን ብሏል"የብስራት ኤፍ ኤም 101.1 ፓርትነር በመሆን ከጣቢያው ጋር በትብብር ''ብስራት-ስፖርት" የተሰኘውን ፕሮግራም ለ12 ዓመታት ሳቀርብ መቆየቴ ይታወቃል።

ይሁንና በእነዚህ ሁለት ቀናት (ረቡዕ እና ሐሙስ መስከረም 28 እና 29) ከእኔ የስራ ትጋት ጋርባልተያያዘ (በግሌ ልፈታው በማልችለው ምክንያት) ከጣቢያው ጋር ያልተግባባንባቸው ጉዳዮች ተፈጥረዋል።

እነዚህ ልዩነቶች መፍትሔ እስኪያገኙ ድረስ (ዛሬ በማለዳ ያስተዋወቅኳችሁን ፕሮግራም ጨምሮ) "ብስራት-ስፖርት" ከሬድዮ አየር ላይ እንደወረደ ስገልጽላችሁ ከታላቅ ይቅርታ ጋር ነው" ሲል ተናግሯል።

ሠዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ የጥበብ ስራዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኒሶታ እያሳየ ነዉ============================ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ ስነ-ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት በ1...
05/10/2025

ሠዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ የጥበብ ስራዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኒሶታ እያሳየ ነዉ
============================

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አለ ስነ-ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት በ1990 ዓ.ም. የተመረቀውና በልዩ የታሪክ አሳሳሉ የሚታወቀው ሰዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ፣ ሥራዎቹን ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኒሶታ ለሚገኙ የጥበብ አፍቃሪዎች እያሳየ መሆኑን አስታወቀ።

ሠዓሊ ተስፋዬ ንጉሴ ከ27 ጊዜ በላይ በግል እንዲሁም ከ47 ጊዜ በላይ በቡድን በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶችና የአውሮፓ ሀገራት ሥራዎቹን በማቅረብ ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈ ሲሆን፣ በሚኒሶታ እያደረገ ያለው ይህ የመጀመሪያ ኤግዚቢሽኑ ተመልካቾቹን ቀልብ ለመሳብ ችሏል።። ሥራዎቹን ካሳየባቸው ታዋቂ ቦታዎች መካከል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም፣ በአሊያንስ ኢትዮ-ፍራንሴዝ፣ በኒውዮርክ እና በአትላንታ በሚገኙ ጋለሪዎች እንዲሁም በቤልጂየም ብራሰልስ ይገኙበታል።

በሠዓሊነት ባሳለፈባቸው ከ28 ዓመታት በላይ፣ በተለይ በዓድዋ ጦርነትና ሌሎች ሀገራዊ ስሜትን በሚቀሰቅሱ (patriotism) ርዕሶች ላይ በሰራቸው ሥራዎቹና በመስመር አጠቃቀሙ ይታወቃል።

ከ25 በላይ የዘይትና የአክሪሊክ ቀለም ሥዕሎችን የያዘው ይህ የሥዕል ትርዒት፣ ላለፉት 2 ቀናት ሲታይ ቆይቶ ዛሬ ምሽት እንደሚጠናቀቅ የገለፀ ሲሆን፣ ህጻናትና አዋቂዎች ሳይለዩ ሁሉም የማህበረሰቡ አባላት እንዲጎበኙት ሰዓሊው የአክብሮት ጥሪውን አቅርቧል።

ቦታ: HILLTOP EVENT CENTER
421 Marie Ave, South Saint Paul, MN 55075

የሚቆይበት ጊዜ: ዛሬ የመጨረሻው ነው።

ይህ ኤግዚቢሽን በሚኒሶታ ለሚኖሩ የጥበብ አፍቃሪዎችና የማህበረሰቡ አባላት፣ የሰዓሊውን የረጅም ጊዜ ልምድና የፈጠራ ችሎታ በአካል ለመመልከት ትልቅ አጋጣሚ ፈጥሯል።ሲል ዘ-ሐበሻ በፌስቡክ ገፁ ዘግቧል።

30/09/2025

Address

Addis Ababa

Telephone

+251910102299

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yetebarek walelegen ይትባረክ ዋለልኝ:

Share