Segon Media ሰጎን ሚዲያ

Segon Media ሰጎን ሚዲያ We deliver balanced and credible national and international news and vacancy adverts to you!

10/10/2024

"ነገር ያበላሻሉ፣ እሳት ይጭራሉ"- መንግስት የቀድሞ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴን

"እኔን አይሰሙኝም፣ አይረዱኝም"- ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ መንግስትን

(መሠረት ሚድያ)- የስራ ግዜያቸው የተጠናቀቀው ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዛሬው እለት በዲፕሎማቱ አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ተተክተዋል።

የፕሬዝደንቷ ለቀጣይ የስራ ዘመን እጩ ሆኖ አለመቅረብም ሆነ እርሳቸው ለመቀጠል አለመፈለጋቸው የአደባባይ ሚስጥር ሆኖ ቆይቷል።

ከትናንት በስቲያ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ አንድ ፅሁፍ የኤክስ (ትዊተር) አካውንታቸው ላይ ካጋሩ በኋላ በርካቶች የተለያዩ ግምቶችን ሲያስቀምጡ ነበር። አንዳንዶች አካውንታቸው ሀክ ተደርጎ ወይም ተጠልፎ ሊሆን ይችላል ሲሉ ሌሎች ደግሞ ጉዳዩ እንደዛ ሳይሆን ፕሬዝደንቷ ለአመታት በመንግስት ሲገፉ ቆይተው በመጨረሻም በይፋ መተንፈሳቸው ነው ብለው አስተያየት ሲሰጡ ተመልክተናል።

በዚህ ዙርያ እስካሁን በብቸኛነት በይፋ አስተያየት የሰጡት የፕሬዝደንት ፅ/ቤት ሀላፊው አቶ ፍቃዱ ሰቦቃ ሲሆኑ እሳቸውም "የፕሬዝደንት ሳህለ-ወርቅ ኦፊሴላዊ አካውንት አለ፣ እኛ አስተያየት መስጠት የምንችለው በእሱ ዙርያ ነው። የተባለው ፅሁፍ በግል አካውንት ላይ ስለተለጠፈ ቢሯችንን አይመለከትም" በማለት ኢትዮጵያ ቼክ ለተባለው ለመረጃ አጣሪ ተቋም ምላሽ ሰጥተው ነበር።

ይህን ክስተት ተከትሎ መሠረት ሚድያ ምንጮቹን ጠቅሶ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በመጪው ጥቅምት ወር ላይ የሚጠናቀቀውን የስራ ዘመናቸውን ተከትሎ በርዕሰ ብሄርነት መቀጠል አንደማይፈልጉ፣ መንግስትም እጩ እንደማያደርጋቸው ዘግቦ ነበር።

ይሁንና ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ የስራ ዘመን በርካታ አስተያየቶችን ያስተናገደ ሆኗል።

አንዳንዶች ሀገሪቱ ጦርነት ላይ በነበረችበት እና ሰላም ያስፈልጋል ብሎ መናገር ሀጥያት መስሎ ይታይበት በነበረበው ግዜ ጭምር ስለ ሰላም መናገራቸውን በማንሳት ያወድሷቸዋል። ይህ በወቅቱ ያደረጉት የሰላም ጥሪ ከስራ አስፈፃሚው አካል ጋር ለነበራችው ቅያሜ አንዱ መነሻ እንደነበር የሚጠቁሙ መረጃዎችም አሉ።

በሌላ በኩል ፕሬዝደንቷ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ሰው በጦርነት ሲረግፍ ያላቸውን የመንግስት የስራ ድርሻ በመጠቀም በበቂ ሁኔታ ህዝብን ደግፈው አልቆሙም፣ ብዙ ግዜ የዳር ተመልካች ነበሩ እንዲሁም ግፍ ለሚፈፅሙ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከለላ የሰጡ ናቸው በማለት ይከሷቸዋል።

በንግግራቸው ሁለት ግዜ "ቀይ መስመር ተጥሷል" ብለው የሚያውቁት ኘ/ት ሳህለወርቅ በተለይ የሰሜኑ ጦርነት ወቅት በጀመረበት እለት "ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል፡ አገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፡የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፡ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል" በሚለው ንግግራቸው ይታወሳሉ።

"ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ በስራ ገበታቸው እያጋጠማቸው ያለ ችግር ነበር ወይ?" በማለት አብረዋቸው ለሰሩ እና አሁንም እየሰሩ ላሉ፣ ስማቸውን ግን በጥያቄያቸው መሰረት ለማንገልፃቸው ሰዎች ጥያቄያችንን ከመሠረት ሚድያ አቅርበን ነበር።

አንደኛው ምንጫችን ጉዳዩን ሲያብራሩ ፕሬዝደንቷ ወደ ስልጣን በመጡ ሰሞን፣ በተለይ በ2011 እና 2012 ዓ/ም ላይ የፕሬዝደንትነት ስራን ብቻ ሳይሆን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስራን ጭምር ደርበው ሲሰሩ ነበር ይላሉ። ለማሳያም ፕሬዝደንቷ ኢትዮጵያን ወክለው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጠቅላላው ጉባኤ ላይ በመገኘት በ2012 ዓ/ም ንግግር ያደረጉበትን ግዜ ያነሳሉ።

"ይሁንና በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቅሬታውን ማቅረብ ጀመረ፣ ፕሬዝደንቷ የእነሱን ስራ ጠቅልለው መስራታቸው በውጭ ጉዳይ አልተወደደም ነበር፣ መንግስት ግን ይህን እያደረገ የነበረው 50 ፐርሰንት ካቢኔውን ሴት ያረገ እና ሴት ፕሬዝደንት የሾመ መሆኑን ጭምር ለአለም ለማሳየት ነበር" የሚሉት እኚህ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጫችን መንግስትም ፕሬዝደንቷን በድጋሚ ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ መልሶ ልኮ እንደማያውቅ ይጠቁማሉ። ይህም ብቻ ሳይሆን ከአንዳንድ አለም አቀፍ ስብሳባዎች ላይ ቀስ በቀስ እንዲቀሩ እየተደረጉ እንደመጡ በማንሳት ይህም በፕሬዝደንቷ ዘንድ እንዳልተወደደ ተናግረዋል።

ይሁንና ጠ/ሚር አብይ አህመድ በወቅቱ ሳይታሰብ ወደ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ መኖርያ በመሄድ ጉዳዩን በማስረዳት ሁኔታውን ለማለዘብ ሙከራ አድርገው እንደነበር ታውቋል።

አንዳንድ ክስተቶች በዚህ ላይ ተደራርበው ነገሮችን እንዳወሳሰቡ የሚጠቁም መረጃ የሰጡን ደግሞ ሌላዋ የፕሬዝደንቷ የቅርብ ሰው ነበሩ።

እኚህ ምንጫችን እንደ ምሳሌ ያነሱት ከፕሪቶርያው ስምምነት መፈረም በኋላ ሰላም እንዲሰፍን አስተዋፅኦ ያደረጉ ተብለው በርካታ ግለሰቦች እና ጦርነቱን በሁሉም ወገን ሲመሩ የነበሩ ግለሰቦች እና ቡድኖች በወዳጅነት አደባባይ በተካሄደ ፕሮግራም ላይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሸለሙ "ሰላም ይስፈን" ብለው ተናግረው የነበሩት ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ግን ገሸሽ መደረጋቸው እንዳበሳጫቸው ያነሳሉ።

"የእውቅና ፕሮግራሙን የተመለከቱት ቤታቸው ሆነው ነበር፣ ለሽልማት ቢቀር ለመሳተፍ እንኳን ጥሪ አልደረሳቸው ነበር" ብለው ወቅቱን አስታውሰዋል።

በአንድ ወቅት አርቲስት ታሪኩ ጋንኪሲ (ዲሽታ ጊና) በአንድ ኮንሰርት ላይ ስለ ሰላም መውረድ ተናግሮ ክፉኛ ከተተቸ በኋላ ፕሬዝደንቷ በነጋታው በቀጥታ አርቲስቱ ጋር በመደወል "አይዞህ፣ የተናገርከው ሁሉ ትክክል ነው፣ ያንተ ግዜ ይመጣል" ብለው እንደነገሩት ያነሱት እኚህ ምንጫችን ይህ ከአርቲስቱ ጋር ያረጉት ንግግር ግን ከፕሬዝደንት ቢሮ ሾልኮ ጠ/ሚር ቢሮ መድረሱንና ይህን ጥሩ ድባብን እንዳልፈጠረ አስረድተዋል።

ሌላኛው መሠረት ሚድያ ያነሳው ጥያቄ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ከጠ/ሚር አብይ አህመድ ጋር ስላላቸው የስራ ግንኙነት ነበር።

መጀመርያ ላይ እጅግ የሰመረ ይመስል የነበረው የሁለቱ መሪዎች ግንኙነት ኋላ ላይ እየሻከረ እንደመጣ የአደባባይ ሚስጥር መሆኑን በዚህ ዙርያ ያነጋገርናቸው ሁሉም ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ይስማማሉ።

ፕሬዝደንቷ "ነገር ያበላሻሉ" እና "እሳት ይጭራሉ" የሚል ክስ ሲቀርብባቸው እርሳቸው በበኩላቸው ደግሞ "እኔን አይሰሙኝም፣ አይረዱኝም" የሚል እሰጥ አገባ ውስጥ እንደቆዩ ትዝብታቸውን ያጋሩን ምንጮች ይህ ንትርክ ገፍቶ መጥቶ በ2016 ዓ/ም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመክፈቻ ስብሰባ ላይ ፕሬዝደንቷ የመክፈቻ ንግግር ካደረጉ በኋላ በፕሮቶኮል እና ክብር ተደርጎ በማይታወቅ መልኩ ጠ/ሚሩ ፕሬዝደንቷ አዳራሽ ውስጥ እያሉ ጥለው እንዳወጡ ያስታውሳሉ።

በግል ባህሪያቸው "ትንሽ አስቸጋሪ ሊሆኑ ይችላሉ" የሚባሉት ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ አንዳንድ ግዜ በተደጋጋሚ የመነጫነጭ እና በስራ አለመርካት አብረዋቸው ለሚሰሩ ሰዎች ፈታኝ እንደሆኑ የሚያነሱ አሉ።

"ከግል ጠባቂ ጀምሮ እስከ ፅ/ቤት ያሉ ቶሎ ቶሎ ስራ የመቀያየር ነገር አለ፣ አብሮ መስራት አስቸጋሪ ነው፣ ሰው አብሯቸው አይቆይም፣ በስራም አይረኩም" ያሉት አንድ አብረው የሰሩ እና መረጃ የሰጡን ግለሰብ ነገሮችን እጅግ በጥልቀት እና በጥንቃቄ ማየት መፈለጋቸው አንዳንዴ ስራዎችን አስቸጋሪ ያደርገዋል ይላሉ።

እንደ ምሳሌ የሚያነሱት የማህበራዊ ሚድያ ፖስቶችን እንኳን እርሳቸው አይተው፣ ፎቷቸውን መርጠው እና አሰናድተው ካልሆነ እንደማይለጠፍ ያስረዳሉ። ጥንቃቄው መልካም ቢሆንም ስራን ግን እጅግ ፈታኝ እንደሚያደርጉ የሚያነሱ አሉ። ሌላው ቀርቶ ተፅፎ የሚሰጣቸው ንግግርን በቀይ አስምረው፣ አስተካክለው እና ኤዲት አርገው እንጂ በቀጥታ እንደማያነቡ አብረዋቸው የሰሩ ይናገራሉ።

በሌላ በኩል በውጭ ሀገራት፣ በተለይ ለአመታት ባሰሩባቸው የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት እጅግ ከፍተኛ ክብር እና አድናቆት እንደሚቸራቸው በስፋት ይነሳል።

ይህ እንዳለ ሆኖ ግን በሀገራቸው፣ በተለይ በስራ አስፈፃሚው የፖለቲካ አካል "የምለውን አይሰሙም" የሚለው አካሄድ በትናንትናው እለት በትዊተር ላሰፈሩት ፅሁፍ መዳረሻ እንደሆናቸው እነዚህ የምንጮቻችን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

የፕሬዝደንቷን የትዊተር ፅሁፍ ተከትሎ አንዳንድ የሚድያ ዘመቻዎች በመንግስት ካድሬዎች እና በመንግስት ባለስልጣናት ጭምር እንደተጀመረባቸው ተመልክተናል።

ለምሳሌ የቦሌ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አለምፅሐይ ሽፈራው "ሀገር መምራት መታደል ነው፣ እድሉን መጠቀም ግን ጥበብ ይጠይቃል" የሚል አንድ ፅሁፍ በትናንትናው እለት በግል የፌስቡክ ገፃቸው ላይ አጋርተው የነበሩ ሲሆን ከ16 ሰአት ቆይታ በኋላ አጥፍተውታል።

ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በፅሁፋቸው "ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ በታሪክ አንዴ ብቻ ሊገኝ የሚችል እድል ገጥሟት የታላቋ ሀገር ፕሬዝደንት ሆነች! ከዛን ግዜ ጀምሮ ምን ለሀገር ሰራች ብለን የምናነሳው አንድም ነገር የለም" ያሉ ሲሆን አክለውም "ፕሬዝደንቷ በቆየችበት ግዜ ይህን ማድረግ ተስኗት ቆይቷል" ብለው ለጥፈው ነበር። እኚህ የመንግስት ሀላፊ ትንሽ ቆይተው ደግሞ "ካረጁ አይበጁ" የሚል ፅሁፍ አቅርበው አሁን ድረስ በገፃቸው ላይ ይገኛል።

በተመሳሳይ የኢቢሲ ምክትል ስራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ነብዩ ባዬ በቅርቡ ከፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ጋር የነበራችውን አንድ ንግግር በፌስቡክ ገፃቸው ካጋሩ በኋላ በፅሁፋቸው ወደ መጨረሻው ላይ ፕሬዝደንቷ "ለብዙ ነገር ዝምታ መልሳቸው ነበር ብዬ አላምንም። ያመኑበትን ተናግረዋል።
ዝምታ ትርጉሙ አልተቀየረምም ብዬ አስባለሁ። እኔም ባለፈው አንድ አመት ኢትዮጵያ ውስጥ ነበርኩ። እኛ ቀጥ ያሉና በግልፅ እየተናገሩ እጅግ በተጋነነ የፕሮቶኮል አጀብ የኖሩ ርዕሲተ ብሔር ድንገት ያንኑ ድምፃቸውን በሰማሁ በአንድ ቀን ልዩነት እንደዚያ ድብስብስ ያለ መልዕክት ያስተላለፉት ምን ለማለት እንደሆነ እንደሚነግሩን ተስፋ አደርጋለሁ" ብለው ሀሳባቸውን አጋርተዋል።

መረጃን ከመሠረት!

የባለቤቷን ሀብት ለመዉረስ በማሰብ ከወንድሟና ከወንድሟ ሚስት ጋር በመሆን በባሏ ላይ የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ================================👇በአር...
28/12/2023

የባለቤቷን ሀብት ለመዉረስ በማሰብ ከወንድሟና ከወንድሟ ሚስት ጋር በመሆን በባሏ ላይ የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ
================================👇
በአርሲ ዞን አርሲ ነገሌ ከተማ ነዋሪ የሆኑት የ45 ዓመቱ አቶ ከተማ አበበ የተባሉ ግለሰብ ከግብረ አበሮቿ ጋ በመሆን የገደለችው ግለሰብ በእስራት ተቀጣች። አቶ ከተማ በንግድ ስራ የሚተዳደሩ የነበሩና ከመጀመሪያ ሚስታቸው ጋ በተለያዩ ምክንያቶች በፍች ከተለያዩ በሗላ ወ/ሪት ትግስት ደረጀ የተባለች የአርሲ ነገሌ ከተማ ነዋሪ ጋር ይተዋወቁና በትዳር ይጣመራሉ።
ሟች አቶ ከተማ አበበ በሸቀጣሸቀጥ ንግድ የተዋጣላቸዉ ሰዉ ሲሆኑ ረዳት ሰራተኛ ለመቅጠር ሲፈልጉ ባለቤታቸው ትግስት ሌላ ሰዉ ከሚቀጠር ወንድሜ ስራዉን ቢያግዝ ብላ ሀሳብ ስታቀርብ አቶ ከተማም በሀሳቡ ተስማምተው ሙሉቀን ደረጀ የተባለው ወንድሟ ስራ ይጀምራል።

አቶ ሙሉቀን ትንሽ ቆይቶ ፍቅር የጀመረ ሲሆን መደበኛ የሱቅ ስራውን እየዘጋ በመሆኑ ከአቶ ከተማ ጋር ግጭት ገብቶ ከቤት አስወጥቶ ሌላ ሱቅ የሚጠብቅ ሰው የቀጠረ ሲሆን ከቤት ከወጣ ጀምሮ ከእህቷ ጋር በመሆን አቶ ከተማን ለመግደል እቅድ አውጥተው የካቲት 10 ቀን 2015 ከምሽቱ 6:00 ትግስት ደረጀ፣ ሙሉቀን ደረጀ እና የሙሉቀን ፍቅረኛ ሰላም ፋንታሁን ፣ከተማ አበበን በተኛበት በመጥረቢያ ቆራርጠዉ ከገደሉት በኋላ ቤት ዉስጥ ይቀብሩታል ።

ድርጊቱን ከፈፀሙ በኋላ ከተማ አበበ ቤት እንዳልመጣ ለፖሊስ ያመለክታሉ።ፖሊስ የአቶ ከተማ አበበ መጥፋት ከደረሰዉ በኋላ ክትትል ሲጀምር ሙሉቀን ወደ አዲስ አበባ መሄዱን ሲሰማ በመጠራጠር እህቱንና ፍቅረኛዉን በቁጥጥር ስር ያዉላቸዋል።

ትግስት በቁጥጥር ስር ዉላ ምርመራ ሲደርግባት ወንድሟ ድርጊቱን እንዳቀነባበረዉ ትናገራለች።ፖሊስም ባለቤቱንና የሙልቀን ፍቅረኛ ሰላም ፋንታሁንን በቁጥጥር ስር አውሎ ሙሉቀንን ሲፈልግ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በቁጥጥር ስር ያዉላቸዋል።

ፖሊስና አቃቢ ህግ በጋራ በመሆን ምርመራ መዝገቡን በማጣራት ክስ ይመሰርታል።የምዕራብ አርሲ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ሀብት ያላግባብ ለመዉረስ በፈፀሙት ድርጊት እያንዳንዳቸዉ ላይ የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንደወሰነባቸዉ የምዕራብ አርሲ ዞን ፖሊስ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሃላፊ ኮማንደር ከድር ችቦ በተለይ ለብስራት ቲቪና ራዲዮ ገልፀዋል።

09/11/2023

አደጋ የበዛበት መዝናናት😭😂

👇ዜና/News👇     ========በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታዉ ተባበር በርታ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ዉስጥ እድሜዉ 45 ዓመት የተገመተ አንድ ሰው ሰኔ 0...
13/06/2023

👇ዜና/News👇
========
በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታዉ ተባበር በርታ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኝ ወንዝ ዉስጥ እድሜዉ 45 ዓመት የተገመተ አንድ ሰው ሰኔ 05/2015ዓ.ም ህይወቱ ወንዝ ውስጥ አልፎ ተገኝቷል።
የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጠላቂ ዋናተኞች ከሁለት ሰዓት ፍለጋ በኋላ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ሲሆን አስከሬኑን አግኝተዉ ለፖሊስ አስረክበዋል።

በቄለም ወለጋ ሀዋገላን ወረዳ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ዳግም ጥቃት ፈጸሙ!!ሰኔ 27/2014 ዓ.ም////////////////////////////////////በቄለም ወለጋ ዞን ሀዋ ገለን ወረዳ ፤...
04/07/2022

በቄለም ወለጋ ሀዋገላን ወረዳ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ዳግም ጥቃት ፈጸሙ!!
ሰኔ 27/2014 ዓ.ም
////////////////////////////////////
በቄለም ወለጋ ዞን ሀዋ ገለን ወረዳ ፤ ለምለም ቀበሌ ዉስጥ መንደር 20 ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ በዛሬዉ እለት የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት ከ200 በላይ በርካታ ንጹሀን #የአማራ ዜጎች ህይወት እንዳለፈ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ለ ዳጉ ጆርናል ተናግረዋል።

ስማቸዉ እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ምንጭ እንደተናገሩት በዛሬዉ እለት የሽብር ቡድኑ በከፈተዉ ጥቃት ቁጥራቸዉ በዉል የማይታወቅ ንጹሀን እንደተገደሉ ነግረዉናል። በጥቃቱ በርካታ ህጻናት እና እናቶች መገደላቸዉንም ገልጸዉልናል።

የነበረዉ የሽብር ቡድኑ ሀይል ብዛት የነበረዉ በመሆኑ በአካባቢዉ የሚገኙ የሚሊሻ የጸጥታ ሀይሎች ተጨማሪ ሀይል እስኪመጣ ወደ አካባቢዉ መግባት እንዳልቻሉም ነዋሪዎቹ አንስተዋል።

በጥቃቱ ምን ያህል ሰዎች ህይወታቸዉ እንዳለፈ በዉል ባይታወቅም ቁጥራቸዉ ከፍተኛ የሆነ ንጹሀን ተገድለዋል ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም የአካል ጉዳት የደረሰባቸዉ በርካታ ዜጎች እንደሚገኙ እና ቁስለኞቹንም ከአካባቢዉ ለማስወጣት እንደተቸገሩም ነዋሪዎቹ ይናገራሉ።
ጥቃቱን ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊት በቦታው ቢገባም አሁንም ስጋት ላይ መሆናቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡

126ኛው የአድዋ ድል በዓል አከባበር በሚኒሊክ አደባባይ ክብር ለአባቶቻችን     💚💛❤️
02/03/2022

126ኛው የአድዋ ድል በዓል አከባበር በሚኒሊክ አደባባይ
ክብር ለአባቶቻችን

💚💛❤️

እንኳን ለ126ኛ የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ!💪==============================አድዋ በአፄ ሚኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ የጦር አመራርነት ሰጭነት በመላ ኢትዮጵያውያን ድንቅ ተጋ...
02/03/2022

እንኳን ለ126ኛ የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ!💪
==============================
አድዋ በአፄ ሚኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ የጦር አመራርነት ሰጭነት በመላ ኢትዮጵያውያን ድንቅ ተጋድሎ ከኢትዮጵያውያን አልፎ ለመላው የጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ዓርማ፤ በደም የተፃፈ የማይደበዝዝ ታላቅ ድል ነው!
መልካም በዓል!!!

Address

Addis Ababa

Telephone

+251973054204

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Segon Media ሰጎን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Segon Media ሰጎን ሚዲያ:

Share