Hagere tv

Hagere tv Peace full country

17/07/2025

የቴሌቪዥን ግብር‼️
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቴሌቪዥን ግብር ክፈሉ የሚል ማስጠንቀቂያ እየላከ መሆኑን የደረሰኝ ጥቆማ ያመላክታል።
ከባለፈው 2015 ዓ.ም ጀምሮ ከ50 ኪሎዋት በላይ ተጠቃሚ የሆኑ ደንበኞች የቴሌቪዥን አገልግሎት በየወሩ ከመብራት ጋር 10 ብር በዓመት አጠቃላይ 120 እንዲከፍሉ እየተደረገ መሆኑ ይታወቃል።
አሁን ማንኛውም ቴሌቪዥን ያለው ሰው ግብር የመክፈል ግዴታ አለበት በማለት በዛሬው ዕለት ለቴሌቪዥን ባለይዞታዎች የግብር ክፈሉ ማስጠንቀቂያ እየተላከ መሆኑን ከአዲስ አበባ/ቦሌ/የደረሰኝ ጥቆማ ያመላክታል።

17/07/2025

ከ41 ሚሊዬን ብር በላይ ተወሰደ‼️
በአማራ ከልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማበር ወረዳ መዘዞ ንዑስ ወረዳ በትላንትናዉ እለት ከሌሊቱ 7 ሰዓት ላይ ከ3 ባንኮች ከ41 ሚሊዮን ብር በላይ በታጠቁ ሀይሎች አንደተወሰደ ታውቋል።
በንዑስ ወረዳዉ ከሚገኙ ከቡና ባንክ 11ሚሊዬን 550ሺህ ብር፣ከፀዳይ ባንክ 1ሚሊዬን 28ሺህ ብር እንዲሁም ከአባይ ባንክ 29 ሚሊዬን 365ሺህ ብር በአጠቃላይ 41ሚሊዬን 943 ሺህ ብር መወሰዱን ወረዳው አሳውቋል።

17/07/2025

የቡሬ ግንባር ምሽግ‼️
በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ድንበር አዋሳኝ ላይ በምትገኘው ቡሬ ግንባር የኤርትራ ጦር ያዘጋጀውን ምሽግ የሳታላይት ምስል ከላይ አያይዘነዋል።
ቡሬ ግንባር በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ከባድ ውጊያ ከተካሄደባቸው የጦር ግንባሮች አንዱ ሲሆን የኤርትራ ጦር አሁን ላይ ተጨማሪ ምሽጎችን እያዘገጀ ስለመሆኑ ከሳታላይት ምስል ተመልክተናል።
Peace 🕊🕊🕊🕊

17/07/2025

ባህርዳር‼️
የባህርዳር ከተማ ፀጥታ ም/ቤት ከዚህ በፊት ተጥለው የነበሩ ክልከላዎችን በከፊል አንስቷል።
ከእነዚህም መካከል፦
1. "ማንኛውም የንግድ እንቅስቃሴ ያለገደብ 24 ሰዓት ክፍት በማድረግ እንዲሰሩ ተወስኗል፣

2. ከባጃጅ እና ከሞተር ሳይክል ውጭ ሁሉም ተሽከርካሪዎች ያለ ገደብ እንዲንቀሳቀሱ ተወስኗል፣

3. ማንኛውም ሰው ያለምንም የሰዓት ገደብ እንዲንቀሳቀስ ተፈቅዷል፣

👉 ማሻሻያ ያልተደረገባቸውና አሁንም የተጣሉ ግዴታዎችን በተመለከተ፦

1. ማንኛውም ተሽከርካሪ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ የፊት ለፊትና የኋላ ሰሌዳ አሟልቶ መንቀሳቀስ አለበት። ይህንን ሳያደርግ ተገኝቶ በጸጥታ ሀይሉ ለሚወሰደው ማንኛውም ህጋዊ እርምጃ ሀላፊነቱን ራሱ ይወስዳል ፣

2. ማንኛውም እግረኛ ሲንቀሳቀስ ማንነቱን የሚገልጽ የቀበሌ የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት፣

3. የጸጥታ ሀይሉ እና በሚኖሩበት ቀበሌ ወይም ቀጠና ወይም ብሎክ ብቻ መሳሪያ ይዘው እንዲንቀሳቀሱ ከፈቀደላቸው መሳሪያ ፈቃድ ኩፖን ከተሰጣቸው ውጭ የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ ነው፣

4. የባጃጅ ተሽከርካሪ ከአለበት 12:00 ሰዓት በኋላ ይዞ መንቀሳቀስ ክልክል ነው፣

5. ባለ 2 እግር ሞተር በማንኛውም ሁኔታ ይዞ መንቀሳቀስ በፍጹም የተከለከለ ነው"ብሏል።

11/07/2025

በ 3 ቀን ውስጥ 689 ተዋጊ‼️
ከሃምሌ 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባለፉት 3 ቀናት ብቻ 689 በላይ የህወሃት ተዋጊዎች ካምፓቸውን ከድተው እራሱን የትግራይ ሰላም ሰራዊት/TPF/ ብሎ ወደሚጠራው የህወሓት ተቃዋሚ ጦር ተቀላቅለዋል።
የከዱ ወታደሮች ቁጥር❗👇👇
1. ከአርሚ 24: 65 ወታደር
2. ከአርሚ 43: 57 ወታደር
3. ከአርሚ 44: 205 ወታደሮች
4. ከአርሚ 22: 34 ወታደሮች
5. ከአርሚ 26: 12 ወታደሮች
6. ከአርሚ 50: 31 ወታደሮች
7. ከአርሚ 60: 9 ወታደሮች
8. ከአርሚ 92: 86 ወታደሮች
9.ከአርሚ 15: 27 ወታደሮች
10.ከአርሚ 31: 22 ወታደሮች
11.ከአርሚ 33: 36 ወታደሮች
12.ከአርሚ 35: 19 ወታደሮች
13.ከአርሚ 42: 15 ወታደሮች
14.ከአርሚ 11: 26 ወታደሮች
15.ከአርሚ 13:- 7 ወታደሮች
16. ከአርሚ 17: 11 ወታደሮች
17. ከአርሚ 70 (ከሱዳንን ሸረሪና): 5 ወታደሮች
18. ከአርሚ 8: 13 ወታደሮች
19. 9 ወታደራዊ ኮማንድ በድምሩ 689 ተዋጊዎች ህወሃትን ከድተው "ነፃ መሬት" በሚል ህወሃትን ለመታገል የተመሰረተውን የትግራይ ሰላም ሰራዊትን መቀላቀላቸውን ምንጮቻችን ገልፀውልናል።

11/07/2025

“ኢራንን ዳግም ልናጠቃ እንችላለን” _ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር‼️
ኢራን የደበቀችውን ዩራኒየም ልታወጣ ትችላለች የሚል ስጋት መኖሩን አንድ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ተናገሩ።

አሜሪካ ጥቃት ከሰነዘረችባቸው ሦስቱ የኢራን የኑክሌር ጣቢያዎች መካከል ከአንዱ የተከማቸው ዩራኒየም ሊወጣ ይችላል ያሉት ባለስልጣኑ፤ መሰል እንቅስቃሴዎች ከታዩ እስራኤል ዳግም ኢራንን እንደምታጠቃ ጠቁመዋል።
===================

11/07/2025

ለአንዴ ውሃ ሽንት 20ብር‼️
ለአንድ ውሀ ሽንት ቫትን ጨምሮ 20 ብር‼️
አዲስ አበባ – የሽንት ቤት አገልግሎት ዋጋ ንረት የበርካቶችን ኪስ እያሳሰበ ነው። በአዲስ አበባ በተለይም በመርካቶ አካባቢ የሚገኙ ነጋዴዎች እና የህብረተሰብ ክፍሎች በቀን እስከ 100 ብር ለሽንት ቤት አገልግሎት እንደሚያወጡ እየገለጹ ነው።
አንዳንድ የሽንት ቤት አገልግሎት ሰጪዎች የዋጋ ጭማሪ በማድረግ አንዴ ለመሸናት 20 የኢትዮጵያ ብር (ከቫት ጋር) እያስከፈሉ ይገኛሉ።
ይህ የዋጋ ጭማሪ ብዙዎችን አስገርሟል።

22/09/2021

የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ፀጥታ ምክር ቤት አስቸኳይ ውሳኔዎችን አሳልፏል።

የምክር ቤቱ ሙሉ የውሳኔ ሀሳብ ቀጥሎ ቀርቧል።

መስከረም 12/2014 ዓ.ም
የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ፀጥታ ምክር ቤት በከተማችን ወቅታዊ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ ቀደም ሲል የትህነግ ወራሪ ኀይል በክልላችን ሰርጎ በመግባት በየከተሞች የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቆጣጠር ተብሎ ተጥሎ የነበረውን የሰዓት እላፊን እና ሌሎች የተለያዩ ውሳኔዎችን በከተማችን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ችግሮች እንዳይስፋፉ ማስተካከያ መደረጉ ይታወሳል።

ነገር ግን በክልላችንን የተጋረጠብንን "የህልውና ጉዳይ" የአልተገነዘቡ አካላት ለከተማችን የማይመጥን አንዳንድ ህገ ወጥ እንቅስቃሴዎች እየተስተዋሉ መሆናቸውን የፀጥታ ምክር ቤቱ ገምግሟል።

ስለሆነም የሚከተሉትን መስተካከል የአለባቸው ነገሮች የፀጥታ ምክር ቤቱ ተወያይቶ ክልከላ እንዲደረግ ወስኗል።

1ኛ/ስምሪት ከተሰጠው የፀጥታ ኀይል ውጭ በከተማችን ማንኛውንም አይነት የጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ አስፈላጊ ሆኖ ስላላገኘው እንዲከለል ምክር ቤቱ ወስኗል።

2ኛ/ለንግድ ስራ ከተፈቀደላቸው ቦታ ውጭ የእግረኛና የተሽከርካሪ መንገድ ዘግቶ መጠጥ ቤት ማስተናገድ፣ ኮበልስቶን መንገዶችን ዘግቶ ማንኛውንም ግብይት መፈፀም በጥብቅ የተከለከለ ነው።

3ኛ/ በከተማችን በተናጥልም ሆነ በቡድን የተደራጀ የትኛውንም ህጋዊም ይሁን ህጋዊ ያልሆነ ቁማር ቤት ከፍቶ መጫዎት እና ማጫዎት ፈፅም የተከለከለ ነው።

4ኛ/ በከተማችን በመንግስት ከተፈቀደለት ተቋም ውጭ ምንም አይነት ወታደራዊ ስልጠና መሰልጠንና ማሰልጠን ፈፅሞ የተከለከለ ነው።

5ኛ/ በመጠጥ ቤቶች አካባቢ ነዋሪዎችን የሚረብሽ ሁከትና ግርግር በመፍጠር ለሰላማዊ ነዋሪዎች ስጋት መሆን እና ተዛማጅ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ የማይፈቀድ መሆኑ በመግለፅ ተላልፎ የሚገኝ አካል ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰድ እንደሚችል ፀጥታ ምክር ቤቱ ወስኗል።

"የከተማችን ሰላም በጋራ እናስከብር!"
የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ምክር ቤት

መስከረም 12/2014 ዓ.ም
ባሕርዳር

18/10/2020

Sggg

03/10/2020

trial broadcast

18/09/2020

Address

Addis Ababa
@@@@

Telephone

+251927292998

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hagere tv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category