YeneTech.com

YeneTech.com YeneTech - 24/7 !

ቴክኖሎጂ ከመዝናኛ ጋራ እየተዋዛ የሚቀርብበት!
(3)

°ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል!" በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ዋለ፡፡ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 9/2017 በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የአዲስ አበባ ከተማ ...
18/03/2025

°ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል!" በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ዋለ፡፡

ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 9/2017 በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶችን ያሳተፈበት ማጠቃለያ ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡

አስተዳደር ሴቶች፣ ሕፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የሚገኙ ሴቶች፣ ህፃናት፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋዊያ መብትና ደህንነት ለማስጠበቅ ፤ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ሁለንተናዊ ተሳትፎ ና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ድርጅቶች ጋር በትብብርና በቅንጅት ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

ስለሆነም በዓለም አቀፍ 114ኛ በሀገራችን ለ49ኛ ጊዜ "ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል'' በሚል መሪ ሀሳብ በመከበር ላይ ያለውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ ስኬታማ ወጣት ሴቶች ተሞክሮአቸውን ያካፈሉበት መርሀ ግብር ተከናውኗል፡፡

በዝግጅቱም የከተማችን ከፍተኛ ሴት አመራሮች እና ተጋባዥ እንግዶች ጨምሮ 2000 በላይ ሴቶች የተገኙበት በተለያዩ ኪነጥበብ ክንዋኔዎች ተዘጋጅቶ ታላላቅ እንግዶች በተገኙበት የተሳተፉበት የማጠቃለያ ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡

ዘንድሮ በዓሉ በሀገራችን ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶ ተሳትፎ ይረጋገጣል " በዓለም ዓቀፍ ደረጃ For All Women And Girls Rights: Equality Empowerment!" በሚል መሪ ሀሳብ ሲከበር በሴቶች ላይ የሚደርሱ ማናቸዉንም ብሎም ሴቶችን ማብቃት ከመቸዉም በላይ ትኩረት ሊሰጠዉ የሚገባዉ አጀንዳ መሆኑን ገልፀዋል።

በመጨመረሻም በዘርፍ ያሉ የክፍለ ከተማ ሰዎች በሴቶች ላይ አተኩሮ የተከረው አከባበር በነበራቸው ተሳትፎ የምስክር ወረቀት ተረክበዋል፡፡ በልዩነት ደግሞ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሰርፍኬት ተረክበዋል፡፡

ሚዲያ እና የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በቅርበበት ለመስራት እንዲያችል ምክክር ተካሄደ፡፡የምክክር መድረኩ"የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማ...
14/03/2025

ሚዲያ እና የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ በቅርበበት ለመስራት እንዲያችል ምክክር ተካሄደ፡፡

የምክክር መድረኩ"የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚዲያ ድርሻ የላቀ ነው" በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅት የቢሮው አማካሪ ዶክተር ታደለ ደመኮ፤ ቢሮው በከተማ አስተዳደር ከሚገኙ 50 በላይ ቢሮዎች በተለየ መልኩ በሰው ልጆች ላይ አትኩሮ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

የሴቶችን ተጠቃሚነት እና ተደራሽነት እንዲሁም ክንውኑ ምን ይመስል ነበር የሚሉትን ከ ሰፊ ማብራሪያ ጋር ሰተዋል ለሚዲያዎች፡፡ወደ ፊትም በይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ እና ተጨባጭ መረጃዎችን ማግኘት እንደሚቻልም ጨምረው ገልፀዋል፡፡

እንዲሁም ቢሮው ከሰው ልጆች ፅንስት እስከ ግብዓት መሬት ድረስ እንደሚሰራ ገልፀው፤ በ2017 ግማሽ በጀት ዓመት የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ በርካታ ጥረቶች መደረጋቸውን ተናግረዋል።

እንደ ዶክተር ታደለ ገለፃ በዚህ በመዲናይቱ በግማሽ በጀት ዓመቱ ከተፈጠረው 142ሺህ የስራ ዕድሎች 52 በመቶ ሴቶች ናቸው።

ከለውጥ በዋላ በሴቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ በመስራቱ በተጨባጭ የሴቶች ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጠ እየተቻለ መሆኑን ያነሱት የቢሮው አማካሪው፤ በሴቶች ላይ የሚስተዋለውን አይችሉም የሚለውን ኋላ ቀር ትርክት በይችላሉ መቀየር አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ ከተማ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ለነገ የማይባል ነው ብለዋል።

ሚዲያ ለማጥፋትም ሆነ ለማልማት ሚናው የጎላ እንደሆነ በመግለፅ፤ የሚዲያ ባለሞያዎች ለሴቶች ድምፅ ሊሆኑ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

እስካሁን በነበረው ሂደት የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ሚዲያዎች ለሚያደርጉት ተሳትፎ ምስጋና አቅርበዋል።

በመዲናይቱ ሴቶች በሰላም ማስከበር፣ በፅዳት፣ በአከባቢ ጥበቃ፣ በበጎ ፍቃድ፣ በደም ልገሳና ሌሎች ዋጋቸው በማይተመኑ ማህበራዊ አገልግሎቶች ላይ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።

11/01/2025

የድምፃዊ መሳይ ተፈራ -ደህና ይግጠምሽ በተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ፡፡

ማስታወቅያ…A🎤O የሳውንድ ሲስተም ኪራይ የድሮ VHS ወደ ፍላሽ እንገለብጣለን:: እናንተ ብቻ ይደውሉ በተጨማሪም ለፕሮፌሽናል ሳውንድ ኢንጅነሪንግ ብቻ የሚያገለግል Cable Tester በቀላ...
04/01/2025

ማስታወቅያ…
A🎤O የሳውንድ ሲስተም ኪራይ
የድሮ VHS ወደ ፍላሽ እንገለብጣለን:: እናንተ ብቻ ይደውሉ በተጨማሪም ለፕሮፌሽናል ሳውንድ ኢንጅነሪንግ ብቻ የሚያገለግል Cable Tester በቀላሉ ኬብላችሁን ችግሩን የምታውቁበት ቴስተር ነው ይከራዩ ስራዎን በቅልጥፍና ይስሩ፡፡
ከድሮ VHS📼 ወደ ፍላሽ እንገለብጣለን
B- 0911-643422 P-0911-225086

የካሊንባ ዩትዮብ ስፖንሰር ስለሆነ እናመሰግናለን፡፡

ከፍያለ ጌጡ…እስካሁን ካየኃቸው ቱባዊ የባህላዊ የሙዚቃ አቀንቃኞች መሀከል እጅጉኑ ይለይብኛል፡፡ በፋና ላምሮት ቤት… ውበትም ጌጥም ሆኖ እስከ አስራ ሁለተኛ ሳምንት ድረስ ተጉዟል፡፡በዚህኛው ...
22/12/2024

ከፍያለ ጌጡ…

እስካሁን ካየኃቸው ቱባዊ የባህላዊ የሙዚቃ አቀንቃኞች መሀከል እጅጉኑ ይለይብኛል፡፡ በፋና ላምሮት ቤት… ውበትም ጌጥም ሆኖ እስከ አስራ ሁለተኛ ሳምንት ድረስ ተጉዟል፡፡በዚህኛው በአስራ ስምንተኛው ምዕራፍ የተለየ የሙዚቃ አቀራረብ እና አጨዋወት አሳይቶናል፡፡

*ቱባዊ ቃና ድምፅ(ፎክ)

የትም የማይገኝ መለዮ ቃና…ለጥቂቶች ብቻ የሚታደል ውበታዊ ሀገራዊ አንፀባራቂዎች ናቸው፡፡ለሌሎች ፈተናን የሆነ የሙዚቃ ቴክኒክ አጠቃቀም በቀላሉ ሳይቸገር አስደንቆ እንድንማርበት ያደርገናል፡፡ከፍያለ ጌጡ… በጊዜ የተስዕጦን መንገድ ያወቀ እና የነቃ ነው፡፡ ከቀዬው ያወቃቸውን የሚያውቃቸው የሙዚቃ ቃና እና ባህልን ፋንትው አድርጎ በቴሌቪዥን መስኮት አስመልክቶናል፡፡

*የመድረክ ዝግጅት እና አቀራረብ…

የውድድር አንዱ ፈተና የመድረክ ዝግጅት ነው… በራስ መተማመን እንድንለካው የመጣንበትን የሙዚቃ አቀራረብ ይሄ ነው ያለኝ ብለን የምንገልፅበት ትልቁ መድረካችን ነው፡፡ከፍ ያለ ይንን አስመልክቶናል፡፡በአለባበስ፣በእንቅስቃሴ፣ የተለያዩ የሙዚቃ ምርጫ ስኬት፣ የሙዚቃ መሳርያ ተጫዋቾች ጋር ውህደትን የመሳሰሉት ይታያሉ፡፡

*ለየት ያሉ የሙዚቃ ምርጫዎች

ይንን ስገልፅላችሁ በቀላል አትመልከቱት ሙዚቃ መምረጥ ሌላ… የሙረጡትን ሙዚቃ መጫወት ሌላ ነው፡፡ እነዚህ ሁለትን አዛምዶ ማዜም አንዱ የውድድር መልክ ናቸው፡፡ከፍ ያለ ጌጡ ልንሰማቸው የሚገቡ በብዛት በመድረክ የማንሰማውን አስደምጦናል ለምሳሌ ወሮታው ውበት ፣ተስፋዬ ውቤ ፣ይሁኔ በላይ ፣ቻላቸው አሸናፊ እና የመሳሰሉት ይገኛሉ፡፡

በፋና ላምሮት ቤት ብዙ እድሎች ይገኛሉ አንደኛውም ለአምስተኛው የአሸናፊዎች አሸናፊ ላይ በሰርፕራይዝ(ድንቴ ደስታ) ተፈጥሮ፡፡ ከፍ ያለን እምንመለከተው ይመስለኛል፡፡መልካም እድል ይሁንልህ ጓዴ፡፡

የሙዚቃ ዘጋቢ ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.) Selam Chuna Tesfaye Lemlem Yohannes Miheret Yoseph Natnael Sisay Girum Nebiyu

የመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ታቦተ ህግ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም. ወደ መንበረ ክብሩ ይመለሳል!!ላለፉት ሁለት አመታትና ከዛ በላይ ለሚሆኑ ጊዜያት እድሳት ሲደረግለት የቆየው የመንበረ ፀ...
18/12/2024

የመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ታቦተ ህግ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም. ወደ መንበረ ክብሩ ይመለሳል!!

ላለፉት ሁለት አመታትና ከዛ በላይ ለሚሆኑ ጊዜያት እድሳት ሲደረግለት የቆየው የመንበረ ፀባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን እድሳት ወደ መገባደዱ መድረሱን ዛሬ ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም. በተሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተነግሯል።

የካቴድራል የዕድሳት እና የጥገና ስራ ከተጀመረ 773 ቀናት ያስቆጠረ ሲሆን በየጊዜው በገጠመው የሲሚንቶ ችግር እና ሌሎችም ሁነቶች ምክንያት ተጨማሪ 225 ቀናት መውሰዱን ተጠቁሟል።

የህንጻውን ግንባታ ለሚያከናውነው ኮንትራክተር እስካሁን ድረስ ከ124 ሚሊዮን ብር በላይ ክፍያ እንደተከፈለው የተነገረ ሲሆን ቀሪ ክፍያ እንደሚቀረው ነው የተገለጸው።

ታቦተ ህጉ በተባለው ቀን ወደ መንበሩ ለማስገባት ለኮንትራክተሩ የሚከፈለው ከ47ሚሊዮን ብር በላይ ህዝበ ክርስቲያኑ የተለመደውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ተደርጓል።

የቤተክርስቲያን ህንጻው ግንባታ ሂደት 95 በመቶ ደርሷል።

የቤተክርስቲያኑ እድሳት ከሃይማኖታዊና መንፈሳዊ አገልግሎቱ ባሻገር ትልቅ ሃገራዊ አበርክቶ ያለውን ካቴድራሉን እና ቅርጻቅርጾቹን ኪነ ጥበባዊና ቅርሳዊ ይዞታቸውን በጠበቀ መልኩ መታደሱንም ተነግሯል።

የአጼ ኃይለ ስላሴን የንግስና በዓለ ሲመት ያስተናገደው ቅድስት ስላሴ ካቴድራል የመሪዎች፣ የጀግኖች አርበኞች እና የታዋቂ ሰዎች ዘላቂ የማረፊያ ስፍራ ነው፡፡ በብዙዎች ይጎበኛልም፡፡

የካቴድራሉ ግንባታ በ1922 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን በፋሽስት ጣሊያን ወረራና በተለያዩ ምክንያቶች ተጓቶ በ1936 ዓ.ም. መጠናቀቁን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

«ጥሩ ዜና ይዤ እመለሳለሁ ብዬ ነበር አልተሳካም» እናት የእነ ህፃን ሶሊያና የህክምና ጉዳይ በደቡብ አፍሪካ ሆስፒታል ተስፋ አላቸው ተብሎ ተነግሯቸው ተስፋው ወደ እውነት እንዲቀየር ገንዘብ ...
08/09/2024

«ጥሩ ዜና ይዤ እመለሳለሁ ብዬ ነበር አልተሳካም» እናት

የእነ ህፃን ሶሊያና የህክምና ጉዳይ በደቡብ አፍሪካ ሆስፒታል ተስፋ አላቸው ተብሎ ተነግሯቸው ተስፋው ወደ እውነት እንዲቀየር ገንዘብ ተሰብስቦ ወደ ባንኮክ በማቅናት በባንኮክ በተደረገ ምርመራ ተስፋ ቢኖራቸውም በመጨረሻ የተደረገው ህክምና እንደማይሆን እንዳልተሳካ ተነግሮን ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰናል ስትል እናታቸው በሰይፉ በኢቢኤስ ቀርባ ተናግራለች።

የድምፃዊ ግርማ ነጋሽ ሙዚቃ ጳጉሜ አምስት (62) አመት ይደፍናል፡፡(ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)ተወዳጁ ሙዚቀኛ እና የስፖርት ጋዜጠኛ ግርማ ነጋሽ ከበርካታ ተወዳጅ ሙዚቃዎች ውስጥ የኔ ሐሳብ...
08/09/2024

የድምፃዊ ግርማ ነጋሽ ሙዚቃ ጳጉሜ አምስት (62) አመት ይደፍናል፡፡
(ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)

ተወዳጁ ሙዚቀኛ እና የስፖርት ጋዜጠኛ ግርማ ነጋሽ ከበርካታ ተወዳጅ ሙዚቃዎች ውስጥ የኔ ሐሳብ የተሰኘ ሙዚቃ (62) አመቱን ጳጉሜ 5/2016 አመት ምህረት ይደፍናል፡፡

ዘመን ተሻጋሪ የሆነው በዚህ ልክ በትዝታ ማዕበል እያተከዘ በብዞዎች ልብ ውስጥ የተቀመጠ "የኔ ሐሳብ" ሙዚቃ የተለያዩ ወጣት እና አንጋፋ ሙዚቀኞች ይንን ሙዚቃ በራሳቸው ቀለም አቀንቅነዋል::

ከነዛም ውስጥ ሙገስ መብራቱ ፣ አብነት አጎናፍር ፣ ሚካኤል ለማ ደምሰው እና ሌሎችም ጎሮሮአቸውን ለመፈተን በዚህ ሙዚቃ እራሳቸውን ይለኩ ነበር፡፡

የዚህ ሙዚቃ የግጥም ደራሲ ጌታቸው ደባልቄ የዜማ ደራሲ ካሳ ወልዴ አቀናባሪው መርሲ ናልባልዲያን፡፡

ሙዚቀኛ ጋሽ ግርማ ነጋሽ ለዚህ ሙዚቃ ሲናገር "የኔ ሀሳብ ሁሌ እንዳማረባት እኔንም እየጦረች እዚህ አድርሳኛለች'' ብለዋል፡፡

የሙዚቃ ቪድዮ የተሰራበት አጋጣሚ ሲያወጉ "አምሳለ ገነት ይመር የምትባል የወጋየሁ ንጋቱ ባለቤት እሷ ሸምገል እያልን ስንሄድ ፈራች እና አንድ ነገር ተቀርፆ እንዲቀመጥ ሀሳብ ታቀርባለች እኔ ደሞ ይንን ሞያ ሸሽቼ ማለት ቤተሰብ ስላስቸገረኝ… እኔ ራድዮ ጣብያ ነበር ምሰራው በምስራበት በወቅት መጥታ የሬድዮ ጣብያ አለቃዬን አስፈቅዳ ይዛኝ ሄደች ነገሩ እንግዲህ አፍ እያነቃነቁ የሚዘፍኑት "ማይም " አይደል ሚባለው እንደሱ ልንሰራ ነው የሄድነው፡፡ ግን አንድ ያላሟላችሁ ነገር ነበር …እሱ የምንቀዳበት ቴፑ ባትሪ መኖር ነበረበት ግን ባትሪ የለውም😂 ባትሪ ሲኖር ያው ለመስራት ያመች ነበር፡፡

የምንሰራበት ቦታ ስንደርስ ሲታይ ባትሪ የለውም ስለዚህ አማራጭ ያደረግነው እዛው ቢሮ ሬድዮ ጣብያ አካባቢ መስራት ነው አሁን የምታዩት ቪድዮ በዚህ መልክ ተሰርቷል "ብለዋል፡፡

ድምፃዊ ግርማ ነጋሽ የኔ ሀሳብ ሙዚቃ ተሰርቶ አልቆ ከሌሎች የሙዚቃ ሰዎች ጋር ሙዚቃው ተወዳድሮ " ሶስት መቶ ብር" እንዳሸነፉ እና ለራሳቸው "አምሳ ብር" ወስደው ቀሪውን ሙዚቃውን ለሰርሩት እንደሰጡ ጨምረው እንደገለፁ ይጠቁማሉ፡፡

የኔ ቫይብ የመዝናኛ እና የሙዚቃ ዝግጅት እጅጉኑ ያከብሮታል ድምፃዊ ግርማ ነጋሽ፡፡

በማስተዋል የተሰራ አልበም የማስተዋል እያዩ(እንዚራ አልበም) 2016 ገፀ በረከትይድረስ ለማስተዋል እያዩ…(በተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)በየዘመኑ እንዲህ አይነት ክስተት ዘፋኞች ብቅ ይላሉ በ...
06/09/2024

በማስተዋል የተሰራ አልበም የማስተዋል እያዩ(እንዚራ አልበም) 2016 ገፀ በረከት

ይድረስ ለማስተዋል እያዩ…

(በተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ)

በየዘመኑ እንዲህ አይነት ክስተት ዘፋኞች ብቅ ይላሉ በሙዚቃ መንገድ ታሽቶ የመጣ እንዲህ ያለ የሚስብ አቅም ያደርሰናል፡፡ በትዝታ በሀሳብ ላቅ ያለ የማስተዋል የድምፅ እርከን ስፋት ፣ ቀለም ፣ ሬንጅ ፣ የቅኝት ባለቤት ጉሮሮው እንደ ፈለገ የሚተታጠፍ የመሳሰሉት ያየንበት ነው፡፡

አንድ ወዳጄ የፋና ላምሮት ፈርጥ ድምፃዊ ናሆም ነጋሽ ስለዚህ አልበም ስናወራ እንዲህ አለኝ " ወይን እያደር አይደል የሚጣፍጠው ይህ አልበም እንዲያ ነው ደሞ ከ ጣፈጠ በኃላ ደረጃውም ቦታውም ይልቃል"አለኝ፡፡ ልክ ነው በልቤ ያስቀመጥኩት እና በአዕምሮዬ ሲዘዋወር የነበረውን ሐሳብ በሙሉ ቋንቋ ገልፆልኛል፡፡

ጠቅላላ ሙዚቃዎች ሲሰሩ በስሜታቸው እና በስልተ ምቱ በአግባቡ መግለፅ ያስፈልጋል ምክንያቱም የሙዚቃ ነፍሱ እሱ ስለ ሆነ ፡፡በነጠላ ሙዚቃዎቹ አቅም እና ችሎታውን በሚገባ አሳይቶን ወደ አልበሙ ተከስቶ ታዕምራዊ አልበም ሰቶናል፡፡ 'እዚራ' አልበም ተወዳጁን ማዲንጎ አፈወርቅን እንድናስታውስ የሚደርገን ብሎም አብዛኛው በዜማ የሰራው እራሱ ማስተዋል ሲሆን ይህ ሌላኛው የማዳመጥ ክህሎት የመጣበት የሙዚቃ ደረጃ ምን ያህል እንደሆነ ይነገርናል፡፡የሙዚቃ ቫራይቲ(የተለያየ አይነት ስልት እና ሐሳብ ) ሬጌ ፣ ሱዳኒክ ፣ ትዝታ፣ ፎክ (ባህላዊ የሙዚቃ አዛዝያም)፣
የቅኝትሙዚቃዎች ተሰርተዋል፡፡14 የሙዚቃ ክሮች ሲኖሩት ደጉ ትዝታ ፣ መጥቼ ነበር ፣ በምን ቃል፣ ደግሰን ፣ ከፋኝ ፣ እንዚራ የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡

ከአልበሙ የገረመኝ እና የወደድኳቸው የሙዚቃ ስራዎች ከአብዛኛው ጥቂቱን ልገልፅላችሁ፡፡

"ከፋኝ" (ትዝታ) የተሰኘ ሙዚቃ ሐሳብ የግጥም ውህደቱ ለዚህ ዓለም ጉዞ በሰውኛ አገላለፅ ሌላው መንገድ ሰውኛ እውነትን ሆኖ እዉነትነትን ሳይስት ይናገናል፡፡ በመከፍት በህመም መደራረብ ውስጥ ብዙ ዝርዝር ጉዳዮች አሉ አብረን የኖርነው መልክ እያየነው ሲጠወልግ ዛሬ ላይ ያሉ ትናንትናዋን ያላወቁ ሰዎች በመልኳ ሲሳለቁ እሱ ግን ቆም ብሎ ትናንት አውቃታለሁ ለዚህ እንኳን ገላጋይ ዳኛ አያስፈልግም እኔ ምስክር ነኝ በምንም በሁሉም የትማርክ ነበረች ጊዜ ጥሏት እንጂ፡፡ግጥም ጥላሁን ሰማው ዜማ አበበ ብርሀኔ ቅንብር ታምሩ አማረ(ቶሚ)

"የማለዳው ለምለም- ውበቷ ቄጤማው
ጠውልጎ አየሁ ዛሬ - ሲፈርድ እድሜ ዳኛው
አወይ ዘመን - ባዳ አቤት ጊዜ ክፉ
ለምልክት እንኳን - አንድ አለ ማትረፉ"…

"(እቴ)" (ሞደርን ፎክ) ባህል ዘመናዊ የተሰኘው ሙዚቃ ቅንብሩ የዘጠዎቹ /ሰባዎቹ ሙዚቃ ቅርፅ እንድናስታውስ ያደርገናል የሙዚቃ ቅንብሮቹ በምክንያት የተሰሩ የማስተዋል የድምፅ እርከን ስፋት በሚገባው የድምፅ ጉልበት የተጠቀመበት ድንቅ ሙዚቃ ፅዱ ማንነት ገለጣ፡፡ ዜማ ምረት አብ ደስታ ግጥም ናትናኤል ግርማቸው ቅንብር ሚካኤል ሀይሉ(ሚኪ ጃኖ)::

"የቆንጆ ፍቅር - እና- ትንታ ያለበት
ሞት ቅርቡ ነው- እና- ውሀ አታርቁበት
ችዬው ልኑር እንጂ - ስራበው ወይ ስጠማሽ
መቼም ሰው አይድንም - ከሐመልማሎ ገላሽ"

"ጉብልዬ(ቅኝት)" የነፀብራቅ ድምፅ የሙዚቃ ጉልበቱ የታየበት የመጀመርያ ቅኝትን መቆጣጠር ፣ ሁለተኛው የእተቀባበሉ መዝፈን ፈተናው እና የውበት ፍሰቱን በመግለፅ ብዙ ነገሩ ስኬታማ አጫዋች ሆኖ ያየንበት ነው፡፡ሐሳቡ ትዝታን ወደ ኃላ እየቃኘ ስለ አንድ ሰው እሱ በሌለበት ወዳጆቹ ሲነጋገሩ ሲጨዋወቱ፡፡ ግጥም ናትናኤል ግርማቸው ዜማ የህዝብ እና መስተዋል እ ቅንብር ሚካኤል ሀይሉ፡፡

''አጋርሽ መሆኑን ሰምቼ ፣ ያ የጥንት ወዳጅሽ ወዳጄ
እቴ ሙች ግራ ነው የገባኝ ፣ ሕይወት እንቆቅልሽ ሆኖ ባይ
እስኪ ግለጪልኝ ይሄን ነገር ፣ ያ ሰው የዛን ጊዜ ምንሽ ነበር''::

"እመጣለሁ" የፍቅር ትርጉም አንዱ አገላለፅ ይህንን አሳብ የተሸከመ ነው፡፡የግጥሙ ሐሳብ የምትወደው ሰው ህመምን መዋዋስ ሳይሆን እመምን ብቻህን መጋፈጥ ለምትጋፈጥበለት ሰው ደስታውን ሁሉ መመልከት ምክንያቱም ፍቅር በስቃይ ይጣፋል እና…ግጥም እና ዜማ አቡዲ ቅንብር ሚካኤል ሀይሉ፡፡

ከጀርባሽም ብሆንም - እንደ ዓይንሽ ልይልሽ
እንቅፋት ሲያይብኝ - እኔ እንድመታልሽ
------------
እኔ አንቺን - ስለምወድ ስለምወድ
እመጣለሁ ሂጂ እና - በአንቺ መንገድ

እነዚህ እና የመሳሰሉት ጣዕም ያላቸው ሙዚቃዎች ሰቶናል፡፡ነፍስ እንዲዘራ ደግሞ የሙዚቃ ከያኒያን በዚህ ልክ አጥብቀው ሙዚቃ የሚፈልገውን ስሜት ሰተውታል በቅንብር ብሩክ አፈርቅ ፣ ሚካኤል ሀይሉ(ሚኪ ጃኖ) ፣ ታምሩ አማረ(ቶሚ) በጥግም ዜማ ናትናኤል ግርማቸው ፣ ፍሬዘር አበበ ወርቅ ፣ ማስተዋል እያዩ ፣ አብዲ ፣ጥላሁን ሰማሁ ፣ ታመነ መኮንን ፣ ብሬ ብራይት ፣ እሱባለሁ ይታየሁ( የሺ )፣ አበበ ብርሀኔ ፣ ቢኒያምር አህመድ ፣ አንባቸው እሸቱ፣ ምረት አብ ደስታ ማስተሪንግ ሰለሞን ሀይለማርያም የመሳሰሉ ሰርተውታል፡፡

በዚህ አልበም ላይ እጃችሁ ያሳረፋችሁ ሁሉ በግሌ አመሰግናለሁ
አዘጋጅ እና አቅራቢ ተመስገን ኡካሬ የሐጌ ልጅ

የቲክቶክ ጊፍት በአሜሪካ የሀበሾችን ትዳር አፈረሰስማቸው ያልተጠቀሰ ሀበሻ ባለትዳሮች ነዋሪነታቸው በአሜሪካ ሀገር ነው። በጋራ የሚጠቀሙበት የካፒታል ዋን የባንክ አካውንት አላቸው  ከሰባት ወ...
02/09/2024

የቲክቶክ ጊፍት በአሜሪካ የሀበሾችን ትዳር አፈረሰ

ስማቸው ያልተጠቀሰ ሀበሻ ባለትዳሮች ነዋሪነታቸው በአሜሪካ ሀገር ነው። በጋራ የሚጠቀሙበት የካፒታል ዋን የባንክ አካውንት አላቸው ከሰባት ወር በኋላ ባል ወደ ባንክ በአጋጣሚ ሲሄድ እሱ የማያውቀው 50ሺ ዶላር ወጪ መሆኑን ይመለከታል ይላል ፋስት መረጃ ከታዲያስ አዲስ የሰማው ዘገባ፣ ከዛ የባንኩን ኃላፊዎች ሲያናግር 50ሺ ዶላሩ ለቲክቶክ አፕሊኬሽን ወጪ እንደሆነ ይነገረዋል።

ባል ወደ ቤት በመግባት ባለቤቱን ሲጠይቅ "ስራ ስለሌለኝ ለመደበሪያ ብዬ ነው ቲክቶክ ስጠቀም ለጊፍት ያወጣውት" የሚል ምላሽ ከሚስቱ ያገኛል፣ ባል እሺ በማለት ነገሩን ተቀብሎ ከቆይታ በኋላ 50ሺ ዶላሩ ለአንድ ወንድ ቲክቶከር ብቻ ወጪ እንደሆነ ይደርስበታል።

ጉዳዩ ወደ ፀብ ተቀይሮ በመሃል ሽማግሌ ገብቶ ትዳሩ መቀጠል ሳይችል በፍቺ ተጠናቋል።

የጊፍተር ትዳር ተበተነ።

በርካታ ፊልሞች ላይ የምናውቀው ተዋናይ ጌታቸው (ባቡጂ) ትናንት ምሽት ከዚህ አለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።ለቤተሠቡና ለአድናቂዎቹ መፅናናትን እንመኛለን።
25/08/2024

በርካታ ፊልሞች ላይ የምናውቀው ተዋናይ ጌታቸው (ባቡጂ) ትናንት ምሽት ከዚህ አለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል።

ለቤተሠቡና ለአድናቂዎቹ መፅናናትን እንመኛለን።

🚢 ጃፓን በከብት እበት የሚንቀሳቀሱ መርከቦችን እየሞከረች ትገኛለች🌍ጃፓን የአረንጓዴ ልማቷን ለማፋጠን አዲስ ነገር እየሞከረች ሲሆን መርከቦችን ከላም እበት በተሰራ ነዳጅ ለማንቀሳቀስ በሙከራ...
23/08/2024

🚢 ጃፓን በከብት እበት የሚንቀሳቀሱ መርከቦችን እየሞከረች ትገኛለች🌍

ጃፓን የአረንጓዴ ልማቷን ለማፋጠን አዲስ ነገር እየሞከረች ሲሆን መርከቦችን ከላም እበት በተሰራ ነዳጅ ለማንቀሳቀስ በሙከራ ላይ ትገኛለች! 🚢💨

ጃፓን ብክለትን ለመቀነስ እና በ2050 የተጣራ ዜሮ ልቀት ላይ ለመድረስ በምታደርገው ጥረት ይህን ባዮሜቴን የተባለ ከከብት እበት የሚሰራ ልዩ ነዳጅ በመርከቦች ውስጥ ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል መሆኑን ለማየት እየሰራች መሆኑ ተሰምቷል።

ይህ ሙከራ የሚሳካ ከሆነ ጃፓን አረንጓዴ ግቦቿ ላይ እንድትደርስ ብቻ ሳይሆን በዓለም ዙሪያ ያሉ መርከቦች ንጹሕና ዘላቂ ነዳጅን በመጠቀም ይንቀሳቀሱ ዘንድ ትልቅ በር ይከፍታል ተብሎ ይጠበቃል። 🌱⚓

Address

Addis Ababa

Telephone

251931636736

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when YeneTech.com posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share