
27/06/2025
በተራ ቁጥር አንድ ላይ ያለው የብዙ ኢትዮጵያዊ ወጣቶችን ህይወት የሚያበላሽ ስለሆነ ትምህርት ሚኒስተር በደንብ ሊያየው ይገባል
የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና አቻ ግመታ መመሪያ ቁጥር 990/2016 መሠረት በባለሥልጣኑ ማረጋገጫ የማይሰጣቸው የትምህርት ማስረጃዎች፡-
**ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የደረጃ 4 ብቃት ማረጋገጫ(COC) ሳያሟሉ እየተማሩ የነበሩና ትምህርት ከጀመሩ በኋላ ያሟሉ ከሆኑ፤
**ፈቃድ በሌለው የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የተማሩ ከሆነ፤
**የፕሮግራም ፈቃድ በሌለው የትምህርት መስክ የተማሩ ከሆነ፤
**የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ የመቁረጫ ነጥብ ሳያሟሉ የተማሩ ከሆነ፤
**የመጀመሪያ ዲግሪ ተምሮ ለመመረቅ የሚያስፈልገውን ዓመትና Credit hours ሳያሟሉ የተመረቁ ከሆነ እና
**ከውጭ ሀገር ተምረው በኢፊዲሪ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የአቻ ግምት ሳያሰሩ ተምረው የተመረቁ ከሆነ ናቸው፡፡
የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን
በፊስቡክ -https://www.facebook.com/FDRE.ETA
በትዊተር- https://twitter.com/FDRE_ETA
በቴሌግራም -https://t.me/FDRE_ETA
በዌብሳይት Www. neta.gov.et ይከታተሉ።