King Lalibela

King Lalibela Humanity

11/08/2025

ቃል የማይገልፀው ስሜት ፣ ታሪክ ራሱን የደገመበት ጀግንነት ፣ ጊዜን ዋጅቶ ትውልድን አኩርቶ ጨለማን የሚያነጋ ድንቅ ታሪክ ካለበት ከነብሮች ፣ ከአንበሳ ደቦሎች ቀዬ እነማይ ምድር የፈለቀ ሐይል ፣ በአንድ ጥሪ አለሁ ባይ ፣ ከፊት ቀድሞ ተሰላፊው ስምንተኛ በላይ ዘለቀ ክፍለጦር ታሪክ ሰሪው አባ ኮስትር ብርጌድ ነው ።

የዘመነ ካሴ ትውልድ !!

ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ምከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሀዘን መግለጫ'''"""""""""""""""""""""'""""""""""""""""""""""""""""""""""""""የአብይ አህመድ አገ...
05/08/2025

ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ የሀዘን መግለጫ
'''"""""""""""""""""""""'""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
የአብይ አህመድ አገዛዝ በሚከተለው የሽብር መንገድ ምክንያት የኢትዮጵያን ወጣቶችን የመኖር፣ የመማር፣ የመስራት እና የመበልፀግ ተስፋ አጨልሞታል። ለወትሮውም በድህነት ውስጥ የሚኖረው ወጣት በሰላም ወጥቶ የማይገባበት አደገኛ ሁኔታ ተፈጥሯል።

የአገዛዙ ካድሬወች እና የወራሪው ሰራዊት መኮንኖች ከህዝብ በሚዘርፉት ገንዘብ የቅንጦት ኑሮ በሚኖሩበት፤
የኑሮ ውድነቱ ጣሪያ ነክቶ ዜጎች ከተማ ውስጥ ሳይቀር በረሃብ የሚያልቁበት ሁኔታ እንግዳ ሳይሆን የተለመደ የሀገሪቱ መገለጫ ሆኗል።

የአብይ አህመድ የጦርነት ፕሮጀክት የነበረውን ኢኮኖሚ መብላቱ ሳያንስ ለሜጋ ፕሮጀክቶች ጭምር ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት በሀገር ስም የሚመጣን ገንዘብ አገዛዙ አማራ ክልል ለሚያደርገው ጦርነት አውሎታል።

የማምረቻ ኢንዱስትሪወች ተዘግተው፣ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ሽባ ሆኖ አረመኔው አገዛዝ ለማያልቀው የጦርነት አዙሪት የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላን አጠናክሮ ቀጥሎበታል።
በእነዚህ እና መሰል አገዛዙ በፈጠራቸው ምክንያቶች ስደትን አማራጭ ያደረጉ ወጣቶች በሞት መንጋጋ ማለፍ ምርጫቸው ከሆነ ውሎ ያደረ ጉዳይ ነው።

በመሆኑም በዚህ ዓመት ብቻ በጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም 48፤ ጥር 10 ቀን 2017 ከ 20 በላይ፤ መጋቢት ወር 2017 ዓ.ም 31 እንዲሁም ሐምሌ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ከ60 በላይ ኢትዮጵያዊያን ድህነት እና ጦርነትን በመሸሽ ስደትን መርጠው በጀልባ ሲጓዙ በደረሰ አደጋ ህይወታቸውን አጥተዋል። ይህ አሳዛኝ ክስተትም በአገዛዙ ሚዲያወች በኩል ለይስሙላ እንኳን ሽፋን አይሰጠውም።

የአማራ ፋኖ በጎጃም በዚህ መንገድ ህይወታቸውን ባጡ የሀገራችን ወጣቶች ከፍተኛ ሀዘን የተሰማው መሆኑን እየገለፀ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ይመኛል።

የሀገራችን ወጣቶች ከስደት ይልቅ ፀረ- አብይ አህመድ አገዛዝ ትግሎችን ተቀላቅለው የተነጠቀውን ሀገር በትግል ማስመለስ ምርጫቸው እንዲያደርጉ ጥሪ እናቀርባለን!!

አዲስ ትውልድ! አትውልድ! ስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!

ይህ ከታች የምታዩት ቲክቶከር እና ማህበራዊ አንቂ ጎጃሜ ትክክለኛ ስሙ ማን ይባላል?
04/08/2025

ይህ ከታች የምታዩት ቲክቶከር እና ማህበራዊ አንቂ ጎጃሜ ትክክለኛ ስሙ ማን ይባላል?

ተናግረን ያልፈፀምነው፣አቅደን ያላሳካነው ፣ጀምረን ያልጨረስነው ፣ፎክረን ያልማረክ ነው ፣ተኩሰን ያልገደልነው ጠላት የለም። እራሳችንንም ከአገልጋይ የስርአቱ ባለማረጎች ጋር አናወዳድርም። በደ...
03/08/2025

ተናግረን ያልፈፀምነው፣
አቅደን ያላሳካነው ፣
ጀምረን ያልጨረስነው ፣
ፎክረን ያልማረክ ነው ፣
ተኩሰን ያልገደልነው ጠላት የለም።

እራሳችንንም ከአገልጋይ የስርአቱ ባለማረጎች ጋር አናወዳድርም። በደርግ ዘመን "ኢትዮጵያ ትቅደም"፤ በኢህአድግ ዘመን "አብዮታዊ ደሞክራሲ"፣ በብልፅግና ዘመን "መደመር" እየተጠመቁ ባገኙት የውለታ ባለ ማረግ ጀኔራሎች ጋር የሚያመሳስለን አይኖርም። የአድሱ ትውልድ መሪዎች ነን። ማርከን እጅ ተማርከን በህዝብ ፊት ታሪክ የምናበላሽ ብርሃኑ ጁላም አንሆንም። እናም የቀጣዩን ተጋድሎ እና ድላችንን ለማየት ያብቃን።

@ዝናቡ ልንገረው ደለለ

03/08/2025

የአዲስ አበባ ህዝብ ከእራብ ጦርነት ይሻላል ብሏል

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ መግለጫ """""""'"'"'""'"'"'"'"'"'"'"'''"''"''"'''"'"'"'"'"'"'"'""'"'"''"'"'""'"'ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ምየኢትዮጵያ ...
01/08/2025

ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ መግለጫ
"""""""'"'"'""'"'"'"'"'"'"'"'''"''"''"'''"'"'"'"'"'"'"'""'"'"''"'"'""'"'
ሐምሌ 25 ቀን 2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎች አብይ አህመድን ለማስወገድ ትብብር ማድረግ እንዳለባቸዉ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ የገለፅነው እና አቋም የያዝንበት ጉዳይ ነው።

እስካሁን ባለው ሂደት አገዛዙን የሚታገሉ ኃይሎች መተባበር እንዳለባቸው በልሂቃኑ በኩል እየተደረገ ያለው ጥሪ ለሚፈጠረው ተጫባጭ ትብብር ገንቢ ሚና የሚጫወት መሆኑንም ተገንዝበናል።

ከሰሞኑ ፀረ-ብልፅግና ትግል እንደሚያደርጉ ከገለፁ የኦሮሞ የፖለቲካ ኃይሎች በኩል እየተደረገ ያለውን የትብብር መንፈስ እና የጋራ አቋም በመልካም የምናየው መሆኑን እናሳውቃለን።

በእኛ በኩልም በኢትዮጵያ አንድነት እና ህልዉና ላይ የሚያምኑ፤ በአማራ ላይ መዋቅራዊ የህልውና አደጋ መድረሱን የሚቀበሉ፤ በብሔር ብሔረሰቦች
እኩልነት እና ፍትህ የሚያምኑ
እና በአብይ አህመድ አገዛዝ መወገድ ላይ የሚያምኑ የኢትዮጵያዊያን ኃይሎች ለሚያደርጉት ተጨባጭ ትብብር ዝግጁ መሆናችንንም እናረጋግጣለን!!

አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ

አፋጎ

01/08/2025

ሼር አድርጉ ጓዶች!!!

ድርጅታችን የአማራ ፋኖ በጎጃም አብዮታዊ ትግላችንን ዳር ለማድረስ 7/24 ስራ ላይ ነው‼️
ወምበራ-መተከል-ጎጃም ተከስተናል ።

የጀመርነውን የህልውና ትግል በድል ለመቋጨት በሁሉም ከባቢና ሁኔታ ድርጅታዊ ተልኳችንን እንፈፅማለን ።ራሳችንን እንመለከታለን፤በራሳችንን አቅም ማድረግ ከምንችለውም በላይ ለማድረግ እንጥራለን ።

እስከ ምፃት አማራ!

ክፋት ለማንም፣በጎነት ለሁሉም !

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!!
©Hailemichael Bayeh

አሳዛኝ ዜናየብልፅግናው ስርዓት የታጋዮችን እናት እና አባት : እህትና ወንድም በተለያዩ እስር ቤቶች አጉሮ እያሰቃየ መቆየቱ ይታወቃል:: በአሁኑ ጊዜ ግን የታጋይ ቤተሰቦች በተገኙበት አጋጣሚ...
27/07/2025

አሳዛኝ ዜና

የብልፅግናው ስርዓት የታጋዮችን እናት እና አባት : እህትና ወንድም በተለያዩ እስር ቤቶች አጉሮ እያሰቃየ መቆየቱ ይታወቃል::
በአሁኑ ጊዜ ግን የታጋይ ቤተሰቦች በተገኙበት አጋጣሚና ሁኔታ ከደርግ የቀይ ሽብር ስርዓት በባሰ ሁኔታ ነፃ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል::
በዚህም የ75 ዓመት እድሜ ሽማግሌ የሆኑትን የአርበኛ አበበ ፈንታውን አባት አቶ ፈንታው ደርበውን በቆቦ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን እያስቀደሱ በነበሩበት አውደ ምህረት ፊት ለፊት የአገዛዙ ሰራዊት ረሽኗቸዋል::

Asres Mare Damtie እንኳን ተወለድክልን ❤💪💪
27/07/2025

Asres Mare Damtie እንኳን ተወለድክልን ❤💪💪

26/07/2025

የአርበኛ ዘመነ ካሴን ጥሪ ተቀብለው እየተመሙ ነው።

1-ዘላለም አበራ 2-ንጉሱ መሀሪ 3-ስማቸዉ ጌትነት የተባሉ አድማ ብተናዎች የመሬችን አርበኛ ዘመነ ካሴን ጥሪ በመቀበል አስራ ዓለቃ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድን ተቀላቅለዋል።

ዘሜ የአዲሱ ትውልድ መሪ✊💪አባ መቻል✊💙 #ምልክቴ
26/07/2025

ዘሜ የአዲሱ ትውልድ መሪ✊💪

አባ መቻል✊💙

#ምልክቴ

የድጋፍ ጥሪበወንድማችን በዶ/ር አንዷለም ዳኜ ድንገተኛ ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ልጆቹንና ቤተሰቦቹን ለማገዝ እንዲሁም እርሱንም ሕያው ሊያደርጉ የሚችሉ ሥራዎችን ለመሥራት በዩኒ...
04/02/2025

የድጋፍ ጥሪ

በወንድማችን በዶ/ር አንዷለም ዳኜ ድንገተኛ ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ልጆቹንና ቤተሰቦቹን ለማገዝ እንዲሁም እርሱንም ሕያው ሊያደርጉ የሚችሉ ሥራዎችን ለመሥራት በዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደሥራ ተገብቷል።

እነዚህን የታሰቡ ሥራዎችን በትብብር እውን ማድረግ ይቻል ዘንድ ከዚህ በታች በሦስት የዩኒቨርሲቲው ሀኪሞች ስም በተከፈተው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ድጋፍ ማድረግ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ስለምታደርጉት ድጋፍ በቅድሚያ ከልብ እናመሰግናለን።

አካውንቱ የተከፈተው በዶ/ር ኃይለማርያም አወቀ፣ ዶ/ር አምሳሉ ወርቁ እና ዶ/ር መኳንንት ይመር ስም ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦1000676116978

chanie dagnaw

Address

Addis Ababa

Telephone

+251921642138

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when King Lalibela posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to King Lalibela:

Share