Yetneberk Tadele

Yetneberk Tadele NB: Please read our RULES before commenting on this page
1. No hate speech is allowed
2. Do not spam our page with offensive images or videos.

Do not use obscene, rude, crude, or insulting nicknames towards the admin of this page.
3. Do not harass, threaten, embarrass, swear at, sexually harass or abuse another participant.
4. For your safety, please do not post personal information like (ID number, phone number, smart card number) on our wall or in the comments.

5. One-liner comments that are negative, defamatory in nature, or intende

d to incite hostility may be moderated.
6. Duplicate postings (to queries already answered or any efforts at spam) will be viewed as 'flooding' and will be deleted.

7. Responses to any posts or users that are guilty of violating the above rules, and that also violate them, will also be moderated accordingly.

8. Any links posted to this page that don't have anything to do with our objectives will be deleted.

9. This platform is intended to be a space to share News information, political and social criticism especially in Ethiopia not inclined to any of the identity politics or religious groups.

* Please note: If you repeatedly disregard the above rules, you will be banned from our page.

20/09/2025

ጃዋር አዝሎ ስልጣን ላይ ያወጣናል ብላችሁ የምትቁለጨለጩ ጉደኞች፤ እንዴት ናችሁ? የኢትዮጵያን ፖለቲካ በዜሮ አብዝታችሁ መላ ቅጡን አሳጥታችሁ እንዲያቀረሸን ያደረጋችሁ ብኩኖች መሆናችሁን እንዳትረሱት በየመሀሉ እየመጣን እናስታውሳችሁዋለን። 😷😷😷

ግዕዝ ቋንቋ ነው ቋንቋ ደግሞ መግባቢያ ነው መመራመሪያም ይሆናል ቋንቋ ብሄርም ሐይማኖትም ጎሳም ጎጥም የለውም ለምሳሌ ኦሮሚኛ የኦሮሞ ብቻ ቢሆን ኖሮ ኬኒያ ድረስ ኡጋንዳ ድረስ ሱማሊያ ድረስ...
17/09/2025

ግዕዝ ቋንቋ ነው ቋንቋ ደግሞ መግባቢያ ነው መመራመሪያም ይሆናል ቋንቋ ብሄርም ሐይማኖትም ጎሳም ጎጥም የለውም ለምሳሌ ኦሮሚኛ የኦሮሞ ብቻ ቢሆን ኖሮ ኬኒያ ድረስ ኡጋንዳ ድረስ ሱማሊያ ድረስ ዘልቆ አይነገርም ነበር በምስራቅ አፍሪካ ሱሐሊኛንና ኦሮሚኛን የሚያክል በስፋት የሚነገር ቋንቋ የለም አረብኛ የአረቦች ብቻ ቢሆን ኖሮ ኢትዮጵያውያን ኡስታዞችና ኡላማዎች ሃይማኖታቸውን አያስተምሩበትም ነበር ሐገር እንጂ ቋንቋ ድንበር ኖሮት አያውቅም::

ኦሮቶዶክስ ሐይማኖት በግዕዝ ቅዳሴ ቀድሳ ወይማ አስቀድሳ ሊሆን ይችላል ሐይማኖቷን የምታስተምረውም ሆነ የምታስፋፋው ግን በአማርኛ ነው።
ሙስሊሞችም ብትሆ አማርኛን በስፋት የምትጠቀሙበት አግባብ አለ የተለያዩ ሐዴሶችና ነሺዳዎች በአማርኛ የሚታተሙበት ሁኔታ መኖሩ እሙን ነው አማርኛ ደግሞ ነገረ ስራው ሁሉ ከግዕዝ ነው የመነጨው የቋንቋው ስሪት ከግዕዝ የተወረሰ ነው። በስልጣኔ የትናየት ጥለውን የሄዱት ምዕራባውያን እንኳን በየ ዩኒቨርሲቲዎቻቸው ግዕዝን እያስተማሩ ባለበት በዚህ ጊዜ እኛ የትም ሳንደርስ እንዲህ በነገሮች መጠላለፋችን ያስደንቃል በግዕዝ የተለያዩ ጥበቦች በፅሑፍ ሰፍረው ይገኛሉ ተብሎ ይታመናል የመድሐኒት ቅመማ ጥበቦች (በመፅሐፈ ፈውስ ሰፍረው የሚገኙ ጥበቦች) የምህንድስና እና የቅርፃቅርፅ ጥበቦች የሙዚቃና የስነ ፅሑፍ ፍሰቶች የስነ ክዋክብትና የጂኦግራፊ ጥበቦች በቀደምት አባቶች ተፅፎና ተጠርዞ በተለያዩ ዘመኑን በሚመስሉ ጥቅሎችና መቅረፀ ድንጋዮች ተፅፈው እንደሚገኙ ኢንሳይክሎፒዲያና ዊኪፒዲያ በዝርዘር ተንትነው እወነታውን አስቀምጠውታል አርኪዮሎጂስቶችም በተለያዩ ጊዜዎች በቁፋሮ ተቀብረው ያገኟቸው ግዕዘኛ ፅሑፎች እማኝ ምስክሮች ናቸው ይህም ሆኖ ግን
ከግዕዝ ይልቅ አረበኛ የተሻለ ነው የሚል ካለ ማስረጃ አቅርቦ መሞገቱ ይቀላል አረብኛ ጠቃሚ የሆነበትን መንገድ በዝርዝር በመግለፅ እና እንደ አንድ ሳብጀክት ቀርቦ ዜጎች እንዲማሩበት መታገሉ ይሻላል እንጂ አንዱን አውግዞና አንዱን ለማግነን መሽቀዳደሙ ትክክል አይሆንም በበኩሌ ግዕዝንም ሆነ አረብኛን ብማር ደስታውን አልቾለውም!!
ምክንያቱም አለም ከአረብኛ ቋንቋ እጅጉን ተጠቃሚ እንደሆነች አይካድም አሁንም ሆነ ድሮም ለሂሳብ ቀመር ምቹ ሆኖ የአለም ህዝብ እየተጠቀመበት የሚገኘው ቁጥር አረብኛውን ቁጥር ነውና ሁሉም የራሱ የሆነ ጥሩ አበርክቶ እንዳለው መተማመኑ መልካም ነው።

ከግድቡ ወደ ወደቡ! 😀 😀 From the Dam to the Port! 🇪🇹 Go Ethiopia Go! ✊🔥
14/09/2025

ከግድቡ ወደ ወደቡ!
😀 😀
From the Dam to the Port! 🇪🇹 Go Ethiopia Go! ✊🔥

12/09/2025

"ምነው ሊወድቅ ሲል...?!"
===//====
ከሰሞኑ በያዝኩት አዲስ አቋም ሳቢያ ብዙ አስተያየቶች ተሰጥተዋል። ሁሉም በሚባል መልኩ ከተቃዋሚዎች ጎራ የተሰነዘሩ አስተያየቶች ሲሆን በተመሳሳይ መልኩ አስተያየቶቹም አንድና አንድ አይነት ናቸው፦ “ለሆድህ ብለህ፣ ተከፋይ፣ ችግር ክፉ ነው፣ ኮንዶሚኒየም ፍለጋ.....” እና የመሳሰሉት ሲሆኑ ከእነዚህ ለየት ያለው እና ትንሽ በውስጡ ሀሳብ ያዘለ የሚመስለው “ምነው ባለቀ ሰአት፤ ሊወድቅ ሲል፤ ምናለ ዝም እንዳልክ ብትቀር ...” የሚሉት ትንሽ ኮርኮር ስላደረጉኝ ሀሳብ ልሰጥባቸው ፈለግሁ።

“ምነው ሊወድቅ ሲል ደገፍክ?!”

አንደኛ፦
እውነት ሊወድቅ ነው እንዴ? በየት በኩል ነው የሚወድቀው? ምን ታይቷችሁ ነው ሊወድቅ ደረሰ ያላችሁት? ምነው ለኔ አልታየኝ አለ?

ሁለተኛ፦
ይሄኛው ሲወድቅ ማን ነው እየመጣ ያለው? ማን ነው ስርፋውን ሊወስድ ዝግጁ የሆነ? አለ? እርግጠኛ ናችሁ?

እንግዲህ እኔ እነዚህን እና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ራሴን ጠይቄ ለራሴ መልስ ሰጥቼ ነው ይህን አቋሜን ልይዝ የቻልኩት። እናንተም ለራሳችሁ ብቻ ታማኝ ሆናችሁ ራሳችሁን ጠይቁና ለራሳችሁ መልሱ።......... የኔ መልስ እንዲህ ነበረ......

አንደኛ፡-
እኔ የሚወድቅ የመንግስት ስርአት ፈጽሞ አልታየኝም። ይልቁንም እለት እለት እየበረታና እየተጠናከረ ሀይልን በእጁ እያደረገ ያለ የመንግስት ስርአት ነው ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየኝ። ይህ መንግስት የሚወድቅ ቢሆን ኖሮ ገና ያኔ የለውጥ ወጀብ ውስጥ ሆኖ ምንም የጠራ አንዳች የፖለቲካ መስመር አስምሮ ሳያሳይ፣ ከላይ እስከ ታች የተተበተበ የፖለቲካና የማህበራዊ ቀውስ ውስጥ እያለ፣ ይልቁንም የለውጡን ፍላጎትና አካሄድ አስቀድመው ተረድተው በአጭር ለማስቀረት ከራሱ ከውስጡ የወጡ ሀይሎች በፈጠሩት ሽብርና በቆሰቆሱት ጦርነት እንደ ገለባ በእሳት ተለብልቦ ትብያ በሆነ ነበር - ያኔ ገና በእንጭጩ!.....ያን ማዕበል የተሻገረና ህዝባዊ መሰረቱን አደላድሎ ደጋፊ ካበዛ በሁዋላ፣ አለማቀፍ ተደራሽነቱን ካስፋፋ በሁዋላ፣ አሁን ህዝቡ በተቃዋሚና በመንግስት መካከል ያለውን ልዩነት ልክ እንደ በጋ ሰማይ ጥርት አድርጎ ማየት ከቻለ በሁዋላ፣ አይፈጸሙም የተባሉ የአባይ ግድብን ጨምሮ ህልቆ መሳፍርት ሜጋ ፕሮጄክቶችን አሳክቶ ካሳየ በሁዋላ፣ ...... ከዚህ ሁሉ ነገር በሁዋላ ይሄ መንግስት ወደ መውደቂያው ተቃርቧል ብዬ ለማሰብ አሁን የደረስኩበት የእውቀት ደረጃና የቀሰምኩት የእድሜ ልምድ ፈጽሞ አይፈቅዱልኝም። እያበድኩ ካልሆነ በስተቀር፣ የሆነ የብሄር ከረጢት ውስጥ ገብቼ ካልሆነ በስተቀር፣ በፍጹም ጥላቻ ታውሬ ካልሆነ በስተቀር፣ ወይም ኢትዮጵያ ፍርስርሷ ቢወጣ የጥፍሬ ቅሻሻ ያህል የማይሰማኝ ሰው ካልሆንኩ በስተቀር .....ይሄ መንግስት ወደ መውደቂያው ቀርቧል ብዬ ላስብም ላወራም፣ የፖለቲካ አቋሜም አድርጌ ላስብ ከቶ አልችልም!!!!

ሁለተኛ፦
ከምርጫ 97 በሁዋላ የኢህአዴግ እድሜ ለጥቂት ጊዜም ቢሆን የተራዘመው እነ ልደቱ አያሌውን፣ እነ አየለ ጫሜሶንና መሰል የተቃዋሚ ቡድኖችን ወደ ፓርላማ ስቦ ማስገባት በመቻሉ ነበር። ምንም እንኳ ለህዝብ የረባ ነገር ባይሰሩለትም የፖለቲካው ምህዳር የሰፋና የህዝብ ድምጽ የሚሰማበት ፓርላማ እንዳለ ለማሳየት ተጠቅሞበታል። ምናልባት የወደቀውም ምርጫውን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮ (ከግርማ ሰይፉ በስተቀር) አጠቃላይ ተቃዋሚዎችን አባሮ ፓርላማውን ለብቻው በመቆጣጠሩ ነው። ይህን ያነሳሁልህ ለምን መሰለህ፤ ያሁኑ ፓርላማ “እኛ ወደድነውም ጠላነውም” የብዙ ፓርቲዎች ውህድ ነው። እነአብን እዝያ አሉ፣ እነ ኦነግ፣ ኢዜማ፣ ሌሎችም በስም ብዙ የማይታወቁ እንዲሁም የግል ፖለቲከኞችም አሉበት። ይሄን እንደ ቀላል አትየው። ሰፋ አድርገህ ስታየው በእነዚህ ሁሉ ቡድኖች ውስጥ የተደራጁ ብዙዎች ከመኖራቸውም በላይ የፖለቲካው ጅረት በአንድ በኩል ብቻ ይፈሳል ብለህ ልትደመድም አትችልም። ይህ ለዚህ መንግስት ተጨማሪ ጉልበት ነው።....(ይሄ ሰፊ ሀገራዊና አለማቀፋዊ እይታ ያለው ትንታኔ ይፈልጋል)....በአጭሩ ግን ይህም የዚህን መንግስት ስርአት “ሊወድቅ ቀረበ” ብለን አፍ እንዳመጣ እንዳንናገር የሚያደርግ ነው።

ሶስተኛ፦
ይህ መንግስት ነገ ጠዋት ቢወድቅ ተስፋችንስ ማን ነው? ማንን ነው ተስፋ ያደረግነው? እኛ ተስፋ ያደረግነውንስ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተስፋ ያደርገዋል? ነው ወይስ “ግድ የለም ይውደቅና ማን እንደሚተካው እናስብበታለን” የሚል ስሜታዊነት ነው? ማንን አዘጋጅተን ነው? አሁን የምናያቸው ተቃዋሚ የተባሉ ሰዎችም ሆኑ ቡድኖች እውነት የኢትዮጵያ ቤዛ ናቸው? እውነት?........ እውነታው ግን አንዳቸውም ፋይዳ ያላቸው አይደሉም! እስካሁን ነፍጥ ያነሳውም ሆነ፣ በተቃውሞ ተደራጀሁ ብሎ የነገረን ሁሉ እዚህ ግባ የሚባል ሀገራዊ ራዕይ ያለው ወይም አቅም ያለው፣ ወይም ፍላጎት ያለው አይደለም። እንዲያውም “ና ግባና ምራን” ቢባል የሚደነጋገርና ግራ የሚጋባ በስሜት እና በጥቂቶች ጭብጨባ ላይ ብቻ የተኮፈሰ ሀይል እንደሆነ ነው የሚገባኝ።.....

እና ወዳጆቼ “ሊወድቅ ሲል ደገፍከው” ያላችሁኝን ነገር በዚህ መልክ ነው አብላልቼ ፈትቼ “ብደግፈው ኢትዮጵያ ትጠቀማለች” ያልኩት።..... ይቆየን!!

12/09/2025

የኢትዮጵያ ችግር እንኩዋን ለጠቅላይ ሚንስትሩ ለራስዋ ለኢትዮጵያም ከአቅምዋ በላይ ነው:: ምን ለማለት ነው:- ለዘመናት ሲከማች የመጣው ችግር
- ድህነት
- ዘረኝነት
- ጥላቻ
- ስራ አጥነት
- የኢኮኖሚ መዳሸቅ
- ድንቁርና
- ከሀገሩ ይልቅ ለውጭ ሀገራት ጥቅም የሚሰራ ዜጋ ብዛት
- ከታማኝነት እና ከታዛዥነት ይልቅ ጥቅመኛና ሆዳምነት
- በስልጣን መባለግ
- ነገን በጋራ ጥቅም ውስጥ ማየት አለመቻል ጨለምተኝነት

እንዚህና የመሳሰሉት የተቆለሉ ችግሮች በአንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ብቻ ይፈታል ብሎ ማሰብ እና ለዚህ ሁሉ ችግር ደግሞ አብይን ተጠያቂ አድርጎ ማቅረብ ከላይ ከዘረዘርኩት ችግሮች በአንዱ ወይም በሁለቱ ተጠቂ የመሆን ምልክት ነው::

ችግሮች አሉብን ችግሮቻችንን ተቀራርበን በመነጋገር መፍትሄ እንፈልግላቸው:: ከዝያ ውጭ የኢትዮጵያ ችግር አብይ ነው እያሉ ቀንና ሌት መለፈፍ የህዝብን ጆሮ ከማደንቆር ውጪ አንዳች ጠብ የሚል መፍትሔ ለሀገራችን አያመጣም:: "መንግስትን ጥለን እኛ እንሞክረው" የሚል ቅዠትም በተደጋጋሚ ተሞክሮ የታየ ስህተት ነው!!

Let’s take a step back and think. Ethiopia’s challenges are not the result of one person or one administration, but the accumulation of issues from many past regimes. Real solutions take time. Rushing or blaming everything on the Prime Minister won’t help. What we need now is patience, calm, and unity—coming together is the only way forward.

12/09/2025

ዳህላክ ለየለት

12/09/2025

Listen to this

12/09/2025

የኤርትራ መንግስት ትናንት ባወጣው መግለጫ “ኢትዮጵያ የአሰብ ወደብን ጥያቄና የቀይ ባህር ጉዳይ ማንሳቷ በውስጧ ያለውን የእርስ በእርስ ችግር እና የኑሮ ውድነትን በመሸፋፈንና የህዝብ ድጋፍ ለማግኘት ነው” በማለት ገልጿል።

ያስቃል!!

በእውነት የኤርትራ መንግስት አርጅቷል ከምንል ጃጅቷል ብንል ይሻላል።
1ኛ) የኑሮ ውድነትን ያመጣብን ወደብ በማጣታችን ምክኒያት መሆኑን እንደምንገነዝብ አይገነዘብም።

2ኛ) የውስጥ ግጭት ችግራችን መነሻው የአሰብን ጉዳይ እንዳናነሳ እርስ በእርስ እየተናከስን እንድንኖር ከሚያደርጉ የውጭ ሀይሎች አንዱና ዋነኛው ራሱ የኤርትራ መንግስት መሆኑን የማናውቅ ይመስለዋል።

3ኛ) የኢትዮጵያ ህዝብ አሰብና ቀይ ባህርን አስመልሳለሁ የሚል መንግስት ሲያገኝ በዚህ ምክኒያት ህዝቡ አንድ ቢሆን “እሰየው” የሚያስብለው እንጂ ቅር እንደማይለው ለማሰብ አይችልም።

በጥቅሉ ግን እንኳን መንግስት ግለሰብም ቢሆን ሲጃጅ አደባባይ ባይውል ይመረጣል።

09/09/2025

ገና ለገና መንግስትን ደገፍክ ተብሎ በተቃዋሚዎች እንዳይተች ፈርቶ የግድቡን መጠናቀቅ ደስታውን ላለመግለጽ አፉን የሸበበውን ሰው ምን ትሉታላችሁ? ይሄ ሸለምጥማጥ!!

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ በመመረቁ የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ******************************የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ብጹ...
09/09/2025

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ በመመረቁ የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ
******************************

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፥ በሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ መመረቅ የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ።

ቤተክርስቲያኗ ለኢቢሲ በላከችው መግለጫ “ለዘመናት ኢትዮጵያን ቋሚ አድርገው ካቆዩ ዐምዶች መካከልም ፈለገ ግዮን የተባለው የዓባይ ወንዝ እና 'ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር - ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች' የሚለው የተስፋ ቃል እንደሆነ የታመነ ነው” ብላለች።

የኢትዮጵያ ትዕምርት ተደርጎ የሚወሰደው ፈለገ ግዮን በእኛ ዘመን ለሕዝቡ ብርሃን እያበራ አገልግሎት መስጠት የሚችልበት ሁኔታ ተፈጥሮ በማየታችን ከሁሉ አስቀድመን ለእግዚአብሔር አምላካችን ምስጋና እናቀርባለንም ተብሏል በመግለጫው።

“የዛሬዋን ቀን በመናፈቅ የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ዕለት አንስቶ አቅማችሁ የፈቀደውን ሁሉ ለዚህ ሥራ በማዋጣት ታሪክ በመልካም የሚያስታውሰውን ዋጋ የከፈላችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ልጆቻችንን እንኳን ደስ አላችሁ” ብላለች ቤተክርስቲያኗ በላከችው መግለጫ።

በመጨረሻም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ወደቀጣይ የልማት ሥራ የሚያሸጋግር እንዲሆን ብሎም ሰላም በምድራችን ላይ እንዲሰፍን ሁሉም ኢትዮጵያውያን በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባ በመግለጫው ተጠቅሷል።

በደርግ ጊዜ ነው የተወለድኩት - የኢትዮጵያ ስሟ ልክ  እንደ ዳዊት ጸሎት  መሸ ነጋ እየተደጋገመ በሚጠራበት፣ የሀገር ፍቅር ስሜት እንደ ኦክሲጅን በሚማግበት፣ በኢትዮጵያዊነት ፍቅር ያበደ ዘ...
08/09/2025

በደርግ ጊዜ ነው የተወለድኩት - የኢትዮጵያ ስሟ ልክ እንደ ዳዊት ጸሎት መሸ ነጋ እየተደጋገመ በሚጠራበት፣ የሀገር ፍቅር ስሜት እንደ ኦክሲጅን በሚማግበት፣ በኢትዮጵያዊነት ፍቅር ያበደ ዘመን ነበር። ኢህአዴግ መጣና ስሟን ማንሳት ወንጀል ሆኖ ያስወቅስ ያሳስር ጀመር። መሪዎቿ ኢትዮጵያ ላለማለት "ሀገሪቱ" እንዳሉ እንዳሳነሷት አንሰው አለፉ። ~~ ዛሬ መሪዋ ስሟን ጠርቶ የህዝብ መዝሙሯን ዘምሮ በአደባባይ እንዲህ ሲያነባ በስሟ እምባዉን ሲያፈስ በማየቴ እጅግ በጣም ደስታ ተሰምቶኛል። ይህ ነው በነገው ትውልድ ላይ (በዛሬ አላልኩም) በመጪው ትውልድ ላይ የሀገር ፍቅር ስሜትን የሚያሳድረው። ይህ ታዳጊዎች በየክፍሉ ከሚማሩት የሲቪክ ትምህር በላይ ጉልበት ያለው ሀገራዊ ስነልቦናን ሊገነባ የሚችል ድርጊት ነው። በህይወቴ እንዲህ ባለ ከፍታ በሀገር ፍቅር ስሜት ተውጠው እምባቸውን ሲያፈሱ አልቅሰው ካስለቀሱኝ አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣ አትሌት ሀይሌ ገ/ስላሴ ቀጥሎ ሶስተኛው ታሪካዊ ቀን ነው!! እናመሰግናለን።

አብዛኞቻችን ሀሳብ የማብላላት ችግር ፣ ከተነገረው ውስጥ ያልተነገሩ ዝርዝር ሀሳቦችን የማውጣት(infer) የማድረግ ውስንነት አለብን። አሁን ለምሳሌ ስለጨረቃ ግርዶሹ እና ስለአባቶች ጥበብ ሲ...
08/09/2025

አብዛኞቻችን ሀሳብ የማብላላት ችግር ፣ ከተነገረው ውስጥ ያልተነገሩ ዝርዝር ሀሳቦችን የማውጣት(infer) የማድረግ ውስንነት አለብን።
አሁን ለምሳሌ ስለጨረቃ ግርዶሹ እና ስለአባቶች ጥበብ ሲወራ "ኢንተርኔት ላይ ያለ መረጃ" የሚል ማጣጣያ ታመጣላችሁ... አባቶቻችን ከኢንተርኔቱ በፊት አስልተው መመዝገባቸውን እና የስነፈለክ ምርምር እንደአሁኑ በዘመናዊ መሳሪያ ሳይራቀቅ እነሱ ዕውቀቱ ነበራቸው የሚለውን አብላልቶ እንደመውሰድ ጭራሽ የቻት ጂፒቲ ን መልስ ለዋቢነት ታያይዛላችሁ።😄
"የዶ/ር ሮዳስ የምርምር ውጤት አይደለም።" ያለም አለ። ለእናንተስ አፍም የለኝ🙂
የማነስ ስነልቡናን በምንም ማከም አይቻልም። ዝም ብሎ ይማረን እንጂ....
መልካም ሰኞ!
@እጸገነት ከበደ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yetneberk Tadele posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yetneberk Tadele:

Share

Yetneberk Tadele Page

Yetneberk Tadele is an Ethiopian journalist who worked for several media houses since 2010. He created this page along with www.yeahun.com website to share news information about Ethiopia and Eastern Africa.