Yetneberk Tadele

  • Home
  • Yetneberk Tadele

Yetneberk Tadele NB: Please read our RULES before commenting on this page
1. No hate speech is allowed
2. Do not spam our page with offensive images or videos.

Do not use obscene, rude, crude, or insulting nicknames towards the admin of this page.
3. Do not harass, threaten, embarrass, swear at, sexually harass or abuse another participant.
4. For your safety, please do not post personal information like (ID number, phone number, smart card number) on our wall or in the comments.

5. One-liner comments that are negative, defamatory in nature, or intende

d to incite hostility may be moderated.
6. Duplicate postings (to queries already answered or any efforts at spam) will be viewed as 'flooding' and will be deleted.

7. Responses to any posts or users that are guilty of violating the above rules, and that also violate them, will also be moderated accordingly.

8. Any links posted to this page that don't have anything to do with our objectives will be deleted.

9. This platform is intended to be a space to share News information, political and social criticism especially in Ethiopia not inclined to any of the identity politics or religious groups.

* Please note: If you repeatedly disregard the above rules, you will be banned from our page.

ሰሞኑን የትግራይ ወጣቶች "እናንተ ወንበር ላይ ልትቀመጡ፤ እኛ ዊልቸር ላይ አንቀመጥም" በማለታቸው የተናደደው አቶ እስታሊን የተባለ ወሬ አምራች ጦር ሰባቂ ነጋዴ "እንዴት አንሞትም ትላላችሁ...
31/07/2025

ሰሞኑን የትግራይ ወጣቶች "እናንተ ወንበር ላይ ልትቀመጡ፤ እኛ ዊልቸር ላይ አንቀመጥም" በማለታቸው የተናደደው አቶ እስታሊን የተባለ ወሬ አምራች ጦር ሰባቂ ነጋዴ "እንዴት አንሞትም ትላላችሁ፣ እንዴት እግራችን አይቆረጥ ትላላችሁ፤ ታዲያ እኛ አሜሪካ ተቀምጠን ሌላ ስራ አንሰራ፣ አልተማርን ምን በልተን እንኑርላችሁ፡ ሳትወዱ በግድ በጦርነት ትማገዳላችሁ እኛም ለወላጆቻችሁ ቪዲዮ በሊንክ እንሸጥላችሁዋለን" በማለት ሰላም ይውረድ በሚሉ የትግራይ ወጣቶች ላይ ቁጣውን አዝንቧል። ሙሉውን ከዚህ በታች አያይዤላችሁዋለሁ! መጥኔ ለትግራይ እናት! ሌላ ምን ይባላል?!

ስለምን ጴንጤን አከብራለኹ?ስለትዝታው በሌላ ቀን እናወራለን። ከልጅነት ጀምሮ በቃለ እግዚአብሔር፣ በዜማ ያሳደገችው ቤተ ክርስቲያን ነች። ይህንን የመንፈስ ቅዱስ ፀጋ አንድ ከትክለለኛው የመዳ...
30/07/2025

ስለምን ጴንጤን አከብራለኹ?

ስለትዝታው በሌላ ቀን እናወራለን። ከልጅነት ጀምሮ በቃለ እግዚአብሔር፣ በዜማ ያሳደገችው ቤተ ክርስቲያን ነች። ይህንን የመንፈስ ቅዱስ ፀጋ አንድ ከትክለለኛው የመዳን ትምህርት በመለየት፣ ሁለት ለክርስቲያናዊው ትውፊትና ስርዓት ባለመገዛት፣ ሦስት ፍፁም ዋልጌና ጨዋነት የሌለው ሰው በመሆን አርክሶታል። ይህ እንዴት ይታረም? የዚህ አጭር ፅሑፍ ዓላማ አይደለም።

ዋናው ይህ አጭር ማስታወሻ ማተኮር የፈለገው ይህንን ብልግና፣ ጋጣወጥነትና ሊናገሩት የሚያፀይፍ ተግባር ጋር የተባበሩ፣ ውንብድናውን ያፀደቁ፣ መድረክ ያመቻቹ እንደመልካም አጋጣሚ የተጠቀሙ በተለምዶ “ጴንጤ”የሚባሉ ራሳቸውን “ወንጌላውያን” ብለው የሚጠሩ ወንጀላውያን ሰዎችን እንዴት እናክብር? ሀገር የጋራ: እምነት የግል ብለን እንኑር? ሰርግና ለቅሶ እንድረስ? ለእግዜር ሰላምታስ የተገቡ ናቸው?

ትብብሩ በካውንስል ደረጃ ስለሆነ ነው ይህንን የጠየኩት።

ከዚህ ብልግና ራሳቸውን ያራቁ ግለሰቦች ጥቂት ቢሆንም የሰጡትን አስተያየት ተመልክቻለኹ። እነርሱን በጅምላ እዚህ ውስጥ እንዳላስገባ እሰጋለኹ። ራሳቸውን ስላከበሩ እኔም ክብራቸውን ላለመንካት እጠነቀቃለኹ። የወመኔ ማናጆውን ግን ምን ላድርገው ነው ጥያቄው?

29/07/2025

"እነሱ ወንበር ላይ ሊቀመጡ
እኛ ዊልቸር ላይ አንቀመጥም!!"

What a wonderful way to say NoMoreWar

አላስፈላጊ የቋንቋ ቅራቅንቦ ህዝብን ማደናገርና ሀገር ማደህየት እንጂ ምንም ጥቅም የለውም! አንድ ብሄራዊ ቋንቋ  ለሀገር ደህንነትና ብሄራዊ ጥቅም አንዲሁም ለህዝብ አንድነትና ሰላም ብሎም ለ...
15/07/2025

አላስፈላጊ የቋንቋ ቅራቅንቦ ህዝብን ማደናገርና ሀገር ማደህየት እንጂ ምንም ጥቅም የለውም! አንድ ብሄራዊ ቋንቋ ለሀገር ደህንነትና ብሄራዊ ጥቅም አንዲሁም ለህዝብ አንድነትና ሰላም ብሎም ለኢኮኖሚ እመርታ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው! በዚህስ ይበርቱ ብለናል ክቡር ፕሬዝዳንት!

ድሮስ ትግራይን የመገንጠልና ኢትዮጵያን የማፈራረስ ቅዠት ካልተሳካ እዚያ ምን ይሰራሉ?! እውነታውን ውጠው መስተካከል እንጂ። በኢትዮጵያ ፖለቲካ በርካታ የተቀባዠሩ ሁኔታዎችን ታዝበናል እንደ ...
12/07/2025

ድሮስ ትግራይን የመገንጠልና ኢትዮጵያን የማፈራረስ ቅዠት ካልተሳካ እዚያ ምን ይሰራሉ?! እውነታውን ውጠው መስተካከል እንጂ። በኢትዮጵያ ፖለቲካ በርካታ የተቀባዠሩ ሁኔታዎችን ታዝበናል እንደ ኦሮሞ ኦርቶዶክስና ትግራይ ሲኖዱስ ተብዬ ከፋፋይ ዘረኝነት ግን አላየንም። በአለም ያሉ ሰዎች ለግል ጥቅማቸውና ለሆዳቸው ያሻቸውን ቢያደርጉ "ጉዳዩ ይገባናልና" ከቻልን እንታገላቸዋለን ካልቻልን በትዝብት አይን እናያቸዋለን። ሰማያዊውን መንግስት አይተው ያሳዩናል፣ ለመንግስተ ሰማያት ተዘጋጅተው ያዘጋጁናል የምንላቸው "መነኮሳት" የዘር ኮሮጆ ውስድጥ ገብተው ፖለቲካ ሲፈተፍቱ ግን እጅግ ተስፋ ያስቆርጣል። ብቻ እንኳን ቅዠቱ አልፎላቸው ለመመለስ አበቃቸው እንጂ ሌላ ምን ይባላል! ቢችሉ ግን ከዚህ በሁዋላ ከካሜራ ፊት ርቀው ወደ በአታቸው ቢገቡ ለእነሱም ንሰሀ ይሆናል እኛንም ከማስኮነን ይድናሉ!!!

አወይ ዳያስፖራ!ድሮ ሀገር ቤት ያለ ሰው አንዲት ዘመድ ውጭ ሀገር ካለችው በቃ መላ ቤተሰቡ እንደ ዘመናይ እንደ ስልጡን ይቆጠር ነበር - እንኳን ዋናው ዳያስፖራ ይቅርና የሚያውቁት ሁላ በስሙ...
09/07/2025

አወይ ዳያስፖራ!
ድሮ ሀገር ቤት ያለ ሰው አንዲት ዘመድ ውጭ ሀገር ካለችው በቃ መላ ቤተሰቡ እንደ ዘመናይ እንደ ስልጡን ይቆጠር ነበር - እንኳን ዋናው ዳያስፖራ ይቅርና የሚያውቁት ሁላ በስሙ "ብዙ ያወቁ" ተደርገው ይታዩ ነበር።

የዘንድሮ ዳያስፖራ! ~
በስንት ቴሌቭዥንና ራዲዮ ጣቢያ "አንዴ ቁጭ በይና ድምጽሽን እንስማው፣ አናግሪን" ብለው የሚለምኗት የኢትዮጵያ የሚዚቃ ንግስት አስቴር አወቀ በዲያስፖራው ድርጊት ፍጹም ግራ ተጋብታ ለዘመናት የምትውረገረግበትን መድረክ ገታ አድርጋ፤ ማይክራፎኗን ዝቅ አድርጋ "ምነው ምን ነካችሁ?" ስትል ድንጋጤዋን ሳትደብቅ ተናገረች።

"ለመሆኑ ፕሮግራሙን ልታዩ "ልትታደሙ" ነው ወይስ ፎቶ ልታነሱ ነው የመጣችሁት?" ስትል በአደባባይ ጠይቃለች - ዳያስፖራውን!

እጅግ የሚያሳፍር ነው። የሙዚቃ ኮንሰርት ለመታደም ሄዶ እንደ ፎቶ አንሺ ከመጀመርያ እስከ መጨረሻ ፎቶና ቪዲዮ ማንቀጫቀጭ ምን ይሉታል? አንዳንድ ጊዜ መች፣ ምን፣ ለምን ያህል ጊዜ የሚሉ ነገሮችን አስቦ አለመንቀሳቀስ አሳፋሪ ነው። ከሁሉ በላይ ቪ አይ ፒ ከፍሎ ገብቶ ከፊት ተደርድሮ ፎቶ ማንሳት የራስን ጊዜ ማባከን ብቻ ሳይሆን የፕሮግራሙን ተዋንያንም መረበሽ ይሆናል።

ከአመታት በፊት ባርሴሎና የሚባለው የስፔን እግርኳስ ክለብ ሶስት የሚገርሙ እጥቂዎች ነበሩት።እነኚህ አጥቂዎች ሜሲ ኔይማር እና ሱዋሬዝ ይባላሉ።በዛን ወቅት የነበርነው የባርሳ ወይም የተቀናቃኙ...
08/07/2025

ከአመታት በፊት ባርሴሎና የሚባለው የስፔን እግርኳስ ክለብ ሶስት የሚገርሙ እጥቂዎች ነበሩት።እነኚህ አጥቂዎች ሜሲ ኔይማር እና ሱዋሬዝ ይባላሉ።በዛን ወቅት የነበርነው የባርሳ ወይም የተቀናቃኙ ክለብ ደጋፊዎች ይሄ ክለብ ሶስቱ ተጫዋቾች ከሌሉ ጨርሶ የሚፈርስ ክለቡንም የሚደግፍ ሰው ፈፅሞ የሚጠፋ ይመስለን ነበር።ባርሴሎና የሚባለው ክለብ ሶስቱ ተጫዋቾች ከመፈጠራቸው በፊት እንደነበረ ሶስቱ ባይኖሩም መኖሩ እንደሚቀጥል ረስተነው ነበር።
የሚገርመው ነገር ሜሲ ኔይማር እና Suarez ክለቡን ከለቀቁት አመታት ተቆጥረዋል። ሶስቱም ተጫዋቾች ክለቡን ከለቀቁት በኋላ የድሮ ዝናቸው እንጂ የፈጠሩት አንድም አዲስ ታሪክ አንድም አዲስ ነገር የለም ።እንደውም ባርሳ እያሉ በገነቡት ስም ነው ሁሉ ቀጣሪ የሚያገኙት።
ባርሴሎና ግን በአዳዲስ እና ወጣት ተጫዋቾች አሁንም ከከፍታው ማማ ላይ ተቀምጦ አለ።
Koan AD
What a word! 👌👌👌

ፋሲል ደሞዝ ታማኝን አልወቀሰም! ታማኝም በፋሲል ጉዳይ የሚወቀስበት ጉዳይ የለም!ወንድሙ ሲያጋድል የሚውለው ኩታራ በታማኝ ላይ የሚጮኸው  ሰበብ ነው!  ለፋሲልም አዝኖ አይደለም። ጫካ ያሉ ወ...
06/07/2025

ፋሲል ደሞዝ ታማኝን አልወቀሰም! ታማኝም በፋሲል ጉዳይ የሚወቀስበት ጉዳይ የለም!

ወንድሙ ሲያጋድል የሚውለው ኩታራ በታማኝ ላይ የሚጮኸው ሰበብ ነው! ለፋሲልም አዝኖ አይደለም። ጫካ ያሉ ወንድሞቹን እርስ በእርስ ሲያገዳድል የሚውል የፖለቲካ ቅጥ አንባር የማያውቅ፣ የህዝብ የረዥም ጊዜ ጥቅም የማይገባው ጥርቅም ለፋሲል ሊያዝን አይችልም። ሙዚቀኞች በዚህ ወቅት መዝፈን የለባቸውም እያለ ሲዘምት የከረመ ኩታራ አሁን ተነስቶ የፋሲል ጉዳይ ሊያስጨንቀው አይችልም። የፈለገው ለሰበብ ነው። መጮሂያ ነው።

ይህ ምክንያት እየፈለገ በታማኝ ላይ የሚጮኸው ወንድሙን ሚሊሻና ፋኖ እያለ ሲያጋድል የሚውል መንጋ እጁን ሳይታጠብ ወደገባበት ፖለቲካ ታማኝ ቢጠጋለት ለማድመቂያ እጁን ስሞ ይቀበለው ነበር።

ኩታራው በታማኝ ላይ ሰበብ ፈልጎ የሚጮህባቸው ጉዳዮች አሉ። "አብይ ስር ወደቀ" ምናምን ይለዋል። ግን አብዛኛው በየሰልፉ የአብይ አህመድ ባነር አሳታሚ የነበር ነው! ሲፈልግ አብይን የተሸከሙትን ጀግኖቼ የሚል ነው።

በዛ ክፉ ዘመን ስለ አማራ ጭፍጨፋ ማንም ሳያነሳ ታማኝ በየነ ሲጮህ እንዳልኖረ አሁን ፌስቡክና ቲክቶክ ላይ ስለ አማራ ፖለቲካ የተለማመደ ሁሉ ሰበብ እየፈለገ የሚጮኸው ከታማኝ የተሻለ ሰርቶ፣ ታማኝ በደል ፈፅሞ አይደለም። አንድም ታላቅን የመዝለዝ ህመም፣ ሁለትም ከትህነግና ሌሎቹ ሳያጣራ የተቀበለው የትርክት መአት ሰለባነት፣ አሊያም የስካር ፖለቲካ ነው። ስድብና ዘለፋ ፖለቲካ የሚመስለው ስለተጠራቀመ ነው።

ታማኝ ሰርቶም የሚጮህ ኩታራ በርካታ ነው። ዝም ብሎም የሚጮኸው በርካታ ነው። ይህ ሰውዬ ምን አድርጎ ነው? ተብሎ ቢጠየቅ ይህ ነው የሚባል ነገር አያመጡም!

የአብይ ደጋፊ ነበር የሚሉት አብይን ተሸክመው የመጡትን ጀግና አድርገው የትግሉ ፊት አውራሪ ናቸው እያሉ ነው!

በአንድ በኩል ዝም አለ፣ በዚህ ጊዜ ጠፋ ይሉትና በሌለበት፣ ጠፋ ባሉት ደግሞ ይከሱታል። በሌለበት። የመስደብ፣ የመዝለፍ ጩኸት ነው። በሽታ ነው።

ታማኝ አሸዋ ሲበትን ለሚውለው ኩታራ ተራራ ነው። በአደባባይ አገዛዝን የተጋፈጠ፣ በሰብአዊ እርዳታ የደረሰ፣ ግዙፍ ሚዲያ አቋቁሞ ያጋለጠ ሰው ነው። ታማኝ ህዝብ በተጠቃ ጊዜ ጎላ ያለ ድምፁን ያሰማ ሰው ነው። ይህ ሁሉ ጩኸቱ ድብልቅልቅ ያለ ኩታራ ሁሉ የታማኝን ያህል አላጋለጠም። ግን ትልቆችን እየተከተለ መዝለፍ አመል ሆኖበት በየቀኑ ይዘልፈዋል! የፋሲል ጉዳይም ሰበብ ነው። መዝለፊያ ነው። ኩታራው ትግል የሚመስለው ትልቆችን መዝለፍና ማንጓጠጥ ነው። ታማኝ የዚህ በሽተኛ ኩታራ ሰለባዎች መካከል አንዱ ነው! ምን ሰራህ ቢሉት ከዚሁ ሶሻል ሚዲያ ላይ ግሩፕ ከፍቶ ከመሳደብ ውጭ ምንም ያልፈየደው ሁሉ ራሱን ታጋይ አድርጎ ትልቆቹን ሲያንጓጥጥ መዋል ሆኗል አሁን ትግሉ!

ችግር ቢኖር ኖሮ እንኳን ኩታራው በሙያም፣ በትውውቅም፣ በምንም ለፋሲል ከታማኝ አይቀርበውም። በሁለቱ መካከል ገብቶ ለማራራቅም ለማቀራረብም አይችልም። ግን ሰበብ ይፈልጋል። ለመስደብ፣ ለመዝረፍ፣ ያለ ስም ስም ለመስጠት። ይህን ደግሞ ትግል ይለዋል። ኩታራው!
Getachew Gashaw

አያ አበበ አጎቴ ነው። ስም ያለው ገበሬ ነው። "ጉዛም ነኝ!" ይላል። አምራች ገበሬ ነኝ ለማለት፤ ጸዳ ያለ አርሶ አደር ነው። እና ሊጠይቀኝ እና በዚያውም ሰርግ ሊጠራኝ ከጎጃም ተነስቶ ቤቴ...
14/06/2025

አያ አበበ አጎቴ ነው። ስም ያለው ገበሬ ነው። "ጉዛም ነኝ!" ይላል። አምራች ገበሬ ነኝ ለማለት፤ ጸዳ ያለ አርሶ አደር ነው።
እና ሊጠይቀኝ እና በዚያውም ሰርግ ሊጠራኝ ከጎጃም ተነስቶ ቤቴ መጣ....ስንጨዋወት ስለ ሃብታምነት ተነሳና አላሙዲ ላይ ደረስን።😂
አጎቴ "አንደኛ ሃብታም ነው!" ስለው ደነገጠ። ...እሱን የሚበልጥ ተገኘ።
"ኸረ! አሁን አንደኛ ሃብታም ነው የምትሉት እንደኔ ዘጠና ቀፎ ሰቅሏል ወይ?....ስንት የሚታለብ ላም አለው?...እንደኔ በአንድ ጊዜ ሶስት ልጅ ድሮ ቀየውን ሶስት ቀን አብልቷል ወይ?...😂😍" በጥያቄ ወጠረኛ!!
"አንተ ላይ እማ አይደርስም አጎቴ። ሆሆ.."😂
Daniel Tefera

እቴጌ ህይወት መኮንን.እባላለሁ በታማኝነት እና በጨዋነት ማርና  ቅቤ   በማቅረብ ደንበኞችን አፍርቻለሁ  አሁንም በጥራት. በታማኝነት እንደምሰራ ደንበኞቼ ምስክር ናቸው። የባልትና ውጤቶችንም...
07/06/2025

እቴጌ ህይወት መኮንን.እባላለሁ በታማኝነት እና በጨዋነት ማርና ቅቤ በማቅረብ ደንበኞችን አፍርቻለሁ አሁንም በጥራት. በታማኝነት እንደምሰራ ደንበኞቼ ምስክር ናቸው። የባልትና ውጤቶችንም ጀምሪያለሁ ። ስለዚህ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ ሀገር ያላችሁ ደንበኞቼ ዛሬ አዲስ ማር እና ቅቤ ጣዝማ ማር ይገባል እዘዙኝ፤ በታማኝነት እና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ አቀርባለሁ እዚሁ ሶሻል ሚዲያ ላይ ለአራት ተከታታይ አመታት በጥራት እና በንፅህና ብዙ ደንበኞችን አፍርቻለሁ ስራዬም ምስክር ነው። አሁንም ስራዬን አበረታቱልኝ ሼር ላይክ በማድረግ ተባበሩኝ።
አድራሻ ቦሌ አራብሳ
ስልክ. 0935751531
0968198252
ደውሉልኝ በታማኝነት አቀርባለሁ ።
Etege Hiwot Mekonenn

፩ "የብሔር የፓርቲ ፖለቲካ በሕግ ይታገድ"-ይህንን ያሉት በፌዴራል የምክክር መድረክ ላይ የታደሙት የመከላከያ፣ የደህንነትና የፖሊስ አባላት ናቸው። ሀሳባቸው ብቻ ሳይሆን አገላለፃቸው ጭምር ...
01/06/2025

፩ "የብሔር የፓርቲ ፖለቲካ በሕግ ይታገድ"
-
ይህንን ያሉት በፌዴራል የምክክር መድረክ ላይ የታደሙት የመከላከያ፣ የደህንነትና የፖሊስ አባላት ናቸው። ሀሳባቸው ብቻ ሳይሆን አገላለፃቸው ጭምር የሚገርም ነበር።
ደግሞም ይህንን ብለው አላበቁም፤ በየአካባቢው ለሚታየው ቁርሾ እና ቁርቋሶ ዋና ምክንያቱ በሀገራችን ያለው የቋንቋ ፌዴራሊዝም ነው፤ እናም ለአስተዳደር አመቺ በሆነ አቀማመጥ መቀየር አለበት፦ አሉ።
ሌላም ሌላም ሌላም፣ ጠንከር ያለ ሐሳብ አቅርበዋል፦ የፀጥታ አካላቱ።

ሌላው የገረመኝ የመንግስት አመራሮች ያቀረቡት ሐሳብ ነው። የክልል ፕሬዝዳንቶች፣ ሚኒስትሮች፣ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ያሉበት ቡድን ነው ይኼ።
"የሀገሪቱ ህገ መንግስት ተቀዶ ይጣል የሚሉ አሉ፤ ይሻሻል የሚሉ አሉ፤ ስለዚህ የሕገመንግስት ጉዳይ በአጀንዳነት መያዝ አለበት" የሚል ሐሳብ አቀረቡ። የፌዴራሊዝም አወቃቀር ጉዳይም አጀንዳችን ይሁን ብለዋል። (የሚመሩት ክልል የተደራጀበትን ሁኔታ በካልቾ እንደመምታት ያለ ነው ሐሳባቸው)
ኧረ ሌላም ሌላም (አስደናቂ) ሃሳብ አቅርበዋል፦ ነገሩን በFacebook ለመዘርዘር አይመችም እንጂ በግል አስገርመውኛል።

ደግሞ የውህድ ማንነት ጉዳይ በአፅንኦት ይታይልን ያሉ አሉ። ውህድ ማንነት የተባለው፣ ከሁለት ብሔር አባላት የተወለደ ሰው ነው። ማነኝ ነው የሚለው? ሀገሩ የት ነው? የትም ቦታ መብት የለውም፤ ስለዚህ የሁለት ብሔር ተወላጆች መብት መረጋገጥ የሚችልበት ሁኔታ አጀንዳ መሆን አለበት ያሉ አሉ።
የአዲስ አበባ ጉዳይ፣ የማንነት ጉዳይ የሚነሳባቸው የውስጥ ድንበሮች ጉዳይ፣ የባንዲራ ጉዳይ.....ብላ፣ ብላ፣ ብላ...በአጀንዳነት ይያዝልን ብሏል፦ ሚሊንየምን አዳራሽን የሞላው ታዳሚ።
---
መውጫ
---
ወዳጄ፤
ለ3 ቀናት በቆየውና ዛሬ በተጠናቀቀው የፌደራል ባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ላይ ያልተነሳ ጉዳይ የለም።
በአጭሩ ምክክሩ ሸጋ ነበር፦ ተስፋ ያጭራል።
እዚህ ላይ ደግሞ የፖለቲካ እስረኞች ቢፈቱና ቀጣዩ ውይይት ላይ ቢሳተፉ ደግሞ 👌👌👌
(ወሰን ሰገድ ገ/ኪዳን)
------------
ተስፋ አለኝ! አምናለሁ አንድ ቀን ይህ በሀገሬ ሰማይ እውን ይሆናል! ተስፋ አልቆርጥም!!

ጨዋ የተዋህዶ ልጅ ሱራፌል ብስራት እና ዶ/ር ሄርሜላ ተስፋዬ መልካም የትዳር ዘመን እመኝላችሁዋለሁ
25/05/2025

ጨዋ የተዋህዶ ልጅ ሱራፌል ብስራት እና ዶ/ር ሄርሜላ ተስፋዬ መልካም የትዳር ዘመን እመኝላችሁዋለሁ

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yetneberk Tadele posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yetneberk Tadele:

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share

Yetneberk Tadele Page

Yetneberk Tadele is an Ethiopian journalist who worked for several media houses since 2010. He created this page along with www.yeahun.com website to share news information about Ethiopia and Eastern Africa.