መንክር ሚዲያ-Menker Media

መንክር ሚዲያ-Menker Media ዝማሬ፤ስብከት፤ወቅታዊ መረጀ ማስተላለፊያ ገፅ

በአቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ የተከፈተው ክስ ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም ለምን ሆነ???ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መመስረቷ ይታወቃል።...
18/07/2025

በአቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ የተከፈተው ክስ ቄሱም ዝም መጽሐፉም ዝም ለምን ሆነ???

ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መመስረቷ ይታወቃል። አቶ ትዝታው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ለዓመታት 365/6 ቀናት በተለያየ ርእስ ሲሳደብ እንደኖረ ሁሉም የሚያውቀው ሀቅ ነው። ከ50 ሚሊዮን በላይ አማኝ አላት ተብሎ የሚነገርላትን ቤተክርስቲያን ለዓመታት ሲሰድብ የኖረን ግለሰብ ቤተክርስቲያን "በሕግ ይጠየቅልኝ" ብትልም ሕጉ የሚሰራው ግን ተቋምን ለሚሳደብ ሳይሆን በተለያየ ምክንያት መንግሥትን ለሚወቅስ ለሚተች ብቻ ነው።

ከወር በፊት አንዲት ህጻን ገና በአስተሳሰብ ያልበሰለች በቲክቶክ በጫወታ መሀል የድሬ ደዋን ንዋሪ አለባበስ የሚያጎድፍ ቃላት ተናገረች ተብሎ ከድሬ ደዋ አ/አ ድረስ ለሕግ መከበር ብዙ የደከመ የጸጥታ አካል ከ50 ሚሊዮን በላይ አማኝ የሚከተላትን ቤተክርስቲያን ከፍ ዝቅ እያደረገ ሲሳደብ የነበረን ግለሰብ በሕግ ከመጠየቅም በላይ በሰፊው ቤተክርስቲያንን ይሳደብ ዘንድ በሚልንየም አዳራሽ ፕሮግራም እንዲያዘጋጅ ፍቃድ ተሰጥቶታል።

እንዲህ ያለ ግለሰብ የትኛውንም ተቋማት ሲሳደብ ሲያንቋሽሽ ህዝብ ከህዝብ ያራርቃል ፣በሀገሪቱ ፍትህ ስርአት ላይም እምነት ያሳጣል።ተበዳይ በሕግ ያላገኘውን ፍትህ በጉልበት ለማግኘት ወደ መሞከር ያሸጋግራል። ይሄ ደግሞ እንደ ሀገር ሰላም ያሳጣል። ህዝብ ከህዝብ ያራርቃል። ተቋም ከተቋም ያናንቃል። ትዝታውን በሕግ አግባብ እንዲጠየቅ ማድረግ ጥቅሙ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ነው። ማንም ተነስቶ የትኛውም ተቋም ላይ የጥላቻ ንግግር እንዳይናገር ያስተምራል።

አቶ ትዝታው ሳሙኤል ቤተክርስቲያንን ለዓመታት እንዴት ሲሳደብ እንደነበር በማስረጃ የተደገፈ ክስ የደረሳችሁ የፍትህ አካላት የቀረበላችሁን ማስረጃ መሰረት በማድረግ ፍትህን እንድታሰፍኑ እንጠይቃለን ። ይሄን ባታደርጉ ግን ነገ በየ ሚዲያው እየወጣ ተቋማትን የሚሳደብ ትውልድ እንዲበረክት እያመቻቻችሁ እንደሆነ መታወቅ አለበት። ከየትኛውም የሃይማኖት ተቋም ይሁን በአስተምሮት ላይ ከመወያየት በዘለለ የጥላቻ እና የማጥላላት ሀሳብ በሚዲያ ቢያስተላልፍ በሕግ አግባብ መጠየቅ አለበት።

በዚህ የዘገየ የፍትህ ስርአት ላይ ሊጠየቁ የሚገባቸው አካላት

1ኛ, የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሕግ ክፍል ጉዳዩን ምእመኑ ደስ እንዲለው ብቻ ነው የጀመራችሁት ወይስ እውነት ቤተክርስቲያን መሰደቧ አሳስቧችሁ መብቷን ለማስከበር?

2ኛ,በፖለቲካው ሜዳ ላይ ውሃ ቀጠነ የሚለው የሀገሪቱ የፍትህ ስርአት ሃይማኖት ሲነካ ሲሰደብ ሲንቋሸሽ አይመለከተውምን?

3, ፕሮቴስታንታዊ ሃይማኖት ተቋማት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ሰድቦ አንቋሾ ዛሬ እንደገና አብራችሁ አምልኮ ለመፈፀም በሚልንየም አዳራሽ ትገኙ ይሆን? ከተገኛችሁ ነገ የእናንተን ተቋም የሚሳደብ ትውልድ ሲመጣ በየትኛው የፍትህ ስርአት ትጠይቁት ይሆን? እና ዛሬ በጋራ ሆኖ ስርአት አልባን ሰው ለፍትህ ማቆም አይሻልምን?

4ኛ, የዚህን ግለሰብ በሕግ መጠየቅ ስታበስሩን የነበራችሁ የቤተክርስቲያኒቱ ሚዲያዎች አሁን ያለበትን የክስ ሂደት ለምን ለምእመኑ እየተከታተላችሁ አታደርሱም?

እኛ ግን እንደ ጀመርን ዛሬም ቤተክርስቲያንን የደፈረ ግለሰብ በሕግ እንዲጠይቅ ደጋግመን እንጠይቃለን ።

መንክር ሚዲያ-Menker Media

መንክር ሚዲያ-Menker Mediaን በተለያዩ የSocial Media Platform ላይ ለመከታተል ከታች የተቀመጠውን Link ተጭነው ቤተሰብ ይሁኑ።

በYou Tube👇👇👇
http://www.youtube.com/

በFacebook 👇👇👇👇
https://www.facebook.com/MenkerMedia21?mibextid=ZbWKwL

በTiktok👇👇👇
tiktok.com/

በTelegram👇👇👇👇
https://t.me/MenkerMedia21

በWhatsApp👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4xtde1NCrPbBLUZA1O

"በኮሜዲያን እሼቱ ስራ አልቅሻለሁ"
16/07/2025

"በኮሜዲያን እሼቱ ስራ አልቅሻለሁ"

#

በዓለ ሲመታቸውን በግብርና ሥራ ያከበሩት ሊቀ ጳጳስ!!!ብፁዕ አቡነ ይስሐቅብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ሊቀ ጳጳስ ዘወላይታ  ሲመተ ጵጵስና የተቀበሉት ሐምሌ 9ቀን 2009  ዓ/ም የዛሬ 8 ዓመት ነበ...
16/07/2025

በዓለ ሲመታቸውን በግብርና ሥራ ያከበሩት ሊቀ ጳጳስ!!!
ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ሊቀ ጳጳስ ዘወላይታ ሲመተ ጵጵስና የተቀበሉት ሐምሌ 9ቀን 2009 ዓ/ም የዛሬ 8 ዓመት ነበር ።ያቺ ቀን በወላይታ ላለቺው ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በቅዱስ ሲኖዶስ አድሮ ሥራውን የሠራባት ፣ የብርሃን ጮረ የፈነጠቀበት፣ የአባቶች ራዕይ እውነት የሆነበት ፣ ቀንዳችንን ከፍ ከፍ ያለበት ፣የደስታ እንባ ያነባንበት፣የከበርንበት ልዮና ክቡር ቀን ነበረች ።

እነሆ ዛሬ በዚህ 8 ዓመት ውስጥ 320 የነበረው የአብያተ ክርስቲያናት ብዛት 90 ተጨምሮ 410 ደረስን በመንበረ ጵጵስናው 9 ገዳማትና አድባራት ዛሬ 20 ደርሰዋል ፣ 37 ዓመት የዘለቀው የደብረ መንክራት አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ፍጻሜውን አግኝቶ ተመርቋል ፤በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ( ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ) የሚል የማዕረግ ስም ተሰጥቶታል ። አብነት ት/ቤት በሁሉም ወረዳ ይሉቁንም በርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ መንክራት አቡነ ተክለሀይማኖት ገዳም 50 አዳሪ ተማሪዎች ዜማና ንባብ እየተማሩ ይገኛሉ በቅኔ ማኅሌት ሲያገለግሉ ላዬ ሁሉ የነገይቱ ቤተክርስቲያን ከፍታ መገመት አይቸግረውም በጠቅላላ ይህ 8 ዓመት ለወላይታ የመባረክና የከፍታ ዘመን ነው ።ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። መድኃኔዓለም ለብፁዕ አባታችን ረጅም ዕድሜ መልካም ጤንነትን ያድልልን። አሜን ።

መንክር ሚዲያ-Menker Media
በውስጥ የደረሰን መልእክት ነው።

ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ለተነሳባቸው ጥያቄ መልስ ሰጡ
14/07/2025

ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ለተነሳባቸው ጥያቄ መልስ ሰጡ

14/07/2025

ከርእሰ ሊቃውንት አባ ገ/ኪዳን የተላከ መልእክት ።

ዝርዝር ሀሳባቸውን በዚህ Link ፈውስ መንፈሳዊ ቻናል ላይ ያገኙታል።
https://youtu.be/G15xeED-EYI?si=R9KdpfDE5FSudbDX

ሼር በማድረግ የልጅነት ግዴታዎን ይወጡ።

የብፁዕ አቡነ ማርቆስ መልእክት
10/07/2025

የብፁዕ አቡነ ማርቆስ መልእክት

ተክሊል ለማን ነው የሚፈቀደው? አንዱ ድንግል ሆኖ አንዱ ባይሆን ጋብቻቸው በምን ሊሆን ይገባል?
09/07/2025

ተክሊል ለማን ነው የሚፈቀደው? አንዱ ድንግል ሆኖ አንዱ ባይሆን ጋብቻቸው በምን ሊሆን ይገባል?

08/07/2025

ስርአተ ተክሊል፣ስርአተ ቁርባንን በተመለከተ ለብዙዎች ጥያቄ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ረቡዕ ምሽት 1:00 ሰዓት በመንክር ሚዲያ ዩቱብ ቻናል ይጠብቁን።

መንክር ሚዲያ-Menker Mediaን በተለያዩ የSocial Media Platform ላይ ለመከታተል ከታች የተቀመጠውን Link ተጭነው ቤተሰብ ይሁኑ።

በYou Tube👇👇👇
http://www.youtube.com/

በFacebook 👇👇👇👇
https://www.facebook.com/MenkerMedia21?mibextid=ZbWKwL

በTiktok👇👇👇
tiktok.com/

በTelegram👇👇👇👇
https://t.me/MenkerMedia21

በWhatsApp👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4xtde1NCrPbBLUZA1

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መንክር ሚዲያ-Menker Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share