24/02/2023
አገራችን በአፍሪካ የእንስሳት ሀብት ቁንጮ እንድትሆን ያደረጋት ቅንና ትጉ ሕዝብ ፣ ዛሬ ያለውንና የምንኮራበትን፣ ሕይወቱንም ጭምር ሊያጣ በረሃብ ከሚቀስፍ የመልዐከ ሞት ሠራዊት ጋር ተጋፍጦ መድረሳችንን የሚጠብቅ ሕዝብ ሆኗል ቦረና፡፡
ይህ በዚች ምድር ተወልዶ ላደገ ሁሉ የእናት ጡት የሆነ ማኅበረሰብ ዛሬ የእንዳንዳችንን አነስተኛ ግን ፈጣን ድጋፍ ይሻል፡፡ አትሌቶች፣ አርቲስቶች ፣ፖለቲከኞች መንግሥታዊና መመንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሁሉ ከሞት መንጋጋ ሊታደጉት ካልተረባረቡ በኅሊና፣ በታሪክና በፈጣሪ የፍርድ ሚዛን ፊት የሚቆሙበት ሠዓት ነው፡፡
ሁሉም ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ ዕውቀት ያለው በሀሳቡ፣ ጉልበት ያለውም በጉልበቱ የድርሻውን ለማበርከት ይንቀሳቀስ፡፡ ከፊት ቀድመው በግል፣ በቡድንም ሆነ በድርጅት ለአፋጣኝ ምላሽ ለማስተባበር ጥሪ ከሚያቀርቡልን እውነተኞች ጎን እንሰለፍ፡፡
ወርቃለማሁ ንጋቱ