RiseUp Ethiopia

RiseUp Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from RiseUp Ethiopia, News & Media Website, Addis Ababa.

ለምን እስራኤል ወታደር እስልምናን እንዲማር እና አረብኛ እንዲማር የግዴታ አደረገች።የስለላ ሰራተኞች የሃውቲ ግንኙነቶችን የመለየት ችግር ስላጋጠማቸው በሁቲ እና በኢራቅ ቀበሌኛ ልዩ ስልጠና ...
26/07/2025

ለምን እስራኤል ወታደር እስልምናን እንዲማር እና አረብኛ እንዲማር የግዴታ አደረገች።

የስለላ ሰራተኞች የሃውቲ ግንኙነቶችን የመለየት ችግር ስላጋጠማቸው በሁቲ እና በኢራቅ ቀበሌኛ ልዩ ስልጠና ላይም መርሃ ግብሩ ያተኩራል።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በስለላ ክንፍ ውስጥ ያሉ ሁሉም ወታደሮች እና መኮንኖች በአረብኛ ቋንቋ እና እስላማዊ ጥናት እንዲሰለጥኑ ግዴታ አድርጓል። ይህ ጅምር በጥቅምት 7፣ 2023 አካባቢ ከስለላ ውድቀት በኋላ የመጣ ነው ሲል እየሩሳሌም ፖስት ዘግቧል።

ይህ የስልጠናው አዲስ ተጨማሪ አላማ የስለላ ሰራተኞችን የትንታኔ አቅም ማጠናከር ነው። በሚቀጥለው ዓመት መጨረሻ 100 በመቶው AMAN (የእስራኤል ወታደራዊ ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት የዕብራይስጥ ምህጻረ ቃል) ሰራተኞች በእስላማዊ ጥናት የሰለጠኑ ሲሆን 50 በመቶው ደግሞ የአረብኛ ቋንቋ ስልጠና ይወስዳሉ።

ለውጡ የታዘዘው በኤማን አለቃ - ሜጀር ጄኔራል ሽሎሚ ቢንደር ነው።

የስለላ ሰራተኞች የሃውቲ ግንኙነቶችን የመለየት ችግር ስላጋጠማቸው በሁቲ እና በኢራቅ ቀበሌኛ ልዩ ስልጠና ላይም መርሃ ግብሩ ያተኩራል።

እንደ ዘገባው ከሆነ በየመን እና በሌሎች የአረብ አካባቢዎች ጫት - መለስተኛ የአደንዛዥ እፅ ተክል በማህበራዊ ሁኔታ የሚታኘክ ሲሆን የንግግር ግልፅነትን ይጎዳል።

አንድ ከፍተኛ የአማን መኮንን ለጦር ሠራዊቱ ራዲዮ እንደተናገሩት "እስከ አሁን ድረስ በባህል፣ በቋንቋ እና በእስልምና ጥሩ ደረጃ ላይ አልደረስንም። በእነዚህ አካባቢዎች መሻሻል አለብን። የመረጃ መኮንኖቻችንን እና ወታደሮቻችንን በአንድ መንደር ውስጥ ያደጉ የአረብ ልጆች አድርገን አንለውጥም፣ ነገር ግን በቋንቋ እና በባህል ጥናት ጥርጣሬን እና ጥልቅ አስተውሎትን በውስጣቸው እንዲሰርጽ ማድረግ እንችላለን።"

የሰራዊቱ ራዲዮ ወታደራዊ ጋዜጠኛ ዶሮን ካዶሽ እንደገለጸው ለአረብ እና ኢስላማዊ ትምህርት የሚሰጥ አዲስ ክፍል ይኖራል።

በተጨማሪም IDF በእስራኤል መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የአረብ እና መካከለኛው ምስራቅ ጥናቶችን ለማስተዋወቅ የተቋቋመውን TELEMን እንደገና ለመክፈት አቅዷል። ቀደም ሲል መምሪያው በበጀት እጥረት ምክንያት ተዘግቶ የነበረ ሲሆን በዚህም ምክንያት ሀገሪቱ አረብኛን የሚማሩ ሰራተኞች ቁጥር በእጅጉ ቀንሷል።

19/07/2025

We do not accept any refugee

ለምንድነው አንዳንድ አገሮች 8 ሚሊዮን ስደተኞችን ከዩክሬን ለመቀበል ፍቃደኛ የሆኑት ነገር ግን 2 ሚሊዮን የፍልስጤም ስደተኞችን ለመቀበል ፈቃደኛ ያልሆኑት?

ማንም የፍልስጤም ስደተኞችን አይቀበልም - ሌላው ቀርቶ እነርሱን የሚደግፉ መስለው የሙስሊም መንግስታትም ጭምር።

በዮርዳኖስ ተቀባይነት አግኝተው ንጉሱን ለመግደል እና አገሪቷን ለመያዝ ሞክረው ከሶሪያ ጋር ተባብረው ከፍተኛ ጦርነት አስነሱ።
ወደ ሶርያ ተባረሩ፣ እዚያም ችግር ፈጥረው ወደ ሊባኖስ ተወሰዱ።
በሊባኖስ ሀገሪቱን ሙሉ በሙሉ ያወደመ የእርስ በርስ ጦርነት እንዲቀሰቀስ አድርገዋል።
በግብፅ የሽብር ጥቃቶችን ፈጥረዋል። ግብፅ ሃማስን በአሸባሪ ቡድን ፈርጆ ድንበሩን ከረጅም ጊዜ በፊት ዘግታለች። የጋዛን ወረራ ለመከላከል ያላቸው መከላከያ የበርሊን ግንብ ይመስላል።

በኩዌት ወራሪውን ኢራቃውያንን ደገፉ እና ከተሸነፉ በኋላ ተባረሩ።
በጋዛ ሃማስ ስልጣን ከያዙ በኋላ በትንሹ 600 የፋታህ ደጋፊዎችን ጨፍጭፈዋል።

25/06/2025

በ1970ዎቹ በሰሜን ኢትዮጵያ (በትግራይ/ኤርትራ) በአንድ ሚሽነሪ ትምህርት ውስጥ በትግርኛ ቋንቋ በታዳጊዎች የተዘመረ ዝማሬ ነው::
👉ርዕስ:- ምስጋና ምስጋና
👉ዘማሪ:- አዲሱ ወርቁ

ሰኔ 10 2017 በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከ  #ግድያ ውጪ የትኛውንም ዓ...
17/06/2025

ሰኔ 10 2017
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከ #ግድያ ውጪ የትኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ተጠያቂ የማያደርግ አዋጅ ጸደቀ፡፡
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ በህዝብ አንደራሴዎች ምክር ቤት ጸድቋል፡፡
አዋጁ በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ (Under cover investigation) እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታ ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያትና ከፈቃዱ ውጪ በሆኖ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም ይላል።
የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ(ዶ/ር) በአዋጁ 5/15 ላይ የቀረበው ዐረፍተ ነገር ትንሽ ከባድ መስሎ እንደታያቸው ተናግረው አዋጁ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
እንደዚህ ዓይነት አዋጅ በተለይ ሽብርን ለመከላከል ለሀገራችን ያስፈልጋታል ሲሉ የምክር ቤት አባሉ ተናግረዋል፡፡
‘’የሆነው ሆኖ ግን አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ከግድያ በስተቀር ለሚፈጽመው ወንጀል አይጠየቅም ይላል፡፡ አንደኛ ወንጀል ፈጽሟል ይላል፣ ወንጀል ፈጽሞ አለመጠየቅ ትክክለኛ አይመስለኝም፡፡ ወይም ድርጊቶቹ ተዘርዝረው ህጋዊ መብት የተሰጠው ሰው ሚወስዳቸው እርምጃዎች ወንጀል አይደሉም ብለን ማለፍ እንጂ አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ለሚፈጽመው ወንጀል ከግድያ በስተቀር የሚለውን ሰው እንደፈለገ እንዲሆን የሚያደርግ ነው’’ ሲሉ አለሙ(ዶ/ር) ሃሳበቸውን አስረድተዋል፡፡
ሌላ ሙሉቀን አሰፋ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው "እኔ በግሌ እንደተፎካካሪ የፖለቲካ ሰው አዋጁ ባለሀብቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን እና የታዋቂ ሰዎችን መብት የሚገድብ ነው" ብለዋል፡፡
"እንዲያውም የመናገር መብትን ይከለክላል የሚል እምነት ነው እኔ ያለኝ "ያሉት የምክር ቤት አባሉ ‘’ምክንያቱም አዋጁን ስናየው በ10 ዓመት ገድቦ ነው የወጣው’’ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
‘’ህግ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ነው ተግባራዊ መደረግ ያለበት’’ ያሉት አቶ ሙሉቀን ‘’ስለዚህ ከ10 ዓመት ወዲህ ብሎ ማውጣቱ የተወሰኑ ግለሰቦችን ወይም ቡድኖችን ለማጥቃት ያሰበ ስለሆነ ለሀገራችንም ጥሩ አይደለም የሚል እምነት አለኝ’’ ብለዋል፡፡
‘’በአለም አቀፍ ስምምነቶች ላይ እንደተገለጸው ሀይልን በመጠቀም፣ ንጹሃንን በማስገደድ አላማቸውን ለማስፈጽም የሚሳተፉ ተዋናዮችን ተጠያቂ ለማድረግ ሳይሆን አዋጁ እየዋለ ያለው በዋነኝነት የመንግስት ተቃዋሚዎችን፣ መንግስት ውስጥ ሆነው መንግስትን የሚተቹትን እና ጋዜጠኞችን ነው’’ ያሉት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) ናቸው፡፡
‘’የአዋጁን ዝርዝር ካየንው በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንጋጌዎችን ይዟል’’ ያሉት የምክር ቤት አባሉ ‘’ለምሳሌ የፋይናንስ ድህንነት አገልግሎት አጠራጣሪ ግብይትን ለ7 ቀን አግዶ ማቆየት ይችላል ይላል ያውም ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ’’ ብለዋል፡፡
‘’አዋጁ በሽፋን ስር ምርመራ የሚያካሄድ መርማሪ ከግድያ ወንጀል ውጭ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም ይላል’’ ያሉት ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) ‘’ለምሳሌ መርማሪው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ተደራድሮ ከሆነ ከወንጀለኛው ጋር መቀበሉን ብናውቅ አይጠየቅም ማለት ነው? ማሰቃየት ቢፈጽም፣ የመብት ጥሰት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው? መሆን ያለበት ግን ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው አለም አቀፍ ድንጋጌዎች የተካተቱ ወንጀሎችን አለመፈጸሙ ነው’’ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሌላው አቶ ዘካሪያስ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ‘’አዋጁ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት እንደሚሉት ተቃዋሚን እና የሚዲያ ሰዎችን ለማፈን አይደለም’’ ብለዋል፡፡
አቶ ሳዲቅ አደም የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው ‘’አዋጁ ጠንከር ያለ መሆኑን ተናግረው ጠንከር ያለበት ምክንያትም ግልጽ ነው’’ ሲሉ ተናግረዋል፡፡ያለንበት ቀጠና አስቸጋሪ ነው፤ ሽብርተኝነት የሚበዛበት በመሆኑ የአዋጁ ከበድ ማለት ተገቢ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ከመብት አንፃር ሊታዩ የሚችሉ ነገሮች አሉ ያሉት አቶ ሳዲቅ ከህገ መንግስታችንም ስንነሳ ፍጹም የሚባል መብት የለም ብለዋል፡፡
‘’ከመብቶች ሁሉ የላቀ ዋና መብት የሚባለው በህይወት የመኖር መብት ነው ይህ መብትም ፍጹም አይደለም’’ ሲሉ የተናገሩት የምክር ቤት አባሉ ‘’ስለዚህ መብት የሚባለው ነገር ለህዝብ፣ ለማህበረሰብ እና ለሀገር ድህንነት ሲባል በየትኛውም ሀገር መብቶችን ፍጹማዊ አድርጎ የሚያስቀምጥ የለም’’ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
‘’ስጋት አድርጎ የሚወስድ ወገን ሊኖር ይችላል ግን ለምን ይሰጋል?’’ ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ ‘’ይህ አዋጅ ሲወጣ ለመጠርጠርም መሟላት ያለበት ነገር አለ ማንኛውም ወገን እነዚህ በአዋጁ የተቀመጡ ነገሮችን ካሟላ አይነካም ዋናው መስፈርቱን ማሟላት ነው’’ ብለዋል፡፡
‘’አዋጁ የወጣው በንድፍ ሃሳብ የምንፈራቸውን ለመከላከል ሳይሆን በተግባር እያየን እየኖርንበት ያለውን ነው’’ የሚሉት አቶ ሳደቅ ‘’ሽብርተኝነት በሀገራችን በስፋት አለ ኤ ቤ ሲ ብለን ልንጠራቸው የምንችላቸው ግለሰቦች እና ወገኖች አሉ ስለዚህ ይህን ለመከላከል ለምን እንሰጋለን’’ ብለዋል፡፡
የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሮ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ የሚደረገው ምርመራ ልዩ መሆኑን ተናግረው አዋጁ አንድን ቡድን ለማጥቃት ታስቦ የወጣ አይደለም ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው በማሻሽያ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሶስት ተቃዉሞ በአንድ ድምጽ ተአቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡

16/06/2025

Iranian state TV attacked while on air in latest wave of Israeli strikes on Tehran

12/06/2025

Caligula

መንግስት የነዳጅ ሽያጭ ላይ 15 በመቶ የተጨማሪ እሴት ታክስ ማስከፈል ሊጀምር ነው፡፡ላለፉት ወራት ቀስ በቀስ የነዳጅ ድጎማን እያነሳ ያለው መንግስት ሙሉ በሙሉ ድጎማውን ከማቆም ባሻገር ተጨ...
11/06/2025

መንግስት የነዳጅ ሽያጭ ላይ 15 በመቶ የተጨማሪ እሴት ታክስ ማስከፈል ሊጀምር ነው፡፡
ላለፉት ወራት ቀስ በቀስ የነዳጅ ድጎማን እያነሳ ያለው መንግስት ሙሉ በሙሉ ድጎማውን ከማቆም ባሻገር ተጨማሪ እሴት ታክስ ሊያስከፍልበት ማቀዱ ተሰምቷል፡፡
የፌዴራል መንግስት የ2018 ረቂቅ በጀት እንደሚያሳየው ከነዳጅና የነዳጅ ውጤቶች 15 በመቶ ቫት በማስከፈል ከ3 ቢሊየን ብር በላይ ለመሰብሰብ ማቀዱን ያሳያል፡፡
የፌዴራል መንግስት የ2018 የገቢ በጀት በሚል ለፓርላማው የቀረበው ረቂቅ በጀት ከስኳርም 1 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር እና ከጨው 337 ሚሊየን ብር ተጨማሪ እሴት ታክስ ለመሰብሰብ መታቀዱን ያሳያል፡፡
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው።

31/05/2025

የኢትዮጵያ የባህር በር መዳረሻ ማግኘት እየተባለ ካለው በላይ ስትራቴጂያዊ ነው - እና ይሄ ነገር እንዳይሆን ማን ነው በጣም የሚፈራው?
ኢትዮጵያ የባህር ወደብ የማግኘትን አስፈላጊነት በሚገባ ለመረዳት በመጀመሪያ ይህ እርምጃ በቀጠናው ላይ የሚያመጣውን ቀጥተኛ ውጤት ተረድተን ከፍተኛ ኪሳራ ውስጥ የሚገኙትን ሀገራት እና ተዋናዮችን መለየት አለብን። ይህ ሲሆን ብቻ ነው አንዳንድ የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች ሰላምን በማስፈን ሽፋን ይህን አገራዊ ጥቅም በረቀቀ መንገድ የሚቃወሙትን ትክክለኛ ምክንያት ማጋለጥ እና መረዳት የምንችለው።
1. ኢትዮጵያ ቀጥታ የባህር መዳረሻ ለምን ፈለገች።
ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት እና በአፍሪካ ፈጣን የህዝብ ቁጥር እያስመዘገቡ ካሉት አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ወደብ የሌላት ሀገር ነች። በአሁኑ ወቅት ከ95 በመቶ በላይ የሚሆነው የባህር ንግድ በጅቡቲ በኩል ያልፋል። ይህ ጥገኝነት ተጋላጭነትን ይፈጥራል፣ ኢኮኖሚያዊ ተወዳዳሪነትን ይገድባል፣ እና ከመጠን በላይ የትራንስፖርት ወጪዎችን ያስገድዳል። እናም ሌሎች ብዙ ጠቀሜታዎች አሉት ወናም ጥቂቱን አብረን እናያለን...
ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ኢትዮጵያ የቀይ ባህር መዳረሻን ለማረጋገጥ ያላትን ፍላጎት እንደ ቅኝ ግዛት ሳይሆን እንደ ህልውና ኢኮኖሚያዊ አስፈላጊነት በግልፅ ተናግረዋል። እሱ ትክክል ነው። ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ በውጭ ወደቦች ላይ ስትታመን የረዥም ጊዜ መረጋጋት እና ብልጽግና ማስመዝገብ በጭራሽ አትችልም።
- ኢትዮጵያ የወደብ መዳረሻ ካገኘች ከሚጎዱ አገሮች
1) ኬኒያ - አንደኛዋ እና ዋነኛዋ ነች ግን የኛ ፖለቲከኞች የ ኬንያን ስም ስያነሱ አይሰማም።
የኬንያ የሞምባሳ ወደብ በአሁኑ ጊዜ በርካታ ወደብ የሌላቸው አገሮችን ያገለግላል፡-
-ኡጋንዳ (45+ ሚሊዮን ሰዎች+ )
-ደቡብ ሱዳን (11 ሚሊዮን+ )
-ዲሞክራቲክ ኮንጎ (30 ሚሊዮን+)
ኢትዮጵያ በኤርትራ ወይም በሶማሌላንድ በኩል የባህር መዳረሻ ካገኘች ኡጋንዳ እና ደቡብ ሱዳን አጭር፣ ርካሽ እና ቀልጣፋ የንግድ መስመሮችን ያገኛሉ። ዩጋንዳ ከሩቅ ሞምባሳ ሸቀጣ ሸቀጦችን ከማጓጓዝ ይልቅ በኢትዮጵያ በኩል ማስገባት ትችላለች። ደቡብ ሱዳን ቀድሞውኑ በኡጋንዳ በኩል ታስገባለች; ኡጋንዳ መስመር ከቀየረች ደቡብ ሱዳንም እንዲሁ ይሆናል።
ይህ ማለት ኬንያ አጠቃላይ የሰሜን ኮሪዶርን ልታጣ፣ ከ3+ ሀገራት እና ከ90 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ጋር ያለውን የንግድ ግንኙነት እንድታቋርጥ ስጋት አለባት - ይህ በኢኮኖሚዋ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
2) ጅቡቲ – በኢኮኖሚው በኢትዮጵያ ላይ ጥገኛ ነች።
ጅቡቲ ከኢትዮጵያ የወደብ አጠቃቀም በዓመት ከ1.6-2 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ታገኛለች። ይህ ከጅቡቲ አጠቃላይ ምርት ውስጥ ጉልህ ድርሻ ይይዛል። ኢትዮጵያ በጅቡቲ ላይ ያላትን ጥገኝነት ብትቀንስወይም ብትቆም ጉዳቱ ፈጣን እና ከባድ ይሆናል። የጅቡቲ ስልታዊ ጠቀሜታ ይቀንሳል፣ እናም ኢኮኖሚያቸው ይወድቃል ለዛም ትልቅ ስጋት አለባቸው።
እናም በተለያዩ ግዜኣቶች በኢትዮጵያ ያለውን የፖለቲካ አለመረጋጋት ጅቡቲ የአማፂያን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍ ሆነ እንደምታመቻቸት ማንም ጭንቅላት ያለው ሰው ልረዳው ይችላል ። ጅቡቲ የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችን ወይም የወደብ ድርድርን ለሚቃወሙ ቡድኖች የገንዘብ ድጋፍ የማድረግ ዓላማም ሆነ ፍላጎት አላት።
3) ግብፅ - የተጽእኖ ማጣት ስጋት የቆየ ጠላትነት
የግብፅ ቀዳሚ ስጋት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ቢሆንም፣ ፕሮጀክቱ ወደ መጠናቀቅ ሲቃረብ ፍርሃቷ እየቀነሰ ነው ወይም ምንም ነገር ማድረግ እንደማይችሉ የተረዱ ይመስለኛል። ሆኖም ግብፅ የግድቡን ፕሮጀክት ለማዘግየት ወይም ለማደናቀፍ የውስጥ የኢትዮጵያን ክፍፍል ስትጠቀም ቆይታለች። GERD አሁን ወደ ስራ ሊገባ በተቃረበበት ወቅት፣ ግብፅ ቀስ በቀስ ተሳትፎዋን ልትቀንስ ትችላለች - አሁንም ብሆን ግን በኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ የጥላቻ ተዋናይ ሆና ቆይታለች እናም የኢትዮጵያ በጥባጭ ፖለቲከኞችን ለብዙ አመታት ስት ቀልብ ኖራለች።
4) ታንዛኒያ- ሩዋንዳን እና ቡሩንዲን አጣለው ብላ ትሰጋለች እናም ደግሞ ኢትዮጵያ የባህር በር ካገኘኘች በርግጥም ታጣቸዋለች ስለዝህም ኢትዮፕያን የባህር በር ፍላጎት ከሚቃወሙት ሃገራት እንዷ ነች።
5) ኤርትራ( ሻቢያ) - እውነቱን ለመናገር የ ኤርትራ መንግስት ቀጥተኛ ጠላት አይደለም, ግን ልክ እንደኞቹ ፖለቲከኞች ቅጥረኛ ጠላቻታችን ነው ።
ኢትዮጵያ የወደብ መዳረሻ ካገኘች ኤርትራ ከሚጎዱት ሃገራቶች ውስጥ አይደለችም። ይሉቁንስ ከኢትዮጵያ ጋር ሰላማዊ የኢኮኖሚ አጋርነት ለሁለቱም አገሮች ይጠቅማል አብሶ ደግሞ ለ ኤርትራ በጣም ወሳኝ ነው። በባህል፣ በታሪክ እና በመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ኤርትራና ኢትዮጵያ የተሳሰሩ ናቸው። የጋራ ሃይማኖት፣ ጋብቻ እና የኢኮኖሚ ማሟያዎች ትብብራቸውን ምክንያታዊ አስፈላጊ ያደርጉታል።
እነኝህ ከላይ የተጠቀሱት አገራት በ አንድም ሆነ በሌላ በተለያዩ ግዜአቶች ኢትዮጵያ ጭንቅላቷን ከፍ ለማረግ በሞከረች ቁጥር ጭንቅላቷን ስደቁሱ የኖሩ እናም ኢትዮጵያዊያን አማፂያኖችን እየቀጠሩ ደም ስያፋስሱ ለአመታት የኖሩ አሁንም እያደረጉ ያሉ ናቸው።
6) የኢትዮጵያ አፈቀላጤ ፖለትከኞች.

30/05/2025
Testimonies from the late Al-Fatih Irwa, former National Security Advisor of Sudan who played an outsized role in reshap...
18/04/2025

Testimonies from the late Al-Fatih Irwa, former National Security Advisor of Sudan who played an outsized role in reshaping the Horn of Africa in the 1980s, note that Isaias Afwerki regretted inheriting a barren Eritrea, in contrast to the TPLF, who took over the lush parts of Southern Ethipia.

Recent testimonials of a Sudanese Intelligence Officer on the Proxy war between Sudan and Ethiopia from 1970s to early 1990s

ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣንን ምን ነካው?!ምን ተቸገረ?!ምንድነው ማሥፈጸም የፈለገው?!አንድ አሽከርካሪ ሣምንት ባልሞላ ግዜ ውሥጥ አራት ግዜ የትራፊክ ቅጣት?! የተለያዩ ሠዎች ላይ የተከሠ...
02/04/2025

ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣንን ምን ነካው?!ምን ተቸገረ?!ምንድነው ማሥፈጸም የፈለገው?!
አንድ አሽከርካሪ ሣምንት ባልሞላ ግዜ ውሥጥ አራት ግዜ የትራፊክ ቅጣት?! የተለያዩ ሠዎች ላይ የተከሠተ ነው።
መንገዱን ሙሉ መኪና ደርድሮ መቅጣት የሢሥተም ችግርን ቁልጭ አድርጎ የሚያሣይ አይመሥልም? መንገዱ በሚቀጡ ተጨናነቁ።
አንድ አንድ የ አአ ትራፊክ ፖሊሥ ያሥቆምሃል! እዚህ ጋር ሊጫን ሢፈልግ፣ቼክ ሊያደርግህ እና ሊቀጣህ ሢፈልግ በተመሣሣይ የማሥቆም ሥልት 'ምንአጥፍቼ ይሆን!' የሚል ጥርጣሬ ውሥጥ ይከትሃል።
"መንጃፍቃድ!" ይልሃል አያይህም...ሌላ የሚያሥቆመውን፣ የሚቀጣውን እያማተረ፣ እያሥቆመ ።ከዛም የመኪናህ ፊት ለፊት ቆሞ ካርኒ መጻፍ ይጀምራል።መቀጣትህን የምታውቀው ሢጽፍ ነው።
"ፈርም!" ይልሃል በተሠላቸ እና በደከመ ድምጽ ። ደብሮት .. ድብርት ውሥጥ ይጥልሃል።
"ምን አጠፋሁ?!" ብለህ ትጠይቀዋለህ ካልገባህ።
"ሥትታጠፍ ፍሬቻ አላበራህም ምናምን!" ወዘተ፣...ሊመለከትህ ፣ጥፋትህን ሊያሥረዳህ ሁሉ ፍቃደኛ አይደለም።ኧረ አንዳንዱ ሊያይህ እንኳ ይደብረዋል። ሊያመንጭቅህ ሁላ ይቃጣዋል።ትፈርምለታለህ።
"እንዴት መታጠፊያ ላይ ቆመህ ፍሬቻ አለማሣየቴን አየህ?ደግሞሥ ዘመናዊ መኪኖች ፍሬቻ በራሣቸው ያጠፋሉሣ?"ሥትለው።
"ፈርም!" ይልሃል ደግሞ ።
ከተናደደብህ የቅጣቱን ገንዘብ መጠን ካርኒው ላይ አይጽፈውም(እዚህ እንደምታዩት) ፤ የት ሄደህ ፍቃድህን እንደምትቀበል አይነግርህም።በየባንኩ እና በየፖሊሥ ጣቢያው ሥትንከራተት አንድ ቀንህን ሙሉ ከሥራ ውጪ አፈር ይበላል።
በሣምንት አራት ግዜ ሢቀጣህ ደግሞ ኢማጅን። በአሥፓልቱ ላይ ለመጓዝ ትሣቀቃለህ። የድሮ ሃብታም ቤት ጫማ አሥወልቀው ወለላቸውን እንደምትረግጠው አይነት 😍።ሥራህን ትተህ በእግር መጓዝ እጣ ፈንታህ ሊሆን ሁሉ ይችላል።
ጥፋትህ ሆነም አልሆነም ለቅሬታ ቢሮአቸውን አፈላልገህ ሥትሄድ ሃላፊው ሥብሠባ ናቸው ወይንም ቢሮ የሉም።ከተቀጣህ- ጥፋተኛም ሆንክ አልሆንክ በቃ! ማንም ዞር ብሎ አያይህም።
በመጀመሪያ የሚነግረኝ ቢኖር.....
👉ቅጣት ዲጂታላይዝ ለማድረግ ምን ቸገራቸው?!በቴሌ ብር ይከፈል አልነበር እንዴ?!አሁን ወደ ማኑዋል ለምን ተመለሡ?
👉በቀላል በምክርና በማሥተማር ሊታለፉ የሚገቡን ጉዳዮች ለምን ውድ ቅጣት ተጣለባቸው?ለምንሥ ተገልጋይን ማጉላላት ውሥጥ መክተት ተፈለገ?
👉ቅጣት ያለጥፋት ሆን ተብሎ አሽከርካሪ ላይ ቢጫን በምን አግባብ ነው ሣያሠለች በፍጥነትና በቅልጥፍና ማሥረዳትና መከራከር የሚቻለው ??
👉በቅጣት መጉላላትን መፍጠር እየለፋ ግብር የሚከፍለውን ነጋዴ ግዜውን በአግባቡ ተጠቅሞ ምርታማ እንደማያደርገው አይታወቅም ወይ?
ሢቀጥል...
አዲሡ የትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ 557 ን ሢጸድቅና ሢተተገብሩት... ከማህበራዊ አኗኗር አኳሃን፣ ከኢኮኖሚ ኪሣራ አንጻር፣ቅድመ ቴክኖሎጂን ከመጠቀም አንጻር፣ዘመናዊ ሥርአትን ከመተግበር አንጻር፣ከአሥፈጻሚ ዲሢፕሊን አንጻር ሣይሆን ገቢን ከመሠብሠብ ፍላጎት ብቻ የተቃኘ አይመሥላችሁም?
ሢሠልሥ....
የትራፊክ ፖሊሥ እኮ ግለሠባዊ ተንቀሣቃሽ ፍርድ ቤት ማለት ነው ። ህግን ይተገብራል እዛው ይበይናል፣እዛው ይቀጣል። ከአድሎ የጸዳ ፣ በሥነምግባር የታነጸ፣ራሡን ለአገልጋይነት ያበቃ ፣ የሠለጠነ ተሞክሮ ያለው መሆን አለበት ብዬ አምናለሁ።
አንዱን ቻሌንጅ ሥታደርገው በቡድንተኝነት ተሣሥሮ በቅጣት ዜጋን ማበሣጨት ተገቢ አይደለም የሚል ግምትን ሊያሦሥድ ይችላል።
የትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን መመሪያዎችን አውጥቶ ሢተገብር ከመልካም ተሞክሮ የተቀዳ አሠሪ ፣ ግልጸኝነትና ዘመናዊ በክትትል፣ቁጥጥር እና ክፍያ ሥርአት ውሥጥ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም አቅም ሊኖረው ይገባል ፤ ራዳር፣ ካሜራ፣የክፍያ ሥርአት ዲጂታላይዜሽን ወዘተ የመሣሠሉትን ቢጠቀም ተቋሙ ይዘምናል፣ተገልጋዩ አግባብ ካልሆነ ከእንግልት ይድናል...ሃገር ምርታማ ትሆናለች። ብቻ ኤክሥፖዠር ያሥፈልገዋል።
ዘመናዊ መንገድ ተሠራ .. ማሥተዳደሩንም ዘመናዊ ለማድረግ ምን ተሣነ!?
ቆይ የሃገሪቱን ዲጂታላይዜሽን ጉዞ።ካሽለሥ ሦሣይቲን የመፍጠር ጉዞ አይጻረርም? ከኦንላይን ሥርአት ወደ ማኑዋል ካርኒ መሸጋገር አግባብ ነው?

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when RiseUp Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to RiseUp Ethiopia:

Share