Arat ayin Media አራት ዓይን

Arat ayin Media አራት ዓይን ወቅታዊና ትኩስ ሁሉን አቀፍ ዜና ይቀርብበታል

እስራኤል ሊባኖስን ላይ ጥቃት ፈፀመትትራንፕ ፑቲን ይንቀናል ህውሃት ጦርነት እያሰበ ይሆን?👇👇👇👇👇
05/07/2025

እስራኤል ሊባኖስን ላይ ጥቃት ፈፀመት
ትራንፕ ፑቲን ይንቀናል
ህውሃት ጦርነት እያሰበ ይሆን?
👇👇👇👇👇

05/07/2025

በክብር ሸኙት

👉 አሳ ልንበላ ነው‼ከሕዳሴ ግድብ 5 ሺህ 895 ቶን የዓሣ ምርት ተገኘ   | በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚገኘውን የዓሣ ምርት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ...
05/07/2025

👉 አሳ ልንበላ ነው‼

ከሕዳሴ ግድብ 5 ሺህ 895 ቶን የዓሣ ምርት ተገኘ

| በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚገኘውን የዓሣ ምርት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ።

በቢሮው የእንስሳትና ዓሣ ሃብት ልማት ዳይሬክተር አቶ ሃይሉ ይርጋ እንዳሉት
የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በዓመት 15 ሺህ ቶን ዓሳ ማምረት የሚያስችል አቅም በክልሉ እንዳለ በጥናት መለየቱን አመልክተዋል፡፡

የፊታችን መስከረም ወር ላይ የሚመረቀው የሕዳሴ ግድብ ለዓሣ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

በግድቡ ሰው ሠራሽ ሐይቅ ለሚከናወነው የዓሣ ልማት ሥራ አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ 849 ወጣቶች በ35 የዓሣ መንደሮች መደራጀታቸውን ጠቅሰው÷ ከእነዚህ መካከልም 547ቱ ወደ ሥራ ገብተው ተጠቃሚ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

ለማህበራቱ በዓሣ ማስገሪያ መረብና በዓሣ ምግብ አሰራር እንዲሁም ዓሣ የማስገር ክህሎት እንዲያዳብሩ የሚያስችል ስልጠና መሰጠቱን ጠቁመዋል።

ከተለያዩ አካላት በተገኘ ድጋፍም ለዓሣ ማስገሪያ የሚውሉ 54 ጀልባዎችና 1 ሺህ 600 መረቦችን ማቅረብ መቻሉን አብራርተዋል፡፡

በ2017 በጀት ዓመትም ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሰው ሰራሽ ሐይቅና ሌሎች 5 ሺህ 895 በላይ ቶን በላይ የዓሣ ምርት መመረቱን ጠቅሰዋል፡፡

ከታላቁ የህዳሴ ግድብ በዘንድሮ ዓመት ብቻ

1. 5ሺህ 895 ቶን የዓሣ ምርት ተገኝቷል።
2. 849 ወጣቶች በ35 የዓሣ መንደሮች ተደራጅቷል።
3. 547ቱ ወደ ሥራ ገብተው ተጠቃሚ ሆነዋል።
4. ለዓሣ የማስገሪያ የሚሆን 54 ጀልባዎች ቀርቧል።
5. 1ሺህ 600 መረቦች ስራ ላይ ውሏል።

05/07/2025

ሁሌ ይገርመኛል ይሄ ሰውዬ ሞቼ ተነሳሁ ነው የሚለውኮ

         🚌 በጋሞ ዞን ብርብር ከተማ አስተዳደር በተለምዶ "ሁለተኛ ዳጌት"  ወይም " 455 "ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ከአርባምንጭ ወደ ወላይታ ሶዶ በመጓዝ ላይ የሚገኝ የFSR ባስ አን...
05/07/2025



🚌 በጋሞ ዞን ብርብር ከተማ አስተዳደር በተለምዶ "ሁለተኛ ዳጌት" ወይም " 455 "ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ከአርባምንጭ ወደ ወላይታ ሶዶ በመጓዝ ላይ የሚገኝ የFSR ባስ አንድ ወይፈን ለማዳን በወሰደዉ እርምጃ ከመስመሩ ጥሶ በመዉጣት ተፈታኝ ተማሪዎችን ጭኖ ከጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲት ሲጓዝ በነበረ FSR ባስ ጋር ተጋጭቷል።

🚌 በአደጋዉ ከ10 በላይ ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል ጉዳት እንዲሁም በንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በግጭቱ ምንም አይነት የሞት አደጋ አልተመዘገበም
ጉዳት የደረሰባቸዉ ግለሰቦች በብርብር አስተዳደር ፖሊስ አባላት እና በሕዝቡ ትብብር በብርብር መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸዉ ይገኛል።

በጥንቃቄ በማሽከርከር በሰዉ እና በንብረት ላይ የሚደርስን አደጋ እንከላከል።🚌

👉የብርብር ከተማ ፖሊስ
Sheger Report

ቡርኪናፋሶ የምዕራባውያን ተቋማት አገደች !የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ሀገሪቱን የማበጥበጥ ሰላም የመንሳት ማህበራዊ እረፍት የማሳጣት አላማ አላቸው ያሏቸውን አራት በምዕራባውያ...
05/07/2025

ቡርኪናፋሶ የምዕራባውያን ተቋማት አገደች !

የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ሀገሪቱን የማበጥበጥ ሰላም የመንሳት ማህበራዊ እረፍት የማሳጣት አላማ አላቸው ያሏቸውን አራት በምዕራባውያን እና አሜሪካ የሚመሩ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ፈቃዳቸውን መቀማቱን እና ሌሎች ሁለት ማህበራትን ማገዱ ተነገረ ።

እ.ኤ.አ. በሴፕቴምበር 2022 በተካሄደው መፈንቅለ መንግስት ስልጣኑን የተቆጣጠረው የቡርኪና ጦር ሃይል ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የብሄራዊ ሉዓላዊነትን ማስመለስን ከቅድሚያ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ በማድረግ በ"ግጭት " ተግባር የተከሰሱ ዲፕሎማቶች ከሀገር እንዲባረሩ ተደርገዋል፣በርካታ የውጭ ሚዲያዎችም ለመዝጋት ተገደዋል።

የወታደራዊው መንግስት ቀጣይነት ያለው የጸጥታ እርምጃዎች አካል የሆነዉና በሰኔ ወር አጋማሽ ላይ የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ባወጣው ድንጋጌዎች መሰረት ሀገሪቱን ለብጥብጥ እና ግጭት ለመዳረግ እያሴሩ ነዉ ያሏቸውን አራት የውጭ መንግስታዊ ያልሆኑ ማኅበራት ለሶስት ወራት ታግደዋል፣ ሁለቱን በመረጃ ጥሰት ክስ በመመስረት ፍርድ ቤት አስቁመዋቸዋል ይህ እርምጃም ቀጣይነት እንዳለዉ አረጋግጫለሁ ሲል የመንግስት ሚኒስትርን ዋቢ በማድረግ የዘገበው አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ነዉ ።

እስራኤል በሊባኖስ ላይ መአት አወረደች! / ቤይሩት /በእስራኤል እና በሊባኖስ ቡድን ሂዝቦላ መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መጣሱ ተነገረ ። እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ በሚገኙ ከ...
05/07/2025

እስራኤል በሊባኖስ ላይ መአት አወረደች! / ቤይሩት /

በእስራኤል እና በሊባኖስ ቡድን ሂዝቦላ መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መጣሱ ተነገረ ።

እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ በሚገኙ ከተሞች ላይ በሶስት ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ባደረሰችዉ ጥቃት አንድ ለሞት እና በርካቶች ቆስለዋል ። ተብሏል።

የሊባኖስ የህዝብ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ቅዳሜ ዕለት በይፋዊው ብሄራዊ የዜና አገልግሎት (ኤንኤንኤ) ባወጣው መግለጫ “የእስራኤል ሶስት ሰው አልባ አውሮፕላኖች በቢንት ጀቢል ከተማ በሚገኘው ሳፍ አል-ሃዋ አካባቢ በተሽከርካሪ ላይ ባደረሱት ጥቃት” “አንድ ሰው ገድሎ ሁለት ሰዎችን አቁስሏል” የጉዳቱ መጠን ሊጨምር ይችላል ።ብሏል።

በሌላም በኩል የእስራኤል ጦር በቤይሩት ደቡባዊ መግቢያ ላይ በተሽከርካሪ ላይ ባደረገችው ድብደባ፣ የአገሪቱ ብቸኛ የንግድ አውሮፕላን ማረፊያ አቅራቢያ አንድ ሰው ገደለ እና ሌሎች ሦስት ሰዎችን አቁስሏል። ሲል አልጀዚራ ዘግቧል ።

ሚኒስቴሩ በተጨማሪም ከዛሬዉ ጥቃት በፊት በሊባኖስ ከሶሪያ እና ከእስራኤል በተያዘው የጎላን ሃይትስ ድንበሮች ላይ በሚያልፉ ሁለት ገደላማ እና ድንጋያማ ተራራማ አካባቢዎች በምትገኘዉ በሼባ የእስራኤል ሰው አልባ አውሮፕላኖች ባደረሱት ጥቃት አንድ ሰው መቁሰላቸውን ኤንኤንኤን ገልጿል።

በተመሳሳይ በቢንት ጄቤይል አውራጃ በምትገኘው ቻክራ ከተማ ላይ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት አድርጋለች።በዚህም ሁለት ሰዎች ቆስለዋል ሲል የሊባኖስ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ገልጿል ።

ምንም እንኳን እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 27 በአሜሪካ አደራዳሪነት የተኩስ አቁም ስምምነት ከሂዝቦላህ ጋር ከአንድ አመት በላይ የቆየውን ጦርነት ለማስቆም ቢሞክርም እስራኤል በሊባኖስ ላይ በየቀኑ የቦምብ ድብደባዋን ቀጥላለች።

እስራኤል የአየር ጥቃቷ በሂዝቦላህ እና በሌሎች ቡድኖች ባለስልጣናት እና ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ነው
ብትልም የእስራኤል ጥቃት የቤይሩትን ደቡባዊ ዳርቻዎች ያሉ ከተሞችን ብዙ ጊዜ በመምታቱ የመኖሪያ ሕንፃዎችን በማውደሙ አካባቢውን ለቀው በሚሰደዱ ነዋሪዎች መካከል ሽብር እና ትርምስ ፈጥሯል።

እንደሚታወቀው በተኩስ አቁም ስምምነቱ ሂዝቦላህ ከእስራኤል ድንበር 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው ሊታኒ ወንዝ በስተሰሜን ያለውን ተዋጊዎቹን በማስወጣት ለተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ሃይሎች ያስረከበ ቢሆንም እስራኤል ወታደሮቿን ከአገሪቷ ሙሉ በሙሉ እንድታስወጣ ቢጠበቅባትም በደቡባዊ ሊባኖስ ስትራቴጅ ነው በምትላቸው አምስት ቦታዎች አስቀምጣለች ይህን ስፍራ አሜሪካ እንድታስለቅቅላቸዉ ሲል የሊባኖሱ ፕሬዝዳንት ጆሴፍ አውን ጥያቄያቸውን እያቀረቡ ይገኛል ።

ስናዘጋጅ አልጀዚራን AP የዜና ወኪልን ኤንኤንኤን ለምንጭነት ተጠቅመናል ።

፦ ታዴ የማመይ ልጅ

ፑቲን ለእኛ ንቀት አለዉ ! ትራምፕ "ፑቲን ዩናይትድ ስቴትስ  ጦርነቱ እንዲቆም ላቀረበችዉ ጥሪ የመለሰዉ ምላሽ ለአሜሪካ  ያለውን ንቀት በግልፅ ያሳያል"/ ትራምፕ/የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ...
05/07/2025

ፑቲን ለእኛ ንቀት አለዉ ! ትራምፕ

"ፑቲን ዩናይትድ ስቴትስ ጦርነቱ እንዲቆም ላቀረበችዉ ጥሪ የመለሰዉ ምላሽ ለአሜሪካ ያለውን ንቀት በግልፅ ያሳያል"/ ትራምፕ/

የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ባደረጉት የስልክ ጥሪ በተሰጣቸዉ ምላሽ መከፋታቸዉን ገለፁ ። ሩሲያ በዩክሬን ላይ የምታደርገውን ጦርነት ለማስቆም አትፈልግም ሲሉም ተናግረዋል ።

ሐሙስ ዕለት ከፑቲን ጋር ከተነጋገረ በኋላ ዋሽንግተን ሲመለሱ ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት "ዛሬ ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር ባደረግኩት ውይይት በጣም ተበሳጨሁ, ምክንያቱም እሱ እዚያ ያለ አይመስለኝም, እና በጣም አዝኛለሁ" ብለዋል ።

ለዩክሬን ስለሚደረገው የጦር መሳርያ ድጋፍ በተመለከተም አርብ እለት ከዋሽንግተን ተነስተው ወደ አዮዋ ሲሄዱ ትራምፕ “የጦር መሳሪያዎችን ፍሰት ሙሉ በሙሉ አላቆምንም፣ ነገር ግን ጆ ባይደንን ብዙ መሳሪያዎችን በመላክ የአሜሪካን መከላከያዎች ማዳከም አደጋ ላይ ስለጣለን እንደድሮዉ አንልክም ሲሉ የሚያደርጉትን ድጋፍ መቀነሳቸዉን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል ።

የሁለቱን መሪዎች የስልክ ልዉዉጥ ተከትሎ
"አሁንም እንደገና ሩሲያ ጦርነቱን እና ሽብርን የማስቆም አላማ እንደሌላት እያሳየች ነው" ሲል ዘለንስኪ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተናግሯል ።

አሜሪካ የሁለቱን ሀገራት ጦርነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እያደረገች ቢሆንም ፑቲን በበኩሉ የግጭቱ "ሥር መሠረቱን" ከተፈታ ብቻ እንደሚያቆም ማስታወቁን ቀጥሏል ። ሩሲያ ስለጉዳዩ ባወጣችው አጭር መግለጫ ዩክሬን ለኔቶ መስፋፋት ይጠቅም ዘንድ ከኔቶ ጥምረት ጋር መቀላቀልን የጀመረችዉን ጉዞ እና የምዕራባውያን ድጋፍ ካላቆመች መቼም እንዴትም ወደ ድርድር እንደማያመሩ አሳዉቀዋል ። ሲል AP የዜና ወኪል ዘግቧል ።

፦ ታዴ የማመይ ልጅ

በመዲናዋ ተገንብተዉ የተጠናቀቁ ከ15,960 በላይ ፕሮጀክቶች ተመርቀዉ ከነገዉ እለት ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለ...
05/07/2025

በመዲናዋ ተገንብተዉ የተጠናቀቁ ከ15,960 በላይ ፕሮጀክቶች ተመርቀዉ ከነገዉ እለት ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ገለፁ፡፡

ከተማ አስተዳደሩ በ2017 በጀት ዓመት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው የጎላ ዘርፈ-ብዙ የልማት ስራዎችን በማቀድና ተግባራዊ በማድረግ ከ15 ,960 በላይ የተለያዩ ትልልቅ ፕሮጄክቶች ከነገ እሁድ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ ተመርቀዉ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ እናትዓለም መለሰ ተናግረዋል፡፡

ለአገልግሎት ክፍት ከሚሆኑት እና ከሚመረቁትፕሮጀክቶች መካከል የመንገድ፣ የውሃ፣ የቤቶች ልማት ፣ የመስሪያ ቦታዎች፣ የወጣቶች ስፖርት ማዘወተሪያ ሜዳዎች፣ በአረንጓረዴ ልማት የተሰሩ እና ሌሎች ለህብረተሰቡ ፋዳቸው ጉልህ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ያካተቱ ናቸው ተብሏል፡፡

ፕሮጀክቶቹ በ91 ቢሊዮን ብር ወጪ በመንግስት እና በ4 ቢሊየን ብር ወጪ በህብረተሰቡ ተሳትፎ የተገነቡ ሲሆን ፤ የተጠቀሰው በጀት ብቻ ሳይሆን ሌሎች በሂደት ላይ ያሉ ፕሮጀክቶችም በፈጣን ክትትል ሥራው ውስጥ እንዳሉ ወ/ሮ እናት ዓለም መለሰ በሰጡት ማብራሪያ ገልፀዋል፡፡

በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ በበጀት ዓመቱ አጠቃላይ ከተያዘለት በጀት ውስጥ 71 በመቶ የሚሆነዉን ለካፒታል ፕሮጀክት ግንባታ እና ለድህነት ቅነሳ ፕሮግራም እንዲውል በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን፣ ገልጸው፣ ለትራንስፖርት ለዳቦ ፍብሪካ ድጎማ፣ ለባሶች ግዥ፣ ለተማሪዎች ምገባ፣ ለጤና መድህን ፕሮግራሞች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም የቢሮው ኃላፊ አስረድተዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ለወጣቶች ስራ እድል በሰጠዉ ትኩረት ከ366ሺ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶች የስራ ዕድል እንደተፈጠረላቸውም ተናግረዋል፡፡

የዲያጎ ዦታ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ******************ባለፈው ሀሙስ በትራፊክ አደጋ ህይወቱን ያጣው የሊቨርፑል አጥቂ የዲያጎ ዦታ እና የወንድሙ አንድሬ ሲልቫ የቀብር ስነ ስርዓት በፖ...
05/07/2025

የዲያጎ ዦታ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ
******************

ባለፈው ሀሙስ በትራፊክ አደጋ ህይወቱን ያጣው የሊቨርፑል አጥቂ የዲያጎ ዦታ እና የወንድሙ አንድሬ ሲልቫ የቀብር ስነ ስርዓት በፖርቱጋል ጎንዶማር ተፈፀሟል፡፡

በቀብር ስነሰርዓቱ ቤተሰቦቹ የቡድን አጋሮቹ የእግር
ኳስ ከዋክብቶችን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ተገኝተዋል፡፡

የሊቨርፑል ደጋፊዎች አንፊልድ በመገኘት ለጀግናቸው የአበባ ጉንጉን በማስቀመጥ ሀዘናቸውን ገልጸዋል::

ከ11 ቀናት በፊት ከረጅም ጊዜ የፍቅር አጋሩ ጋር ትዳር የመሰረተው የ28 ዓመቱ ተጫዋች የ3 ልጆች አባት ነው፡፡

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል ቀሪ የሁለት አመት ውል ደመወዙን ለቤተሰቦቹ እንደሚሰጥም ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

በላሉ ኢታላ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዚህ አደጋ እንደተረፈ ታቃላቹ ?ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከ 11 ዓመት በፊት በ 2014 ከዚህ አሰቃቂ ዘግናኝ አደጋ ተርፏል ፣ እሰከአሁን ድረስም አለ ፤ ዕድሜን ከጤና ጋርም ...
05/07/2025

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዚህ አደጋ እንደተረፈ ታቃላቹ ?

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከ 11 ዓመት በፊት በ 2014 ከዚህ አሰቃቂ ዘግናኝ አደጋ ተርፏል ፣ እሰከአሁን ድረስም አለ ፤ ዕድሜን ከጤና ጋርም ይስጠው ወደፊትም 🙏

Address

Addis Ababa

Telephone

+251938668562

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arat ayin Media አራት ዓይን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Arat ayin Media አራት ዓይን:

Share