Arat ayin Media አራት ዓይን

Arat ayin Media አራት ዓይን Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Arat ayin Media አራት ዓይን, Media/News Company, Addis Ababa.

ወቅታዊና ትኩስ ሁሉን አቀፍ ዜና ይቀርብበታል
👉 ትኩረት የሚሹ ነጥቦች
🔴 ተደማጭ ጉዳዮች
🕘 ወቅታዊ
⚽ስፖርታዊ ጉዳይ
🌎አለም አቀፍ ዜና
🎭መዝናኛ
👉በተጨማሪም📻 በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ማክሰኞ ከ8:00 እስከ 9:00 እሁድ ከ3:00 እስከ 4:00 ይደመጣል።🚨
አራት አይን በሁሉም ቦታ

16/10/2025

ውለታ የማትረሳው ሰይፍሻ እንኳን ደስ አለህ !!!

የአፋር ክልል መንግሥት የቀይ ባህር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ከፌደራል መንግሥት ጋር በመተባበር እንደሚሰራ አስታወቀቀይ ባህር ከአፋር ክልል 60 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና በታሪክም የኢትዮ...
15/10/2025

የአፋር ክልል መንግሥት የቀይ ባህር ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ከፌደራል መንግሥት ጋር በመተባበር እንደሚሰራ አስታወቀ

ቀይ ባህር ከአፋር ክልል 60 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኝና በታሪክም የኢትዮጵያ አካል በመሆኑ የባህሩን ባለቤትነትን ለማረጋገጥ ከፌደራል መንግሥት ጋር በመተባበር እንደሚሰራ የክልሉ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለአሐዱ ገልጿል

የቢሮው ኃላፊ ሙሃመድ አሊ፤ "በታሪክ የኛ የነበረውን ቀይ ባህር ባለቤትነት በሰላማዊ መንገድ እና አስፈላጊውን መሰዋእትነት በመክፈል ኢትዮጵያ የባህር በር የሌላት ሀገር እንዳትሆን በትኩረት እንሰራለን" ሲሉ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ለዘመናት የቀይ ባህር ባለቤት እንደሆነች የተለያዩ መረጃዎች እንዳሉና ቀይ ባህር ከኢትዮጵያ እጅ የወጣው ከ27 ዓመት በፊት መሆኑን አንስተው፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ለማስመለስ በሚያደርገው ጥረት ሁሉ የአፋር ሕዝብና መንግሥት ከጎኑ መሆኑን ገልጸዋል።

የአፋር ሕዝብ ኢትዮጵያ የቀይ ባህር ኮሪደርን የምታገኝበት ኮሪዶር መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፤ የባህር በር ጥያቄው በአጭር እና በረጅም ጊዜ መሳካቱ አይቀርም ሲሉ ጠቁመዋል።

የባህር በር ጥያቄ ሀገራዊ አጀንዳ ከመሆን ባለፈ ዓለም አቀፋዊ አጀንዳ የተደረገበት ወቅት በመሆኑ፤ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለሀገር ጥቅም በመተባበር የኢትዮጵያ መንግሥት በወደብ ጉዳይ ላይ በሚያደርገው ጥረት ከጎኑ መቆም አለባቸው ሲሉም ተናግረዋል።

ሰላም ታስቀድማለች ድህነትን ትፋለማለች መውጫ መግቢያ በሯን ታበጃለች ይህ አይቀሬ ጉዳይ መሆኑን ተገንዘበው ወንድም እህቶቻችን በፈጠነ ጊዜ ለድርድር እራሳቸውን ዝግጁ ማድረግ አለባቸው

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በ80ኛው የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕርና በህንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ለሚገኙ ሁሉም ሀገራት እኩል ልማትና ደህንነትን ለማረጋገጥ "ሁሉን አቀፍ አካሄድ" እንደምትከተል በመግለጽ፤ ሕጋዊ የፖሊሲ ግቧን በዲፕሎማሲያዊና በሰላማዊ ተሳትፎ እንደምታስቀጥል ለዓለም መንግሥታት ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በ6ኛው የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በአባይ ግድብና በቀይ ባህር እንደመገኘቷ፤ እጣ ፋንታዋ እና መፃኢ እድሏ ከሁለቱ ውሀዎች ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ሀገሪቱ ካላት ጂኦግራፊያዊ፣ ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ዳራ አንፃር የጋራ ልማትን ለማጠናከር ሰላማዊ ዕድሎችን የሚፈጥር በጋራ ጥቅም እና አጋርነት መርህ ላይ የተመሰረተ የባህር ዳርቻን የማረጋገጥ ውይይት መጀመሯን የገለጹት ፕሬዝዳንት ታዬ፤ ይህም አጀንዳ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከጊዜ ወደ ጊዜ ትኩረት እየሳበ መምጣቱን መግለጻቸውም አይዘነጋም፡፡

#አሐዱ

ክርስትያኖ ቃሉን ጠብቋል ፥ ታላቁ ሰው ታላቅ ነው !❤🙏: ከአንድ ወር በፊት ዶሚኒክ ስዞቦዝላይ ክርስቲያኖ ሮናልዶን ማሊያውን ጠየቀው። ነገር ግን ሮናልዶ ቀድሞውኑ ለሌላ ተጫዋች ሰጥቶት ነበ...
15/10/2025

ክርስትያኖ ቃሉን ጠብቋል ፥ ታላቁ ሰው ታላቅ ነው !❤🙏

: ከአንድ ወር በፊት ዶሚኒክ ስዞቦዝላይ ክርስቲያኖ ሮናልዶን ማሊያውን ጠየቀው። ነገር ግን ሮናልዶ ቀድሞውኑ ለሌላ ተጫዋች ሰጥቶት ነበር ። ቢሆንም ፖርቹጋላዊው ኮከብ በሚቀጥለው ግጥሚያ በግል እንደሚሰጠው ቃል ገባለት።

ትናንት ሃንጋሪው ዶሚኒክ ዞቦዝላይ ፈገግ ብሎ የአርአያውን ማሊያ በመጨረሻም እንደሰጠው አረጋግጧል። ዶሚኒክ ዞቦዝላይ በ92ተኛው ደቂቃ ላይ ጎል አስቆጥሮ የፖርቹጋላዊያንን ደስታ አላሽቷል።

እናም ፖርቹጋል ቀሪ ጨዋታ እየቀራት ማረጋገጥ የምትችልበትን ደስታ ነጠቀ። ነገር ግን ክርስትያኖ ሮናልዶ ማልያውን በትህትና ሰጥቶታል። ክርስትያኖ ሮናልዶ ቃሉን ጠብቋል።ታላቁ ሰው ታላቅ ነው !! ❤🙏

የሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ ወሳኝ ርዕስ መሆኑን አማካሪያቸው ተናገሩየኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "በጣም አስፈላጊ እና ወሳኝ" መሆኑ...
15/10/2025

የሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ ወሳኝ ርዕስ መሆኑን አማካሪያቸው ተናገሩ

የኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጉዳይ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "በጣም አስፈላጊ እና ወሳኝ" መሆኑን ከፍተኛ አማካሪያቸው ማሳድ ቡሎስ ተናገሩ።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የአፍሪካ፣ የአረብ እና የመካከለኛው ምሥራቅ ከፍተኛ አማካሪው ለሳዑዲው አል አረቢያ እንደተናገሩት፤ ትራምፕ ከመጀመሪያው የሥልጣን ዘመናቸው አንስቶ በግድቡ ዙሪያ የበኩላቸውን ሲያከናውኑ ነበር።

ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ከዓባይ ወንዝ በምታገኘው የውሃ መጠን ላይ ተጽዕኖ ይኖረዋል በሚል ከሱዳን ጋር በመሆን በግድቡ የውሃ ሙሌት እና አስተዳደር ላይ አስገዳጅ ስምምነት እንዲደረስ ስትጠይቅ የቆየችው ግብፅ፤ በተደጋጋሚ በጉዳዩ ላይ አሜሪካ ጣልቃ እንድትገባ ስትጠይቅ ቆይታለች።

ፕሬዝዳንት ትራምፕም በመጀመሪያው የሥልጣን ዘመናቸው የሁለቱ አገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናትን በማቀረራብ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ከመሞከራቸው ባሻገር በተለያዩ ጊዜያት ግድቡን በተመለከተ አነጋጋሪ አስተያየት በመስጠት ይታወቃል።

የፕሬዝዳንቱ አማካሪ፤ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጉዳይ የትራምፕ ትኩረት እንዳለው በመጥቀስ ወሳኝ አጀንዳ መሆኑን ተናግረዋል።

ስልክ ቁጥርዎ በድንገት ሊቋረጥ ይችላል! ሲም ካርድዎን ከማቋረጥ የሚከላከሉ የ Ethio Tecom ወሳኝ ህጎች!~ ይህ መረጃ ባንክ ፣ የተለያዩ Social media ምትከፍቱበትን Sim ካርድ...
15/10/2025

ስልክ ቁጥርዎ በድንገት ሊቋረጥ ይችላል! ሲም ካርድዎን ከማቋረጥ የሚከላከሉ የ Ethio Tecom ወሳኝ ህጎች!

~ ይህ መረጃ ባንክ ፣ የተለያዩ Social media ምትከፍቱበትን Sim ካርድ ስለሚመከት በደንብ ያንብቡት !

የሞባይል ስልክ ቁጥርዎን ለረጅም ጊዜ ስላልተጠቀሙ ብቻ በድንገት ተቋርጦ (Deactivated) ያውቃል? ስልክ ቁጥርዎ ከስራ፣ ከቤተሰብ እና ከባንክ አካውንትዎ ጋር የተያያዘ ወሳኝ ንብረት ነው። የሲም ካርድ መቋረጥ በቴሌኮም ሕግጋት መሠረት የሚፈጸም ሲሆን በቀላሉም ሊመለስ አይችልም።

ስልክ ቁጥርዎ ከጥቅም ውጪ እንዳይሆን እና አገልግሎትዎ እንዳይቋረጥ የሚከላከሉ ወሳኝ እርምጃዎች እነሆ፡

📵 የመቋረጥ መንስኤዎች እና መፍትሄዎች

1. ለረጅም ጊዜ አገልግሎት አለመጠቀም (Inactivity)

የኢትዮጵያ ቴሌኮም እና ሌሎች የዓለማችን ኦፕሬተሮች፣ ሲም ካርድዎ ለተወሰነ ጊዜ (ለምሳሌ ከ90 ቀናት በላይ) ምንም አይነት እንቅስቃሴ (Activity) ማለትም ጥሪ አለመደወል፣ መልዕክት አለመላክ ወይም ዳታ አለመጠቀም ካሳየ ሊያቋርጡት ይችላሉ።

📌 መፍትሄ ፦ ስልክ ቁጥሩን በየሶስት ወሩ (በ90 ቀናት ውስጥ) ቢያንስ አንዴ ጥሪ ያድርጉ፣ መልእክት ይላኩ ወይም አነስተኛ የሞባይል ዳታ ይጠቀሙ። ምንም እንኳን በውስጡ ባትሪ ባይኖርም፣ አልፎ አልፎ ጥቅም ላይ መዋሉን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው።

2. የቴሌኮም ዕዳ (Debt) መኖር

አልፎ አልፎ ቴሌኮም ወይም ሌሎች አገልግሎቶች ላይ ያሉ ዕዳዎች (ለምሳሌ የዳታ ብድር) በወቅቱ ካልተከፈለ አገልግሎቱ እንዲቋረጥ ሊያደርግ ይችላል።

📌 መፍትሄ ፦ በስልክ ቁጥርዎ ላይ ምንም አይነት ዕዳ አለመኖሩን ያረጋግጡ። ዕዳ ካለብዎት በተቻለ ፍጥነት ይክፈሉ።

~ የቴሌ እዳ ኑሮባችሁ ለረዥም ጊዜ ካልከፋላችሁ መስመሩ ሊታገድ ይችላል እና እየከፈላችሁ 😀!

3. የሲም ካርድ ምዝገባ መረጃ ትክክል አለመሆን

በምዝገባ ጊዜ የሰጡት መታወቂያ መረጃ (ለምሳሌ የቀድሞ መታወቂያ) ከወቅታዊ ህጋዊ መታወቂያዎ (ለምሳሌ ብሔራዊ መታወቂያ) ጋር የማይመሳሰል ከሆነ፣ ቴሌኮም መረጃዎን እንዲያስተካክሉ ሊጠይቅ ይችላል። ይህንን ችላ ማለት መቋረጥን ያስከትላል።

📌 መፍትሄ ፦ የሲም ካርድዎ በእርስዎ ስም መመዝገቡን እና መረጃዎ የዘመነ መሆኑን ያረጋግጡ። ችግር ካለ ወደ ቅርብ የቴሌኮም ቅርንጫፍ በመሄድ ማስተካከያ ያድርጉ።

4. ሲም ካርድን በተበላሸ ሁኔታ መያዝ

ሲም ካርዱ ራሱ በአካል ከተጎዳ (ከተሰበረ ወይም ከተቧጨረ) ወይም በስልኩ ማስገቢያ (Slot) ላይ ለረጅም ጊዜ ሳይገባ ከቆየ፣ ሊጎዳ ይችላል።

📌 መፍትሄ ፦ ሲም ካርድዎን በትክክለኛው የስልክ ማስገቢያ ውስጥ ያስቀምጡ። በቅርብ ጊዜ ከተበላሸ ወይም የማይሰራ ከሆነ ከመቋረጡ በፊት በአዲስ ሲም ካርድ እንዲተካ ይጠይቁ።

❗️ የስልክ ቁጥርዎ የዲጂታል ማንነትዎ አካል ነው! ከመቋረጡ በፊት በየጊዜው በመጠቀም እና በስምዎ መመዝገሩን በማረጋገጥ ራስዎን ይጠብቁ።

🗣️ ስልክ ቁጥርዎ ለረጅም ጊዜ ተቋርጦበት ያውቃል?

Source: Andebet

በጠና ታመዋል'በዱዓም ሆነ በፀሎት' አስቧቸው !❤️‍🩹 : የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት  ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) የጤና እክል ገጥሟቸዉ ለህክምና ወደ...
15/10/2025

በጠና ታመዋል'በዱዓም ሆነ በፀሎት' አስቧቸው !❤️‍🩹

: የቀድሞ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ (ሙፍቲ) የጤና እክል ገጥሟቸዉ ለህክምና ወደ ቱርክ ሀገር መሄዳቸውም ተነግሯል።

ታላቁ አባት ሀጅ ዑመር ኢድሪስ ያጋጠማቸው የጤና እክል ምንነት እስካሁን በይፋ አልተነገረም። ሙፍቲ ከገጠማቸው የጤና እክል አላህ አፊያ እንዲያረጋቸው ዱዓ እንዲደረግላቸው ጥሪ መቅረቡን ጠቅሶ የዘገበው ነጃሺ ቴሌቪዥን ነው።

"የሰው ልጅ ሰላም ምንጩ ፈጣሪውን መፍራት መቻሉ ነው።”ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጂ ዑመር ኢድሪስ ፤ ታላቁ አባት ጤናዎት እንዲመለስ ልባዊ መሻታችን ነው!!❤️🙏❤️

እንስሳት አስይዞ መበደር በኢትዮጵያ ሊፈቀድ ነው*******************************" የኬንያ የጎረቤት ሀገራት ተሞክሮን በመውሰድ የእንስሳት ልየታ እና ምደባ መስራት ተጀምሯል።...
15/10/2025

እንስሳት አስይዞ መበደር በኢትዮጵያ ሊፈቀድ ነው
*******************************"



የኬንያ የጎረቤት ሀገራት ተሞክሮን በመውሰድ የእንስሳት ልየታ እና ምደባ መስራት ተጀምሯል።

ለመበደሪያ እንዲውል የባንክ ማዕቀፍ መዘጋጀቱን ከግብርና ሚኒስትር ሰዎች አራት አይን ተከታትለናል።

ከእንስሳት ተዋፅኦ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድ በእንስሳት ሀብት ቀዳሚ ብትሆንም የዋጋ ንረቱ ከፍተኛ ስለመሆኑ የሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ሀላፊዎች በሰጡት ምላሽ

ከ70 እስከ 75% የመኖ ችግር ወይም የመኖ ቀረጥ መሆኑን ገልፀዋል። በመንግስት በኩል ሰፊ ውይይት ተደርጎበት መኖን ከቀረጥ ነፃ የማድረግ ስራ እየተሰራ ይገኛል።


ታሪኩ ከበደ

የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩየኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ራይላ ኦዲንጋ በዳረባቸው የልብ ሕመም ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆ...
15/10/2025

የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የኬንያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ራይላ ኦዲንጋ በዳረባቸው የልብ ሕመም ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በ80 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ሬውተርስ ዘግቧል፡፡

አንጋፋው የኬንያ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ በሕንድ ሀገር ሕክምናቸውን ሲከታተሉ እንደነበር ተመላክቷል፡፡

 “ በየቦታው የሰራናቸውን ሆቴሎች አይነት አንዷን ድሬዳዋ እናስቀምጣለን ብለን አቅደናል” - ሻለቃ ኃይሌ➡️ “ደብረ ብርሃን ሆቴል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ነው፤ በቀጣዮቹ ሦስት፣ አራት ወራት...
14/10/2025



“ በየቦታው የሰራናቸውን ሆቴሎች አይነት አንዷን ድሬዳዋ እናስቀምጣለን ብለን አቅደናል” - ሻለቃ ኃይሌ

➡️ “ደብረ ብርሃን ሆቴል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ነው፤ በቀጣዮቹ ሦስት፣ አራት ወራት ወደ ሥራ ይገባል” - አቶ ጋዲሳ ግርማ

አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ በሆቴልና ሪዞርት ግንባታ ረገድ ወደ ድሬዳዋ ከተማ እየገቡ መሆኑን፣ የከተማዋን ከንቲባና ካቢኔውን አግኝተውም ቃል እንደተገባላቸው ዛሬ ገልጸዋል፡፡

የኃይሌ ሆቴሎች ሪዞርቶች ግሩፕ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ጋዲሳ ግርማ በበኩላቸው፣ ድሬዳዋ ላይ የሆቴልና ሪዞት ግንባታ በቅርቡ እንደሚጀመር ዛሬ ምሽት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል፡፡

ሻለቃ ኃይሌ፣ በድሬ ከተማ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፣ “ኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በየከተማዎቹ እየገነባን ነን፡፡ እስካሁን በአስር ከተሞች ተከፍተዋል፡፡ ሌላ ሦስት ደግሞ በግንባታ ላይ ናቸው፡፡ አሁን ደግሞ የድሬው 14ኛው ይሆናል” ብለዋል፡፡

“መምጣት ካለብን በጣም የዘገየንበት ቦታ ነው፡፡ ግን አሁን ድሬዳዋ እየገባን ነው፤ ክቡር ከንቲባውንም ካቢኔውንም አግኝተን በጣም ጥሩ ቃል ገብተውልናል” ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ሥራው ቶሎ እንደሚጀመር ጠቁመው፣ “በየቦታው የሰራናቸውን ሆቴሎች አይነት አንዷን ድሬዳዋ እናስቀምጣለን ብለን አቅደናል፡፡ መጀመሪያ ስናጠና ቢዝነሱ እንዴት ነው ? የሚለውን ነው፤ ድሬዳዋም ከኢትዮጵያ ቀደምት ከተሞች አንዷ ነች፤ በቢዝነሱም” ነው ያሉት፡፡

ስለድሬዳዋው ሆቴል ግንባታ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የኃይሌ ሆቴሎች ሪዞርቶች ግሩፕ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ጋዲሳ ግርማ፣ “የቦታ ልየታና ገበያውን ለማየት ሂደን ነበር ዛሬ፡፡ ኢንቨስትመንት ላይ የሚሰሩ የመንግስት አካላት ቦታዎችን አሳይተውናል፤ ወደ ቀጣዩ ሂደት እንቀጥላለን” ብለዋል፡፡

ግንባታውን በቅርቡ የመጀመር እቅድ እንዳላቸው፣ በዚህ ቀን ይጀመራል የሚል ቀን ገና እንዳላስቀመጡ ገልጸው፣ “የመሬት ርክክብ ባለቀ በማግስቱ ግንባታ እንጀምራለን” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

የጎንደርና ደብረ ብርሃን ፕሮጀክቶችን እያጠናቀቁ በመሆኑ ቀጣዩ አቅጣጫ ወደ ድሬ እንደሆነ የጠቆሙት አቶ ጋዲሳ፣ “ደብረ ብርሃን ሆቴል የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ነው ያለው፤ በቀጣዮቹ ሦስት አራት ወራት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባል፡፡ የጎንደር ደግሞ ከሰባት ውራት እስከ አንድ አመት ይወስዳል” ብለዋል፡፡

በጎንደሩ ፕሮጀክት የጸጥታው ሁኔታ ምን አይነት እንቅፋት እንዳፈጠረባቸው ማብራሪያ ሲጠየቁም፣ በዚህ ረገድ አስተያየት አለመስጠትን መርጠዋል፡፡

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


‎የደሴ ከተማ አሰ/ር ፖሊስ መምሪያ የሌዛ ደሳለኝ ግድያ በተመለከተ ተከታዩን መረጃ ሰጥቷል።‎‎ ወጣት ሌዛ ደሳለኝ የተባለች የከተማችን ነዋሪ በቀን 28/01/18 ዓ,ም በደሴ ከተማ ቦርከና ...
14/10/2025

‎የደሴ ከተማ አሰ/ር ፖሊስ መምሪያ የሌዛ ደሳለኝ ግድያ በተመለከተ ተከታዩን መረጃ ሰጥቷል።

‎ ወጣት ሌዛ ደሳለኝ የተባለች የከተማችን ነዋሪ በቀን 28/01/18 ዓ,ም በደሴ ከተማ ቦርከና ቀበሌ ልዩ ስሙ ሀቢታት አካባቢ ባልታወቁ ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ ተፈፅሞባት ህይወቷ ማለፉ ይታወቃል።

‎የተፈፀመው የወንጀል ድርጊትም ለፖሊስ መረጃው እንደደረሰው በፍጥነት በቦታው ደርሶ አስፈላጊውን ተግባር አከናውኗል።

‎የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አማካኝነት የፍትህ አካላትን ያካተተ የምርመራ ቡድን በማዋቅር ምርመራው በታክቲክና በቴክኒክ ማስረጃዎችን በማጣራት ወንጀል ፈፃሚውን አካል በቁጥጥር ስር ለማዋል እየሰራ ሲሆን በቀጣይ የምርመራ ቡድኑ የደረሰበትን የምርመራ ውጤት ለህዝብ የምናሳውቅ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን።

‎ስለሆነም ህዝቡ መሰል የወንጀል ክስተቶች ውስብስብ መሆናቸውን በመረዳት ድርጊቱ የሚፈልገውን ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ፖሊስ አስፈላጊውን ክትትልና ምርመራ አድርጎ ውጤቱን ለህዝብ እስኪያሳውቅ ህዝባችን በተለመደው ትዕግስቱ እንዲጠብቀን ሲል የመርምራ ቡደኑ ገልጿል።

‎ፖሊሰ መምሪያው ለሟች ቤተሰቦችና ጓደኞች እንዲሁም ወዳጀ ዝምዶች መጽናናትን ይመኞል።
‎የደሴ ከተማ አሰ/ር ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

የቀጠለው የትግራይ ክልል ኃይሎች ተቃውሞዛሬ ከመቐለ ዓዲግራት የሚወስደውን ጎዳና የዘጉ የትግራይ ኃይሎች ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ ጎዳናው እንደዘጉ ነበሩ። ትላንት የግዚያዊ አስተዳደ...
14/10/2025

የቀጠለው የትግራይ ክልል ኃይሎች ተቃውሞ

ዛሬ ከመቐለ ዓዲግራት የሚወስደውን ጎዳና የዘጉ የትግራይ ኃይሎች ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ ጎዳናው እንደዘጉ ነበሩ። ትላንት የግዚያዊ አስተዳደሩፕሬዝደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ፣ የህወሓት ሊ/መንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤልን ጨምሮ የሠራዊቱ ከፍተኛ አዛዦች ከተቃዋሚዎቹ የሠራዊት አባላት ጋር ስላካሄዱት ዝግ ስብሰባየተባለ ነገር የለም።

የእለቱ መረጃዎች -የትግራይ መከላከያ ኃይል የሚባለዉ ወታደራዊ ሥብስብ አባላት የደሞዝና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች እንዲከበሩላቸዉ በመጠየቅ የጀመሩት ተቃዉሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል።ተቃዋሚዎቹ ትናንት የ...
14/10/2025

የእለቱ መረጃዎች



-የትግራይ መከላከያ ኃይል የሚባለዉ ወታደራዊ ሥብስብ አባላት የደሞዝና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች እንዲከበሩላቸዉ በመጠየቅ የጀመሩት ተቃዉሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል።ተቃዋሚዎቹ ትናንት የመቀሌን ዛሬ ደግሞ ከመቀሌ አድግራት የሚያጉዘዉን መንገድ ዘግተዉ ዉለዋል።

የማዳጋስካር ጦር ኃይል የሐገሪቱን የመንግሥትነት ሥልጣን መቆጣጠሩን አስታወቀ።ጦሩ ሥልጣን መያዙን ያስታወቀዉ ከሐገር የሸሹት ወይም የተደበቁት ፕሬዝደንት የማዳጋስካርን ፓርላማ መበተናቸዉን ካስታወቁ ከሰዓታት በኋላ ነዉ።

-በእስራኤል ጦር ድብደባና በምግብ እጦት ለረሐብ ለተጋለጠ,ዉ የጋዛ ሕዝብ ሰብአዊ ርዳታ ለማቅረብ ሁሉም መተላለፊያዎች እንዲከፈቱ ለጋሽ ድርጅቶች ጠየቁ።እስራኤልና ሐማስ ባደረጉት ሥምምነት ሁለቱ ወገኖች የሚያደርጉት የታጋቾችና የእስረኞች ልዉዉጥ እየተገባደደ ነዉ።የአስከሬን ልዉዉጡ ግን ጊዜ ይፈጃል ተብሏል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251938668562

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arat ayin Media አራት ዓይን posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Arat ayin Media አራት ዓይን:

Share