Sello Media

Sello Media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sello Media, Media/News Company, Addis Ababa.

  !​በፖለቲካ መድረክ ላይ ትልቁና የመጨረሻው ዳኛ ሕዝብ ነው። ሕዝብ ደግሞ የሚሰጠውን ፍርድ በምሬት ወይም በጩኸት ሳይሆን በሰላማዊ መንገድ በምርጫ ካርዱና ለልማት በሚያሳየው ዝግጁነት ይገ...
28/05/2026

!

​በፖለቲካ መድረክ ላይ ትልቁና የመጨረሻው ዳኛ ሕዝብ ነው። ሕዝብ ደግሞ የሚሰጠውን ፍርድ በምሬት ወይም በጩኸት ሳይሆን በሰላማዊ መንገድ በምርጫ ካርዱና ለልማት በሚያሳየው ዝግጁነት ይገልጻል።

ቁሕዴፓ አመራሮች በአዲስ አበባ መግለጫ አውጥተው የፈጠሩት ሁካታ ካለፈው የታሪክ ስህተት ያልተማረና የቁጫን ሕዝብ ንቃተ-ሕሊና የናቀ የከሰረ ፖለቲካ ማሳያ ነው።

​ቁሕዴፓ በቁጫ አካባቢ በሕዝብ ዘንድ ሙሉ በሙሉ መተፋቱንና የመደገፊያ መሬት ማጣቱን በሚገባ ያውቀዋል። ለአመታት የሕዝብን ስሜት በመኮርኮርና በማንነት ስም በመነገድ የቆየው የፖለቲካ ቁማር ማብቂያው ላይ ደርሷል።

ፓርቲው በምርጫ ሜዳው ላይ ወርዶ መወዳደርና ማሸነፍ እንደማይችል ሲረዳ መሸነፉን አስቀድሞ በማረጋገጡ ገና ምርጫው ሳይካሄድ የሽንፈት ማስተባበያ ሰበብ ማዘጋጀት ጀምሯል።

የሕግ አንቀጾችን መጥቀስና ተገለልን ማለት ሕዝባዊ መሠረት ማጣትን ለመሸፈን የተዘረጋ የሽንፈት መጋረጃ ነው።

​የቁጫ ሕዝብ ዛሬ የትናንቱን የውዥንብር ፖለቲካ ወደ ኋላ ጥሏል። በአካባቢው ለብልጽግና ፓርቲ የወጣውና የታየው ተዓምራዊ የሕዝብ ማዕበል የሚያረጋግጠው አንድ እውነት አለ። ሕዝቡ የሚፈልገው ጩኸት ሳይሆን ልማት፣ ሁከት ሳይሆን ሰላም፣ መገለልን ሳይሆን አብሮነትን ነው።

​ያ የታምር ሰልፍ ለቁሕዴፓ አመራሮች የፖለቲካ ሞት የዕርድ አዋጅ ነበር። ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ለብልጽግና ያለውን ታማኝነትና ድጋፍ ሲያሳይ፣ ተቃዋሚዎች የወደፊት ዕጣ ፈንታቸው ጨለማ መሆኑን ተረዱ።

ከዚህ ማዕበል ማምለጥ እንደማይችሉ ሲያውቁም ምርጫው እንዲራዘም ወይም እንዲሰረዝ መጮኽን እንደ ብቸኛ አማራጭ ወሰዱት።

እውነተኛ የሐሳብ ልዕልና ያለው ፓርቲ የሕዝብን ድምፅ አይፈራም ምርጫ እንዲራዘምም አይማጸንም። የቁሕዴፓ ጩኸት የጥንካሬ ሳይሆን የከፍተኛ ፍርሃት መግለጫ ነው። መሸነፍን በፀጋ መቀበል ያቃተው ፖለቲካ፣ ተቋማትንና ሥርዓቱን በመወንጀል የራሱን ውድቀት ለማስታገስ ይሞክራል።

የሕዝብን ልብ ማሸነፍ አቅቶት፣ በምርጫ ሳጥን ውስጥ የሚጠብቀውን ውርደት በመፍራት አዲስ አበባ መሽጎ የሽንፈት መግለጫ የሚያረቅ የከሰረ ኃይል አለ።

​የቁጫ ሕዝብ ወደ ኋላ አይመለስም ድምፁንና ውሳኔውን በተግባር አሳይቷል። የቁሕዴፓ ጩኸትም ቀድሞ የተረጋገጠ ሽንፈትን በጩኸት ለመቀየር የሚደረግ የሰነፎች የመጨረሻ ትግል ብቻ ነው።

27/05/2026
ፍርድ ቤት የሰጠው ምንም ዓይነት የቅጣት ውሳኔ በሌለበት ሁኔታ የፈጠራ ወሬዎችን እያቀነባበሩ ለሕዝብ ማቅረብ ራሱ የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ከባድ ስህተት ነው።የፍትሕ መድረኩ የሕግ አዋ...
20/05/2026

ፍርድ ቤት የሰጠው ምንም ዓይነት የቅጣት ውሳኔ በሌለበት ሁኔታ የፈጠራ ወሬዎችን እያቀነባበሩ ለሕዝብ ማቅረብ ራሱ የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስከትል ከባድ ስህተት ነው።

የፍትሕ መድረኩ የሕግ አዋቂዎችና የዳኞች መድረክ እንጂ የሶሻል ሚዲያ አክቲቪስቶች የውሸት ፕሮፓጋንዳ ማሰራጫ አይደለም። በማኅበራዊ ሚዲያ የሀሰት ጩኸትና የፈጠራ ወሬ የሕግን ሂደት ለመቀየር የሚደረገው ጥረት ከንቱ ሆኖ ይቀራል።

ኅብረተሰቡም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት እንዲህ ዓይነት የተደራጁ የሐሰት ወሬዎችን ውድቅ በማድረግ መረጃዎችን ከራሱ ከፍርድ ቤቱ ይፋዊ መዝገብ ብቻ እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን።

12/05/2026
በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ "ቃል መግባት" እንደ ባህል "ተግባር" ደግሞ እንደ ናፍቆት በነበረበት ዘመን ተወልደው ያደጉ እንደ ቡንካሾ ያሉ ግለሰቦች ዛሬ የሚታየው የተግባር ሩጫ ግራ ቢ...
09/05/2026

በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ "ቃል መግባት" እንደ ባህል "ተግባር" ደግሞ እንደ ናፍቆት በነበረበት ዘመን ተወልደው ያደጉ እንደ ቡንካሾ ያሉ ግለሰቦች ዛሬ የሚታየው የተግባር ሩጫ ግራ ቢያጋባቸው አይገርምም።

ቡንካሾና መሰሎቹ "ያልሰራ በካርድ ይቀጣ" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ንግግር እንደ ፖለቲካ ፍጆታ ሊጠቀሙበት ቢሞክሩም እውነታው ግን ከእነሱ የትችት አድማስ በላይ ርቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ "ያልሰራን በካርድ ቅጡ" ሲሉ በባዶ ሜዳ ላይ ቆመው ሳይሆን በሰሩት ስራ ተማምነው ነው።

እንደ ቡንካሾ ያሉ ተቺዎች በጽሁፍና በንግግር ሲጠመዱ አመራሩ ግን የህዳሴውን ግድብ ውሃ ሞልቶ፣ ተራሮችን አልምቶና የከተሞችን ቆሻሻ ገፅታ በኮሪደር ልማት አጽድቶ በተግባር እየመለሰ ይገኛል።

ለቡንካሾዎች ፖለቲካ የቃላት ጨዋታ ነው ለአመራሩ ግን ፖለቲካ ማለት ህዝብን በስራ ማገልገል ነው።

ኢትዮጵያ ስንዴ ትልካለች ሲባል "የማይሆን ህልም" ነው ብለው ሲተቹ የነበሩ ወገኖች፣ ዛሬ ምርቱ መርከብ ላይ ሲጫን ለማየት አይናቸው ቢታወርም ታሪኩ ግን እየተጻፈ ነው። ቃልን በተግባር የመለወጥ ጥበብ ማለት እንዲህ ነው።

ቡንካሾ በፌስቡክ ገጹ "ቃል አልተጠበቀም" ብሎ ሲጽፍ በመሬት ላይ ግን ገበሬው በመስኖ ስንዴ ህይወቱን እየቀየረ ነው። ታዲያ ማነው መቀጣት ያለበት ? ቃልን በተግባር የገነባው መሪ ወይስ ሀቁን የካደው ተቺ?

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የደረሰችበት የዲፕሎማሲ ከፍታና የብሪክስ (BRICS) አባልነት እንዲሁም እንደ ዓድዋ መታሰቢያ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የንግግር ውጤቶች አይደሉም። እነዚህ ስራዎች የ"ቃል-ተግባር" ትርክትን በደም እና በአጥንት ያጸኑ ናቸው።

"በካርድ ቅጡ" የሚለው ንግግር ለቡንካሾዎች ማስፈራሪያ ሳይሆን ለሰራው አመራር የልበ ሙሉነት መግለጫ ነው።

በመጪው ጊዜ ህዝቡ ካርዱን በእጁ ሲይዝ የሚፈርደው በፌስቡክ ትረካ ሳይሆን በአይኑ ባየው ልማት ነው። የቡንካሾ ጽሁፎች በአየር ላይ እንደሚበን ጢስ ሲጠፉ፣ የአመራሩ የልማት አሻራዎች ግን ለትውልድ የሚሻገሩ ሀውልቶች ሆነው ይቆማሉ።

ስለዚህ ህዝቡ ካርዱን የሚጠቀመው ቃልን ወደ ተግባር ለቀየረ ኢትዮጵያን ከአፈር ወደ ብርሃን ላወጣ አመራር እውቅና ለመስጠት መሆኑ አያጠራጥርም።

ቡንኬ ከፌስቡክ ትችት ውጪ ዕቅድ እና ራዕይ የሌለ ሰው ነች !

ፍርድ ቤት የያዘውን ጉዳይ በሚዲያ ጋጋታ ለማሸነፍ ለምን ታሰበ? የስዩም ተሾመ ሚዛናዊነት የጎደለው ውንጀላ! የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1238/2013) ይህ አዋጅ በሚዲያና በፍት...
05/05/2026

ፍርድ ቤት የያዘውን ጉዳይ በሚዲያ ጋጋታ ለማሸነፍ ለምን ታሰበ?
የስዩም ተሾመ ሚዛናዊነት የጎደለው ውንጀላ!

የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1238/2013) ይህ አዋጅ በሚዲያና በፍትህ አካላት መካከል ያለውን ግንኙነት በዝርዝር ያስቀምጣል። መገናኛ ብዙሃን በፍትህ ሂደት ላይ ያሉ ጉዳዮችን ሲዘግቡ ትክክለኛ፣ ሚዛናዊና የሕግ የበላይነትን ያከበሩ መሆን እንዳለባቸው ይጠቁማል።

ፍርድ ቤቶች የዜጎች የመጨረሻ የመብት ማስከበሪያ ናቸው። ፍርድ ቤቶች በሕግ አውጭው አካል አስቀድመው የወጡ ሕጎችን የመተረጎም ሥልጣን የተሰጣቸው በየትኛውም አካል ተፅዕኖ ውስጥ ሳይወድቁ ነፃና ገለልተኛ ሆነው የፍህት ስርዓቱን የሚያሳልጡ ተቋማትም ናቸው። መገናኛ ብዙሃን ፍርድ ቤት በያዘው ጉዳይ ላይ ሚዛናዊ ያልሆኑ ዘገባዎችን ማሰራጨት እንደማይችሉ የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ ይደነግጋል።

የዳኝነት ነፃነት ( በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥ አንቀጽ 79)፦ ፍርድ ቤቶች በማንኛውም ደረጃ የዳኝነት ስልጣናቸውን ሲጠቀሙ ከማንኛውም የተፅዕኖ ፈጣሪ አካል (ሚዲያን ጨምሮ) ነፃ መሆናቸውን ያመላክታል።

ምንም እንኳን አዋጁ ይህንን ቢያስቀምጥም አንዳንድ የማህበራዊ ሚዲያ አንቀሳቃሾች ይህንን ድንጋጌ ወደ ጎን በመተው ፍርድ ቤት በያዛቸው ጉዳዮች ላይ ሚዛናዊነት የጎደላቸውን ዘገባዎችን የመስራት እና የፍርድ ቤት የዳኝነት ስርዓት ላይ ተፅዕኖ የመፍጠር ስራዎችን ሲሰሩ ይስተዋላል።

ለአብነትም ከሰሞኑን ጦማሪ ስዩም ተሾመ ነፃ ውይይት በተሰኘው የዩቲዩብ ዝግጅቱ ላይ በጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተያዘውን የአቶ ብርሃነ መስቀል ክንፈ የማራማይንስ ማዕድን ምርመራ እና ማዕድን ማምረት ስራ ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ ጉዳይን ሚዛናዊነት በጎደለው መልኩ በዘፈቀድ በሚዲያ ሲያራግብ ተስተውሏል።

ጉዳዩን የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በከባድ ሙስና ክሥ የእርሡን እና የግብር አበሩን እያየ የሚገኝ ሲሆን፤
የፌደራል የመጀመሪ ደረጃ ፍ/ቤት እና የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ግራ ቀኙን በፍታብሔር ችሎቶች እያከራከሩ ለመጨረሻ ውሣኔ ተቀጥሮ ሣለ ለምን አሁን ሚዲያ ላይ ማሥጮህ ተፈለገ?

ፍርድ ቤት ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ በያዘው ጉዳይ ላይ የሕግ የበላይነትን ባለከበረ መልኩ በአክቲቪስት ስዩም ተሾመ አማካኝነት ለአንድ ወገን ያደላ ሃሰተኛ መረጃ መሰራጨቱ በብዙዎች ዘንድ ቅሬታን ፈጥሯል።

ሚዲያ እውነተኛ መረጃን ከሁለት ወገን አጣርቶ ገለልተኛ በሆነ መልኩ መረጃን ለሕዝብ የማድረስ ኃላፊነት ያለው ቢሆንም ስዩም ተሾመ ያልተረጋገጡ መረጃዎችን የማሰራጨት እና ፍርድ ቤት የያዘውን ጉዳይ ላይ ውሳኔ ሲሰጥበት ተስተውሏል።

ፍርድ ቤት ውሳኔ ለመስጠት ከጫፍ በደረሰው ጉዳይ ላይ
ስዩም ተሾመ ከአንድ ወገን ተላከልኝ ያለውን መረጃ ይዞ ወደ ሚዲያ መውጣት ለምን አሰፈለገ። ይህ ከሚዲያ ስነምግባር ያፈነገጠና ሚዛናዊነት የጎደለው ውንጀላ በፍርድ ቤት ላይ ተገቢነት የሌለው የሚዲያ ጫና በማሳደር የፍህት ስርዓቱን ለማደናቀፍ ያለመ ሴራ መሆኑን ሕዝብ ሊረዳ ይገባል።

ጉዳዩን በተመለከተ ፍርድ ቤት በራሱ አሰራር ተገቢውን ብይን የመስጠት ሙሉ ስልጣን ያለው ቢሆንም በሚዲያ ጋጋታ ይህን ዕውነታ ለመደበቅ እና የፍህ ስርዓቱ ላይ ጫና ለማሳደር በግልጽ ዘመቻ መከፈቱን መረዳት ይቻላል።

ስዩም ተሾመ የሰራው ሚዛናዊነት የጎደለው ዘገባ የፍርድ ቤትን ነፃነት የሚነካ፤ ለአንድ ወገን ያዳላ፤ በእውነተኛ መረጃ ላይ መሠረት ያላደረገ፤ በፍርድ ቤት አሰራር ላይ ጣልቃ ለመግባት ያለመና በሕግ የተያዘ ጉዳይን በሚዲያ ፕሮፓጋንዳ ለማሸነፍ ያለመ መሆኑ አነጋጋሪ ሆኗል።

ሕዝብን በአሉባታ ልታደናግር ትችል ይሆናል እንጂ ውሸት ስለደጋገም እውነት አይሆንም፤ የለቅሦ ቦታ እየቀያየረሩ አብዝቶ ሰለተለቀሠ ሐቀኝነት አይረጋገጥም፤ ሌላኛው ወገን እውነትን ይዞ ሕግን አክብሮ ጉዳዩ በሀላፊነት ስሜት ስለመራ ሀቅ የለውም ማለት አይደለም፤ ከዚህ በኋላ ዱቡሻ ሚዲያ ኔትዎርክ እውነታውን በሚዛናዊነት ለሕዝባችን በተከታታይ የሚያቀርብ ይሆናል።

 : ምርጫ ቦርድ ኢሶዴፓ ያቀረባቸውን 309 ዕጩዎች ከምርጫ ውድድር ውጪ አደረገ!የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፖርቲ (ኢሶዴፓ) ቦርዱ ለሕዝብ ይፋ ያደረጋቸውን 309 ዕጩዎች ሕጋዊ መስፈርቱን ...
05/05/2026

: ምርጫ ቦርድ ኢሶዴፓ ያቀረባቸውን 309 ዕጩዎች ከምርጫ ውድድር ውጪ አደረገ!

የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፖርቲ (ኢሶዴፓ) ቦርዱ ለሕዝብ ይፋ ያደረጋቸውን 309 ዕጩዎች ሕጋዊ መስፈርቱን ተከትሎ መመዝገቡን፣ የተመዘገቡ 309 "ዕጩዎች ልዩ መብት" እንዲከበር ዶክተር ራሔል ባፌ ለቦርድ በጻፉት ደብዳቤ ጠይቀዋል። "ስህተት ያልሰሩ ዕጩዎችን ከመሬት ተነስቶ ነዉ ከምርጫው ወጥተዋል ያለው።" ሲሉም ለዶቼቬለ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ለ7ተኛውጠቅላላ ምርጫያቀረባቸውን 309 ዕጩዎች ከውድድሩ ውጪ ማድረጉን አስታወቀ። ቦርዱ በፓርቲው አመራሮች መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ፍርድ ቤት "ፖርቲውን ወክለው የሚወዳደሩ ዕጩዎች በሕግ አግባብ ሊስተናገዱ ይገባል" በሚል በመወሰኑ ተከትሎ መሆኑን ጠቅሰል።
ችግሩን ለመፍታት ጥረት ማረጉን የገለፀው ምርጫ ቦርድ፣ ጥረቱ ባለመሳካቱ በፓርቲው ለሕዝብ ይፋ ተደርገው የነበሩት ዕጬዎች"ምርጫ ላይ እንዳይሳተፉ ከውድድሩ ውጭ" ያደረጋቸው መሆኑን ገልጿል። በፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ራሔል ባፌ የሚመራው ኢሶዴፓ ለቦርዱ በጻፈው ምላሽ" የዕጩዎች ልዩ መብት እንዲከበር"ጠይቋል። ፓርቲው ውሳኔውን በመቃወም ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አቤቱታ አስገብቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሚያዝያ 24 ቀን ለኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) በጻፈው ደብዳቤ ፓርቲው ለ7ተኛ ጠቅላላ ምርጫ ያቀረባቸው ዕጩዎች "ከውድድሩ ውጪ" መደረጋቸውን ይጠቅሳል። ቦርዱ በፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር ራሄል ባፌ አማካኝነት ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ተወዳዳሪ ሆነው ተመዝግበው የቀረቡትን ዕጬዎችን ለሕዝብ ይፋ ቢያደርግም በዕጩዎቹ ላይ በእነ አቶ አጫሞ ቦቄ በኩል ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቀርቦበታል ብሏል።

ፍርድ ቤቱ በውዝግብ ላይ ባሉት የፓርቲው አመራሮች የቀረቡትን ዕጩዎች ውድቅ ማድረጉንና ፖርቲውን ወክለው የሚወዳደሩ ዕጩዎች በሕግ አግባብ ሊስተናገዱ ይገባል በሚል ውሳኔ መስጠቱን የጠቀሰው ምርጫ ቦርድ ተቃውሞ የቀረበባቸውን እጩዎች የያዘ የድምፅ መስጫ ወረቅት ወደ ማተማያ ቤት ገብቶ ለህትምት ዝግጁ ቢሆንም በሁለቱ ወገኖች ተፈጠረ ባለው ችግር መፍትሔ እስከሚያገኝ ሳያሳትም መቆየቱንም ገልጿል። ቦርዱ ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት ከሁለቱም ወገኖች ጋር ውይይት ቢያደርግም ውጤት ሊገኝ እንዳልቻለ ጠቅሷል።

የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፖርቲ (ኢሶዴፓ) ቦርዱ ለሕዝብ ይፋ ያደረጋቸውን 309 ዕጩዎች ሕጋዊ መስፈርቱን ተከትሎ መመዝገቡን፣ የተመዘገቡ 309 "ዕጩዎች ልዩ መብት" እንዲከበርም ዶክተር ራሄል ባፌ ለቦርዱ በጻፉት ደብዳቤ ጠይቀዋል። "ስህተት ያልሰሩ ዕጩዎችን ከመሬት ተነስቶ ነዉ ከምርጫው ወጥተዋል ያለው።"

ቦርዱ ለዚህ ዉሳኔ ያቀረበዉ ምክንያት ምንድን ነው?

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኢሶዴፓ እወዳደርበታለሁ ባለባቸው ምርጫ ክልሎች "ሌሎች የፖለቲካ ፖርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ያስመዘገቡ በመሆኑ፤ መራጩ ሕዝብ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ድምፅ መስጠት ስላለበት፤ የፖርቲው አመራሮችም ዕጩ ተወዳዳሪዎችን በተሰጠው የጊዜ ገደብ ማቅረብ ባለመቻላቸው፣ ቦርዱ አገር ውጭ የሚደረገውን የድምፅ መስጫ ወረቀት ህትመት ከዚህ በላይ ሊያዘገይ የሚችል ባለመሆኑ፣ የሌሎች ፖርቲዎችን የመወዳደር እና የመመረጥ መብት ችግር ላይ የሚጥል ሆኖ በማግኘቱ፣ ከዚህ በላይ ጊዜ ሰጥቶ ሊጠብቅ እንደማይችል አስታውቋል። ቦርዱ አክሎም የፍርድ ቤት ውሳኔን የማክበር ግዴታ ያለበት መሆኑን ጠቅሶ ፖርቲው አስቀድሞ ያቀረባቸው ዕጬዎች "ምርጫ ላይ እንዳይሳተፉ ከውድድሩ ውጭ ያደረጋቸው መሆኑን" አስታውቋል።

DW Amharic

ጋሞን ማከፋፈል ዓላማው ያደረገ ነውረኛ ፓርቲ ህጋዊ እውቅና በሌለው መዋቅር ስም ቅስቀሳ ማድረግ ህገወጥ ተግባር ነው። አንድ የፓርቲ እጩና የህግ ባለሙያ ነኝ ከሚል አካል የማይጠበቅ አሳፋሪ ...
04/05/2026

ጋሞን ማከፋፈል ዓላማው ያደረገ ነውረኛ ፓርቲ

ህጋዊ እውቅና በሌለው መዋቅር ስም ቅስቀሳ ማድረግ ህገወጥ ተግባር ነው። አንድ የፓርቲ እጩና የህግ ባለሙያ ነኝ ከሚል አካል የማይጠበቅ አሳፋሪ የወንጀል ተግባር!

አቶ ቡንካሾ ሀንጌ በራሱ የማህበራዊ ሚዲያ ላይ ህጋዊ መሰረት እና እውቅና በሌለው ወረዳ
"ጋሞ ዞን ካምባ ምርጫ ክልል ባልታ ዙሪያ ወረዳ ቦኮ ቀበሌ" በማለት ያጋራው ሀሰተኛ መረጃ ህዝቡን አስቆጥቷል።

ለምርጫ ቅስቀሳ የ“ሕጋዊ መዋቅር” (የተመዘገበ ፓርቲ፣ እጩ ወይም የተፈቀደ ዘመቻ) ማድረግ ብቻ ይፈቀዳል። የሌለ መዋቅር ብሎ መጠራት እና በዚህ ስም መቀስቀስ ህገወጥ ተግባር ብቻ ሳይሆን አደገኛ ወንጀልም ነው፤ ህዝብን ማከፋፈልም ጭምር።

አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ነኝ የሚል አካል አጠቃላይ የፖለቲካ አስተያየት መግለጽ፣ ፖሊሲ ላይ መከራከር፣ ዜጎችን ያንን ፓርቲ እንዲመርጡ ማበረታታት (voter education) ከማድረግ አልፎ ሐሰት መረጃ መስጠት በህግ የምያስጠይቅ ወንጀል ነው።

ሀሳብ መሸጥ እንጅ ሀሰተኛ መረጃ ማሰራጨት አይፈቀድም። ፖለቲካ ግቡ የጋራ የሆነ ዓላማን ማስፈፀሚያ መሳሪያ ነው። ጋዴፓ ጅምር አካባቢ የምስረታ ዓሃማው ይኼ ልሆን ይችል ነበር፤ በስተመጨረሻም ዓላማውን ከሳተው ፓርቲ ሰዎች ከወጡ በኋላ ደጋፊ ያጡ እነቡንካሾ አይነቶች በሀሰተኛ መረጃ ህዝብን ማደናገር ጀምረዋል።

ዛሬ ላይ ከፓርቲ ቁመና ይልቅ የጩኸት ማስተጋቢያ አምፕልፋየር የሆነው ቡድን በምርጫ ቦርድ ያልተመዘገበን ድርጅት "ሰላም-ጋዴፓ" በሚል ስያሜ ማንቀሳቀስ የህዝብን አመኔታ ከማሳጣቱም በላይ የፖለቲካ ግልጽነትን የሚያጎድል ተግባር ነው፤ በመሆኑም ተለዋዋጭና አሳሳች ስሞችን ከመጠቀም ይልቅ እንደ "ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት" ግልጽ የሆኑ መጠሪያዎችን መጠቀም ይገባል።

ማደናገርን አስወግዶ በህጋዊ መንገድ መንቀሳቀስ ለሀገር ሰላምና መሰረታዊ በመሆኑ፣ ተዓማኒነት ያለው የለውጥ ጉልበት ለመፍጠር ከስሜታዊነት በጸዳ መልኩ ራስን በግልጽ ማስተዋወቅና ለህግ ተገዢ መሆን አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።

በተለይ አሁን ላይ የፓርቲው ህልውና የተሰኙ አንደበተ ቁልፍ ሰዎች የሚያደርጉት ተግባር ሌላ ነው። ድርጅቱን ስሙንና ግቡን ሳይቀይሩ ጯሂ የሚዲያ ተቋም አድርገውታል። ይህ ስስ በሆነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ለተቀባይነት እና ለዝና የሚያመቻምች ስራ መሆኑ የሚያጠያይቅ አይደለም። ግን እስከመቼ ?

ህዝብ ይሰለቻል መበጥበጥንም አይፈልግም። ጋዴፓ ከዛሬ 7 ዓመት በፊት መስራቾቹ ጭምር የተውት ፓርቲ ሆኗል።

ድምፃቸው ገደል ማሚቱ ሆኖ የሚሰማቸው የወሬ ስንቆች አሉ። ተው እንበላቸው ።

በጋሞ ዞን፣ ገረሴ-ቦንኬ ምርጫ ክልል የሠላም ጥምረት ፓርቲ ዕጩ የሆኑት ቡንካሾ ሀንጌ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን (NEBE) መመሪያዎች በግልጽ በመጣስ ትናንት በቦንኬ ጮሻ ገበያ ሕገ...
03/05/2026

በጋሞ ዞን፣ ገረሴ-ቦንኬ ምርጫ ክልል የሠላም ጥምረት ፓርቲ ዕጩ የሆኑት ቡንካሾ ሀንጌ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን (NEBE) መመሪያዎች በግልጽ በመጣስ ትናንት በቦንኬ ጮሻ ገበያ ሕገ-ወጥ የምርጫ ቅስቀሳ አካሂደዋል።

​በገበያ ስፍራዎች፣ በንግድ ማዕከላትና በህዝብ መገልገያዎች ውስጥ የፖለቲካ ቅስቀሳ ማድረግ በምርጫ ህጉ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ እየታወቀ፤ ፓርቲው ህግን በገሃድ መጣሱ የዴሞክራሲያዊ ምርጫን መሰረት የሚንድ እና የህግ የበላይነትን የሚፈታተን ድርጊት ነው። ፍትሐዊና ተዓማኒ ምርጫ ሊረጋገጥ የሚችለው ሁሉም ተወዳዳሪዎች ያለምንም ልዩነት ለሕግና ለሥነ-ምግባር ደንቦች ተገዥ ሲሆኑ ብቻ ነው!

​ስለሆነም፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የሚመለከታቸው የህግ አስከባሪ አካላት በዚህ የህግ ጥሰት ላይ አፋጣኝና አስተማሪ የሆነ አስተዳደራዊ እርምጃ (ከማስጠንቀቂያ እስከ ቅስቀሳ ማገድ) በመውሰድ፤ የምርጫው ሂደት ፍትሐዊና ህጋዊ መሆኑን በተግባር እንዲያረጋግጡ አበክረን እንጠይቃለን።



#ምርጫ

ገንዘብ አይሰራው የለ!...ዛሬም ተረኛ ተከፋይ  #ቁራ እና  #ሱስ ያደነዘዘው አላዋቂን አጋለጠች!አንድ ለሚዲያ ቅርብ ነኝ የሚል ሰው ከአንድ ወገን (ወንጀለኛ) ብቻ ሰምቶ መበየን በራሱ ፍር...
03/05/2026

ገንዘብ አይሰራው የለ!...

ዛሬም ተረኛ ተከፋይ #ቁራ እና #ሱስ ያደነዘዘው አላዋቂን አጋለጠች!

አንድ ለሚዲያ ቅርብ ነኝ የሚል ሰው ከአንድ ወገን (ወንጀለኛ) ብቻ ሰምቶ መበየን በራሱ ፍርደ ገምድልነት ከመሆኑም በቂ ማጣራት አለመፈለጉ በራሱ የወንጀለኛውን እጅ እርዝማኔ እና ምን ያክል ሽብርተኛ መሆኑን ያሳያል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሀገር ከእውነታው ወርዳ በሚዲያ አሉባልታ ተመሪ ለማድረግ ብዙ ተከፋይ ሚዲያዎች እየተፈበረኩ ሀሰትን በግርድፋ ሲደረድሩት ይታያል።

ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ እንዳሳወቅነው ብርሀነመስቀል የተባለ የሽብር አለቃ የተወነጀለበት ወንጀሎች ዝርዝር በርካቶች ናቸው።

ከኮንትሮባንድ አንስቶ ህገ ወጥ መሬት መቀራመት እንዲሁም ሽብርተኝነትን በገንዘብ እና በመሳርያ እስከመደገፍ መሆኑ ግልጽ ነው።

ለዚህ ወንጀሉ ታድያ ፍ/ቤት በቁጥጥር ስር አውሎት ጊዜ ወስዶበት ተገቢውን ምርመራ ለማከናወን የተቻለውን ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል።

ታድያ የዚህ ሰው ሀብት የደበቀውን ማንነት በየወቅቱ ከእጁ ሽርፍራፊ ገንዘብ በመቅመስ ክልልን ብቻ ሳይሆን ሀገርን የማፍረስ ዘመቻውን ተረክበው የሚያራግቡ ጥቂት የሀሰተኛ ሚዲያዎች ከሰሞኑን ጩኸታቸው አይሏል።

ይባስ ብሎ የእነርሱ አሉባልታ ተደማጭነት ሲያጣ አንድ የተባለውን ሁላ አውሪ እንቶ ፈንቶ አክቲቪስት ነኝ ባይ ግለሰብ መጠቀሚያ በማድረግ ጉዳዩን ሳያጣራው ወደ ሚዲያው ሊያወጣው ሲዳዳው ተመልክተናል።

የህዝብን የመልማት ጥያቄ በማንኳሰስና በትላንት የህውአት ስርዓት ከበርቴዎችን ዛሬም ለማንገስ አንዳንድ የሚዲያ ሰው ነን የሚሉ በፍትህ ስርዓት ውስጥም ያልጠፉ በሚለገስላቸው ፍርፋሪ ደፋ ቀና ከማለት ያልቦዘኑ ከንቱዎች እንቅልፍ አጥተው ቅዠታቸው ቀጥሎ ይገኛል...
ሀቁ ግን ደቡብ ኢትዮጵያ ከፍ ባለ ልዕልና በልማት እና ሰላም ሀዲድ ጉዞ ላይ ነች።

ነገሩ ''ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቅረጣል!'' እንዳይሆን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በተያዘው ልማት የተለመደ ትብብራቸውን በማድረግ በሀሰተኛ ትርክት እንዳይሸወዱ ዘንድ መልዕክታችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251911853624

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sello Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sello Media:

Share