ETHIO MEDIA

ETHIO MEDIA media and company

ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ ሀበሻ፣ምኒልክ የዓድዋ -ድል ራስ💪ብራቮ ምኒልክ ፣ብራቮ ጣይቱ👏ምኒልክ ዛሬም ንጉስ ነው💪👏💪💪
01/03/2023

ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ ሀበሻ፣

ምኒልክ የዓድዋ -ድል ራስ💪
ብራቮ ምኒልክ ፣ብራቮ ጣይቱ👏

ምኒልክ ዛሬም ንጉስ ነው💪👏💪💪

መልካም በዓል 🙏
11/09/2022

መልካም በዓል 🙏

በሕመም እና ልዩ ልዩ ምክንያቶች በሆስፒታሎች ለምትገኙ ወገኖች በሙሉ፣በልዩ ልዩ ምክንያቶች በተለይም በአገዛዙ ግፍ ምክንያት በእስር ለምትገኙ ወገኖች በሙሉ፣ከሞቀ ጎጇችሁና ከቀያችሁ ተፈናቅላ...
11/09/2022

በሕመም እና ልዩ ልዩ ምክንያቶች በሆስፒታሎች ለምትገኙ ወገኖች በሙሉ፣
በልዩ ልዩ ምክንያቶች በተለይም በአገዛዙ ግፍ ምክንያት በእስር ለምትገኙ ወገኖች በሙሉ፣
ከሞቀ ጎጇችሁና ከቀያችሁ ተፈናቅላችሁ ለምትገኙ ወገኖች በሙሉ፣
በስደት ላላችሁና በበዓድ አገር ሕይወት እንዳሰባችሁት ላልሆነላችሁ በሙሉ እንዲሁም
የኑሮ ሁኔታዎች ባለመሟላታቸው የአውደ ዓመትን ወግ ለማጣጣም ላልታደላችሁ በሙሉ፤

እንኳን ለ2015 ዓ/ም የዘመን መለወጫ አደረሳችሁ። ፈጣሪ በጎውን ነገር ሁሉ ያቀርብላችሁ ዘንድ መልካም ምኞቴ ይድረሳችሁ!

አቶ ክርስቲያን ታደለ

10/09/2022

ይህ ትውልድ ሁለት አማራጭ አለው::
1)እንደ አባቶቻችን እኛ ሙተን አንተ ማነህ ሲሉህ አማራ እንደምንለው መሆን ሌላኛው አማራጭ ፈርተህ ፣ተርመጥምጠህ ሸሽተህ አንተ ማነህ ሲሉህ እእእእ እያልክ መኖር

ፋኖ ሞላ ደስዬ❤

የባህል አምባሳደር ሆና ተሾመች!የሸዋን ባህል፣ ቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት በአገር ውስጥና በዓለምአቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ አርቲስት ብሌን ማሞን አምባሳደር አድርጎ መረጠ።
10/09/2022

የባህል አምባሳደር ሆና ተሾመች!

የሸዋን ባህል፣ ቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት በአገር ውስጥና በዓለምአቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅ አርቲስት ብሌን ማሞን አምባሳደር አድርጎ መረጠ።

በነገራችን መሃል…!!"…የመንግሥት አክቲቪስቶች ስለሚያወሩት ተያዘ ተለቀቀ ጉዳይ እኔንም ግራ እየገባኝ ነው። በራያ ግንባር ውጊያው እንደቀጠለ ነው። የሚሞተውና የሚቆስለው ስፍር ቁጥር የለውም...
10/09/2022

በነገራችን መሃል…!!

"…የመንግሥት አክቲቪስቶች ስለሚያወሩት ተያዘ ተለቀቀ ጉዳይ እኔንም ግራ እየገባኝ ነው። በራያ ግንባር ውጊያው እንደቀጠለ ነው። የሚሞተውና የሚቆስለው ስፍር ቁጥር የለውም። ውጊያው ያለው የአላውሀ ወንዝን ተሻግሮ በጉብየና በበላጎ ተራራወች ላይ ነው። ይህ የአላውሀ ወንዝ በላይኛው በኩል ያለው ተራራው በመከላከያ የተያዘ ተራራ ነው።

"…አላማጣ ደረስን፣ መቀሌ ልንገባ ነው የሚሉት ከየት አምጥተው እንደሆነ አልገባኝም። የራያው ግንባር ልክ እንደ ጎንደር እና እንደ ሰቆጣው ግንባር በወታደራዊ ዲሲፒሊን እየተመራ አይደለም። የራያ ህዝብ ሞት ቀለቡ ከሆነና በመንግሥት ከተረሳ ቆየ። የዐቢይ አሕመድ መንግሥት በራያ በኩል ለምን ወደፊት መግፋት እንደማይፈልግ እሱና የሚያመልከው አጋንንቱ ናቸው የሚያውቁት።

"…እውነት ብቻ…!!

ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ በድጋሚ  የፌደራል ፖሊስ መለዮ በለበሱ ፖሊሶች መወሰዷ ተሰማ!ጳጉሜ 02/2014 ዓ.ም (ኢትዮ ሚዲያ) ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ በድጋሚ  የፌደራል ፖሊስ መለዮ በለበሱ ፖሊ...
07/09/2022

ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ በድጋሚ የፌደራል ፖሊስ መለዮ በለበሱ ፖሊሶች መወሰዷ ተሰማ!

ጳጉሜ 02/2014 ዓ.ም (ኢትዮ ሚዲያ) ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ በድጋሚ የፌደራል ፖሊስ መለዮ በለበሱ ፖሊሶች መወሰዷ ተረጋግጧል።

"ሽሮ ሜዳ ገበያ አካባቢ
ሲቪል የለበሰ ሰው መጀመሪያ አነጋገረን፤ መዓዛን እንደሚፈልጋት ሲነግራት ማነህ፣መታወቂያ አለህ በማለት ሲነጋገሩ በመቀጠል ፓትሮል ላይ የነበሩ ከ5 ያላነሱ ፖሊሶች መካከል ሁለቱ ወርደው በመምጣት መዓዛን እንደሚፈልጓት ነገሯት።

የፌደራል ፖሊሶችን እያየሽ ስለሆነ መታወቂያ ማሳየት አይጠበቅብኝም በማለት ፍቃደኛ አልነበረም።

ፖሊሶች ይዘዋት ሲሄዱ የት ነው የምትወስዷት ስላቸው ወደ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ሜክሲኮ ነው የምንወስዳት አንችን አንፈልግሽም" እንዳሏት የሮሃ ጋዜጠኛ እና የስራ ባልደረባዋ ምስራቅ ተፈራ ያረጋገጠች መሆኗንና ሲከታተሏቸው የቆዩ ስለመሆኑ ሁኔታው አመላካች ስለመሆኑም አሚማ ዘግቧል።

14/08/2022

- ኮኔሌል ደመቀ ዘውዱ በቁጣ የተናገረው መግለጫ " አብይን አስቆጣ ከእንግድህ በሗላ የአማራ ህዝብ ባንድራ እየያዘ በየጥርጊያው በየ አስፋልቱ ''ሆይ ሆይ አይልም አያልቅስም

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ2015 በጀት ዓመት 3.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ገለጸየኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በ2015 በጀት ዓመት የያዛቸውን ዕቅዶች ለማስፈጸም 3.2...
20/07/2022

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለ2015 በጀት ዓመት 3.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው ገለጸ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በ2015 በጀት ዓመት የያዛቸውን ዕቅዶች ለማስፈጸም 3.2 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው አስታወቀ። ኮሚሽኑ ከዚህ በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ ለሚያከናውናቸው ተግባራት የሚውል 208.6 ሚሊዮን ብር ከተለያዩ የልማት አጋሮች ለማሰባሰብ ማቀዱንም ገልጿል።

ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ ይህን ያስታወቀው ትላንት ማክሰኞ ሐምሌ 12፤ 2014 ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተባባሪ እና አማካሪ ኮሚቴ ባቀረበው የ2015 በጀት ዓመት ዕቅድ ላይ ነው። በ35 ገጾች የተዘጋጀው የዕቅድ ሰነዱ፤ ኮሚሽኑ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን ቁልፍ ተግባራት፣ በዕቅድ አፈጻጸም ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮች እና መፍትሔዎችን ጨምሮ ሌሎችን ጉዳዩችንም አካትቷል።

በ2015 በተለያዩ ደረጃዎች በተለዩ አጀንዳዎች ላይ ሀገራዊ ምክከር ለማከናወን ያቀደው ኮሚሽኑ፤ ወደዚህ ስራ ከመግባቱ በፊት የኮሚሽኑን ዋና እና ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችን ማደራጀት እንዲሁም የበጀት እና ሀብት አጠቃቀምን የማሳደግ ተግባራትን እንደሚያከናውን በሰነዱ ሰፍሯል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርዓያ፤ በበጀት ዝግጅት ወቅት ለኮሚሽኑ ያስፈልገዋል በሚል ተይዞ የነበረው በጀት 4 ቢሊዮን ብር እንደነበር ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።

ፕ/ር መስፍን “የሀገሪቱን ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት የመጨረሻውን ዝቅተኛ በጀት ነው ያወጣነው” ሲሉ ኮሚሽኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር ሊያቀርበው የተዘጋጀው የበጀት ጥያቄ በርካታ ነገሮችን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነ አስረድተዋል። “ይሄ ገንዘብ ለሀገራዊ ስራ ስለሆነ፤ ያን ያህል የሚያስደነግጥ አይደለም” ሲሉም የበጀት ጥያቄው በገንዘብ ሚኒስቴር ተቀባይነት ያገኛል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።

የራያ ቆቦ ህዝብ ውሀ ለመቅዳት የሚሰቃየው ስቃይ ••• ራያ ቆቦ 45 ቀበሌወች እና 1ከተማ አስተዳደር ያካተተ ሲሆን ለአንድ አመት ሙሉ መብራትና ውሀ ባለመኖሩ ለከፋ ችግር ተጋልጯል። ወቅቱ ...
20/07/2022

የራያ ቆቦ ህዝብ ውሀ ለመቅዳት የሚሰቃየው ስቃይ •••
ራያ ቆቦ 45 ቀበሌወች እና 1ከተማ አስተዳደር ያካተተ ሲሆን ለአንድ አመት ሙሉ መብራትና ውሀ ባለመኖሩ ለከፋ ችግር ተጋልጯል። ወቅቱ ክረምት ስለሆነ የተጣራ የምንጭ ውሀ ማግኘት ስለማይቻል ከውሀ ብክለት ጋ የተያያዘ የጤና ችግር እንዳይገጥም ተፈርቷል።

"ኦነግ ሸኔ አንድ እግሩን አዲስ አበባ፣ አንድ እግሩን ወለጋ የተከለ ነው።" - አቶ ማሙሸት አማረኦነግ ሸኔ የፌደራሉንና የክልሉን መንግስታዊ መዋቅር የተቆጣጠረ ነው። ገዥው ፓርቲ በክልሉ ባ...
13/07/2022

"ኦነግ ሸኔ አንድ እግሩን አዲስ አበባ፣ አንድ እግሩን ወለጋ የተከለ ነው።" - አቶ ማሙሸት አማረ

ኦነግ ሸኔ የፌደራሉንና የክልሉን መንግስታዊ መዋቅር የተቆጣጠረ ነው። ገዥው ፓርቲ በክልሉ ባሉ መዋቅር የሽብር ቡድኑን በመደገፍ የዘር ፍጅቱ አገር አቀፍም ሆነ አለም አቀፋዊ ትኩረት እንዳያገኝ በማዘናጋት፣ አጀንዳ በማስቀየር፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ራሱን የሚከላከልበት ሁኔታን በመንፈግ ለጥቃት እንዲጋለጥ በማድረግ ለተፈፀመው ወንጀል ሁሉ ተጠያቂ ነው። የመንግስት ሚዲያዎች ወይ ከሽብር ቡድኑ ጎን ይቆማሉ፣ ወይ የዘር ፍጅቱን እንዳላዬ ያልፉታል።

በአጭሩ ኦነግ ሸኔ የአማራን ዘር ያጠፋል፣ መንግስት መዋቅራዊ ድጋፍ ያደርግለታል፣ የመንግስት ሚዲያዎች ወንጀሉ ትኩረት እንዳያገኝ ይሸፋፍናሉ።

ታሪክን የኋሊትወያኔ 1980ዎቹ  ወደ ስልጣን ሲመጣ ወለጋ ያለው አማራን ከወለጋ ለማስወጣት ማሣድድ ሲጀምር ሼህ ጂብሪልና ሸህ ያሢን የተባሉ አማርኛ ተናጋሪ ሙስሊሞችን በአሰቃቂ የገደለ ነበር...
10/07/2022

ታሪክን የኋሊት

ወያኔ 1980ዎቹ ወደ ስልጣን ሲመጣ ወለጋ ያለው አማራን ከወለጋ ለማስወጣት ማሣድድ ሲጀምር ሼህ ጂብሪልና ሸህ ያሢን የተባሉ አማርኛ ተናጋሪ ሙስሊሞችን በአሰቃቂ የገደለ ነበር። ያኔ ታዲያ አገዳደሉ ልክ እንደዛሬው ነበር ጭካኔው። ሸህ ጂብሪልን በብረት ምጣት አግሎ ከነ ነብሱ ጠብሰው ነበር የተገደሉት።

ዛሬ ደግሞ ለናሙና ያክል አንድ ምሣሌ ላንሣ

ስለ ኡስታዝ አረቡ ያሢን(1980ቹ በኦነግ የተገደሉት የሸህ ያሢን ልጅ)
በሆሮ ጉዱሩ ከላይ ስማቸው የጠቀስኳቸው የሸህ ያሢን ልጅ የሆኑትና ጃርደጋ ከተማ ኢማምና የዳዕዋ ዘርፍ አላፊ በመሆን እንደ ጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ ኦርቶዶክሱም ሙስሊሙም ፔንጤውምጋ እጅግ በጣም ተቀባይነት ያላቸውና በሰላምና መረጋጋት ስራ ዘርፍ ላይ እጅግ በጣም ለውጥ ሲያመጡ የነበሩ ህዝቡን አማራ ኦሮሞ ሙስሊም ክርስቲያን ሣይሉ ብልፅግና ፓርቲ ለመረጠው ህዝብ ሊያመጣው ያልቻለውን ሰላም እሳቸው ግን በቀላል መንገድ ህዝቡን በማነጋገር በትልቅ ተቀይነት ሰላም ማምጣት የቻሉ ቢሆንም የነፍጠኛ ደጋፊ ተብለው በኦነግ መራሹ ብልፅግና ታስሮ የተፈታ ቢሆንም አሁንም ላይ የጫካው ኦነግና ኦነግ መራሹ መንግስት እየታገሉ አማራው ህዝባቸው ጋር ተሳደዋል።
ብልፅግና ተደጋጋሚ ቃታ ስቦባቸዋል። ኦነግ ሸኔ በዋናነት አተኩሮባቸዋል።

ታዲያ የለውጡ መንግስት መጣ በተባለበት መጀመሪያ አከባቢ 2011-2012 ቁጥራቸው በወጉ ያልተነገረላቸው ያልተዘገበላቸው አማሮች እንዳለቁ ለማስታወስ እወዳለሁ። ሲጀመር ግን ወለጋ ላይ ኢንርኔት ባለመኖሩ ግፉ ቀማሹ ወገኔ ከወላጆቼ ጨምሮ 10% ተዘግቧል ለማለት ይቸግራኛል።

ጥያቄ አለኝ በተለይ ለሙስሊሞች

1. ለአህመዲን ጀበል የት አለ መግለጫው?? የት አለ ስለፉ?? የወለጋ ሙስሊሞች ከጎናቹህ ነን በሉና። ለምን እንደማትሉን ሚስጥሩ ገብቶናል። ራያ አባ ማጫ ፋኖ ነው ስላለ እናንተም ከአንድ ምንጭ ስለምትቀዱ ነው!!!
2. ሙጂብ አሚኑ የት አለ መፈክሩ ሸኔ አሸባሪ በሉሃ ስልፍ ጥሩ እስኪ አሳዩን?
3. የአዲስ አበባ ወጣት መስቀል አዳባባይ ካልተሰበስብን ተብሎ ስልፍ አንደተቀወጠው መውጫ መግቢያ አተን ወገን ሣያቅልን በየዱሩ ለምንታረደው ሲሆን ምነው ፀጥ አላቹሁ?????

እኛ ወለጎች ከዚህ የምንረዳው የጎንደሩ ስልፍ አላማው ለሌላ አላማ ነበር ማለት እንችላለን።
አንዳንዶች አማራነትን ኦርቶዶክስነት በማስመሰል አማራነትን ሲያወግዙ አይተን ታዝበናል።
ያለማሽሟጠጥ ጨፍጫፊውን ስም ሳይጠሩ ከተጠያቀቂነት ለመዳን ብቻ ሲፅፉ አይተን ታዝበናል።
አማራነትን ወይስ ባለጌነትን ነው የጠላቹት???

ማሣሰቢያ
ወድ የአማራ ሙስሊምና ኦርቶዶክስ
በያለህበት የሁሉም ገፈት ቅማሽና ሟች እኔና እናንተ እንደመሆናችን ነቅተን በአንደነት ልንቆም ይገባናል። የመጨረሻው የአማራነት ሩም ውስጥ እንገኛለን። አንድ መሆን አቅቶን ከዚህ ካስወጡን አማራ ብሎ ብሔር የለም የሚሉት ጠላቶቻችን ይበታትኑንናል ለየብቻ እንታረዳታለን። ከመሆኑ በፊት አብረን እንስራ

አማራነት ይለመልማል
ኢትዮጲያዊነት ይቀጥላል

ከሞሃመድ እንድሪስ
ከወለጋ

Address

AA
Addis Ababa
10000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ETHIO MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ETHIO MEDIA:

Share