06/07/2022
እናም የረሱልን አደራ ችላ ያልን በሚመስል መልኩ ሶላትን ዘንግተናል። የረሱል አደራ ምን ነበር? ይህን ሁላችሁም የምታዉቁትን ታሪኽ ላጋራችሁ፦
በነብዩ (ሰዐወ) ላይ ሕመም ይጠናባቸው ጀመር። ዓኢሻ (ረዐ) ቤት ሆነው ታስታምማቸው ዘንድ እንዲፈቅዱላቸው ሚስቶቻቸውን ሁሉ አስፈቀዱ። ፈቀዱላቸውም።
የመጨረሻዎቹ ሰዐታት ሲደርሱ ሶሀቦች ሁሉ በነብዩ(ሰዐወ) መስጂድ ተሰባስበው ክፍ ባለ ድምፅ ያጉረመርሙ ጀመር።ረሱል(ሰዐወ) ድምፅቸውን ሰምተው ምን እንደሆኑ ሲጠይቁ። በርሳቸው ተረብሸው እንደሆነ ተነገራቸው።
ረሱልም (ሰዐወ) “ተሽክማቹ ያሉበት ውሰዱኝ” አሉ። እንደደረሱም ሶሀቦች እንዲህ አሏቸው “እናተ ሰዎች ሆይ! የኔ ሁኔታ አስፈርቷችኃልን?? ሶሀቦችም “አዎን አንቱ የአላህ መልዕክተኛ” በማለት መለሱላቸው እርሳቸውም እንደሚከተለው አሏቸው። “እናንተ ሰዎች ሆይ! የእኔና የእናንተ የቀጠሮ ቦታ ዱኒያ አይደለችም።ቀጠሮችን ሀውድ ዘንድ ነው።ከዚሁ ሆኜ ያየሁት ይመስለኛል።እናተ ሰዎች ሆይ የሶላት ነገርን አደራ፦ አሏህን ፈርታቹ ሴቶቻችሁን ጠብቁ። እናንተ ሰዎች ሆይ! ድህነት ያገናችኃል ብዬ አልፈራም።ይልቁንም በኃብት ትጥለቀለቁና ስትፎካከሩ ያለፉት ህዝቦች እንደጠፉት ሁሉ እናንተም ሀብት ያጠፋችኃል ብዬ እፈራላችኃለው።”
“እነንተ ሰዎች ሆይ! አላህ ባሪያውን ከዚህ አለምና እርሱ ጋር ከመገናኘት የትኛውን እንደሚመርጥ አማረጠው።ባሪያውም በአሏህህ ጋር መገናኘትን መረጠ።” ሶሀቦች ንግግራቸውን ጸጥ ረጭ ብለው ያዳምጡ ነበር።•••
ይልቅስ የገበያና የአውራ ጎዳናዎች፣ የመጓጓዣና የንግድ ማዕከላት ጭርታ ሳይሆን አስፈሪው ጭርታ የመስጂድ ጭርታ ነው። ምን ነበር የረሱል የመጨረሻ ቃል?
«ሶላታችሁን አደራ!!!»
▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የቴሌግራም ቻናል-
You can view and join right away.