ET ART MEDIA - ኢቲ አርት ሚዲያ

ET ART MEDIA - ኢቲ አርት ሚዲያ ኢቲ አርት ሚዲያ የተዋሕዶ ልሳን

ለመስቀል በዓል መግቢያ ባጅ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ፡፡በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተመጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ የመስቀል በዓል መግቢያ ባጅ...
17/09/2025

ለመስቀል በዓል መግቢያ ባጅ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተመጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ የመስቀል በዓል መግቢያ ባጅ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እያዘጋጀ መሆኑን ገለጸ፡፡
መስከረም ፯ ቀን ፳፻፲፷ ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ የሙዚየም ዝግጅትና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ዋና ክፍል ለመስቀል በዓል መግቢያ ባጅ በዲጂታል ቴክኖሎጂ እያዘጋጀ መሆኑን ገልጿል፡፡
የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሶፍት ዌር ኢንጂነሮቹ እንደ እንደ ገለጹት “እንደ ቤተክርስቲያን ልጅነታችን መሥራት የሚገባንን ለማገዝ ነው የሚመጣነው የትኛውም መሥሪያ ቤት ሥራን ለማቅለል ዘመኑ በደረሰበት ዘመናዊ ዲጂታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ ሥራን ለማቅለል እየተሠራ ነው፡፡ ብለዋል፡፡
“ዛሬ ይዘን የቀረብነው ዲጂታል መፍትሔ የቤተክርስቲያን ባጅ ማኔጅመንት ለመሥራት ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በወረቀት፣ በእጅ በመጻፍ በብዙ ድካም ሲሰራ የነበረውን ሥራ ዘመኑ በደረሰበት የቴክኖሎጂ በታገዘ መልኩ ለማቅለል በቴክኖሎጂ እየሠራን ነው ሲል ኢንጂነር በቀለ ዴቢሴ ገልጿል፡፡” ባለሙያውም አክሎ ይህ ሲስተም ሁለት ነገሮችን ያቀላል የመጀመሪያው በጣም አድካሚና ጊዜ የሚፈጅ የነበረውን የወረቀት ሥራን ያቀላል፤ ሁለተኛው ተጠያቀነት ባለበት መልኩ ባጁን መቆጣጠር ይቻላል በማለት ያስረዳል፡፡
ኢንጂነር ጳውሎስ ታደሰም እንደገለጸው “ቀድሞ ይዘጋጅ የነበረው ባጅ ሴሪያል ቁጥር ብቻ ያለው ነበር፤ ባጁ ምንም እንኳ ከጀርባው ማኅተም ቢኖረውም ማንም ሰው ከለር ፕሪንተር ያለው አመሳስሎ ፕሪንት አድርጎ መግባት ይቻላል፤ አሁን ግን ኪው አር ኮድ (QR Code) ስላለው በሞባይል አፕሊኬሽን ስካን በማድረግ ባጁን መለየት ይቻላል፤ ተመሳሳይ ፕሪንት አድርጎ የሚመጣው ሰው መግባት አይችልም ሲስተሙ ያጋልጣል፡፡ በመግቢያው በር ላይም ይህን ቼክ የሚያደርጉ አሉ” ብሏል፡፡
ሁለቱም ባለሙያዎች እንደተናገሩት እንደ ቤተክርስቲያን ልጅነታችን ዛሬ የተጀመረው ሲስተም እንደ ማስጀመሪያ ትልቅ ነገር ነው በደረስንበት የሙያ ዘርፍ ቤተክርስቲያን ማገልገል፣ የቤተክርስቲያን ሥራ መማቀላጠፍ ከሁላችንም ይጠበቃል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም የቅርስ ጥበቃ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር መምሪያ ዋና ኃላፊ በኩረ ትጉኃን ቀሲስ ምትኩ ከንቲባ ባስተላለፉት መልእክት ባጁ በዘመናዊ ዲጂታል የተዘጋጀ ቴክኖሎጂ የሚቆጣጠረው ስለሆነ ለበዓሉ የሚመጡ ታዳሚዎችም ባጁን በጥንቃቄ ሊይዙት ይገባል ሲሉ መልእክተቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ዘገባዉ የEOTC TV ነው

17/09/2025
12/09/2025

እንኳን አደረሳችሁ
መልካም አዲስ አመት
ዲኮ ሪል ስቴት
ሰሚት ሰባ ሁለት ሳይት ከልዩ ቅናሽ ጋር
0910727516 , 0995010101 , 0941577777

https://youtu.be/TPPwkXg28Bs
12/09/2025

https://youtu.be/TPPwkXg28Bs

የንሰሃ እድሜ ሲሰጠን ሰይጣንም ደስ ይለዋል..እኔ የምችል አይደለዉም አንተ ወደራስህ መልሰኝ ወኖቻችን ዲ/ን እያሱ ከምንያህል ጋርበተጨማሪም በነዚህ ማህበራዊ ሚዲያዎች ይከተሉንFacebook: h...

11/09/2025

እንኳን አደረሳችሁ መልካም አዲስ አመት ዲኮ ሪል ስቴት ሰሚት ሰባሁለት ሳይት ከልዩ ቅናሽ ጋር 0910727516 , 0995010101 , 0941577777

11/09/2025

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ 2018 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ

እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሠላም አሸጋገረን
10/09/2025

እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሠላም አሸጋገረን

09/09/2025

እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሠላም አሸጋገረን!

የዘመን መለዎጫውን ምክንያት በማድረግ በአቃቂ ቃሊቲ ለምትገኘው ታሪካዊቷ ፈንታ ፈለገ ብርሃን ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ በዓለወልድ ቤተ ክርስቲያን የቦታ እዳ ለመክፈልና ህንፃ ቤተክርስቲያኗን ገንብቶ ለትውልድ ለማሻገር በሚደረገው ከፍተኛ ርብርብ የበኩልዎን ያበርክቱ።

ቅድስት ድንግል ማርያም የአዲስ አመት እቅዳችሁን ታሳካላችሁ።

የደብሩ የባንክ አካውንትቶች

ንግድ ባንክ 1000514325198
አባይ ባንክ 9282111062436614

አድራሻ አቃቂ ቃሊቲ ጥሩነሽ ቤጅንግ ሆስፒታል ጀርባ

09-13-98-54-01
09-12-81-94-85
09-12-08-15-17

በኃይልህ ሠለም በጌጠኛ ቤትህም ልማት ይሁን። መዝሙር 121 (22)፥ቁ7

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ የደስታ መግለጫ መልዕክት አስተላለፉ።የቅዱስነታቸው መልእክት የሚከተለው ነው።በስመ አብ ወወልድ ወመንፈ...
09/09/2025

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ የደስታ መግለጫ መልዕክት አስተላለፉ።
የቅዱስነታቸው መልእክት የሚከተለው ነው።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ወስሙ ለካልእ ፈለገ ግዮን ወውእቱ ዘየዐውድ ኵሎ ምድረ ኢትዮጵያ፦
"የሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው፤ እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል " (ዘፍ 2+13)

ኢትዮጵያ የሚለው ስም ጽርዓዊ፣ ደኃራዊ ስም ሲሆን ቀደም ሲል የኖኅ የልጅ ልጅ በሆነው በኵሽ ምክንያት የኵሽ ምድር እንዲሁም ምድረ አዜብ፣ ምድረ ሳባ፣ ምድር ኣግዐዚት በመባል ተጠርታለች፡፡ ለዘመናት ኢትዮጵያን ቋሚ አድርገው ካቆዩ ዐምዶች መካከልም ፈለገ ግዮን የተባለው የዓባይ ወንዝ እና ‹‹ኢትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ኀበ እግዚአብሔር- ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች›› (መዝ. 67÷31) የሚለው የተስፋ ቃል እንደሆነ የታመነ ነው፡፡ በመሆኑም በመግቢያችን ላይ ባነሳነው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የኢትዮጵያ ትእምርት ተደርጎ የተጠቀሰው ፈለገ ግዮን በእኛ ዘመን ለሕዝቡ ብርሃን እያበራ አገልግሎት መስጠት የሚችልበት ሁኔታ ተፈጥሮ በማስከተልም የዛሬዋን ቀን በመናፈቅ የግድቡ ግንባታ ከተጀመረበት ዕለት አንስቶ አቅማችሁ የፈቀደውን ሁሉ ለዚህ ሥራ በማዋጣት ታሪክ በመልካም የሚያስታውሰውን ዋጋ የከፈላችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ልጆቻችንን እንኳን ደስ አላችሁ! ለማለት እንወዳለን፡፡

በመጨረሻም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ወደቀጣይ የልማት ሥራ የሚያሸጋግር እንዲሆን፤ ከምንም በላይ _ ሰላም በምድራችን ላይ እንዲስፍን ሕዝባችንም እግዚአብሔር የሰጠው በነፃነት የመኖር መብት ተከብሮለት የልማቱን በረከት መሳተፍ እንዲችል ሁሉም ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በትኩረት ሊሠሩ ይገባል ስንል አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም.

09/09/2025

ልዩ የበዓል ዝግጅት ለአዲስ ዓመት ይተብቁን
ምርት እና አገልግሎትዎን ለማስተዋወቅ
09-38-60-61-62 ይደዉሉ
መልካም አዲስ አመት

ዛሬ ጷጉሜ 2 ከሚሊኒየም አዳራሽ ለባሌ ጎባ አቡነ ተክለሃይማኖት ልዩ መርሐግብር
07/09/2025

ዛሬ ጷጉሜ 2 ከሚሊኒየም አዳራሽ ለባሌ ጎባ አቡነ ተክለሃይማኖት ልዩ መርሐግብር

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ET ART MEDIA - ኢቲ አርት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ET ART MEDIA - ኢቲ አርት ሚዲያ:

Share