Orthodox Media

Orthodox Media Dhugaan Dhugaadha sobaan hin madaalamu. Namni Afaan dhaloota isaatin haa baratuun Galma keenya, Sirna uumamaan hunda jabeeffanna.

የጸሎት መጀመሪያ***"ከዓመፀኛ ከንፈር ከሸንጋይም አንደበት፥ አቤቱ፥ ነፍሴን አድናት።" (መዝ. 119/120፥2)***ከእግዚአብሔር ፊት ስንቆም ቀድመን ስለምን እንጸልያለን? ብለን እንጠይቃለ...
22/09/2025

የጸሎት መጀመሪያ
***
"ከዓመፀኛ ከንፈር ከሸንጋይም አንደበት፥ አቤቱ፥ ነፍሴን አድናት።" (መዝ. 119/120፥2)
***
ከእግዚአብሔር ፊት ስንቆም ቀድመን ስለምን እንጸልያለን? ብለን እንጠይቃለን። በርግጥ መንፈሳዊ ሕይወት በደረቅ ፎርሙላ አይመራም። ነገር ግን ከእግዚአብሔር ፊት ስንቀርብ ቀድመን ልናስበው የሚገባን ነገር አለ፦ እግዚአብሔርን በሽንገላ ኅሊና እና አንደበት እንዳንቀርበው። እግዚአብሔር ሽንገላን ይጸየፋልና። ሽንገላ ማለትም ያልሆኑትም መስሎ መታየት፣ የማያምኑትን እንደሚያምኑ ሆኖ ለማሳየት መሞከር፣ ከልብ ያልሆነ ምስጋና እና ውዳሴን ማቅረብ ነው። ወዳጄ በእግዚአብሔር ፊት ከልብህ ያልሆነ ነገርን ይዘህ ከምትቀርብ ዝም ብለህ አንገትህን ዝቅ አድርገህ በብዙ ድካምህ የተነሣ ከእግዚአብሔር ፊት ለመቆም የማትችል ነገር ግን ከእግዚአብሔር ቸርነት እና ትእግስት የተነሣ በፊቱ የቆምህ መሆኑን አውቀህ "ኃጢአተኛ መሆኔን በጥቂቱ አውቃለሁ፤ በሚገባ እንዳውቅ ደግሞ አንተ ግለጥልኝ፤ በፊትህ ያልሆንኩትን መስዬ እልዳልቆም፣ አንተንም እንዳልሸነግልህ ስለራሴም ስለአንተም እውነቱን የማውቅበትን ቅን ኅሊና ስጠኝ፤ አርነትን የሚያወጣ እውነትህን ግለጥልኝ" ብሎ መለመን ይሻላል። ከዚያ ቀጥሎ ለተደረገልን መልካም ነገር ሁሉ አመስግነን የምንፈልገውን ሳይሆን የሚያስፈልገንን ይሰጠን ዘንድ እንደ አባት መጠየቅ ይገባል። ከሽንገላ አንደበት ከወጣን እግዚአብሔር በድካማችን ይረዳናል፤ ኃይል የእርሱ ነውና። በግርጥም ከሽንገላ አንደበት የሚያድነንም እርሱ ነው፤ ክቡር ዳዊት ""ከዓመፀኛ ከንፈር ከሸንጋይም አንደበት፥ አቤቱ፥ ነፍሴን አድናት፤" እንዳለ። (መዝ. 119/120፥2)"

ዜና እረፍትበሐረር ጥንተ አድባራት ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና በደብረ አድዕኖ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ዲያቆናት እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ሲያገለግሉ የነ...
22/09/2025

ዜና እረፍት
በሐረር ጥንተ አድባራት ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና በደብረ አድዕኖ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ዲያቆናት እንዲሁም በሰንበት ትምህርት ቤት ሲያገለግሉ የነበሩት
ዲ/ን ዮሐንስ ማማሩ እና
ዲ/ን በአምላክ አለምአየሁ
በትናንትናው ዕለት በተፈጠረ አደጋ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
አምላከ ቅዱሳን ነፍሳቸውን በቅዱሳኑ እቅፍ ያኑርልን።
ለወላጅ ዘመዶቻቸው ፣ለቤተሰብ እንዲሁም ለአገለገሉበት ደብር አገልጋዮች በሙሉ መጽናናትን እንመኛለን።

ኦርቶዶክሳዊ ሰነልቦና ከሌለክ እንደዚህ መሸከሙ አይገባክም   የሚመስልክ ለኦርቶዶክሳዊው ግን መሰቀል ማለት ....📌 ለሌሎች የሚያውጀው ወንጌሉ ነው📌 ከሌሎች ተለይቶ የክርስቶስ መሆኑ የሚያሳ...
22/09/2025

ኦርቶዶክሳዊ ሰነልቦና ከሌለክ እንደዚህ መሸከሙ አይገባክም የሚመስልክ ለኦርቶዶክሳዊው ግን መሰቀል ማለት ....
📌 ለሌሎች የሚያውጀው ወንጌሉ ነው
📌 ከሌሎች ተለይቶ የክርስቶስ መሆኑ የሚያሳይበት ማዕተብ ነው
📌 ጠላትን ረግጦ የሚገዛበት ምልክቱ ነው።
📌 ለዓለም ሰላምን የሚያውጅበት ዓርማው ነው ።

ሊቃውንትና ምሁራን የሚሳተፉበት ሕዝባዊ ሲኖዶስ እንዲቋቋም ጠየቁ“አባቶቼ ጳጳሳት፣ ሲኖዶሳዊ ጉባኤያችሁን ፍትሕ የማትሰጡበት ከኾነና ከማኅበረ ምእመናን ጋራ መገናኘታችሁ እየተቋረጠ ከሔደ፣ ስለ...
22/09/2025

ሊቃውንትና ምሁራን የሚሳተፉበት ሕዝባዊ ሲኖዶስ እንዲቋቋም ጠየቁ
“አባቶቼ ጳጳሳት፣ ሲኖዶሳዊ ጉባኤያችሁን ፍትሕ የማትሰጡበት ከኾነና ከማኅበረ ምእመናን ጋራ መገናኘታችሁ እየተቋረጠ ከሔደ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያንና ስለ ሀገር አንድነት ሲባል ሕዝባዊ ሲኖዶስ ሊቋቋም ይገባል!” - ዶ/ር ዘሪሁን ሙላቱ
˜˜˜˜˜˜˜
ዐበይት ነጥቦች፡-
• ቅዱስ ሲኖዶስ፣ መንፈስ ቅዱስ የሚመራው ሳይኾን የግለሰቦች ፍላጎትና ጥቅም የሚዘውረው ከኾነ እግዚአብሔር ስለማይደሰትበት፣ ልዕልናው እና ቅድስናው አጠያያቂ ይኾናል፤
• ይህን አሠራር እግዚአብሔር ስለማይደሰትበት፣ ቡራኬውን ወደ እርግማን ይቀይረዋል፤እናስተምር ቢሉ አእምሮውን ጥበቡን ይነሳቸዋል፤ ጩኸታቸውንም የማይሰማቸው ይኾናሉ፤
• ምእመኑን በትውልዱና በጎሣው ምክንያት እየለዩ ጭፍን ጥላቻ የሚያንጸባርቁና ከሕግ አግባብ ውጭ የኾኑ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትን ማየት ብርቃችን አይደለም፤
• ገንዘብና ዘመድ የሌላቸው ሊቃውንትና ካህናት፣ ፍትሕን ፍለጋ የሚንገላቱት የተለየ በደል ፈጽመው ሳይኾን፣ ከጎሣና ጥቅም የጸዳ አባትና ሲኖዶሳዊ አካል ስላጡ ብቻ ነው፤
• “እኛና መንፈስ ቅዱስ ፈቅደናል”የሚለውን የሐዋርያትን የጉባኤ ቃል ለይምሰል እየጠቀሱ በዋጋ የሚያስተምሩ አባቶችን መመልከታችን የትንቢቱ ፍጻሜ ላይ መድረሳችንን ያረጋግጣል፤
• “የአ/አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ ለሠራተኛ ቅጥር 400ሺሕ ብር ጉቦ መቀበሉ ታወቀ” ሲባል፣ ያሰናብቱታል ወይም አግደው ጉዳዩን ያጣሩታል ብለን ገምተን ነበር፤ ለካ ሰውዬው ጎይትኦም እንጂ ዘሪሁን ባለመኾኑ ግምታችን ሳይሳካ ቀርቷል፤
• ይህ፣ ከማንነትህ ጋራ ተያይዞ የሚመጣብህ ዕዳ ነው፤ እንደ ሥራ አስኪያጁ ዓይነት ስምና ማንነት ሲኖርህ፣ በአባ ሆይ ችሎት ዘንድ ያለመከሠስ ጸጋ እንዳለህ ያመላክታል፤
• የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ፣ በዓለማዊ ፍርድ ቤትና ገዢዎች ዘንድ እንዲያዝ ማድረግ፣ ከጳጳሳቱ ጉባኤ፣ ከቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ይጠበቃልን?
†††
• ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ለግፉዓን ፍትሕ አለመስጠቱ፣ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየመጣ ያለውን ተቋማዊ ክስረት ማሳያ እንደኾነ ልንረዳው ይገባል!!
• “ክርስቶስ አማላጅ ነው” የሚል መጽሐፍ የጻፈና የሚያስተምር መምህር በመንፈሳዊ ኮሌጅ መቀጠሩን እያወቃችሁ ዝም ያላችሁት ግለሰባዊ አካሔድ ላይ ስለምታተኩሩ ነው፤
• ስለተሾሙለት ሕዝብ ሳይኾን ባሕር ማዶ ለመሻገር የምረጡኝ ዘመቻ በአሁኑ የጳጳሳቱ ጉባኤ የተሰማ አይደለምን? ሓላፊነት እየደራረቡ ሁለት ሦስት ደመወዝ መውሰድስ የጽድቅ ነው?
• የምእመናን አቤቱታ እንዳይሰማ፣ “የአባ እገሌ ልዩ ሀገረ ስብከት ነው፤” እየተባለ አህጉረ ስብከት ከሲኖዶሳዊ አሠራር ውጭ ኾነው በጳጳሳቱ ይኹንታ ብቻ የሚተዳደሩበትስ ቀኖና አለን?
• ከዓመት እስከ ዓመት የሚንከባለሉ ችግሮችን ማየታችን፣ ሲኖዶሱ ፍትሕን ለመስጠት ያለውን ልዕልና በግለሰቦች ፍላጎት ሥር እንዳዋለው ሊያስረዳን ይችላል፡፡
• ይህ ከሚያስከትለው አደጋ አንዱ፣ የቤተ ክርስቲያን በዓለማዊ ፍ/ቤት መዳኘትና ምእመናን እየተፈራረሙና እያስወሰኑ በቦርድ እንድትመራ ማድረግ መኾኑ ሩቅ አይመስልም፡፡
• በቤተ ክርስቲያን ችግሮች ውሳኔ የማትሰጡ ከኾነ እናንተ እነማን ናችሁ? የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የማያሳስባችሁ ከኾነና ከምእመናን ጋራ የምትገናኙበት መንገድ እየተቋረጠ ከሔደ…
• …ማኅበረ ምእመናኑ ያመኑበት፣ ለአመራሩና ውሳኔው የሚገዙለት፣ ይኹንታና ውክልና የሰጣቸው ሊቃውንትና ምሁራን የሚሳተፉበት ሕዝባዊ ሲኖዶስ ሊቋቋም ይገባል፡፡
†††
“ሕዝባዊ ሲኖዶስ ሊቋቋም ይገባል”
ዶ/ር ዘሪሁን ሙላቱ
(የጥንታውያን ቋንቋዎችና ጽሑፎች ተመራማሪ)
(ግዮን መጽሔት፤ ቅጽ ፩ ቁጥር ፮፤ ግንቦት ፳፻፲ ዓ.ም.)
ቅዱስ ሲኖዶስ ማለት የተቀደሰ ጉባኤ ማለት ነው፡፡ በፍትሐ ነገሥቱ እንደተደነገገው፣ ሲኖዶስ ማለት ቃሉ የግሪክ ሲኾን፣ ትርጉሙም የጳጳሳትና የሊቃውንት ማኅበር ወይም ሸንጎ ወይም ስብሰባ አልያም ጉባኤ ማለት ነው:: በዓመት ሁለት ጊዜ የሚካሔደው የጳጳሳት ጉባኤ መጠርያም ነው፡፡
ይህ ጉባኤ ታሪካዊ አመጣጡ ከዘመነ ብሉይ ጀምሮ ያለ ሲኾን፣ ከጥንት ጀምሮ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ እንከን የለሽ ውሳኔ የሚተላለፍበት፤ ሁሉን በእኩልነት የሚያይ ጉባኤ ነው፡፡ ኾኖም በቅዱስ ሲኖዶስ ስም እንደ ዓለማውያኑ ሸንጎ፣ የሐሰትና የቡድን ውሳኔ የሚተላለፍበት፣ መንፈስ ቅዱስ የሚመራው ሳይኾን የግለሰቦች ፍላጎትና ጥቅም የሚዘውረው ከኾነ እግዚአብሔር ስለማይደሰትበት ልዕልናውና ቅድስናው አጠያያቂ ይኾናል፡፡
በትንቢተ አሞጽ መጽሐፍ ላይ እንደተጠቀሰው፣ እስራኤላውያን እንደዚህ ዓይነት ቅዱስ ጉባኤ በመረጡት ቀን ያደርጉና “እግዚአብሔር ተናገረ፤ ፍርድንም ሰጠ” ብለው ያውጁ ነበር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በመንፈሳዊ አቋማቸውና በቅዱስ ሲኖዶሳቸው ስም የሚያካሒዱት ሃይማኖታዊ ያሉትን ተግባራትና ውሳኔአቸውን ተቃውሟቸዋል፡፡ ይልቁንም፣ በእግዚአብሔር ቀን የእግዚአብሔር ፍርድ እያሉ የሚመኩበትን ቅዱስ ጉባኤን በተመለከተ፣ “የተቀደሰው ጉባኤአችሁ ደስ አያሰኘኝም” በማለት ቃል በቃል ገሥጾአቸዋል፤ የጉባኤያቸውንም ውሳኔ እስከነድርጊቱ ነቅፎታል፤ ይልቁንም ፍትሕን እስካለመጡና የተበደለን እስካልካሱ ድረስ መሥዋዕታቸውን፣ ዝማሬአቸውንና ቊርባናቸውን እንደማይቀበለው አስታውቋቸዋል፡፡
ይህ ዓይነቱን ሲኖዶሳዊ አሠራር እግዚአብሔር አይደሰትበትም፡፡ በእንዲህ ዓይነቱ ቅዱስ በተባለው ጉባኤ፣ ጉቡዓን የሃይማኖት መሪዎች ቢባርኩ፣ እግዚአብሔር ቡራኬያቸውን ወደ እርግማን ይቀይረዋል፤ ቅዳሴያቸውን እግዚአብሔር አይቀበለውም፤ ወንጌል እናስተምር ቢሉ አእምሮውን ጥበቡን ይነሳቸዋል፤ እንዘምር፣ ማሕሌት እንቁም ቢሉ፣ ይጮኻሉ ይጮኻሉ፤ እንዳልጮኹ ኾነው እግዚአብሔር የማይሰማቸው ይኾናሉ፡፡
ዛሬ በብሔር ማንነቱ፣ በትውልድ ስፍራው፣ በጎሣ መሠረቱ ምክንያት ምእመኑን እየለዩ ጭፍን ጥላቻ የሚያንጸባርቁና በማን አለብኝነት ከሕግ አግባብ ውጭ የኾኑ የሃይማኖት መሪዎችና የሲኖዶስ አባላት የኾኑትን እነአቡኑን የዚህ ጉባኤ አባል ኾነው ማየት ብርቃችን አይደለም፡፡ በየፍርድ ቤቱ ፍትሕ ፈልገው የሚንገላቱት የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና ገንዘብና ዘመድ የሌላቸው ካህናት ከሌላው የተለየ በደል ሠርተው አይደለም፤ በየሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች የሚመላለሱበት ምክንያታቸው የፓትርያርኩን አባትነት ጠልተውም አልነበረም፤ እንደ ሃይማኖታቸውም የጳጳሳቱን አባትነትና ቡራኬ ሳይፈልጉት ቀርተው አይደለም፤ ነገር ግን ከጎሣና ከጥቅማጥቅም በጸዳ መልኩ ፍትሕ የሚሰጣቸው አባት ወይም የበላይ ሲኖዶሳዊ አካል ስላጡ ብቻ ነው፡፡
ይኸውም ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ ኾነ፡፡ በእግዚአብሔር ጉባኤ ውስጥ ተሰብስበው በዋጋ በሚሠሩ፣ የሃይማኖት መሪዎቻችን ምክንያት፣ የምእመናን መጠጊያ የኾነችው ቤተ ክርስቲያን በኑፋቄ፣ በሙስና እና በጎሠኝነት ልትታመስና በኢየሩሳሌም አምሳል የምትታወቀው የእግዚአብሔር ሀገር ኢትዮጵያም የድንጋይ ክምር ልትኾን እንደምትችል በትንቢተ ሚክያስ ተጽፏል፡፡ ይህም የትንቢት ፍጻሜ እየኾነ ያለው፣ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋራ ነው፤ እኛና መንፈስ ቅዱስ ፈቅደናል” የሚለውን የሐዋርያትን የጉባኤ ቃል ለይምሰል እየጠቀሱ ነገር ግን ማንነታቸውን ለዋጋ የሰጡ፣ በጉቦ የሚፈርዱ በዋጋ የሚያስተምሩ የሃይማኖት አባቶችን መመልከታችን የትንቢቱ ፍጻሜ ላይ መድረሳችንን ያረጋግጣል፡፡
ምንጊዜም ጸላኤ ሠናይ ውክልናውን የሚያሳየው ገንዘብ በሚወዱ ሰዎች ነው፡፡ ገንዘብን መውደድ ደግሞ የጥፋት ሁሉ መሠረት ነው፡፡ ዛሬ፣ የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደር የጥፋት መሠረት ኾኖ የሚያተራምሰው፣ አፍቅሮተ ንዋይ(የገንዘብ መውደድ) ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የተሠየሙ ሰዎች የአስተዳደር ማጠንጠኛቸው የገንዘቡ መጠን እስከኾነ ድረስ ደግሞ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን ለማፍረስ፣ ማኅበረ ምእመናንን ለመበታተን አባቶች በጨረታው የሚገደዱ ኾነው አላገኘናቸውም፡፡
እንደ ፍትሐ ነገሥት ገለጻ፣ ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል የሚያመለክተው የምእመናንን ኅብረት እስከ ኾነ ድረስ፣ የቤተ ክርስቲያን ትምህርትና አስተዳደሩ መንፈሳዊነቱንና አንድነቱን እንዳያጣ ጳጳሱ በተሾመባቸው ምእመናን ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ድንጋጌው ያስጠነቅቃል፡፡ የፍትሕ መንፈሳዊ ሥርዐት ይህ በኾነበት ኹኔታ አንዳንድ ጳጳሳት ግን፣ የቤተ ክርስቲያን አባልና አካል ከኾኑ ማኅበረ ምእመናን ይልቅ በጣት የሚቆጠሩ ነገረ ሠሪዎችን የመረጡበት ምክንያት በፍትሐ ነገሥቱ ለተዘረዘሩት ለገንዘብ መውደድ ሐሜት እየዳረጋቸው ይገኛል፡፡
ሰሞኑን ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ የዜና ዘገባ እንዳነበብነው፣ “የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ለሠራተኛ ቅጥር 100ሺሕ ብር ጉቦ መቀበሉ ታወቀ” ሲባል፣ አባ ሆይ፣ ሰውዬውን በአንድ ደብዳቤ ያሰናብቱታል ወይም አግደው ጉዳዩን ያጣሩታል ብለን ገምተን ነበር፡፡ ለካ ሰውዬው ጎይትኦም እንጂ ዘሪሁን ባለመኾኑ ግምታችን ሳይሳካ ቀርቷል፡፡ ሥራ አስኪያጁ የተዘገበበትን ጥፋት የፈጸመው ግለሰብ፣ የእነእገሌ ወይም የእነእንትና ብሔር ብትኾን ኖሮ፣ እንኳን ታውቆብህ ዜና ኾኖ በተዘገበ ጉዳይ ቀርቶ በፎርጅድ ጉዳይ ከሥራህም ከደመወዝህም ትሰናበታለህ፡፡ ይህ ከማንነትህ ጋራ ተያይዞ የሚመጣብህ ዕዳ ነው፤ እንደ ሥራ አስኪያጁ ዓይነት ስምና ማንነት ሲኖርህ ግን፣ በአባ ሆይ ችሎት ዘንድ ያለመከሠስ ጸጋ እንዳለህ ያመላክታል፡፡ እርሳቸውም ስላንተ ይከራከራሉ፣ መብትህንም ያስከብራሉ፡፡
ሐሜት እንዳይመስልብኝ በእኔ የደረሰውን እንደማሳያ ላቅርብ፡፡አባ ሆይ፣ ባላወቁት ጉዳይ፣ በ2008 ዓ.ም. ከሥራዬ እንድሰናበት ሸኚ ደብዳቤ ጽፈው ስለነበር በነበረኝ የሥራ ክርክር ባላጋራዎቼም የፓትርያርኩ ደብዳቤ አልታየልንም ብለው ይግባኝ ስለጠየቁ አባታችን ስማቸው በፍርድ ቤት በከንቱ እንዳይነሳ በማሰቤ በብዙ ደጅ ጥናት አናግሬአቸው አውቃለሁ፡፡ እርሳቸው ግን ስለ ስማቸውም ስለ መንበረ ክብራቸውም አልተጨነቁም፡፡ ከዚህም የተነሣ፣ “በምታሸንፍበት መንገድ ሔደህ ልታሸንፍ ትችላለህ” ብለው አሰናበቱኝ፡፡
ፍትሐ ነገሥቱ እንደሚለው፣ “ፓትርያርኩ በራሱ ፍርድ ቤት ያስወስን” የሚለው አንቀጽ የቤት ልጆችን የሚመለከት እንጂ እንደ እኔ አይነቱን በእርሳቸው ዘንድ መጻተኛ የኾንኩትን የማይመለከት መኾኑ የገባኝ ያኔ በተለይ አሁን ነው፡፡ አሁንም፣ እንደ እንጀራ ልጆች የሚቆጠሩ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት በቤተ ክርስቲያን ሥርዐት ፍትሕ የሚሰጣቸው አባት፤ የበላይ አካል የኾነ ይግባኝ ሰሚ ሲያጡ ጉዳያቸው በዓለማዊ ፍርድ ቤት እየተያዘ እስከ ሰበር ፍርድ ቤቶች ድረስ መዝለቃቸውና መብታቸውን ማስከበራቸው አይቀሬ ነው፡፡
በዓለማዊ ፍርድ ቤትና ገዢዎች ዘንድ የአብያተ ክርስቲያናት ጉዳይ እንዲያዝ ማድረግ ማለት ከጳጳሳቱ ጉባኤ፣ ከቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልና ይጠበቃልን? ወይስ ብፁዕ ቅዱስ ከሚባል መንበር ወይም መንፈሳዊ ልዕልና ላይ አለ ከሚባል የሃይማኖት መሪም እንዲህ ማድረግ ይገባዋልን? የቤተ ክርስቲያን መገለጫ የኾኑት ማኅበረ ምእመናን፣ መብታቸውን የሚጠይቁት በመንፈሳዊው ልዕልና መንገድ እንዲመለስላቸው በአክብሮት እንጂ በዓለማዊ ፍርድ ቤቶች ፍትሕ እንደሚያገኙ፣ እነርሱም ቢኾን ሕገ መንግሥታዊ መብታቸው መኾኑን መንገዱ ጠፍቷቸው አይደለም፡፡ ከዚያ ይልቅ ግን ብፁዕ ቅዱስ የሚለው አገላለጽ ለሲኖዶሳዊ መንፈሳዊነት፣ ልዕልናና ለተቋማዊነቱ የተሰጠ በመኾኑንም ቤተ ክርስቲያን ስለ ሁሉም ነገር የፍትሕ ሥርዐት አላት ብለው ስለሚያምኑ ነው፡፡
የሲኖዶሳዊ ሉዓላዊ አሠራር እየቀረ የአብያተ ክርስቲያናትን ጉዳይ ወደ ዓለማዊ አገዛዝ ፍርድ ቤቶች መምራት ማለት፣ የሃይማኖት መሪውን ተቋማዊነት አውርዶ ወደ ግለሰባዊነት ማምጣት ማለት መኾኑን የገባን ስንቶቻችን ነን? በዚህ መንገድ የሃይማኖት መሪዎችም በዓለማዊ አገዛዝ ፍርድ ቤት ከሥሠን ማስቀጣት እንደምንችል የምናውቅ ስንቶቻችን ነን? መልካም!!! ይህም ቅዱስ ሲኖዶስ ለግፉዓን ፍትሕ አለመስጠቱ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየመጣ ያለውን ተቋማዊ ክስረት ማሳያ መኾኑን ልንረዳው ይገባል!! እናም ታላቁ መጽሐፍ፣ "በመላእክት ላይ እንኳን የመፍረድ ሥልጣን አላችሁ፤" ያለው ከቶ ለማን ነው? ለጳጳሳት፣ ለካህናት፣ ለፓትርያርኩ አይደለምን? በዚህ ዓለም ጉዳይ በሥርዐታችሁ በአግባቡ መፍረድ ካልቻላችሁ ከዓለማውያን መሪዎች በምን ልትለዩ ትችላላችሁ? ለምእመናን ጥያቄ መፍትሔ እንድታበጁ፣ መናፍቃንን ለይታችሁ እንድታወግዙ፣ ሽማግሌ ሊኾን የሚችል አንድ አስተዋይ ሰው በእናንተ ዘንድ ሊኖር ይገባል፡፡
እንደ መንፈሳዊ መሪነታችሁ፣ በሃይማኖት ጉዳይ የሚተራመሰውን መንፈሳዊ ኮሌጅ ማጥራት ሲገባችሁ ዝምታን መምረጣችሁ ለምን ይኾን? አሁንም ለአብነት ያህል በመንፈሳዊ ኮሌጆቻችን ከገቡ መምህራን መካከል የአንዱን ቀሣጢ መምህር መጽሐፍ ልጥቀስ፡፡ ይህ ሰው በ2010 ዓ.ም. “መልሕቅ ክፍል ሁለት (አሌትያ)” በሚል መጽሐፉ በገጽ 188 ላይ “ክርስቶስን አማላጅ ነው” ለማለት ሮሜ 8፥34 ላይ ያለውን የሰማንያ አሐዱ መጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም ይፈርዳል የሚለውን ንባብ ሲተች፣“… ከአተረጓጓም ስልት የራቀ ነው በማለትና ይማልዳል የሚለውን ቁልፍ ሥነ መለኮታዊ ቃል የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መተርጉማን ይፈርዳል ብለው መቀየር የለባቸውም፤ ተገቢም አይደለም…” በማለት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከ2000 ዓመታት በኋላ ቃሉን ኾን ብላ የቀየረች አድርጎ መጻፉና እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስን አማላጅ ነው ማለቱ የሚያስወግዘው አይደለምን?እንደዚህ ዓይነት የሐሰት ትምህርት የሚያስተምርን በቅ/ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መቀጠሩን እያወቃችሁ ዝም ማለታችሁ ለምን ይመስላችኋል?
መጽሐፉን አላነበብነውም፤ ስለጉዳዩም አናውቅም እንዳትሉ ብቻ!!! እናንተማ!!! “ስማችሁ የለም” የሚለውን የወንድማችንን መጽሐፍ፣ “እኛን ለመንካት ነው” ብላችሁ ለግል ክብራችሁ ተጨንቃችሁ እንዳቄማችሁበትና እንደተፈራረማችሁበት ይታወቃል፡፡ በአንጻሩ ግን ለመድኃኔዓለም ክርስቶስ ክብር ግድ ሳይሰጣችሁ የኮሌጁን መምህር መጽሐፈ ኑፋቄ ለማውገዝ ምነው ዝም አላችሁ?! አባቶቼ!!!
ይህም አካሔዳችሁ፣ ከሲኖዶሳዊነታችሁ ይልቅ ምን ያህል ግለሰባዊነታችሁ ላይ እንዳተኮረ ያንጸባርቃል፡፡ ስለ ዝናና ክብር የምትጨነቁ ከኾነ ከዓለማውያን በምን ተለያችሁ? በዓለማዊ ባለሥልጣናትና በአባቶች ሥልጣን መካከል ሰፊ ልዩነት አለ፡፡ የአባቶች ሥልጣን ባለቤቱና ሰጪው ነሺውም መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የዓለማዊ ባለሥልጣን ግን በምድራዊ ሥርዐት በፉክክር የሚመጣ ነው፡፡ በዓለማዊ ተቋማት ያለው ፉክክር፥ የደመወዝ፣ የሥልጣን፣ የምቾትና የይገባኛል ነው፡፡ ዓለማውያን ለሥልጣን ማግኘት የሚያደርጉት ፉክክር የሚያስነቅፋቸው አይደለም፤ ነገር ግን በመንፈሳዊ መሪዎች መካከል ያለው የሥልጣን ፉክክር ያስነቅፋል ወይም ስለተሾሙለት ሕዝብ ሳይኾን ባሕር ማዶ ተሻግሮ ገንዘብ ለመሰብሰብ የሚደረገው የምረጡኝ ዘመቻ አሁን ባለንበት በጳጳሳቱ ጉባኤ የተሰማ አይደለምን? ከዚህ የበለጠስ መንፈሳዊ ክስረት ምን አለ? “እነ አቡነ ደርበውስ” የተፈጠሩት አሁን ባለንበት የጳጳሳት አስተዳደር አይደለምን?
‘ደርበው’ ማለቴ የሀገሩን ውስጥ ሠርተው ሳይጨርሱ ለበጀቱና ማለትም ሁለት ሦስት ደመወዝ ለማግኘት ሲሉ ብቻ በፍቅረ ሢመት ተጠምደው ቃል ኪዳን የተቀበሉበትን ሀገረ ስብከትና ሕዝብ እየተዉ ሌላ ሀገረ ስብከት የሚደርቡ፤ የእገሌ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ሓላፊ፤ የእገሌ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ጠባቂ፤ የእገሌ ተቋም ቦርድ ሰብሳቢ፤ የእገሌ ቤተ ክርስቲያን አሳራጊ የሚባሉ ደራቢና ተደራራቢ ጳጳሳትን ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት፣ በበጀት እጥረት ሰበብ አንድ ሥራ አጥተው እየተራቡ ሁለት ሦስት ደመወዝ የሚያገኙ፤ የቤት ኪራይ የሌለባቸው፣ የኑሮ ውድነት የማያስጨንቃቸው፣ ሁሉን ትተው ጌታቸውን የተከተሉ ጳጳሳት፣ ሁለት ሦስት ደመወዝ መውሰዳቸው የጽድቅ ነው ትላላችሁ?
አንዳንድ አባቶችስ፣ "ሲኖዶሱ ጣልቃ እንዳይገባብኝ" እያሉ የምእመናን አቤቱታ እንዳይሰማ የሚያደርጉበት ዘመን አሁን አይደለምን? “ይህ የአባ እገሌ ልዩ ሀገረ ስብከት ነው፤ ሲኖዶሱ አይመለከተውም፤” እየተባለ፣ አህጉረ ስብከት ከሲኖዶሳዊ አሠራር ውጭ ኾነው በጳጳሳቱ ይኹንታ ብቻ የሚተዳደሩበት የፍትሐ ነገሥት አንቀጽ አለን? ሕገ ቤተ ክርስቲያኑስ ቢኾን፣ ከመደበኛው ከፍትሐ ነገሥቱ የሕግ ትርጉም ጋራ ሊጋጭ ይገባዋልን? ሕገ ቤተ ክርስቲያኑ ሊሻሻል የሚችል ሲኾን፣ ፍትሐ ነገሥቱ ግን ቀዋሚ ሕግ አይደለምን?
እውነታው ይህ ከኾነ አባቶቼ፣ ሲኖዶሳችሁ፥ በሲኖዶሳዊ ጉባኤ ፍትሕ የተጓደለበትን ኹኔታ ሁሉ እየመረመረ ፍትሕ የምትሰጡበት ቅዱስ ጉባኤ መኾን ይገባዋል፡፡ ከዓመት እስከ ዓመት ያለው ቋሚ ሲኖዶስ መርምሮ ያላየውን አቤቱታቸውን፣ ምእመናን ለምልዓተ ጉባኤ ሲያቀርቡ፣ “አይ ይህን በቋሚ ሲኖዶስ እናየዋለን፤” እየተባለ ከዓመት እስከ ዓመት የሚንከባለሉ ችግሮችን ማየታችን ሲኖዶሱ ፍትሕን ለመስጠት ያለውን ልዕልና በግለሰቦች ፍላጎት ሥር እንዳዋለው መረዳት እንችላለን፡፡
የአብያተ ክርስቲያናትን ጉዳይ ወደ ፍርድ ቤት እንዲያመራ ማድረጉ ነገ ሊያስከትል የሚችለው አደጋ የተስተዋለ አይመስልም፡፡ ቤተ ክርስቲያን በዓለማዊ አገዛዝ ፍርድ ቤት መዳኘት ስትጀምር ጅብ በቀደደው ውሻ ይገባል እንደሚባለው፣ ማኅበረ ምእመናን እየተፈራረሙ በዓለማዊ አገዛዝ ፍርድ ቤት እያስወሰኑ በቦርድ የሚመራ ቤተ ክርስቲያን የሚያቋቁሙበት ጊዜ ሩቅ አይኾንም፡፡ ይህ በኾነ ጊዜ፣ እገሌን ልሹምብህ እገሌን ልደርብብህ፤ ማለት ይቀራል፡፡ ያን ጊዜ የሚጮኸው ጩኸት የማይጠቅም ጩኸት ይኾናል፤አባቶቼ!!! መንፈሳዊ የኾነ የሃይማኖት መሪ መገለጫው፣ ትሕትናና ጥበብ እንጂ ዓምባገነንነትና አልሸነፍ ባይነት ሊኾን አይገባውም፡፡
በዓለማዊ ባለሥልጣናትና በመንፈሳዊ መሪዎች መካከል ያለው ልዩነት የቅድስና ሊኾን ይገባል እንጂ የአልባሳት ልዩነት ብቻ ሊኾን ባልተገባው ነበር፡፡ ዓለማዊው ባለሥልጣን በቪ8 የሚሔድ ከኾነ መንፈሳዊው የሃይማኖት መሪ ደመና ጠቅሶ እንደ ሐዋርያት መንቀሳቀስ ነበረበት፡፡ ዓለማዊው መሪ በሱፍና በክራቫት ሲያሸበርቅ መንፈሳዊ የሃይማኖት መሪዎቻችን ደግሞ ባሸበረቁበት ልብሳቸው ድውያንን በፈወሱ ነበር፡፡ ይህን በዘመናችን አላየንም፡፡ በዘመናችን ያየነው፣ እነ አቡኑ አለባበሳቸውን የመደብ ልዩነት ሲያደርጉት እንጂ ልብሳቸው የቅድስና መለያ ኾኖ እንደእነ ጳውሎስ ሕሙማንን ሲፈውሱበት፤ እንደ እነኤልሳዕ ባሕር ሲከፍሉበት አልተመለከትንም፡፡
አባቶቼ፣ ነገሩ እንዲህ ከኾነ፣ ከዓለማዊ ባለሥልጣናት በምን ተለያችሁ? በቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት ችግሮች ተወያይታችሁ ደብዳቤ ከመለዋወጥ ባለፈ ውሳኔ የማትሰጡ ከኾነ እናንተ እነማን ናችሁ? አንዳንዶቻችሁ ፓትርያርክ መኾን ሳይቻላችሁ ሲቀር ለፓትርያርኩ እንደራሴ ልንሾምላቸው ይገባል የምትሉ፤ ለሥልጣን የምትፎካከሩ እናንተ እነማን ናችሁ? ፓትርያርኩስ ቢኾኑ ከእናንተ እንደ አንዱ አይደሉምን? ሁላችሁም እንደራሴ ያስፈልጋችኋል!!!
አባቶቼ ጳጳሳት፣ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የማያሳስባችሁ ከኾነና ከማኅበረ ምእመናን ጋራ የምትገናኙበት መንገድ እየተቋረጠ ከሔደ ከዚህ በኋላ እርስ በራሳችሁ የምትመራረጡበትን የእስከ ዛሬውን አካሔድ በማስቀረት፥ ማኅበረ ምእመናኑ ያመኑበት፤ በዐይናቸው የሚያውቁት፤ በእጃቸው የዳሰሱት፣ በትምህርቱ የተማረኩበት፤ ለአመራሩና ውሳኔው የሚገዙለት፣ የሕዝብ ይኹንታና ተመጣጣኝ ውክልና የተሰጣቸው ሊቃውንትና ምሁራን አባቶች ተመልምለው የሚሳተፉበት ሕዝባዊ ሲኖዶስ ሊቋቋም ይገባል፡፡ አዎ እደግመዋለሁ፤ “የተቀደሰው” ጉባኤያችሁ ደስ አያሰኝምና ስለ ቤተ ክርስቲያንና ስለ ሀገር አንድነት ሲባል ሕዝባዊ ሲኖዶስ ሊቋቋም ይገባል!!!
“ኵሎ አመክሩ ወዘሠናየ አጽንዑ”
ገለቶማ !!!
ይቆየን፡፡

+ እኔ ግን እኔ አይደለሁም +አውግስጢኖስ ፈጣሪ የለም ባይ እና በዝሙት የተበላሸ ሕይወት ይኖር የነበረ ሰው ነው:: በቅዱስ አምብሮስ ስብከት ከተመለሰ በኁዋላ ግን ይህ ሰው ፍጹም በንስሓ ተ...
21/09/2025

+ እኔ ግን እኔ አይደለሁም +

አውግስጢኖስ ፈጣሪ የለም ባይ እና በዝሙት የተበላሸ ሕይወት ይኖር የነበረ ሰው ነው:: በቅዱስ አምብሮስ ስብከት ከተመለሰ በኁዋላ ግን ይህ ሰው ፍጹም በንስሓ ተለውጦ በምንኩስና መንገድ ሔዶ እስከ ጵጵስና ደረሰ:: ይህንን የንስሓ ሕይወት መኖር ከጀመረ በኁዋላ ቀድሞ በአመንዝራነት ሕይወት ሲኖር ወዳጁ የነበረች አንዲት ሴት መንገድ ላይ ከሩቅ አይታ ተከትላ ጠራችው::
ወደ ቀድሞ ትዝታውና ኃጢአቱ መመለስ ያልፈለገው ይህ አባትም ጥሪዋን እንዳልሰማ ሆኖ በፍጥነት መሔድ ጀመረ::
ይህች ሴትም እየሳቀች :-
አውግስጢኖስ እኔ እኮ ነኝ! ብላ ጮኸች

እርሱም ወደ እርስዋ ዞሮ :- "እኔ ግን እኔ አይደለሁም" አላት::

ክርስትና የወደቀ የሚነሣበት የረከሰው የሚነጻበት ሕይወት ነው:: በዚህ መስመር ያለፉ ሁሉ ትናንትን እየተዉ ሌላ ማንነትን ይለብሳሉ:: ትልቁ ፈተና ሰዎች ተነሥተህ እያዩህም እንኩዋን መውደቅህን አለመርሳታቸው ነው:: ፈጣሪ "ከእንግዲህ አትበድል" ብሎ ይቅር ቢልህም ሰዎች ግን ይቅር አይሉህም:: "ድመት መንኩሳ ዓመልዋን አትረሳ" እያሉ እየተረቱ ወደ ነበርክበት እንድትመለስ ይገፉሃል እንጂ እንድትለወጥ አይፈቅዱልህም::

ሳውል አሳዳጅ ነበረ ዛሬ ግን ሐዋርያ ነው:: ብዙ ክርስቲያኖች ግን እርሱን ለማመን ተቸግረው ነበር:: ከመመረጡ ጀምሮ "ኸረ እርሱ አይሆንም" ብለው ለፈጣሪ ምክር የሠጡም ነበሩ:: ከተመረጠ በኁዋላም ለመቀበል ተቸግረው ከሐዋርያት አሳንሰው ያዩት አልጠፉም:: እርሱም በትሕትና "ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ" ቢልም : "ጭንጋፍ" ብሎ ራሱን ያለ ጊዜው ከሚወለድ ጽንስ ጋር አነጻጽሮ ዘግይቶ የተጠራ መሆኑን ቢናገርም ከሐዋርያት በምንም የማያንስ ሐዋርያ ነበረ:: እነርሱ በትናንት ማንነቱ ሊያዩት ቢሹም እርሱ ግን "እርሱ አልነበረም" እርሱ መኖር አቁሞ በእርሱ ይኖር የነበረው ክርስቶስ ነበረ::

አንዳንድ ሰዎች የማያምኑህ ከክፋት ተመልሰህ መልካም ስትሆን ብቻ አይደለም:: በጣም መልካም ስትሆንላቸውም አያምኑህም:: ስታከብራቸው ምን አስቦ ነው? ብለው ይጠራጠራሉ:: መልካም ስታደርግላቸው "ምነው ደግነት አበዛሽ? ተንኮል አሰብሽ እንዴ? "ይህቺ ጠጋ ጠጋ ዕቃ ለማንሳት ነው" "there is no free lunch” ብለው ሊሰጉ ይችላሉ:: መልካም የሚያደርግላቸውን ሁሉ ሊያርድ የሚያሰባቸው የሚመስላቸው ሰዎች አሉ:: ፍቅር የትግል ስልት የሚመስላቸው ጨብጠውህ ጣታቸው እንዳልጎደለ የሚቆጥሩ ዓይነት ተጠራጣሪ ሰዎች አሉ::

ዮሴፍ የገጠመው ይህ ነበር:: በሃያ ብር ሸጠው ግብፅ ያወረዱት ወንድሞቹን ይቅር ብሎ በፍቅር ተቀበላቸው:: አባታቸውን ያዕቆብን አስመጥቶ በክብር በግብፅ እንዲኖሩ አደረጋቸው:: ከዓመታት በኁዋላ አረጋዊው ያዕቆብ ሞተ::
ይሄን ጊዜ የዮሴፍ ወንድሞች ድንገት ስብሰባ አደረጉ: "አባታችን ከሞተ በኁዋላ ቢበቀለንስ?!" ብለው ስጋታቸውን ተመካከሩ::
ስለዚህ ዶልተው መጡና እንዲህ አሉት :-
አባታችን ከመሞቱ በፊት እንዲህ ሲል ተናዝዞ ነበር:: እባክህን የወንድሞችህን በደል ይቅር በል:: (ዘፍ 50:15-21) ዮሴፍ ይኼን ሲሰማ አለቀሰ:: ይቅርታን አድርጎም አለመታመኑ አመመው::

እርሱ ለእነርሱ ድሮም ክፉ አልነበረም:: አሁን ደግሞ ላደረሱበት በደል እንኩዋን ፈጣሪውን የሚያመሰግን ሆኖአል:: "እናንተ ክፉ ነገርን አሰባችሁብኝ፤ እግዚአብሔር ግን ዛሬ እንደ ሆነው ብዙ ሕዝብ እንዲድን ለማድረግ ለመልካም አሰበው" ነበር ያለው:: ምንም በደል ቢደርስበት እነርሱ አልተለወጡ ይሆናል እንጂ እርሱ ግን ትናንት የሚያውቁት ዮሴፍ አይደለም:: "እኔ ግን እኔ አይደለሁም" አላቸው::

እኔን ያስደነቀኝ...እመቤቴ ሆይ! እኔን ያስደነቀኝ ከሙታን መካከል ተለይተሽ መነሣትሽ አይደለም፤ ትንሣኤና ሕይወትን በመውለድሽ ነው እንጅ። ሞት በሠለጠነበት ማኅፀን የሕይወት መገኘት እንደም...
21/09/2025

እኔን ያስደነቀኝ...

እመቤቴ ሆይ! እኔን ያስደነቀኝ ከሙታን መካከል ተለይተሽ መነሣትሽ አይደለም፤ ትንሣኤና ሕይወትን በመውለድሽ ነው እንጅ። ሞት በሠለጠነበት ማኅፀን የሕይወት መገኘት እንደምን ይደንቃል?!

ድንግል ሆይ! ወደ ሰማይ ከመውጣትሽ ይልቅ የሰማይ ሁለተኛ ተብለሽ መጠራትሽ ይደንቀኛል። ማሕደረ መለኮት በመሆኑ ምድርን ሰማይ ሰማይን ምድር ያደረገ ሰውነትሽ በምድር ተወስኖ ሊኖር እንደምን ይቻላል?!

እመብርሃን ሆይ! ልጅሽ የጽድቅ ብርሃን ነው አንች ደግሞ የብርሃኑ መገኛ የፀሐይ ክበብ ነሽ፤ የፀሐይ ክበብ ለጊዜው በተራሮች ራስ ቢጋረድ መልሶ ላይወጣ ኖሯልን? ያንችም ትንሣኤ እንደዚያ ነው።

ለጊዜው ሰውነትሽ በመቃብር ውስጥ አደረ ነገር ግን በምሽት የጠለቀችው ፀሐይ በማለዳ እንድትወጣ ያንችም ሰውነት ከመቃብር ወጣ።

እመ አምላክ ሆይ! አምላክን የዳሰሱ እጆች፣ መለኮት የተቀመጠባቸው ጉልበቶችሽ፣ ጌታዬ የጠባቸው ጡቶችሽ በመግነዝ እንደታሰሩ ሊቀር ይገባልን? ገፀ መለኮቱን ያዩ ዐይኖች በሞት እንደተከደኑ ትንሣኤ ዘጉባኤን ይጠብቃሉን? ይህስ አይደለም እመቤቴ በሞት ሥልጣን ሥር አይደለችም።

የጌታዬ እናት ሆይ! ጥንቱንስ ቢሆን የታቦት ማደሪያው በመቃብር ውስጥ ነውን? ቃሉ የተጻፈባትን የሙሴ ጽላት በመቃብር ውስጥ አለች ብሎ የሚያምን የተረገመ ነው። የአሮን በትር የዘለዓለም የክህነቱ ምልክት ሆና በመቅደስ ልትኖር ከተገባት የሐዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህናት የ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ ካህናት ንጉሠ ነገሥት ተብሎ የተሾመባት አማናዊቷ በትረ አሮን በሰማዩ መቅደስ በሕይወት ልትኖር አይገባምን?

በነገራችን ላይ ይህንን ታሪክ አምኖ ለመቀበል ከሐዋርያት በጥምቀት መወለድና የሰማዩ የቅዱሳን ኅብረት አባል መሆን ግድ ይላል። ቤተ ክርስቲያናችን የሰማዩ የቅዱሳን ጉባኤ አባል ስለሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተነሥታለች፣ ወደ ሰማይ ዐርጋለች ብላ ታምናለች። በሰማይ ያሉ ቅዱሳን እያሸበሸቡ እየዘመሩ ተቀብለዋታል። ይህ በዓል በታቦተ ጽዮን ፊት ሲዘምር ያየነው ዳዊት የዘመረበት ዕለት ነው። ያኔ የበፍታ ኤፉድ ለብሶ የዘመረውን መዝሙር 2 ሳሙ. 6፥14ዛሬ የጽድቅ ካባ ደርቦ ዘመረው። ያኔ የድንግል ማርያም ምሳሌ ለነበረችው ታቦት የዘመረውን መዝሙር ዛሬ በአማናዊቷ ታቦት ፊት አቀረበው።

እኔን የሚያስደንቀኝ የእመቤታችን ምሳሌ በነበረችው መቅደስ ሲያገለግሉ የነበሩ ካህናት ሁሉ ዛሬ በአማናዊቷ መቅደስ ፊት ለፊት ቆመው ለማገልገል መብቃታቸው ነው። ሊያዩአት ይመኙ ለነበሩ ሁሉ ዛሬ ተነሥታ በግልጥ አዩአት። ለ እመቤታችን ከተደረገው ይልቅ ለቅዱሳን የተደረገላቸው ብዙ ነው።

የእናቱን ትንሣኤ እንደ ልጇ ትንሣኤ አድርጋችሁ የምታከብሩ የጥምቀት ልጆች ሁላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ወላዲተ አምላክ ማርያም ዐርጋለች።

ሚካኤል በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት ቆሟል 🎤ለተጨነቀች ነፍስ ምህረት ይለምናል ጨለማው እንዲሸሽ እንዲሆን ብርሃን ኦ ቅዱስ ሚካኤል ሰዓለነ እንበል🙏💖†               †         ...
21/09/2025

ሚካኤል በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት ቆሟል 🎤
ለተጨነቀች ነፍስ ምህረት ይለምናል
ጨለማው እንዲሸሽ እንዲሆን ብርሃን
ኦ ቅዱስ ሚካኤል ሰዓለነ እንበል🙏💖
† † †
የነፀብራቅ ዝናር ሚካኤል ታጠቀ
በቅድመ እግዚአብሔር ሕዝቡን አስታረቀ
በእሳታዊው አክናፍ ከክፉ ጋረደ
ልጆቹን ሊባርክ ሚካኤል ወረደ (2)
‹‹ኦ ቅዱስ ሚካኤል››
🥰

ሥውሯ_ማርያምእጢው ወደ ካንሰር ተለውጦል ኬሞ መጀመር አለብሽ አለበለዚያ ትሞቻለሽ አለኝ ዶክተሩ ከዛ ስውሯ ማርያም ገዳም የገና ጾም ላይ መጥቼ ጸበሎን ወስጄ ጠጣው ድጋሜ ውጪ ተመረመርኩኝ ም...
21/09/2025

ሥውሯ_ማርያም
እጢው ወደ ካንሰር ተለውጦል ኬሞ መጀመር አለብሽ አለበለዚያ ትሞቻለሽ አለኝ ዶክተሩ ከዛ ስውሯ ማርያም ገዳም የገና ጾም ላይ መጥቼ ጸበሎን ወስጄ ጠጣው ድጋሜ ውጪ ተመረመርኩኝ ምርመራዬ ሄዶ ሲመጣ ከካንሰር ነጻ ዶክተሮቹ ግራ ተጋቡ ክብር ለድንግል ማርያም የሞቴን ደብዳቤ ቀደደችልኝ።

ጳጳሱ ቤተ ክርስቲያንን አያውቋትም።(መጰጰስ ለመንቆለጳጰስ)  እነዚህ ባለፈው ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ተጥሶ፣ ፍኖተ ሐውርያት ተደምስሶ በባለ ስልጣናት እንግርግሪያ በጉቦና በደቦ ከተሾሙት አንዱ...
21/09/2025

ጳጳሱ ቤተ ክርስቲያንን አያውቋትም።
(መጰጰስ ለመንቆለጳጰስ)

እነዚህ ባለፈው ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ተጥሶ፣ ፍኖተ ሐውርያት ተደምስሶ በባለ ስልጣናት እንግርግሪያ በጉቦና በደቦ ከተሾሙት አንዱ እንደሆኑ አውቃለሁ። በሚድያ የምንፍቅና ትምህርታቸው ሲሰራጭ እሰማለሁ። ለአንዳንዱን አወዛጋቢ ትምህርትም ምዕመናን እየጠየቁን መልስ ሰጥተናል። ብቻ አፍለኛ ፖለቲከኛም ተሀድሷዊ የፕሮቴስታንት መንፈስ የሚያንከባልላቸውም ባለዘመን ናቸው። ባለፈ ድንግል ማርያም ቤዛዊት ዓለም አትባልም ብለው ቤተ ክርስቲያኒቷ የማትለውን ብለው ብዙ አባቶችን ሊቃንትንና ምዕመናንን አሳዝነዋል። ይህም ቤተ ክርስቲያኒቷን ሳያውቋት እንደ ጰጰሱ የሚያሳይ ካልሆነ ምን ይባላል? ወይም ጥመትና ግልጽ ምንፍቅና ካላልነው። ሌላም ብዙ ዝብርቅርቅ ትምህር አስተምረዋል።

ሰሞኑን ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን ለማስመታትና ለማስጠላት “ሙታን ነገሥታትን ስም እየጠራች ንጉሤ እያለች የምትጸልይ ቤተ ክርስቲያን ላሉትም ብትጸልይ ጥሩ ነው” የሚል ምክር አይሉት አልጸለየችም የሚል ቧልት በዐውደ ምሕረት ሲያስተጋቡ ሰማን፤ ለውጥን የሚያመጣው እግዚአብሔር ነው እያሉ እናንተ ምንም አታድርጉ አርፋችሁ ተቀመጡ አይነት ነገር ሲስቡና ሲያሰቡ በቪድዮው ይደመጣሉ። ይኸን ዝም ማለት ከእርሳቸው ጋር መተባበር ነውና የዋሹትን ወይም ያበላሹትን ማስተካከል ወይም ማሳወቅ ይገባል። ቤተ ክርስቲያን ስትጸልይ እገሌ ከእገሌ አትልም። ለሁሉም ለጻድቁም ለኀጥኡም ለገዳዩም ለሟቹም ለሁሉም ነው የምትጸልየው። ሰውየው ይኸንን ሳያውቁ ለም ጰጰሱ? ሊንቆለጳጰሱ?
እርሳቸው
“ሙታን ነገሥታትን ስም እየጠራች ንጉሤ እያለች የምትጸልይ ቤተ ክርስቲያን ላሉትም ብትጸልይ ጥሩ ነው” አሉ

ቤተክርስቲያን ደግሞ እርሳቸው ሳያሳስቧት፡

“እውቀትን እሱን መፍራትንም እግዚአብሔር ይሰጣቸው ዘንድ ስለ መኳንንትና ሥልጣን ስላላቸው እንማልዳለን” እያለች እግዚአብሔርን መፍራትን እውቀትን ያድላቸው ዘንድ ትጸልይላቸዋለች ትማልድላቸዋለች። (ቅዳሴ በእንተ ቅድሳት)

“ነገሥታቱንና መኳንንቱን መሳፍንቱንና በሥልጣን የሚኖሩትን (kings, rulers, princes, those in authority) ባርክ” እያለችም በረከትን ያድላቸው ዘንድ ባርካቸው እያለች ትጸልያለች። (ቅዳሴ ማርያም)

“ሁሉንም በቸርነትህ ጎብኝ፣ ትንንሾችንም፣ ትልልቆችንም፣ ገዥውንና ሕዝቡን፣ ጠባቂውንና መንጋውን” እያለች ለገዢዎች ለመሪዎች ሁሉ ትጸልያለች። (ጸሎተ ኪዳን)

ታዲያ በዚች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጳጳስ ነኝ የሚል ሰው እንዴት አልጸለየችም ብሎ ይከሳታል። አሁን ላይ ያሉትን ስማቸውን ጠርታ ለምን አልጸለየችም ማለት ከሆነ ቀኖናዋ ሥርዓቷ አይፈቅድላትም። የቀደሙትን ነገሥታቱን ስም ጠርታ መጸለይዋ አምነዋት በውስጧ ክርስትና ተነሥተው ውለታ ውለውላት በጸሎት አስቢን ብለው ሕንፃውን ሠርተው መጻሕፍቷን አጽፈው አስደጉሰውላት ነው። ይኸ ግን እነዚያ የሠሩትን የሚያፈርስ የቀደሙት ያከበሩትን የሚያረክስ ነው። በዚያ ላይ አያውቃት አያምናት። እርሱ ከመናፍቃን ወገን ነውና የእርሱን ስም ጠርታ ልትጸልይ አትችልም። ምክንያቱም ስም የለውም። እርሱ በእርሷ ዘንድ ስም አልባ ነው።

እናማ አባ ጳጳሱ አይዋሹ፤ ነገር አያበላሹ። እባክዎት ቤተ ክርስቲያንን ለማስመታት አይቸኩሉ። ሰላማዊትንም አይተናኮሉ።

ወይ ጉዳችን ምን ተሻለን ጎበዝ?

ዐይኑ ዘርግብ፣ ልብሱ ዘመብረቅ የዋህ ፣ ረዳት ፣ ወዳጅ አባት ቅዱስ ሚካኤል! 🌹🌹🌹
21/09/2025

ዐይኑ ዘርግብ፣ ልብሱ ዘመብረቅ
የዋህ ፣ ረዳት ፣ ወዳጅ
አባት ቅዱስ ሚካኤል!
🌹🌹🌹

✍️ከማልቀስ ባለፈ ጠንካራ ሥነ ልቡና የመገንባት ሥራ ያስፈልገናል!***********************************************************ትናንት ጥምረት ለቤተ ክርስቲያ...
21/09/2025

✍️ከማልቀስ ባለፈ ጠንካራ ሥነ ልቡና የመገንባት ሥራ ያስፈልገናል!
***********************************************************

ትናንት ጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ያዘጋጀውን ‘የበይነ መረብ የካህናትና ምእመናን ለቤተ ክርስቲያን አንድነት መድረክ’ ውይይት የተወሰነውን ተከታትየዋለሁ፡፡ አልሆነልኝም እንጂ ሐሳብ እንዳቀርብም ተጋብዤ ነበር፡፡ የሆነው ሆነ የጥቂት ተናጋሪዎች ንግግሩ ስሜት ቀስቃሽ ስለነበርና አንዳንዶቹም ሲያለቅሱ ስላየሁ ስለጠቅላላ ውይይቱና መበረታታት ስላለበት ጉዳይ ሐሰብ እንዲሰጥ ከዚያም አሁን እያነበርነው ያለው ደካማ ሥነ ልቡና ደግሞ አክሳሪ ስለሆነ በጥንቃቄ ማሰብ እንዳለብን ለማሳሰብ ይኸንን ጻፍኩ፡፡

✅በውይይቱ ላይ እነማን ተሳተፉ?

ውይይቱ ላይ ስለወቅታዊው የቤተ ከርቲያንያንና የሀገራቸው ሁኔታ የሚያሳስባቸው ሁሉ የተጋበዙበት የአደባባይ ውይይት ነው፡፡ ቀጣይነት እንዳለውም ተረድቻለሁ፡፡ መቀጠል ያለበትም ነው ብየ አምናለሁ፡፡ በትናንቱ መርሐ ግብር ላይ ከጳጳሳት አቡነ ሉቃስና አቡነ ጴጥሮስ ተገኝተዋል፣ የጥምረቱ ካህናትና ሌሎች አባቶች እንዲሁም ምእመናንም ተገኝተዋል፡፡ ይኸ ጥሩ ጅማሮ ነው፡፡ ራሳችንን ወደ አደባባይ ማምጣትና ድምጻችንን ማሰማት የግድ ይለናል፡፡

✅የመርሐ ግብሩ ዐላማ ምንድነው ነበር?

ከመርሐ ግብሩ መረዳት የቻልኩት ሁለት ዋና ዋና ዐላማዎች እንዳሉት ነው፡፡

 በፈተና መብዛት እየፈዘዘ የመጣው የካህናትና የምእመናን ኅብረት ከዚያም ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገራችን ችግር መፈታት ያላቸው ሚና መቀዝቀዝና ያም በተከታታይ እየሆነ ላለው ሀገራዊ ጥፋት አስተዋጽኦ ማድረጉ፣

 ይህ ቸልተኝነት በቤተ ክርስቲያንም ይሁን በሀገርም ላይ እየሆነ ላለው ዘርፈ ብዙ ፈተና ተጠናክሮ መቀጠል ቀጥተኛ ሚና ያለው መሆኑን ተገንዝቦ ተከታታይ ውይይት የማድረግን አስፈላጊነት የግድ የሚል በመሆኑ የተዘጋጀ ውይይት ነበር፡፡

✅የመርሐ ግብሩ መሪ ቃል?

ለመርሐ ግብሩ የተቀመጠው ‘ኢትዮጵያውያን ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን ሰላምና ሕልውና’ የሚለው መሪ ቃል የሚያሳየው የቤተ ክርስቲያን አባቶች ስለቤተ ክርስቲያናቸው ሲያስቡ ቤተ ክርስቲያናቸውን ከሀገራቸው ነጥለው ለብቻ ለማየት የማይችሉ መሆኑን እንረዳለን፡፡

ይህ በአንድ በኩል ዕጣ ፈንታችን ከሀገሪቱ ጋር የተሳሰረ መሆኑ ጥሩ ጎን የመሆኑን ያህል የቱንም ያህል አቅም ቢኖረን ለብቻችን ልንድን የምንችለበት አማራጭ የሌለን መሆኑ ደግሞ ችግሩን የበለጠ ውስብስብ ያደርገዋል፡፡

ከዚህ ተነሥተን ስለቤተ ክርስቲያን ስናወራ፣ ስለሀገር፣ ስለሀገር ስናወራ ደግሞ ስለቤተ ክርስቲያን መናገር መሆኑን ሰዎች ልብ ሊሉት ይገባል ማለት ነው፡፡ በሀገሪቱ ላይ የሚደረገው ማንኛውም በጎም ይሁን እኩይ ፖለቲካ ማንኛውንም ዜጋ እየጎዳ ይገኛል፡፡ ካህናትና ምእመናንም በተነጠለ ዓለም የማይኖሩ መሆናቸውን እንዲያውም ዋናዎቹ የገፈቱ ቀማሾች መሆናቸውን አውቀው ፖለቲካው በንቃት መከታተል እንዳለባቸው እንገነዘባለን፡፡

✅በውይይቱ የተንጸባረቁ ሐሳቦች መን ይመስላሉ?

ከዚህ ውይይት የሚከተሉትን ነጥቦች ነቅሶ ማውጣት ይቻላል፡፡

o በሀገር ላይ ከፍተኛ ውድቀት በሁሉም ዘርፍ አለ፣

o በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚራመደውና ረጅም ዐመታት እያስቆጠረ ያለ ከፍተኛ የጥላቻ ፖለቲካ ተንሠራፍቷል፣

o ይኸ ጥላቻ ደግሞ ሀገርን እስከማፍረስ የሚያደርስና እያፈረሰም ያለ ነው፤

o ፖለቲካው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከገባ የቆየ ቢሆንም በዚህ ወቅት ደግሞ የበለጠ እየተደላደለ ይገኛል፣ ከዚያም አልፎ ቀኖናውን ተክቶም መተዳደሪያ ወደመሆን እየተሸጋገረ ይገኛል፣

o ኦርቶዶክሳውያን በሁሉም መስክ ተገፊዎችና የተገለሉ እየሆኑ መሄዳቸው ፀሐይ የሞቀው ሐቅ ከሆነ ሰነባብቷል፣

o ከመገፋት ባለፈም ገዳማት፣ አብነት ት/ቤቶች፣ አንዳንድ ቦታዎች ደግሞ ኦርቶዶክሳዊያን ምእመናን፣ ከመገፋት አልፈው ስደትና ግድያ እየተፈጸመባቸው ይገኛል፡፡

o የሚያሳዝነው ደግሞ ይህንን መገፋት ማንሣት በአንድ በኩል እንደወንጀ እየተቆጠረ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ወደ ተግባር የማይለውጥና Consequential ባለመሆኑ በጠላት ዘንድ 'ከማልቀስ ውጭ ምንም አያመጡም’ የሚል ልምድ እየተወሰደበት መሆኑን፣

o ላለፉት 70 ዓመታት ኦርቶዶክሳዊ እሴቶች እንደጠላት ማየት የተለመደ ቢሆንም አሁን ደግሞ አንዱ የፖለቲካ መተያያና ወቅታዊው 'ሀገርን አፍርሶ የመገንባት' ፍላጎት ገዢ መሆኑ መጪውን ጊዜ የበለጠ አስፈሪ ማድረጉ፡፡

o ሲኖዶሱ ራሱን ነጻ አውጥቶ ኦርቶዶክሳዊነትን መመሪያው ያደርጋል ተብሎ ቢጠበቅም ይባስ ብሎ በፖለቲካው ጣልቃ ገብነት ቢያጣም፣ ያም አላሳስበው ብሎ የበለጠ ለፖለቲካው ለመገበር ፈቃጅ ባላቸው አባላቱ ተጽዕኖ ሥር እየወደቀ መሆኑ በግልጽ የሚታዩ ክስተቶች መሆናቸው ተንጸባርቋል፡፡

✅ ከውይይቱ ተነሥተን ምን እናድርግ?

ከዚህ ውይይት ተነሥተን ልናደርጋቸው የሚገቡ አንገብጋቢ ጉዳዮች ምንድናቸው?
በዚህ ውይይት ላይ የተሳተፉ ተናጋሪዎችም ሆኑ ውይይቱን የሰሙ ኢትዮጵያውያን ‘ከእኛ የሚጠበቀ ምንድነው?’ የሚል ጥያቄ መጠየቅ አለባቸው፡፡
በእኔ መረዳት በአጭር ጊዜ ልናደርጋቸውም የምንችላቸው ነገሮች የሚከተሉት ናቸው፣

o አስቀድሞ መብትን መጠየቅ፣ አትግደሉን፣ ሰላም ስጡን፣ ጸጥታ አስከብሩልን፣ ብሎ መጠየቅ ወንጀል አለመሆኑን ማወቅ አለብን፡፡ በአጭሩ ከተሸበብንበት የፍርሐት ቆፈን ወጥተን መብታችንን መጠየቅ አለብን፣

o ጠንካራ ጥያቄ መጠየቅ ያለበን የራሳችንን መዋቅር፣ በተለይም ደግሞ ሲኖዶሱንና ያንን የሚመሩትን አባቶች መሆን አለበት፡፡ ሲኖዶስ ራሱን ነጻ ሳያወጣ ቤተ ክርስቲያንን፣ ልጆቿን ነጻ አያወጣም፣ ለሀገር ሰላምም ሚና ሊኖረው አይችልም፡፡

o ሀገሪቱ አሁን ላለችበት ዋናው ተጠያቂ መንግሥት ተብየው የቀውስ አመራር ነው፡፡ ይኸ ቀውስ እየፈበረከ የፈበረከውን ቀውስ እንኳን በቅጡ ማስተዳደር የማችል ቅጣምባሩ የጠፋበት ሥርዓት ታሪካዊ ተጠያቂ ስብስብ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን ሥርዓት በተደጋጋሚ መጠየቅ አለብን፡፡ ያለቅድመ ሁኔታ ጦርነትን አቁሞ የሚጠየቁ ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንግድ ፈትቶ እውነተኛ መንግሥት መሆን አለበት፡፡

o ምእመናን ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት፣ ቤተ ክርስቲያናቸውን ለመጠበቅና ሀገራቸውን ከመበታተን ለመጠበቅ በጋራ ትግል የሚያደርጉበት ምዕራፍ መሆኑን ማስገንዘብ ነው፡፡

✅በዚህ ውይይት ላይ ያለኝ ትዝብትና መስተካከል አለበት የምለው?

ይህንን የማስገንዘቢያ ውይይት ላዘጋጀው የጥምረት ለቤተ ክርስቲያን ሕብረት ትልቅ አክብሮት አለኝ፡፡ ኦርቶክሳውያን በተለየ ሁኔታ ኢትዮጵያውያን ደግሞ በጠቅላላው አሁን ያለንበት ጊዜ እጅግ አደገኛና አዝማሚያውም በጣም የሚያስፈራ መሆኑን ተገንዝበው ይህንን ወቅታዊ መርሐ ግብር ማዘጋጀታቸው ሊበረታታ የሚገባው ነው፡፡

ነገር ግን በትናንትናው ውይይት ላይ መጀመሪያ አካባቢ እንዲት እኅት ስሜት ቀስቃሽ ንግግር በማድረጓ አብዛኞቹ ሐሳብ አቅራቢዎች ሲያለቅሱ አይቻለሁ፡፡ እርግጥ ነው ያለንበት ሁኔታ ያስለቅሳል፣ ያሳዝናል፡፡ ነገር ግን እኔ ይኸኛውን ሥነ ልቡና ማበረታታት የለብንም ብየ ነው የማምነው፡፡ ይኸ አክሳሪ ሥነ ልቡና መቆም አለበት፡፡

በተለይም ‘ሰዎችን እናነቃለን፣ እንመራለን’ የምንል አካላት ከሁሉ አስቀድመን አሁን እያነበርን ያለውን ይህንን ሽባ የሚያደርግ ልፍስፍስ ሥነ ልቡና መቀልበስ አለብን፡፡ እውነታው እኛ ከዚህ የተሻልን ነን፡፡

በቁጥር ደረጃ ከሆነ ከራሽያ ውጭ የሚስተካከለው የሌለው የኦርቶዶክሳውያን ውጥር ያለን ቤተ ክርስቲያን ነን፡፡ ምንም እንኳን ቤተ ክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ስደትና ጥፋት ከበርካታ አቅጣጫ እየደረሰ ቢሆንም የሕዝባችንን ሞራል ከፍ ማድረግና ከልቅሶና ከጩኸት ባለፈ ራሱን ‘የለውጥ አካል ነኝ፣ ለውጥ ማምጣት እችላለሁ’ ብሎ የሚያስብ ትውልድ መፍጠር አለብን፡፡ ሕዝባችን አድፋጭ እንጂ ኃይል የሌለው አልቃሻም አይደለም፡፡ ያደፈጠውን የመቀስቀስ አቅም ነው ያጣነው፣ መሥራት ያለብን እዚያ ላይ ነው፡፡ ማንቃት፣ መቀስቀስ፣ እንጂ ማልቀስና በዲያብሎስ ፊት መኮሳመን ለጠላት ኃይልና ድል ከመሆን ያለፈ ሚና ያለው አይመስለኝም፡፡ ከአሸናፊነት እንጂ ከተሸናፊነት Position ላይ ሆነን ታግሎ ማሸነፍ አይቻልም፡፡ የአሸናፊው እግዚአብሔር ልጆች በተሸነፈው ዐለም ፊት ማልቀስ አይገባቸውም፡፡ በተለይም አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አካል በባዶው ተአምር እንደፈጠረ የሚፎክር፣ ድሆችን የሚጠየፍ፣ ለሚያለቅሱ መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ ልቅሷቸውን አባብሶ ሶፍት ለማቀበል የሚዳዳው ጨካኝ ሥርዓት በመሆኑ በልቅሶ ልቡን አራርቶና ጥቁር በመልበስ አስፈራርቶ ወደ ቀልቡ መመለስ አይቻልም፡፡ በአጭሩ ማልቀስ ማቆም አለብን፣ ስልታችን ያለንን አቅም እንዴት እንጠቀም በሚለው ላይ መሆን አለበት፡፡ አቅማችን ስናሳይ ብቻ ነው ራሳችንን ማስከበር የምንችለው፡፡ ካልሆነ ግን የድንቢጦች መጫዋቻ ነው የምንሆነው፡፡

እዚህ ላይ አንድ ቁም ነገር መናገር የሚያውቅ መንዜ አጎቴ የሚገጥማትን ግጥም ልጥቀሳት፣

‘የወፎች አለቃ ማማቶች ነበሩ፣
ድንቢጦቹ ሁሉ ወፍ ነው ወፍ ነን አሉ’ ይል ነበር፡፡

የምወድለት ግጥም ናት፡፡ ዛሬ ‘ወፍነን ወንፈን’ የሚሉት ሁሉ መልከ መልካሞቹ እነ ማማቶች መታየት በሚገባቸው ቦታ ለመታየት ካለመሻታቸው የተነሣ ነው፡፡

ጥቂቶች እንደቁራ ደጋግመው ስለጮኹ ብቻ ሀገር ምድሩን የሞሉት ይመስላሉ፡፡ ስናለቅስላቸው ደግሞ የባሰ የልብ ልብ እየተሰማቸው የሚያደርጉትን እያየን ነው፡፡
ማለቀስ ከጀመረን ቆየን፣ ነገር ግን ሁኔታው እየባሰ ሄደ እንጂ ልቅሷችን የፈየደው ነገር የለም፡፡ በአጭሩ ማልቀስ ማቆም አለብን፡፡ ይልቁንም ያለንን የታመቀ፣ ያደፈጠ ኃይል መግለጥና ራሳችንን ወደማስከበር መሸጋገር አለብን፡፡

ይኸው ነው!

21/09/2025

ምን ይሰማችኋል?

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Orthodox Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Orthodox Media:

Share