ፍቅረ ዘማሪያም - Fikre Zemariyam

ፍቅረ ዘማሪያም - Fikre Zemariyam "እርሱንና የትንሳኤውን ኃይል እንዳውቅ ፥ በመከራውም እንድካፈል ፥ ወደ ሙታንም ትንሳዔ ልደርስ ቢሆንልኝ ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።"

‎ፊል ፫፥፲-፲፩

📩 +251 920 63 35 35

†  ቅዳሴ ኤጲፋኒዮስ †★ እጅግ ድንቅና ጥልቅ ምሥጢረ መለኮት ያለበት ቅዳሴ ነው አንብቡት።ለሌሎችም ሼር አድርጉት★እግዚአብሔር በገናናነቱ ገናና ነው። በቅድስናው የተቀደሰ ነው። በምስጋናው ...
20/07/2025

† ቅዳሴ ኤጲፋኒዮስ †

★ እጅግ ድንቅና ጥልቅ ምሥጢረ መለኮት ያለበት ቅዳሴ ነው አንብቡት።ለሌሎችም ሼር አድርጉት★

እግዚአብሔር በገናናነቱ ገናና ነው። በቅድስናው የተቀደሰ ነው። በምስጋናው የተመሰገነ ነው። በክብሩም የከበረ ነው።

ከመቼ ወዲህ የማይሉት ቀዳማዊ ነው። እስከ ዛሬ የማይሉት ማእከላዊ ነው። እስከዚህ የማይሉትም ደኃራዊ ነው።

ለአነዋወሩ ጥንት የለውም። ለአኳኋኑም ፍጻሜ የለውም።
ለዘመኑም ቍጥር የለው። ለዓመታቱም ልክ ቍጥር የለውም።

ለውርዝናውም ማርጀት የለበትም። ለኃይሉም ጽናት ፣ ድካም የለበትም። ለመልኩ ጥፋት የለበትም። ለፊቱ ብርሃንም ጨለማ የለበትም።

ለጥበቡ ባሕር ድንበር የለውም። ለትእዛዙም ይቅርታ መስፈርት የለውም። ለመንግሥቱም ስፋት ዐቅም ልክ የለውም። ለአገዛዙም ስፋት ወሰን የለውም።

በኅሊና የማያገኙት ሥውር ነው። በልቡናም የማይረዱት ምጡቅነው። አንሥርት የማይደርሱበት ረጅም ነው። ዓሣዎች የማይዋኙበት ጥልቅ ነው።

ከተራሮች ራስ ይልቅ ከፍ ያለ ነው። ከባሕር ጥልቅነት ይልቅ ጥልቅ ነው። ነገሥታት የምይነሣሡበት ጽኑ ነው። መኳንንት የማይቃወሙት አሸናፊ ነው።

የጥበበኞችን ምክር የሚያጠፋ ጥበበኛ ነው። የሚመክሩትን ሰዎች አሳባቸውን የሚያስረሳ ዐዋቂ ነው። የጸኑ ልጓሞችን የሚፈታ ኃያል ነው።

የኃጥኣንን ጥርሶች የሚያደቅ ፤ የትዕቢተኞችንም ክንድ
የሚቀጠቅጥ ብርቱ ነው።

የግብዞችን ፊት የሚያዋርድ ክቡር ነው። የዝንጉዎችን ብርሃን የሚያርቅ ከሃሊ ነው። ባልንጀራ የሌለው አንድ ነው።

ዘመድ የሌለው ስሉጥ ነው። ሰማያት ይጠፋሉ ፤ የብስም
ትጠፋለች ፤ ሁሉም እንደ ልብስ ያረጃል። እርሱ ግን እስከ
ዘላለሙ እርሱ ነው።

የባሕር መመላለስዋ ድንቅ ነው። ድንቅስ በልዕልናው
እግዚአብሔር ነው።

የሚመስለው የለም። ከፍጥረትም ሁሉ ከአማልክትም ሁሉ የሚተካከለው የለም። እርሱ ብቻ አምላክ ነው። እርሱም ብቻ ጌታ ነው። ፈጣሪም እርሱ ብቻ ነው። ሠሪም እርሱ ብቻ ነው።

ስላሰበው ጥበብ ረዳት አይሻም። ስለወደደውም ሥራ መካር አይሻም። ሳይሆን ቀድሞ እንደ ሆነ አድርጎ ፤ ያልተደረገውንም እንደ ተደረገ አድርጎ ሁሉን ያውቃል።

ሳይጠይቅ ኅሊናን ይመረምራል። ሳይመረምር ልቡናን
ይፈትናል። ያለ መብራት በጨለማ ያለውን ያያል።

ጻድቁን ጽድቅን ሳይሠራ ያውቀዋል። ኃጥኡንም ኃጢአት
ሳይሠራ ያውቀዋል። ልበኞችን ከአባታቸው አብራክ ሳይወጡ ያውቃቸዋል። ኃጥኣንንም ከእናታቸው ማኅፀን ያውቃቸዋል።

የሚሸሸገው የለም። የሚሠወረውም የለም። ከእርሱም የሚሠወር የለም። ሁሉ በእርሱ ዘንድ የተገለጸ ነው። በዓይኖቹም ፊት የተዘረጋ ነው። ሁሉ በመጽሐፉ የተጻፈ ነው። በሕሊናውም ሁሉ የተጠራ ነው።

ቍጥር የሌላቸው ታላላቆችን መመርመር የሌለባቸውን የተደነቁ የከበሩ ሥራዎችን ይሠራል። ሥራው ከአየነው ይልቅ ዕፁብ ነው።

ኃይሉም ከሰማነው ይልቅ ድንቅ ነው። ጌትነቱም ከነገሩን
ይልቅ ድንቅ ነው።

ከጨለማ ለይቶ ብርሃንን ፈጠረ። ደመናውን መለየት ያውቃል። ውኃውን እንደ ወደደ ይከፍለዋል። የተመረጡትን በደመና ይሠውራል።

ምድርን ፈጠራት ፤ መጠንዋንም አዘጋጀ ፤ ፍጻሜዋንም
እንደምንም ተከተለ ፤ ማዕዘንዋንም አጸና።

ባሕርን ከእናትዋ ሆድ በወጣች ጊዜ በበሮች አነጠራት።
ልብሷንም ደመና አደረገላት። በጉም ጠቀለላት።

ወሰን አደረገላት። በውስጥዋም መዝጊያዎችንና ቁልፎችን አደረገላት። እስከዚህ ድረሺ ከወሰንሺም አትተላለፊ ፤ ማዕበልሽ በውስጥሽ ይመላለስ (ይነቃነቅ) እንጂ አላት።

በበላይዋ ላይ የንጋት ብርሃን ተዘጋጀ። የአጥቢያ ኮከብም
ትዕዛዙን ዐወቀ። እርሱ ከምድር ጭቃን ነሥቶ ሕያው የሆነውን ፈጠረ። በምድርም ላይ እንዲነጋገር አደረገው።

እርሱ እስከ ዓለም ዳርቻ ደረሰ። በጥልቅ ፍለጋም ተመላለሰ።

ከግርማው የተነሣ የሞት ደጆች ይከፈታሉ። የሲኦል በሮችም ባዩት ጊዜ ይደነግጣሉ። ከሰማይ በታች ያለውን ስፋቱን ከሰማይ በላይ የሚሆነውንም እርሱ ያውቃል።

በእርሱ ትእዛዝ ዋግ ከመዝገቡ ይወጣሉ። ከሰማይ በታች ያለ አዜብ(ነፋስ) ይመላለሳል። ዝናምን በምድረ በዳ ያጸናዋል። ሰው በሌለበትና የሰው ልጅ በማይኖርበት ይዘንም ዘንድ።

እርሱ የውኃውን መፍሰሻ ወሰን ፣ ክረምትንም በየዓመቱ
ይከፍታል። በጋውንም ኋላ በጊዜው ያመጣዋል። ደመናውንም በቃሉ ይጠራዋል። ውኃም እየተንቀጠቀጠ ይመልስለታል።

ብልጭልጭታውን እርሱ ይልከዋል ፤ እርሱም ይሄዳል። ምንድር ነው እያለ ይመልስለታል። እርሱ ደመናን በጥበቡ ይቆጥረዋል።
ሰማይን (ጠፈርን) ወደ ምድር ያዘነብለዋል።

እርሱ ብቻ የአርያምን ኃይል ለበሰ። በምስጋናና በክብር
ተጌጠ።

እሳታውያን ኪሩቤል ፣ ብርሃን የለበሱ ሱራፌልም እርሱን
ያመሰግኑታል። በማያርፍ ቃል ፣ ዝም በማይል ፣ በማይደክምም አንደበት ሁሉም ተባብረው ተሰጥኦ ባለበት ባንድ ቃል የጌትነትህ ምስጋና በሰማይ በምድር የመላ ፍጹም አሸናፊ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ይላሉ።

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ጸባዖት ፍጹም ምሉዕ ሰማያተ ወምድረ ቅድሳተ ስብሐቲከ።

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ፍጹም አሸናፊ እግዚአብሔር የጌትነትህ ምስጋና በሰማይ የመላ ነው።
Holy Holy Holy, perfect Lord of hosts, heaven and earth are full of the Holiness of Thy Glory.

ለሌሎችም ሼር አድርጉት



20/07/2025

ድንግል በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ትወልዳለች ብሎ የተነበየ ነቢይ ስሙ ማነው❔
ሀ🔵ነቢዩ ኤርምያስ
ለ🔵ነቢዩ ኢሳይያስ
ሐ🔵ነቢዩ ህዝቅያስ
መ🔵ነቢዩ ዳንኤል

20/07/2025

"መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በእለተ ቀኑ ልጅ አተው በየፀበሉ የሚንከራተቱትን ልጅ ያስታቅፍልን በልጅ ይባርክልን አሜን።🙏

20/07/2025

‘‘የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ።"(ኦሪት ዘጸአት 20:8)’’⛪
«መልካም እለተ ሰንበት ይሁንልን።

💚💛❤

20/07/2025

"ወር በገባ በ13 ቅዱስ ሩፋኤል እግዚአብሔር አብ አቡነ ዘርዓ ቡሩክ አቡነ ዮሐንስ ዘደብረ ቢዝን ናቸው።

ጥበቃቸው አይለየን🙏❤

በስሙ መሰብሰብ በስሙ መስራት🎤ስለ ስሙ መኖር ለስሙ መሞት ጠላት ዲያቢሎስን ምን ባያስደስትም ይህ ነው ክርስትና ይሄ ነው ህይወት🙏💖*** ቸረ ሰንበት13/11/2017 ዓ,ም
20/07/2025

በስሙ መሰብሰብ በስሙ መስራት🎤
ስለ ስሙ መኖር ለስሙ መሞት
ጠላት ዲያቢሎስን ምን ባያስደስትም
ይህ ነው ክርስትና ይሄ ነው ህይወት🙏💖

***
ቸረ ሰንበት
13/11/2017 ዓ,ም

20/07/2025

“13”
“ይውረድ ከሰማይ የምህረት ጠል
ሩፋኤል አሳድገኝ ልበል”
🙏🙏🙏

20/07/2025

➴ዛሬ ሐምሌ 13 ፈታሄ ማህፀን ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡

ወቶ ከመቅረት ካልታሰበ አደጋ ከክፉ ነገር ሁሉ ይሰውረን።እኛንም ለንስሐ ሞት ያብቃን::💖🙏

በቃ ስለሚወደኝ ትንሽ ቆንጠጥ አደረገኝ🤌💖አንድ አንድ ሰወች አሁን ያለሁበትን ሁኔታ አስተውለው ከማዘናቸው የተነሳ በቁጭት "እንዲህ ብታደርግ ኖሮ ፣ እከሌ ሚባል ቦታ ብትሔድ ኖሮ ፣ እንትና ...
20/07/2025

በቃ ስለሚወደኝ ትንሽ ቆንጠጥ አደረገኝ🤌💖
አንድ አንድ ሰወች አሁን ያለሁበትን ሁኔታ አስተውለው ከማዘናቸው የተነሳ በቁጭት "እንዲህ ብታደርግ ኖሮ ፣ እከሌ ሚባል ቦታ ብትሔድ ኖሮ ፣ እንትና ሚባል ሰውን ብታገኝ ኖሮ ፣ እከሌ ሚባል ሆስፒታል ብትደርስ ኖሮ ... እንዲህ አትሆንም ነበር!" ይሉኛል። ይሁን እንጂ እኔ በሕይዎቴ እግዚአብሔር ሳያውቅ ሚሆን ምንም ነገር እንደሌለ ስለማምን፤ የዘወትር መልሴም " ፈቃደ_እግዚአብሔር !!!" ምትል ነበረች።
በቃ ስለሚወደኝ ትንሽ ቆንጠጥ አደረገኝ ፤ የበዛ ጥንካሬን አየብኝና መመስገኛው እንድሆን መረጠኝ ፤ በመከራዬም እንድበረታና ሌሎችን እንዳበረታ ፈቃዱ ሆነ ። ከወሰደብኝ ይልቅ የሰጠኝ የላቀውን ነበርና ሕይዎቴ በምስጋና የተሞላ አደረገው ፤ ስሙ ሁሌም የተመሰገነ ይሁንና !!!
ስለዚህ ይህንን ጽሑፍ ምታነቡ ሁላችሁም
እንደዚያ ባደርግ ኖሮ እንዲህ አልሆንም ነበር ፤ ወይም እንደዚያ ባደርግ ኖሮ እንዲህ እሆን ነበር አትበሉ ። በሕይዎታችሁ ምንም ቢከሰት መሆን የነበረበት ነበርና የሆነው አሜን ብላችሁ ተቀበሉ ። በተፈቀደላችሁ፥ ዛሬ ላይ ደርሳችኋልና ፈጽሞ ሳታማሩ በምስጋና ታጅባችሁ ትግላችሁን ቀጥሉ ።
ሳበቃ
" እግዚአብሔር_ሰጠ_እግዚአብሔር_ነሳ !!!"
/መ/ር ዘር-ይሁን/
ለእኛም ሁሉም ነገር ለበጎ ነው የምንልበት ልብ ይስጠን🙏
በትንሽ ፈተና እግዚአብሔርን ለሚያማርሩ ይጠቅማልና ሼር አድርጉት

19/07/2025

በሌሊት በቤተ መቅደስ ውስጥ እጆቻችሁን አንሡ እግዚአብሔርንም ባርኩ።
ሰማይንና ምድርን የሠራ እግዚአብሔር ከጽዮን ይባርክህ። መዝ 133:2-3

19/07/2025

➴ነገ ሐምሌ 13 ፈታሄ ማህፀን ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡

ወቶ ከመቅረት ካልታሰበ አደጋ ከክፉ ነገር ሁሉ ይሰውረን።እኛንም ለንስሐ ሞት ያብቃን::💖🙏

19/07/2025

ነገ ሐምሌ 13 ቅዱስ ሩፋኤል ሀኪም ሰማያዊ ፈታሄ ማህፀን ነዉ
እንኳን አደረሳችሁ !!!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ፍቅረ ዘማሪያም - Fikre Zemariyam posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

BERNOS MEDIA - በርኖስ ሚዲያ

BERNOS MEDIA - በርኖስ ሚዲያ በማህበረሰብ ውስጥ ገብቶ ኑሮውን ፣ ደስታውን ፣ ሀዘኑን ፣ ወጉን ፣ ባህሉን ፣ ታሪኩን ችግሩን አውጥቶ ጥሩ ከሆነ ሌላው ተካፍሎ እንዲለወጥበት ፣ መጥፎ የማህበረሰብ እንከን ካለ ደግሞ ሰው ይሔንን አውቆ በግዜ በእንጭጩ እንዲቀጨው መረጃ በማቀበል ንቃተ ህሊናው የዳበረ ማህበረሰብ ለመፍጠር በ2013 ዓ/ም የተመሰረተ ሚዲያ ነው፡፡