የአቃቂ ቃሊቲ ነዋሪዎች ድምጽ/the voice of Akaki Kaliti peoples

የአቃቂ ቃሊቲ ነዋሪዎች ድምጽ/the voice of Akaki Kaliti peoples Feed News Information & Advertisement to all facebook users.
እውነተኛ መረጃ እናቀርባለን

ኮሜርሻል ኖሚኒስ በግንባር ቀደም ታማኝ ግብር ከፋይነት ለተከታታይ ስድስት ዓመታት ተሸላሚ ሆኗል*******************************• በ6ኛው የታማኝ የግብር ከፋዮች ሽልማት የወ...
11/10/2024

ኮሜርሻል ኖሚኒስ በግንባር ቀደም ታማኝ ግብር ከፋይነት ለተከታታይ ስድስት ዓመታት ተሸላሚ ሆኗል
*******************************
• በ6ኛው የታማኝ የግብር ከፋዮች ሽልማት የወርቅ ተሸላሚ ሆነናል፤
• በቀጣይም አዳዲስ ሥራዎችን በመጨመር እና ገቢን በማሳደግ የላቀ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንሠራለን፤
• ለእውቅና ሽልማቱን አስመልክቶ የምስጋና መርሐ ግብርም ተከናውኗል፤
አዲስ አበባ ጥቅምት 01/ 2017 (ሲኤን) ኮሜርሻል ኖሚኒስ በ2016 ዓ.ም በከፈለው ዓመታዊ ግብር የወርቅ ደረጃ ግንባር ቀደም ታማኝ ግብር ከፋይ ተሸላሚ ሲሆን፣ በተከታታይ ለስድስት ዓመታት የፕላቲኒየምና የወርቅ ደረጃ ከፍተኛ ግብር ከፋይ በመሆኑም ተመስግኗል፡፡

መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም ስድስተኛው ዙር የፌደራል ታማኝ ግብር ከፋዮች እውቅና እና ሽልማት ሥነ-ስርዓት ላይ የኮሜርሻል ኖሚኒስ ዳይሬክተር ጀነራል ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ተገኘተው የድርጅቱን ሽልማት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ እጅ ተቀብለዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ በመገኘት ለታማኝ ግብር ከፋዮች እውቅና እና ሽልማት የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ሀገራዊ ግዴታቸውን በታማኝነት ለተወጡት ግብር ከፋዮች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በመልዕክታቸው ለበለጠ ጥቅም ሁላችንም የምንካፈለው ግዴታችንም ነው ብለዋል።

ለታማኝነታችሁ መንግስት የከፈላችሁት ግብር በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል በማድረግ ለጋራ እድገታችን ወሳኝ በሆኑ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ባሉ ግዙፍ የሀገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ አስተዋፅዖችሁን በማዋል ይህንን አደራ ያከብራል።

በግብር አሰባሰብ ላይ አወንታዊ ለውጦች እየታዩ ቢሆንም፣ ይህን ጥሩ ጅማሮ ማስቀጠል ይኖርብናል። ሙስናን መቀነስ እና የግብር አሰባሰብ ስርዓታችንን ማዘመን ለሁሉም የተመቸ፣ ግልፅ፣ ቀልጣፋ እና ፍትሃዊ አሰራር ለመፍጠር ወሳኝ ናቸው ብለዋል።

ለእውቅና ሽልማቱ ጥቅምት 1ቀን 2017 ዓ.ም የኮሜርሻል ኖሚኒስ ዋናው መስሪያቤት የምስጋና መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል።

የድርጅታችን ዳይሬክተር ጀነራል ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ በመርሐ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት፤ በግንባር ቀደም ታማኝ ግብር ከፋይነት ያገኘነው ሽልማት የሠራተኞቻችን፣ የማኔጅመንት አባላቱና የደንበኞቹም ጭምር በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ ማለት እወዳለሁ ብለዋል፡፡

በቀጣይ ሥራችንን በማስፋትና ገቢያችንን በማሳደግ የላቀ አፈጻጸም በማምጣት ተጠቃሚነታችንንና ለሀገር የምናደርገውን አስተዋፆ ይበልጥ እናጠናክራለን ብለዋል።

ሀገራዊ ኃላፊነታችን ለመወጣት እንደተጋነው ሁሉ በአገልግሎት አሰጣጣችን አሁን ካላን ጥራት በላቀ ሁኔታ በመፈጸም የበለጠ ውጤታማ መሆን ይገባናል ብለዋል።

ኮሜርሻል ኖሚኒስ ባለፉት ስድስት ዓመታት የወርቅ እና የፕላቲኒየም ተሸላሚ ተቃማኝ ግብር ከፋይ መሆኑ ይታወቃል።

06/10/2024

በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ዛሬ ምሽት 2:10 አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። እኔ ባለሁበት አካባቢ (ቃሊቲ) እኔ ያልሰማሁት የአካባቢው ነዋሪ ሰምቶ መንገድ ዳር ወጥቶ የተሸበረበትን አጋጣሚ ታዝቢያለሁ። የሚመለከተው አካል መግለጫ ቢሰጥ ጥሩ ነው።

ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያምና ግማደ መስቀሉ ንባርኮ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤ ንፍሑ ቀርነ በጽዮን፤ ስብኩ በዓለ ማርያም ወበዓለ መስቀል ዘዮም።ሃሌ...
01/10/2024

ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያምና ግማደ መስቀሉ
ንባርኮ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤
ስቡሕኒ ውእቱ ወልዑልኒ ውእቱ ለዓለም፤
ንፍሑ ቀርነ በጽዮን፤ ስብኩ በዓለ ማርያም
ወበዓለ መስቀል ዘዮም።
ሃሌ ሃሌ ሉያ፤
ወረከበ ደብረ ከርቤ ዕፀ መስቀሉ ለክርስቶስ፡፡
እውነት በእውነት
የክርስቶስ ዕፀ መስቀሉ በደብረ ከርቤ ተቀመጠ፡፡
መስከረም 21 ቀን የግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም ዓመታዊ ንግሥ ነው፡፡ እንኳን አደረሰን፤ እንኳን አደረሳችሁ /ፎቶ ከማኅበራዊ ድረገጽ የተወሰደ/

በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ታራሚዎች ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማምጣት ችለዋል*****...
18/09/2024

በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ታራሚዎች ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማምጣት ችለዋል
****************
በፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩ 21 የተፈጥሮ ሳይንስ የህግ ታራሚ ተማሪዎች መካከል ሰባቱ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችለውን ውጤት ማምጣት ችለዋል፡፡

የቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የመጀመሪያ ደረጃና አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ሳምሶን ወንድሜነህ የህግ ታራሚ ተማሪዎች ምንም እንኳ በህግ ጥላ ስር ቢሆኑም ትምህርታቸውን በአግባቡ ሲከታተሉ መቆየታቸውንና ለውጤት መብቃታቸውን ገልፀዋል፡፡

ተማሪ የህግ ታራሚዎቹ የመልቀቂያ ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀውን የሙከራ ሞዴል ፈተና መውሰዳቸው ለውጤታቸው አበርክቶ እንደነበረው የተናገሩት የትምህርት ቤቱ የጋይዳንስና ካውንስሊንግ ባለሙያ አቶ ለይኩን ግርማ፤ የተቋሙ የስነ ልቦና ባለሙያዎችም ድጋፍ እንዳደርጉላቸው ተናግረዋል፡፡

ታራሚዎችን በማረምና ማነፅ ሂደት ሁሉም ዜጋ ተሳታፊ መሆን እንዳለበት የጠቆሙት በቃሊቲ ማረሚያ ማዕከል የማረምና ማነፅ ትምህርትና ስልጠና ማስተባበሪያ ተወካይ አቶ ታሪኩ ጋዲሳ ተማሪ የህግ ታራሚዎቹን የትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ያመጡት የህግ ታራሚ ተማሪዎች እንደሚሉት በማረሚያ ቤት ውስጥ በእርምት ላይ ሆነው ፈተናውን መውሰድ ከባድ ተፅዕኖ ቢኖረውም ውጤታማ መሆን ችለናል ብለዋል፡፡
ያመጡት ውጤት ለመታረማቸው ማሳያ በመሆኑ የፍትህ ሚኒስቴር በይቅርታና ምህረት መልቀቅ የሚችልበትን እድል እንዲያገኙ ካልሆነም ትምህርታቸውን በርቀት እንዲከታተሉ ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲያመቻችላቸው ጠይቀዋል፡፡
(EBC)

የአዲስ ዘመን መባቻ ላይ ነንና ይቅር እንባባል*****************************“አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፤ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ።”ይቅርታ የሚለው ቃል ሣህል ...
10/09/2024

የአዲስ ዘመን መባቻ ላይ ነንና ይቅር እንባባል
*****************************
“አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፤ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ።”

ይቅርታ የሚለው ቃል ሣህል ከሚለው ከግዕዙ ስርወ ቃል የተገኘ ሲሆን፤ይቅርታ ርኅራኄ ምሕረት ዕርቅ ፍቅር ማለት ነው፡፡ የእንግሊዘኛው አቻ ቃል “ፓርደን/Pardon/” ሲሆን፤ ፔርዱኔሬ/pardoner/ ከሚለው የላቲን ቃል የመጣ ሲሆን፤ የቀጥታ ትርጓሜውም በነጻ መሳናበት ወይም በወንጀል ጥፋተኛ የሆነ ሰው ቅጣቱን መተው ወይም ተግባራዊ አለማድረግ ብሎም ምኅረት ማድረግን ይጨምራል፡፡

ኢትዮጵያችን ካለፉት 50 ዓመታት በላይ በተለይም ካለፉት 30 ዓመታት፤ ጠበብ ስናደርገውም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ጠብ፣ ክርክር፣ መጠፋፋትና መከፋፋት ሀገር ሆናለች።በዚህም ምክንያት እኛ ኢትዮጵያውያን ቂመኞች፣ ዘረኞችና አድመኞች ሆነናል። እለት እለት ውኃ በማይቋጥር ምክንያትና በየአጋጣሚው ሁሉ ስንቆሳሰል እንውላለን፤ እናድራለን። መቀሳሰላችንም ትናንት አብረን ያልኖርንና የማንኖር አስመስሎናል። ይሄንን ቁርሾ ብቸኛው አስወጋጅ መንገድ ይቅርታ መሆኑን ሊቃውንትም መጽሐፍትም በአንድ ቃል የሚመሰክሩት እውነት ነው። ታላቁ መጽሐፍ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ‹‹ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም፡፡›› እንዲል (ማቴ. 6፥13)።

ትናንት ጳጉሜን 4 ቀን 2016 ዓ/ም በዓለም ሁሉ ባሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት የተነበበው ወንጌል የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 18 ከቁጥር 23 እስከ ፍዓሜ ያለው የወንጌል ክፍል ነው። እዚህ የወንጌል ክፍል ላይ “ስለዚህ መንግሥተ ሰማያት ባሮቹን ሊቈጣጠር የወደደን ንጉሥ ትመስላለች። መቈጣጠርም በጀመረ ጊዜ፥ እልፍ መክሊት ዕዳ ያለበትን አንድ ሰው ወደ እርሱ አመጡ።
የሚከፍለውም ቢያጣ፥ እርሱና ሚስቱ ልጆቹም ያለውም ሁሉ እንዲሸጥና ዕዳው እንዲከፈል ጌታው አዘዘ። ስለዚህ ባሪያው ወድቆ ሰገደለትና። ጌታ ሆይ፥ ታገሠኝ፥ ሁሉንም እከፍልሃለሁ አለው። የዚያም ባሪያ ጌታ አዘነለትና ለቀቀው፥ ዕዳውንም ተወለት። ነገር ግን ያ ባሪያ ወጥቶ ከባልንጀሮቹ ከባሮቹ መቶ ዲናር ዕዳ ያለበትን አንዱን አገኘና። ዕዳህን ክፈለኝ ብሎ ያዘና አነቀው። ስለዚህ ባልንጀራው ባሪያ ወድቆ። ታገሠኝ፥ ሁሉንም እከፍልሃለሁ ብሎ ለመነው። እርሱም አልወደደም፥ ግን ሄዶ ዕዳውን እስኪከፍል ድረስ በወኅኒ አኖረው። ባልንጀሮቹ የሆኑ ባሮችም ያደረገውን አይተው እጅግ አዘኑ፥ መጥተውም የሆነውን ሁሉ ለጌታቸው ገለጡ። ከዚያ ወዲያ ጌታው ጠርቶ። አንተ ክፉ ባሪያ፥ ስለ ለመንኸኝ ያን ዕዳ ሁሉ ተውሁልህ፤ እኔ እንደ ማርሁህ ባልንጀራህ የሆነውን ያን ባሪያ ልትምረው ለአንተስ አይገባህምን? አለው። ጌታውም ተቈጣና ዕዳውን ሁሉ እስኪከፍለው ድረስ ለሚሣቅዩት አሳልፎ ሰጠው። ከእናንተ እያንዳንዱ ወንድሙን ከልቡ ይቅር ካላለ፥ እንዲሁ ደግሞ የሰማዩ አባቴ ያደርግባችኋል።”የሚል እጅግ ድንቅ መልእክት አለ። እኛ ኢትየጵያውያን በጠላቶቻችን እንድንለያይ በየዘመናቱ ያልተሰራብን ሴራ የለም። በፈጣሪ እንዳንነጣጠል በስውር ስፌት የተሰፋን ነንና በተሠራው ሴራ ግን አልተለያየንም፤ አንለያይምም።

ስለሆነም በጥላቻ ተለያየተን የተገዳደልንበት፣ አንዳችን አንዳችን ላይ ክፋት ያደረግንበት፣ የተገፋፋንበት፣ የተጣላንበትና የተናናቅንበት ያለፈው ዘመን ይበቃናልና ሁላችን ከራሳችን ጀምሮ ከልብ ይቅር እንባባል። ይቅርታ ከአፍ ብቻ ሳይሆን ከልብ የሚመነጭ ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ካስተማረው አንዱ ስለይቅርታ ነው፡፡ ‹‹ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም፡፡›› እንዲል (ማቴ. 6፥13)
ያለነው በአዲስ ዘመን መባቻ ላይ ነው። አዲሱ ዘመን ደግሞ የተባረከ እንዲሆን ይቅርታንና፣ ይቅር መባባል ይፈልጋል። ያለፈውን ዘመን አሳልፎ አዲሱን ዘመን በሠላም እንዲያስጀምረን ፈጣሪን ለመለመን በየእምነት ቤቶች ከመሄዳችን በፊት መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን ወንድማችንን ይቅር በማለት ዘመኑን እንሻገር። በማቴ 5÷23-24 ባለው ኃይለ ቃል፤ “እንግዲህ መባህን በመሰዊያው ላይ ብታቀርብ፣ በዚያም ወንድምህ አንዳች አንተ ላይ እንዳለው ብታስብ፣ በዚያ በመሰዊያው ፊት መባህን ትተህ ሂድ፤ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፤ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ።” ያለውን አምላካዊ ቃል አስበን አዲሱን ዘመን በይቅርታ ለመቀበል የተዘጋጀን መሆን ይገባናል።

መስኪን እንወዳጃት?.********************ከማኀበረ ቅዱሳን  መደበኛ (የሙሉ ጊዜ አገልግሎት) በተለይም ከቴሌቪዥኑ የ5 ዓመታት የኃላፊነት አገልግሎት ሰሞኑን የለቀቀችው እህታችን ተ...
05/09/2024

መስኪን እንወዳጃት?.
********************
ከማኀበረ ቅዱሳን መደበኛ (የሙሉ ጊዜ አገልግሎት) በተለይም ከቴሌቪዥኑ የ5 ዓመታት የኃላፊነት አገልግሎት ሰሞኑን የለቀቀችው እህታችን ተወዳጇዋ ጋዜጠኛ መስከረም ጌታቸው በመስከረሙ ዋዜማ በ"መስከረም ሚድያ" ተከስታለች። እህታችን ቤተክርስቲያንን ማገልገል የቤተ ክርስቲያን ራሷን ክርስቶስን ማገልገል ነውና ክርስቶስ አገልግሎትሽን ይባርከዋል። እኛም ሳይገባን አገልግለን ክርስቶስ ኢየሱስ በቸርነቱ ባርኮናል። ወንድሞች እንዲሁም እህቶች መስኪን እንወዳጃት?.
https://youtube.com/channel/UCzzbnGov2lpY2yqEl8akJLw...

ነዋሪነቱን በአሜሪካን ሀገር የኾነው አቶ ጥበበ እሸቱ (የገንዬ ልጅ) ለመቄዶኒያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ተቋም በመገኘት ለ7 ሺ 500 ወገኖችን የምሳ ግብዣ እና ስጦታ አበርክቷ...
08/05/2024

ነዋሪነቱን በአሜሪካን ሀገር የኾነው አቶ ጥበበ እሸቱ (የገንዬ ልጅ) ለመቄዶኒያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ተቋም በመገኘት ለ7 ሺ 500 ወገኖችን የምሳ ግብዣ እና ስጦታ አበርክቷል

**********************************************

ጥበበ እሸቱ አብሮ አደጋችን የጋራ ልጆች የሚወዷቸው የአባባ እሸቱ እና የገነት አበበ (ገንዬ) ልጅ ነው። ሁላችን የምንወዳት ገንዬ እኔ ዛሬ ጓደኞቼንና ደጋግ ወንድምና እህቶችን አስተባብሬ ያስቀጠልኩት ነዳያንን ለፋሲካ የማስፈስከው መርሐ ግብር በገንዬ እና በህቴ አማረች ጥላሁን የዛሬ 29 ዓመት የተጀመረ የትሩፋት ሥራ ነው።

እነሆ ይሄንን መልካም ምግባር አብሮ አደጋችን ጥበበ እሸቱ የእናቱን (የገንዬን) መልካም ተግባር ወርሶ ትናንት ሚያዝያ 29 ቀን 2016 ዓ.ም በተከናወነው መርሐ ግብር ላይ አቶ ጥበበ እሸቱ ለመቄዶኒያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን የምሳ መርሐ ግብርና ግምታዊ ወጪያቸው ከ2 ነጥብ 5 ሚልየን ብር በላይ የተለያዩ አልባሳትን የለገሰ መሆኑን ከተለያዩ የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ለማወቅ ችለናል።

አቶ ጥበበ ከዚህ ቀደም በሰሜኑ ጦርነት ጊዜም የተፈናቀሉ ወገኖችን ከመደገፍም ባሻገር 140 ለሚደርሱ የጋሸና አካባቢ ነዋሪዎች ቤት ሰርተው ማስረከባቸውን ሚዲያዎቹ ዘግበዋል።

በቅርቡም በትግራይና በአማራ ክልል ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቃቸውን ጠቁመዋል።

አቶ ቢኒያም በለጠ ለተደረገው ሰብዓዊተግባር በአረጋውያኑ እና በድርጅታቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

ጥበበ እሸቱ በአቃቂ ከተማ ከመንበረ ሕይወት መድኃኔ ዓለም ቤቴ ክርስቲያ ሥር ጋራ ላይ ያደጉ አብሮ አደግ ወንድማችን ናቸው። አቶ ጥበበ ክብረት ይስጥልን።

"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤++++++++++++++++++++++"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤ የህያውን አምላክ ልጅ አሠሩት፤ በቁጣ ጎተቱት፤ በፍቅ...
03/05/2024

"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤
++++++++++++++++++++++

"ሁሉን የያዘውን ያዙት፤ ሁሉን የሚገዛውን አሠሩት፤ የህያውን አምላክ ልጅ አሠሩት፤ በቁጣ ጎተቱት፤ በፍቅር ተከተላቸው። በሚሸልተው ፊት እንደማይናገር እንደ የዋህ በግ በኋላቸው እየተከተለ ወሰዱት፤ ሊቃነ መላእክት በመፍራት እና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤

ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፥ በመኳንንት የሚፈርደውንም በእርሱ ፈረዱበት፤ ለሱራፌል ዘውድ የሚያቀዳጃቸውን የሾህ ዘውድ አቀዳጁት፤ ለኪሩቤል የገርማ ልብስ የሚያለብሳቸውን ለመዘበት ቀይ ግምጃ አለበሱት፤ ኪሩቤል በእሳት ክንፍ ተሸፍነው በፊቱ የሚሰወሩለትን እርሱን ክፉ ባሪያ አሥሮ ፊቱን ጸፋው፤ የመላእክት ሠራዊት በፍጹም መደንገጥ የሚሰግዱለት እየዘበቱበት በፊቱ ተንበረከኩ፡፡

ይህን ያህል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? ይህን ያህል ትእግስት እንደምን ያለ ትእግስት ነው? ይህን ያህል ዝምታ እንደምን ያለ ዝምታ ነው? ይህን ያህል ቸርነት እንደምን ያለ ቸርነት ነው? ኃያል ወልድን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደበደለኛ ሰቀሉት፡፡ ህይወትን የሠራውን ከበደለኞች ጋር ቆጠሩት፤ አዳምን የሠሩ እጆች በመስቀል ቀኖዎት ተቸነከሩ፤ ወዮ በገነት የተመላለሱ እግሮች በመስቀል ተቸነከሩ፡፡

ወዮ በአዳም ፊት የህይወት እስትንፋስን እፍ ያለ አፍ ከሃሞት ጋር የተቀላቀለ የኮመጠጠ መፃፃን ጠጣ፤... ወዮ የወልድን መከራውን የሚናገር ምን አፍ ነው? ምን ከንፈር ነው? ምንስ አንደበት ነው? የፍቁሩ የጌታ ህማማት በተነገረ ጊዜ ልብ ይለያል፤ ህሊናም ይመታል፤ ነፍስም ትንቀጠቀጣለች፤ ሥጋም ይደክማል የማይሞተው ሞተ፤ ሞትን ይሽረው ዘንድ ሞተ፤ ሙታንን ያድናቸው ዘንድ ሞተ። የምትወዱት ሰዎች ፈጽሞ አልቅሱለት፡፡"
/ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ/

ሆሳእና በአርያም፤ እንኳን አደረሳችሁ።
28/04/2024

ሆሳእና በአርያም፤ እንኳን አደረሳችሁ።

ነገ ውድ ኦርቶዶክሳውያን የማይቀሩበት መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል+++++++++መምህራችን መጋቤ ሐዲስ ቀሲስ ምንአለ ኦርቶዶክሳውን ሌሎች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች በሚገባ የሚመልስ ''በተቃዋሚዎች ...
20/04/2024

ነገ ውድ ኦርቶዶክሳውያን የማይቀሩበት መርሐ ግብር ተዘጋጅቷል
+++++++++
መምህራችን መጋቤ ሐዲስ ቀሲስ ምንአለ ኦርቶዶክሳውን ሌሎች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች በሚገባ የሚመልስ ''በተቃዋሚዎች አንዳች አትደንግጡ '' በሚል ርዕስ ያዘጋጁትን መጽሐፍ ነገ ሚያዝያ 13ቀን 2016ዓ.ም አቃቂ ዓለምባንክ በሚገኘው ራማ ኮንስትራክሽን ሕንጻ ላይ ከቀኑ በሰባት ሰዓት ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ መምህራነ ወንጌልና ዘማሪያን በሚገኙበት ያስመርቃሉና በዕለቱ በመገኘት መምህራችንን እናበርታቸው እኛም የበረከቱ ተካፋይ እንሁን።

ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በአገልግሎት ላይ ሳሉ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው++++++++++++++++++++++ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚዘዋወር ...
15/04/2024

ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በአገልግሎት ላይ ሳሉ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው
++++++++++++++++++++++

ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚዘዋወር ስብከታቸው የሚታወቁት ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በአገልግሎት ላይ ሳሉ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ተገለጸ ።

በአሦርያውያን ቤተ ክርስቲያን የአውስትራሊያ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች በእንግሊዝኛ እና ዐረብኛ ቋንቋዎች በሚያስተላልፉት ስብከት የሚታወቁ ሲሆን በሲድኒ በሚገኝ አንድ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ሳሉ በአንድ ግለሰብ አማካይነት በስለት መወጋታቸው ተገልጿል።

የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስም ጥቃቱን የፈፀመውን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተናግሯል። የኒው ሳውዝ ዌልስ የአምቡላንስ አገልግሎት በዕለቱ ጥቃቱ በደረሰበት ወቅት አራት ሰዎች ቆስለዋል ብሏል።

ሊቀ ጳጳሱ የሕክምና እርዳታ ተደርጎላቸው በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተዘግቧል።

በዕለቱ በሠላሳዎቹ ውስጥ ከሚገኝ ወጣት በተጨማሪ በከባድ ሁኔታ ወደ ሆስፒታል የተወሰደው በሀምሳዎቹ ውስጥ የሚገኝ አንድ ሰው መኖሩንና በርካታ ቦታዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰበት ከዘገባው ለመገንዘብ ተችሏል።

09/04/2024

የግእዝ ቁጥሮች በአኀዝ፣ በፊደል እና በዐረብኛ ቁጥር
+++++++++++++++++++++++++++++++++++
– አልቦ =0
፩ አሐዱ =1
፪ ክልኤቱ =2
፫ ሠለስቱ =3
፬ አርባዕቱ =4
፭ ሐምስቱ =5
፮ ስድስቱ =6
፯ ስብዓቱ =7
፰ ስመንቱ 8
፱ ተሰዓቱ 9
፲ አሠርቱ 10
፲፩ አሠርቱ ወአሐዱ 11
፲፪ አሠርቱ ወክልኤቱ 12
፲፫ አሠርቱ ወሠለስቱ 13
፲፬ አሠርቱ ወአርባዕቱ 14
፲፭ አሠርቱ ወሐምስቱ 15
፲፮ አሠርቱ ወስድስቱ 16
፲፯ አሠርቱ ወሰብዓቱ 17
፲፰ አሠርቱ ወስመንቱ 18
፲፱ አሠርቱ ወተሰዓቱ 19
፳ እስራ 20
፳፩ እስራ ወአሐዱ 21
፳፪ እስራ ወክልኤቱ 22
፳፫ እስራ ወሠለስቱ 23
፳፬ እስራ ወአርባዕቱ 24
፳፭ እስራ ወሐምስቱ 25
፳፮ እስራ ወስድስቱ 26
፳፯ እስራ ወሰብዓቱ 27
፳፰ እስራ ወሰመንቱ 28
፳፱ እስራ ወተሰዓቱ 29
፴ ሠላሳ 30
፴፩ ሠላሳ ወአሐዱ 31
፴፪ ሠላሳ ወክልኤቱ 32
፴፫ ሠላሳ ወሠለስቱ 33
፴፬ ሠላሳ ወአርባዕቱ 34
፴፭ ሠላሳ ወሐምስቱ 35
፴፮ ሠላሳ ወስድስቱ 36
፴፯ ሠላሳ ወሰብዓቱ 37
፴፰ ሠላሳ ወሰመንቱ 38
፴፱ ሠላሳ ወተሰዓቱ 39
፵ አርብዓ 40
፶ ሃምሳ 50
፷ ስድሳ 60
፸ ሰብዓ 70
፹ ሰማንያ 80
፺ ተሰዓ 90
፻ ምዕት 100
፻፩ ምዕት ወአሐዱ 101
፻፪ ምዕት ወክልኤቱ 102
፻፫ ምዕት ወሠለስቱ 103
፻፬ ምዕት ወአርባዕቱ 104
፻፭ መዕት ወሐምስቱ 105
፻፮ ምዕት ወስድስቱ 106
፻፯ ምዕት ወሰብዓቱ 107
፻፰ ምዕት ወስመንቱ 108
፻፱ ምዕት ወተሰዓቱ 109
፻፲ ምዕት ወአሠርቱ 110
፻፲ወ፩ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ 111
፻፲ወ፪ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ 112
፻፲ወ፫ ምዕት አሠርቱ ወሠለስቱ 113
፻፲ወ፬ ምዕት አሠርቱ ወአርባዕቱ 114
፻፲ወ፭ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ 115
፻፲ወ፮ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ 116
፻፲ወ፯ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ 117
፻፲ወ፰ ምዕት አሠርቱ ወስመንቱ 118
፻፲ወ፱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ 119
፻፳ ምዕት ወእስራ 120
፻፴ ምዕት ወሠላሳ 130
፻፵ ምዕት ወአርብዓ 140
፻፶ ምዕት ወሃምሳ 150
፻፷ ምዕት ወስድሳ 160
፻፸ ምዕት ወሰብዓ 170
፻፹ ምዕት ወሰማንያ 180
፻፺ ምዕት ወተሰዓ 190
፪፻ ክልኤቱ ምዕት 200
፪፻ወ፩ ክልኤቱ ምዕት ወአሐዱ 201
፪፻ወ፪ ክልኤቱ ምዕት ወክልኤቱ 202
፪፻ወ፫ ክልኤቱ ምዕት ወሠለስቱ 203
፪፻ወ፬ ክልኤቱ ምዕት ወአርባዕቱ 204
፪፻ወ፭ ክልኤቱ ምዕት ወሐምስቱ 205
፪፻ወ፮ ክልኤቱ ምዕት ወስድስቱ 206
፪፻ወ፯ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓቱ 207
፪፻ወ፰ ክለኤቱ ምዕት ወስመንቱ 208
፪፻ወ፱ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓቱ 209
፪፻ወ፲ ክልኤቱ ምዕት ወአሠርቱ 210
፪፻፲ወ፩ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአሐዱ 211
፪፻፲ወ፪ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወክልኤቱ 212
፪፻፲ወ፫ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሠልስቱ 213
፪፻፲ወ፬ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወአርባቱ 214
፪፻፲ወ፭ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሐምስቱ 215
፪፻፲ወ፮ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወስድስቱ 216
፪፻፲ወ፯ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰብዓቱ 217
፪፻፲ወ፰ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወሰመንቱ 218
፪፻፲ወ፱ ክልኤቱ ምዕት አሠርቱ ወተሰዓቱ 219
፪፻፳ ክልኤቱ ምዕት ወእስራ 220
፪፻፴ ክልኤቱ ምሪዕት ወሠላሳ 230
፪፻፵ ክልኤቱ ምዕት ወአርብዓ 240
፪፻፶ ክልኤቱ ምዕት ወሃምሳ 250
፪፻፷ ክልኤቱ ምዕት ወስድሳ 260
፪፻፸ ክልኤቱ ምዕት ወሰብዓ 270
፪፻፹ ክልኤቱ ምዕት ወሰማንያ 280
፪፻፺ ክልኤቱ ምዕት ወተሰዓ 290
፫፻ ሠለስቱ ምዕት 300
፬፻ አርባዕቱ ምዕት 400
፭፻ ሐምስቱ ምዕት 500
፮፻ ስድስቱ ምዕት 600
፯፻ ስብዓቱ ምዕት 700
፰፻ ስመንቱ ምዕት 800
፱፻ ተሰዓቱ ምዕት 900
፲፻ አሠርቱ ምዕት 1000
፳፻ እስራ ምዕት 2000
፴፻ ሠላሳ ምዕት 3000
፵፻ አርብዓ ምዕት 4000
፶፻ ሃምሳ ምዕት 5000
፷፻ ሳድስ ምዕት 6000
፸፻ ሰብዓ ምዕት 7000
፹፻ ሰማንያ ምዕት 8000
፺፻ ተሰዓ ምዕት 9000
፻፻ እልፍ 10,000
፪፻፻ ክልኤቱ እልፍ 20,000
፫፻፻ ሠለስቱ እልፍ 30,000
፬፻፻ አርባዕቱ እልፍ 40,000
፭፻፻ ሐምስቱ እልፍ 50,000
፮፻፻ ስድስቱ እልፍ 60,000
፯፻፻ ሰብዓቱ እልፍ 70,000
፰፻፻ ስመንቱ እልፍ 80,000
፱፻፻ ተሰዓቱ እልፍ 90,000
፲፻፻ አሠርቱ እልፍ 100,000
፳፻፻ እስራ እልፍ 200,000
፴፻፻ ሠላሳ እልፍ 300,000
፵፻፻ አርብዓ እልፍ 400,000
፶፻፻ ሃምሳ እልፍ 500,000
፷፻፻ ስድሳ እልፍ 600,000
፸፻፻ ሰብዓ እልፍ 700,000
፹፻፻ ሰማንያ እልፍ 800,000
፺፻፻ ተሰዓ እልፍ 900,000
፻፻፻ አእላፋት 1,000,000
፲፻፻፻ ትእልፊት 10,000,000
፻፻፻፻ ትልፊታት 100,000,000
፲፻፻፻፻ ምእልፊት 1,000,000,000

Address

Akaki KAlity Sub City
Addis Ababa
251

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአቃቂ ቃሊቲ ነዋሪዎች ድምጽ/the voice of Akaki Kaliti peoples posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የአቃቂ ቃሊቲ ነዋሪዎች ድምጽ/the voice of Akaki Kaliti peoples:

Share