OmniMedia Ethiopia

OmniMedia Ethiopia OmniMedia is a media analytics company based in Ethiopia.

- የኢትዮጵያና የሶማሊላንድ ነገር    - ግብፆች ሶማሊያ ገብተዋል። በጣም ብዙ መሣሪያ እያመላለሱ ሲሆን አሜሪካ ደግሞ ለግብፅ የ1.3 ቢሊዮን ዶላር የጦር መሣሪያ እርዳታ ለመልቀቅ ወስናለች...
23/09/2024

- የኢትዮጵያና የሶማሊላንድ ነገር
- ግብፆች ሶማሊያ ገብተዋል። በጣም ብዙ መሣሪያ እያመላለሱ ሲሆን አሜሪካ ደግሞ ለግብፅ የ1.3 ቢሊዮን ዶላር የጦር መሣሪያ እርዳታ ለመልቀቅ ወስናለች። ይህ እርዳታ በየአመቱ ይሰጥ የነበረና ታግዶ የቆየ ነው። እርዳታው ግብፅ ለእስራኤል ለምታደርግላት የፖለቲካ ድጋፍ ክፍያ መሆኑ ነው። ግብፅና እስራኤል በፕሬዚዳንት ካርተር አስተባባሪነት በአሜሪካው ካምፕ ዴቪድ በ1978 እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር የተደረገ ስምምነት አላቸው። ግብፅ ከዛ ስምምነት በኋላ ፍልስጤማውያንን ከድታ የእስራኤልን ሀገርነት ተቀብላ ሌሎች የአረብ ሀገሮች እንዳይረብሹ ታስተባብራለች። ለዚህም በየአመቱ የ1.3 ቢሊዮን ዶላር የጦር መሣሪያ እርዳታ ይሠጣታል ከአሜሪካ። ይህ በሌሎች የኢኮኖሚና ድህነት ቅነሣ ዘርፎች አሜሪካ ለግብጽ ከምትሠጠው እርዳታ ውጭ ነው። በአጠቃላይ አሜሪካ ለግብጽ በየአመቱ በአማካይ እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር ትደጉማለች።
- የሶማሊያው የውጭጉዳይ ሚኒስትር በዚህ ሳምንት መጀመሪያ አከባቢ በሰጡት ቃለመጠይቅ “የኢትዮጵያን መንግስት እየተዋጉ ያሉ የኢትዮጵያ አማጺዎችን ለመርዳት እንፈልጋለን። ከነርሱም ጋር ግንኙነት ለመፍጠር ጥሪ እናቀርባለን በራሳቸውም ፍላጎት ከመጡ እናግዛቸዋልን ብለን አስበናል” ብለዋል ባለፈው ሳምንት። ከዚህ ቀደም የዛሬ 15 ቀን ገደማ ኦነግ ሸኔና የሶማሊያው አልሻባብ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን ብቻ ሳይሆን እየሰሩም እንደሆነ የኬኒያና የኢትዮጵያ የደህንነት ሰዎች በጋራ መግለጫ ሰጥተው ነበረ። የሚያስገረመው በጋዜጠኛው “ ከህውሃት ጋር ግንኙነት ጀምራችኋል ወይ?” ተብለው የተጠየቁት ሚኒስትረ “ኢትዮጵያ እንድትበታተን የሶማሊያ መንግስት ፍላጎት አይደለም። መበታተኗም ይጎዳናል።” ሲሉ አስገራሚ መልስ ሰጥተዋል። በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ መንግስት በይፋዊ ሁኔታ በአማራ ክልል ከፋኖዎች ጋር፣ በኦሮሚያ ክልል ከኦነግ ሸኔ ጋር ግጭት ውስጥ ይገኛል። በሶማሊ ክልል ይንቀሳቀስ የነበረውና ከፍተኛ አቅም የነበረው የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ወደሰላማዊ ትግል ተመልሶ ግጭት ማቆሙ የሚታወስ ነው። በመሆኑም ሶማሊያ ለኢትዮጵያዊ ታጣቂዎች ድጋፍ እሰጣለሁ ካለች አብረዋት ሊንቀሳቀሱ የሚችሉት ሃይሎች እነዚሁ ሁለት ቡድኖች ብቻ ይሆናሉ ማለት ነው። የሚያስገርመው ነገር ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የምትዋሰነውን ድንበር መቆጣጠር የማትችል ሲሆን ጭርሱን የሶማሊያ መንግስት ከሞቃዲሾ ውጭ ምንም አይነት ተጽዕኖ የሌለው መሆኑ ነው። ምናልባት የሚሰጥ ድጋፍም ካለ በሞቃዲሾ ቢሮዋቸውን እንዲክፍቱ እንዲሁም ከነግብጽ ጋር በይፋ እንዲገናኙ የማገዝ ካልሆነ በቀር ተርፎ የሚሰጥ ገንዘብም፣ የመንቀሳቀሻ ቦታም ሆነ የፖለቲካ አቅም የላትም ሶማሊያ።
- በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ዋና ዋና በደቡብ ሶማሊያ የሚገኙ አየር ማረፊያዎችን ተቆጣጥራለች። እነዚህ ወደቦች በደቡብ ሶማሊያ የሚደረጉ ማናቸውንም የወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ለመቆጣጠር ያስችላሉ ተብሏል። ግብጽ ከሞቃዲሾ እንዳትወጣ ያደርጋታል የተባለው ይህ ወታደራዊ እርምጃ የተወሰደው ጳጉሜ ውስጥ ነበረ። አየርማረፊያዎቹም **በ[Luuq](https://en.wikipedia.org/wiki/Luuq), [Dolow](https://en.wikipedia.org/wiki/Dolow), [Bardhere](https://en.wikipedia.org/wiki/Bardere)፣ [Garbahare](https://en.wikipedia.org/wiki/Garbahare)፣ Shaati Guduud, Waajid, Doolo,Dinsoor, and Berdaale የሚገኙ ናቸው።** የሶማሊያ መንግስት የሚቆጣጠረው ብቸኛው አየርማረፊያ የሞቃዲሾ የሚገኘው የኤደን አዴ አየርማረፊያ ብቻ መሆኑ ነው።
- በዚህም በደቡብና ምስራቅ ሶማሊያ የሚገኙ ጎሳዎች አልሻባብን የገታችው ኢትዮጵያ ነች ብለው ሶማሊያውያንና የሶማሊያ ክልሎች ድጋፍ እየሠጡ ነው። በመቶዎች የሚቆጠሩ ሶማሊያወያን በተለይም በደቡባዊ ሶማሊያ ከተሞች በሰላማዊ ሰልፍ ኢትዮጵያን ሲደግፉ ታይተዋል። የኢትዮጵያን ባንዲራ ይዘው የወጡት እነዚህ ሶማሊያውያን የሶማሊያ ፌደራል መንግስት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲወጡ ያሳለፈ ውሳኔ ትክክል አይደለም የግብጽ ወደ ሶማሊያ መምጣትን እንቃወማለን ሲሉ ታይተዋል። ከዚህ ቀደም ኤርትራና ግብጽ ለሶማሊያው አሸባሪ ቡድን አልሻባብ የመሳሪያ ድጋፍ ሲያደርጉ ቆየተው በኤርትራ ላይ የመሳሪያ ማዕቀብ እንዲጣልባት ተደርጎ ነበረ። ይህም ማዕቀብ የተነሳው በኢትዮጵያ መንግስት ድጋፍና በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጥያቄ መሆኑ ይታወሳል። በሌላ በኩል ሁለት የሶማሊያ ክልል አስተዳደሮች የኢትዮጵያ ወታደሮች ሶማሊያን ለቅቀው ይውጡ መባሉን ተቃወመው እንደነበር የሚታወስ ነው። የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪ ሃይል በተለይም በደቡባዊ የሶማሊያ ክልሎች ማለትም በጁባላንድና ሳውዝ ዌስት ስቴት የሚገኙ ሲሆን በአከባቢው የጎሳ መሪዎች፣ የመንግስት ባለስልጣናትና ነዋሪዎች ተቅባይነት አላቸው።
- ቱርክ በሶማሊያ ተመዘግዛጊ የረጅም ርቀት ሚሣኤሎችንና የህዋ ሮኬቶችን መሞከሪያ ጣቢያ ልታቋቁም ከሶማሊያ ጋር እየተደራደረች ነው። ቱርክ ከሃገሯ ሆና በትንሹ ከ1000 ኪሎሜትር ያላነሰ ርቀት የሚመዘገዘጉ ሚሳኤሎችንና የጠፈር ሮኬቶችን ለመሞከር አትችልም። ቱርክ በሃገራት በተጣበበው የትንሿ ኤሺያ አከባቢ እንደመገኘቷ እንደፈለገች ሚሳኤል እየተኮሰች የሚወድቅበትን ማወቅ አትችልም። ለዚህም ከሶማሊያ ጋር ከተስማማች ወደ ደቡብ ምስራቅ ህንድ ውቅያኖስ በመተኮስ ሙከራ ማድረግ ትችላለች። ከዚህም ሌላ ከሶማሊያ ጋር ለ10 ዓመታት የሚቆይ የሶማሊያን የባህር ድንበር የመጠበቅ ስምምነት የዛሬ 15 ቀን አከባቢ ተጀመሯል። ቱርክ ይህንን አገልግሎት በመስጠቷ ሶማሊያ ከውቅያኖስ ድንበሯ የምታገኘውን ገቢ 30 በመቶ ተካፈላለች። ይህ በእንዲህ እንዳለም ቱርክ በሶማሊያ የውቅያኖስ ድንበር አከባቢ ነዳጅ ለመፈለግ ባገኘችው ፈቃድ መሰረት የነዳጅ ፈላጊ መርከብ አሰማርታለች። ይህንንም መርከብ ለመጠበቅ ሁለት አነስተኛ የጦር መርከቦችን እንደምታሰማራ ተናገራለች። ይህም ወደ ደቡብ ወደ ህንድ ውቅያኖስ የሚተኮሱ ይሆናሉ። ቱርክ የሶማሊያን ድንበር መጠበቅ፣ እንደገና ሶማሊያን እና ኢትዮጵያን ከማደራደር ሚናዋ ባለፈ አሁን ደግሞ የሚሳኤል መሞከሪያ ጣቢያ ልታድርጋት ነው። የሚገርመው የቱርክ ነገር ከቅኝ ግዛት መለስ የሚለው ራሷ ሶማሊያ እንዲህ እንድታደርግ በመጋበዟ ብቻ ነው።
- ሶማሊላንድ የግብፅ የባህል ቋሚ ኢግዚቢሽን እንዲዘጋ ወስናለች። ግብጻውያን ሠራተኞቹም በ72 ሠዓታት ከሀገሪቷ ተባረዋል። ግብጽ በሶማሊላንድ ይህን ያክል ተወላጆቿ ኖረው የባህል ማዕከል ባያስፈልጋትም ማዕከሉን ከፍታ ለረጅም ጊዜ ስትጠቀምበት ቆይታለች። ከሶማሊያ ጋር የመከላከያ ስምምነት የተፈራረመቸው ግብጽ ኢትዮጵያን ለመጉዳት ሶማሊላንድ መጉዳቷ የሚቀር አይደለም። ደሞ የሚገርመው የግብጽ የባህል ማዕከል የሚገኘው ከሶማሊላንዱ ፕሬዝዴንሺያል ቤተመንግስት አጠገቡ መሆኑ ነው። ሶማሊላንዳውያኑ የግብጽ የባህል ማዕከል ሰራተኞች በስውር የስለላ ስራ ላይ የተሰማሩ ናቸው ከሃገሬ ይውጡልኝ ብላ አስወጥታቸዋለች።
- የጅቡቲ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ የታጁራን ወደብ የማስተዳደርና ኢትዮጵያ በዛ ወደብ የመጠቀም ሙሉ መብት እንሰጣታለን ብለዋሉ። በርግጥ ኋላ ላይ ቆየት ብለው ደግሞ ሙሉ ለሙሉ ሳይሆን በጋራ እናስተድረው ነው ያልነው ብለዋል። ወጣም ወረደ ቀዝቃዛ ውሃዋንና የሃገሪቷን 85% የሚሆን ገቢ ከኢትዮጵያ የምትለፈው ጂቡቲ ቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ በፓርላማ ቀርበው ወደብ ያስፈልገናል ሲሉ የምንሰጣችሁ ወደብ የለንም ስትል ነበር። በመስታወት ቤት ያለ ቀድሞ ድንጋይ አይወረውርም እንደሚባለው ኢትዮጵያና ሶማሊላንድ እንዳቀዱት ከሆነላቸው የመጀመሪያ የንግድ ተጎጂ ራሷ ጀቡቲ ትሆናለች። በርግጥም ከመንግስት ድክመት ይሁን ከሌላ ባይታወቅም ኢትዮጵያ ጅቡቲ ላይ 90% የሚሆን የገቢ / ወጪ ንግዷን ማሳረፏ የሚገርም ነው። ኢትዮጵያ በዙሪያዋ የሱዳን ፖርት ሱዳን፣ የኤርትራ አሰብና ምጽዋ፣ የሶማሊላንድ ዘይላ፣ የኬኒያ ሞምባሳና የላሙ ኮሪደር ከበቂ በላይ የወደብ አማራጮች ቢሰጣትም ከጅቡቲ ተጣብቃ ራሷን ቅርቃር ከታለች። በዚህ ምክኛትም ጅቡቲያውያኑ ለኢትዮጵያወያን ያላቸው የወረደ ግምት በጣም የሚገርም ነው። ይህንንም የጅቡቲ ተመላላሽ ሾፌሮች የሚያረጋግጡት እውነት ነው።
- የግብፅ የደህንነት ባለስልጣናትና ሌሎች ከፕሬዝዳንት አል ሲሲ የተላከ መልዕክት ለፕሬዚዳንት ኢሣይያስ አፈወርቂ አድርሰዋል። ግብጽ በህዳሴ ግድብ ምክኛት አናቷን እንደተመታች ድመት በምስራቅ አፍሪካ እየተንደፋደፈች ትገኛለች። ከዚህ ቀድም በሶማሊያ የነበራቸውን መናበብ ሊደግሙት እየተንደረደሩም ይገኛሉ። እንደተለመደው ግብጽ የጦርመሳሪያና ገንዘብ ለአልሻባብ ለማድረስ ኤርትራን ለመጠቅም ያሰብች ይመስላል። በርግጥ የአሁኑን ሁኔታ ለየት የሚያደርግው ግብጽ በቀጥታ በሶማሊያ ወታደሮቿን ለማሰማራት እንድል ማግኘቷ ነው። በዛው ሳምንትም የኢትዮጵያ አየርመንገድ የኤርትራ በረራውን አቋርጧል። ኤርትራ እንደተለመደችው በኤርትራ የሚገኘውን የኢትዮጵያን ሀብትና ንብረት አፍና ይዛለች። ከዚህ ቀደም በነበረው የኢትዮጵያና የኤርትራ ግጭት በተጀመረበት ወቅትም በመቶ ሚሊዮኖች ዶላር የሚያወጡ ኢምፖርትና ኤክስፖርት እየተደረጉ የነበሩ ምርቶችን አፍና መውረሷ የሚታወስ ነው። ይህ እንግዲህ በኤርትራ ኗሪ ኢትዮጵያውያን የተወረሰውን አይጨምርም።
- የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ደግሞ ከሞሮኮ መንግስት ጋር ስብሰባ አካኼደው የተለያዩ የወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ኝኙነቶች ላይ ስምምነት ፈጸመዋል። ይህ የሆነው ባለፈው ወር ነበር። ሞሮኮ ብድሬዳዋ አከባቢ ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚወጣ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ተስማምታለች። ይህንን ያነሳንበት ምክንያት ድንገተኛው የኢትዮጰያና የሞሮኮ ፍቅር ከምስራቅ አፍሪካ ፖለቲካ ትኩሳት ጋር የሚያገናኘው ነገር እንዳለ በመጠርጠር ነው። ሞሮኮ ከታሪካዊቷ የኢትዮጵያ ጠላት ጋር ዘመናትን የተሻገረ መልካም ወዳጅነት ይኑራት እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አለመግባባቶች እየታዩ ይገኛሉ። ሞሮኮን ለረጅም ጊዜ የሚያቆስላት በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካ ህብረትና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት እውቅና የተሰጠውና ከሞሮኮ ተገንጥሎ ሃገር ለመሆን የሚዋጋ ተገንጣይ ቡድን አለ። ሞሮኮ ኢትዮጵያ ለዚህ ቡድን የሰጠችውን እውቅና እንድታነሳ ትፈልጋለች። ኢትዮጵያም ሞሮኮ ከግብጽ ጋር ያላትን ወዳጅነት ቀንሳ በአባይ ጉዳይ ኢትዮጵያን እንድትደግፍ ትፈለጋለች። ወቅቱ ደሞ በሞሮኮና ግብጽ መካከል በግልጽ የሚታይ ጽብ የተነሳበት መሆኑ ሞሮኮ የኢትዮጵያን ድጋፍ አጥብቃ ትፈልጋለች።

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 26 - ጥቅምት 2  2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!===============================================...
20/10/2022

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 26 - ጥቅምት 2 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!
=================================================
እንኳን ለ2015 ዓም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና የስኬትና የእድገት ይሁንላችሁ!
==========================================
ሮፍናን፣ ማዲንጎ፣ ቴዲ አፍሮ ከአንድ እስከ ሶስት በብዛት የተጫወቱ አርቲስቶች ሆንዋል በዚህ ሳምንት፡፡ የባለፈው ሳምንት አንድኛ ተደማጭ ሙዚቀኛ ቀመር ዩሱፍ ወደ ስድስተኛነት ወርዷል፡፡ከባለፈው ሳምንት አንጻር ሲታይ በዙ ሙዚቀኞች በሰንጠረዡ ውስጥ በመግባታቸው በአጠቃላይ የተጫወቱት ሙዚቃዎች ቁጥር ቀንሷል፡፡ ለመሳሌ የዛሬ ሳምንት አንደኛ የነበረው ደምጻዊ ቀመር ዩሱፍ በአጠቃላይ 195 ጊዜ በመጫወት ሲሆን የዚህ ሳምንት አንደኛ ሮፍናን ኝ አንደኛ ለመሆን የተጫወተው መጠን 95 ብቻ ነው፡፡
🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈
ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 26 - ጥቅምት 2  2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!================================================...
20/10/2022

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 26 - ጥቅምት 2 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!
=================================================
እንኳን ለ2015 ዓም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና የስኬትና የእድገት ይሁንላችሁ!
================================================
የማስተዋል እያዩ 'ጀግና'ና የቀመር ዩሱፍ 'ኢሬቻ' ከባለፈው ሳምንት ቀጥለው በዚህ ሳምንትም በሰንጠረዡ አናት ላይ ተቀምጠዋል፡፡ የማስተዋል እያዩ 'ጀግና ከአምስተኛ ወደ አንደኛ ከፍ ሲል የቀመር ዩሱፍ 'ኢሬቻ' ወደ ሁለተኛነት ወርዷል፡፡ ማዲንጎ ሁለት ዚማዎቹ በዚህ ሳምንት ሰንጠረዡ ውስጥ ቆይተውለታል...'ከተለያየን ምን አደርጋለሁ'ና 'ስወድላት'፡፡ የማዲንጎን ሁለት ዜማዎች ጨምሮ አምስት ወንዶችና አምስት ሴቶች ደረጃው ላይ ተሰይመዋል፡፡
በዚህ ሳምንት የሰንጠረዡ ቤተኞች የነቴዲ አፍሮ፣ የነሮፍናን፣ የነጥላሁን ገሰሰና ዳዊት ጽጌ ሙዚቃዎች በዚህ ሳምንት ከተደማጭ ሙዚቃዎች ሰንጠረዥ ወጥተዋል፡፡ ይህም ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡
🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈
ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 19 - መስከረም 25 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!===============================================...
13/10/2022

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 19 - መስከረም 25 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!
=================================================
እንኳን ለ2015 ዓም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና የስኬትና የእድገት ይሁንላችሁ!
================================================

የኢሬቻ ሳምንት በመሆኑ ኢሬቻን የሚያሞግሱ ሙዚቃዎች በዚህ ሳምንት በሰንጠረዡ ውስጥ ተካተዋል፡፡ የቀመር ዩሱፍና ዝናሽ ሎሌ ኢሬቻ የተሰኙ ሁለት ሙዚቃዎች በአንደኝነትና ሶስተኝነት ደረጃ ላይ ይገኛሉ፡፡ የተወዳጁ ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ስወድላት፣ ከተለያየን ምን አደርጋለሁና ሞኙ ልቤ ሙዚቃዎች በሁለተኛ፣ አራተኛና ስምንተኛ ደረጃዎች ላይ ተቀምጠዋል፡፡ ከቴዲ አፍሮ፣ ሮፍናንና ጥላሁን ገሰሰ በመቀጠል በአንድ ሳምንት ብዙ ሙዚቃዎቹ በተለያዩ ሬዲዮና ቲቪዎች ላይ በብዛት የተላለፉለት አርቲስት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈
ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 19 - መስከረም 25 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!==============================================...
13/10/2022

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 19 - መስከረም 25 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!
=================================================
እንኳን ለ2015 ዓም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና የስኬትና የእድገት ይሁንላችሁ!
==========================================
የኢሬቻን በዓል ተንተርሶ ቀመር ዩሱፍ የዚህ ሳምንት ቀዳሚ ሆኗል፡፡ ኢሬቻ የተሰኘው ሙዚቃው 195 ጊዜ ተጫውቷል በሳምንቱ፡፡ በሁለተኛነት በአሳዛኝ ሁኔታ በሞት ያጣነው ተወዳጁ ድምጻዊ ማዲንጎ ይገኛል፡፡ ሙዚቃዎቹ በአጠቃላይ 163 ጊዜ ተጫወተዋል፡፡
ሮፍናን፣ ኢሬቻ በተባለ ሙዚቃዋ ዝናሽ ሎሌ፣ ቴዲ አፍሮና ሌሎችም በተከታታይ ደረጃዎች ላይ ተቀምጠዋል፡፡ የኢሬቻን በዓል ተከተሎ የኦሮምኛ ሙዚቃ ዘፋኞች በዚህ ሳምንት በተወዳጅ አስር ሰንጠረዥ ውስጥ ከአስሩ ሶስቱን ቦታዎች ይዘውታል፡፡
🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈
ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

It is 2015 in Ethiopian calendar. Time for 2014's media spending data. 2015 ገባ። የ2014ን የብሮድካስት ሚዲያ ዳታዎችን እንኮምኩም።  # 1 - ...
07/10/2022

It is 2015 in Ethiopian calendar. Time for 2014's media spending data.

2015 ገባ። የ2014ን የብሮድካስት ሚዲያ ዳታዎችን እንኮምኩም።


# 1 - Radio/TV advertisement spot and spending distribution trend.
# 1 - የሬዲዮና ቲቪ የማሰታወቂያና የገቢ ክፍፍል ቻርት



የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 12 - መስከረም 018 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!==============================================...
04/10/2022

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 12 - መስከረም 018 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!
=================================================
እንኳን ለ2015 ዓም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና የስኬትና የእድገት ይሁንላችሁ!
የመስቀል በዓል የሙዚቃ ሰንጥረዡ ላይ ተጸዕኖው ታይቷል፡፡ የአበባ ደሳለኝ 'መስቀል ይብር' የጉራጊኛ ዜማ፣ የዲዲ ጋጋ 'ዎዜ'፣ የሮፍናን 'ጋሞ ደሬ' እንዲሁም ጸጋዬ ሃይሉና ሜላት በጋራ ያዜሙት ተወዳጁ 'በጉራጌ ደስ አለኝ ' ሙዚቃዎች በተለየ ሁኔታ ተደማጭ ነበሩ፡፡ ደቡብ ኢትዮጵያ በመስቀል በዓል አከባበር የታወቀ ነው መቼም፡፡
ነፍሱን ይማረውና የተወዳጁ ድምጻዊ የማዲንጎ አፈወርቅ 'ከተለያየን ምን አደርጋለሁ' ሙዚቃም ሰንጠረዡ ውስጥ ገብቷል፡፡ በ6ተኛነት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ምናልባት በቀጣይ ሳምንት ሪፖርት ላይ ከአሁኑ ደረጃው ከፍ ብሎ እናየው ይሆናል፡፡
የዳዊት ጽጌ 'አማን ይሁን' ሙዚቃ አሁንም አለ በሰንጠረዡ...ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈
ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 12 - መስከረም 18 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!==============================================...
04/10/2022

የባለፈው ሳምንት (ከመስከረም 12 - መስከረም 18 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!
=================================================
እንኳን ለ2015 ዓም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና የስኬትና የእድገት ይሁንላችሁ!
ለጥቂት ሳምንታት ከሰንጠረዡ ጠፍቶ የነበረው ሮፍናን ወደ ቦታው ተመልሷል..አንደኛ ነው፡፡ ሌላዋ የጠፋች ተወዳጅ አርቲስት አበባ ደሳለኝ የመስቀል በዓልን አስመልክታ ብቅ ብላለች...ሁለተኛ ሆና፡፡ የወዜ ሙዚቃው ዲዲ ጋጋ በዚህ ሳምንት ወደሰንጠረዡ የገባ አርቲስት ነው...ማዲንጎ አፈወርቅም አለ...ነፍስ ይማርልን😪፡፡ ቴዲ አፍሮ አምስተኛ ዳዊት ጽጌ ስድስተኛ ሆነዋል፡፡ የዳዊት ጽጌ "አማን ይሁን" ሙዚቃ የአዲሱ ዓመት ማድመቂያነቱ ቀጥሏል፡፡
🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈🎈
ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከጳጉሜ 3 - መስከረም 04 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!=================================================እ...
21/09/2022

የባለፈው ሳምንት (ከጳጉሜ 3 - መስከረም 04 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!
=================================================
እንኳን ለ2015 ዓም በሰላም በጤና አደረሳችሁ!
አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና የስኬትና የእድገት ይሁንላችሁ!
እንደ አዲስ ዓመት መግቢያነቱ ሰንጠረዡን የተቆጣጠሩት የበዓል በተለየም የአዲስ ዓመት ሙዚቃዎች ናቸው፡፡ አብዛኛዎቹ ሙዚቃቸው ቶፕ 10 የገባላቸው አርቲስቶችም በቶፕ 10 ተደማጭ አርቲስቶች ሰንጠረዥም ውስጥ ይገኛሉ፡፡
በሰሜን ኢትዮጵያ በሚታየው ግጭት ምክንያት የዳዊት ጽጌ ሙዚቃ በአንደኝነት ይመራል፡፡
ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከጳጉሜ 3 - መስከረም 04 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!=================================================...
21/09/2022

የባለፈው ሳምንት (ከጳጉሜ 3 - መስከረም 04 2015 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!
=================================================
ቴዲ አፍሮ አዲሱ ዓመትን በኣንደኝነት ጀምሮታል፡፡ ዳዊት ጽጌ ሁለተኛ ሆኗል፡፡ የዳዊት ጽጌ "አማን ይሁን" ሙዚቃ የአዲሱ ዓመት ማድመቂያ ሆኖ ነበር፡፡
ጥላሁን ገሰሰ ሰንጠረዡ ላይ በሶስተኛነት ደረጃ ይገኛል፡፡ በዚህ ሳምንት የምርጥ አስር ውስጥ የገቡ አርቲስቶች በሙሉ የዓመት በዓል ሙዚቃ ያላቸው ናቸው፡፡ ከነዚህ ውስጥ ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ)፣ ጃኖ ባንድ፣ ሃመልማል አባተ፣ መሳይ ከበደና አብነት አጎናፍር ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በሰነጠረዡ የተካተቱት፡፡

ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከነሃሴ 19 - ነሃሴ 25 2014 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!=============================================በዚህ ሳም...
08/09/2022

የባለፈው ሳምንት (ከነሃሴ 19 - ነሃሴ 25 2014 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 ሙዚቃዎች እነሆ!
=============================================
በዚህ ሳምንት ሰንጠረዥ የማስተዋል እያዩ ‘ጀግና’ ሙዚቃና ለአሸንዳ በዓል የተዜመው 'ሹም ደሬ' አንደኛና ሁለተኛ ሆነዋል፡፡

ቤተኞቹ የጥላሁን ገሰሰ 'ቆሜ ልመርቅሽ'፣ እሱባለው ይታየው (የሺ) 'ቻው ትልና'ና የቬሮኒካ አዳነው ‘ኩርፊያ’ ሙዚቃዎች አሁንም በሰንጠረዡ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የጥላሁን ገሰሰ በ'ቆሜ ልመርቅሽ' ባለፈው ሳምንት ሰንጠረዥ ውስጥ አልነበረም፡፡ በዚህ ሳምንት የይርዳው ጤናው 'ወይ ሃገር'ና የሮፍናኑ ‘ጎቤ’ ሙዚቃዎች ከሰንጠረዡ ወጥተዋል፡፡
የዚህ ሳምንት አዲስ ገቢዎች ‘ሆ በለን (እንደገና የሙዚቃ ቡድን)፣ ‘ግልጹን ስሚኝ (ዘሩባቤል ሞላ)ና ‘የኔ ቀለም (ጸደኒያ ገብረማርቆስ) ሆነው በሰንጠረዡ ተካተዋል፡፡

ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

የባለፈው ሳምንት (ከነሃሴ 19 - ነሃሴ 25 2014 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!=================================================ሮ...
08/09/2022

የባለፈው ሳምንት (ከነሃሴ 19 - ነሃሴ 25 2014 ዓ.ም) የሬዲዮና ቴሌቪዥን ተደማጭ 10 አርቲስቶች እነሆ!
=================================================

ሮፍናንና ቴዲ አፍሮ አሁንም በተደማጭነት ውድድራቸው ቀጥሏል፡፡ ከባለፈው ሳምንት ሶስተኛነትና አራተኛነት ከፍ ብለው በዚህ ሳምንት ሮፍናን አንደኛ ቴዲ አፍሮ ደግሞ ሁለተኛ ሆኗል፡፡

ማስተዋል እያዩ አዲስ መጥ ሆኖ ሰንጠረዡን በሶስተኛነት ተቀላቀሎታል፡፡ ፍቅርአዲስና ጎሳዬ በዚህ ሳምንትም በሰንጠረዡ ውስጥ ቆይታቸውን አራዝመዋል፡፡ ማዲቱ ወዳይ ደግሞ 'ሹም ዳሬ' በተሰኘና ለአሸንዳ በተዘፈነ ዜማዋ አራተኛ ሆናለች...ባለፈው ሳምንት ሁለተኛ ነበረች፡፡
ፍቅርአዲስ ነቃጥብበና ጎሳዬ ተስፋዬ አዳዲስ ነጠላ ዜማዎች ባይኖሯቸውም በተወዳጅ ሙዚቀኞች ሰንጥረዦቹ ላይ ቤተኛ ናቸው፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ቤቲ ጂ፣ ናቲ ማን፣ ራሄል ጌቱና ንጉሱ ጥላሁን ገሠሠ ተቀላቅለዋቸዋል፡፡ ይርዳው ጤናው በዚህ ሳምንት አልቀናውም...ከሰንጠረዡ ወጥቷል፡፡

ይህንን ሰንጠረዥ በካፒታል ጋዜጣ የእሁድ እትሞች፣ በ'ወይ አዲስ አበባ በሸገር ኤፍ ኤም'የሬዲዮ ፕሮግራም፣ በ'ምሽቱን ከዲጄ ሄኒኬ ጋር' በኢትዮ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ በቲክቫህ ሜጋዚን የቴሌግራም ቻናል (https://t.me/tikvahethmagazine) ላይና በOmnimedia Ethiopia የፌስቡክ ገጽ ላይ በየሳምንቱ ይለቀቃል፡፡
ዳታውን ከ24 የበለጡ የቲቪና የሬዲዮ ጣቢያዎችን በአውቶማቲክ ከሚቀርጽና በArtificial Intelligence ራሱ ከሚሰማ ሲስተም የተገኘ ነው፡፡
ይህንን ዳታ ያለምንም ክፍያ በነጻ የፈለገ አካል መጠቀም ይችላል፡፡ ሲጠቀሙም የድርጅታችንን የ Omnimedia Ethiopiaን ስም መጥቀስ አይርሱ፡፡

Address

Africa Avenue
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when OmniMedia Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share