Firdewsa Merit Media

Firdewsa Merit Media ...

03/11/2024

ሙሳኮ አላህ ለርሱ ብሎ ባህሩን እንደሚከፍልለት አያውቅም። ባህሩ ጋር የደረሰውም አስቦበት አልነበረም። ግን አንድ ነገር እርግጠኛ ነበር “ጌታው መቼም በዚያ አጣብቂኝ ውስጥ እንደማይተወው”። አቤት… የቂን፤ ዐጀብ ተወኩል ፤ “ተው(አትስጉ) ጌታዬ ከኔ ጋር ነው” የሚል ተራራ ኢማን!! ኧረ እንዲህ አይነት የቂን ሸልመን ያ ወዱድ!!

Fuad kheyredin

01/11/2024

ለዩሱፍ አለይሂ ሰላም እስር ቤት ሁኖ
መልካም ሰው እንደሆንክ አይተናል አሉት
የግብፅ ቤተመንግስት ሁኖ
መልካም ሰው እንደሆንክ አይተናል አሉት

እውነተኛ መልካምነት ችግሮችና ደረጃወች አይቀያይሩትም ።

መልካም ጁመዓ❤

01/11/2024
22/10/2024

ንብረት እየተቃጠለባቸው ያሉ እህቶችና ወንድሞች፤ ዘመዶቻቸው ወይም ጓደኞቻቸው ካላችሁ አብራችኋቸው ሁኑ። በዚህ ሰዓት ስለሚደነግጡ እና ስለሚደናገራቸው እንዳይጎዱ። ሸይጧንም ስላለ!

ግን ሙስሊም አላህን ከያዘ ለዱኒያ አይጨነቅም። እስከ መቼ እንደምንቆይ የማናውቅ ፍጡሮች ነን። ነገ ለወራሽ ጥለነው እንሄዳለን እንጂ ተከትሎን አይሄድም። ለኛ የሚጠቅመን ዛሬ የሰደቅነውና መልካም ሥራችን ነው። እዚህ የሚቀረው የኛ አይደለም። አታስቡ! ትናንት ምንም ሳይኖረን ሰጥቶን የነበረው አላህ፤ ኢንሻ አላህ ነገም የተሻለ ይተካናል። አብሽር‼ ከልብህ በአላህ ተማምነህ ሶብር ካደረግክ ከነ ሪዝቅህ የፈጠረህ አላህ ጥሎ አይጥልህም። እርሱ የከፈተውን ጉሮሮ ሳይዘጋው አያድርም። አትጨነቅ‼ ምን እንደተያዘልህ አታውቅም። ካልታገስክ ግን ንብረትህንም ምንዳህንም ታጣታለህ። ከታገስክ ደግሞ ምንዳህን ከዚያ ንብረትህንና የተሻለ ነገርን ታገኛለህ።

22/10/2024

አንድ የመርካቶ ሱቅ ሲቃጠል አብሮ የሚጎዳው ሰው ብዙ ነው፡፡የመርካቶ ንግድ በትስስር የሚሰራ ነው፡፡ባለሱቁ ከሌላ ባለሱቅ የብዙ ሺ ብር እቃ አምጥቶ እሱም ለሌላ ባለ ሱቅ የብዙ ሺ ብር እቃ አበድሮ እየተቀባበለ ነው ሚሰራው፡፡እዚህ ላይ የባንክ ብድርም ሌላም አለ፡፡ቀጥሮ የሚያሰራውም ሰው አለ፡፡አሁን ከተቃጠለው ሱቅ ያበደረም የተበደረም በሙሉ አብረው ነው የሚከስሩት፡፡በተለይም አሁን ላይ ኢኮኖሚው በቀዘቀዘበት እና ስራ በጠፋበት በዚህ ወቅት እንኳን እሳት አደጋ ተነስቶ እንዲሁም መንገጫገጩ በዝቶ ስለነበር አደጋው በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ነው፡፡

ልብ ሊባል የሚገባው አንዳንድ የመርካቶ ትንንሽ ሱቆች የሚያንቀሳቅሱት ስራ ሌላ ሰፈር ላይ ጠቅልላ ነጋዴው ተሰባስቦ ከሚያንቀሳቅሰው ይበልጣል፡፡

ስለዚህም በአጭሩ ጉዳቱ የሰፋ እና የከፋ ነው ማለት ይቻላል፡፡ስለዚህም የተቃጠለውን ከማንሳት አንስቶ ፥ የባንክ ብድር በማመቻቸት ፥ ለጥቂት ጊዜም ቢሆን ከግብር ነጻ በማድረግ ፥በሌላም በሌላም አስፈላጊው ድጋፍ ተደርጎላቸው ቶሎ ወደ ስራ እንዲመለሱ ማድረግ የግድ ነው፡፡Ab bella

🤲🤲🤲🤲🤲

22/10/2024

እኛም የአላህ ነን ወደእሱም እንመለሳለን!!
ጌታዬ የሶብርን ምንዳ አትከልክላቸው!!
በተሻለም ነገር ተካላቸው!!

22/10/2024

#ዱንያ ምን ያክል ከሀዲ እንደሆነች አያችሁ አይደል ለአመታት የተለፋለት ሀብት ንብረት በአንድ ጀንበር ሲወድም💔
#አሏህ ሪዝቃችሁን በተሻለ ይተካላችሁያረብ

22/10/2024

አላህ ይርዳችሁ ያረብ

وَلَنَبْلُوَنَّكُم بِشَىْءٍۢ مِّنَ ٱلْخَوْفِ وَٱلْجُوعِ وَنَقْصٍۢ مِّنَ ٱلْأَمْوَٰلِ وَٱلْأَنفُسِ وَٱلثَّمَرَٰتِ ۗ وَبَشِّرِ ٱلصَّٰبِرِينَ

ٱلَّذِينَ إِذَآ أَصَٰبَتْهُم مُّصِيبَةٌۭ قَالُوٓا۟ إِنَّا لِلَّهِ وَإِنَّآ إِلَيْهِ رَٰجِعُونَ

ከፍርሃትና ከረኃብም በጥቂት ነገር፣ ከገንዘቦችና ከነፍሶችም፣ ከፍራፍሬዎችም በመቀነስ በእርግጥ እንሞክራችኋለን፡፡ ታጋሾችንም (በገነት) አብስር፡፡

እነዚያን መከራ፤ በነካቻቸው ጊዜ «እኛ ለአላህ፤ ነን እኛም ወደርሱ ተመላሾች» ነን የሚሉትን (አብስር)፡፡

21/10/2024

ዱኒያ እንዲህ ናት !

Address

Addis Ababa
24264CHURCHILROAD,ADDISABABA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Firdewsa Merit Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Firdewsa Merit Media:

Share