
29/07/2022
ከጎኑ ተወለድን
¤ ኢየሱስ በመስቀል ሳለ ያልሞቱትን ጭናቸውን ሰብረው ማውረድ በጀመሩ ጊዜ አንዱ ኢየሱስ እንደሞተ ለማረጋገጥ ጎኑን በጦር ወጋው። ከጎኑም ደምና ውሀ ፈሰሰ። ዮሐ ፲፱÷፴፩-፴፯
❤ ከዚህ ክፍል ደስ የሚለኝና ሚገርመኝ ነገር ቢኖር እኔ ከተወጋው ጎኑ መወለዴ ነው። "እንዴት?" በሉኝ.. ሔዋን አዳም ተኝቶ በተወሰደው አጥንት ከሱ እንደወጣች እኔም ክርስቶስ ሞቶ ከጎኑ በፈሰሰው ደምና ውሃ ዳግም ተወልጃለሁ።
❤ ውሃው:- መንፈስ የመያዝ ተፈጥሮ ያለው ነውና በዛ ውሃ ተጠምቄ አሮጌውን ማንነት አውልቄ አዲሱንም ህይወት አጥልቄ ከሱ ተወልጃለው።
ደሙ:- ከየትኛውም ሀጥያት እያነፃኝ በሰማይ ልጅና ወራሽ መሆኔን የማህተም ቀለም በመሆን አረጋግጦልኝ ቀጥያለው።
❤❤❤ እኔ የክርስቶስ ከጎኑ የወጣሁ ልጁ ነኝ!❤❤❤