ፈጣን page

ፈጣን page ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል።
ማቴዎስ 6፥34 Optimistic

26/08/2025

🐕 ውሻን ለመያዝ ስጋ ተጠቀም 🥓
🧍ወንድ ልጅ ለመያዝ 👯ሴት ተጠቀም
👯ሴት ልጅን ለመያዝ_______________

Alert!በአለም አቀፍ ደረጃ የወንዶች ቁጥር መቀነሱ እና እጥረት መግጠሙ ተዘገበ‎‎የተባበሩት መንግስታት የ2025 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስነ ሕዝብ አወቃቀር ሪፖርት አወጣ።‎‎ በፕላኔቷ ም...
25/08/2025

Alert!
በአለም አቀፍ ደረጃ የወንዶች ቁጥር መቀነሱ እና እጥረት መግጠሙ ተዘገበ

‎የተባበሩት መንግስታት የ2025 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስነ ሕዝብ አወቃቀር ሪፖርት አወጣ።

‎ በፕላኔቷ ምድር ላይ 7.8 ቢሊዮን ሰዎች አሉ።

‎ - ሴቶች = 5.6 ቢሊዮን ሲሆኑ
‎ - ወንዶች = 2.2 ቢሊዮን

‎ ስለዚህ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሴቶች ለወንዶች ባላቸው አመለካከት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ይመክራል ምክንያቱም ከ 2.2 ቢሊዮን ወንዶች ውስጥ:

‎ - 1 ቢሊዮን ያገባ ነበር
‎ - 130 ሚሊዮን እስራት
‎ -70 ሚሊዮን የሚሆኑት በአእምሮ ጤና ችግሮች እና በተለያዩ በሽታዎች ይሰቃያሉ።

‎ ይህ ማለት ለትዳር የቀረቡት 1 ቢሊዮን የሚሆኑ ወንዶች ብቻ ናቸው።

‎ እና ይህ ቢሊዮን ማን ነው?

‎ - 56% ስራ አጥ ናቸው።
‎ - 3% የሚሆኑት ግብረ ሰዶማውያን ናቸው።
‎ - 1% የካቶሊክ ካህናት ናቸው።
‎ - 10% የሚሆኑት ወላጆች ወይም የቅርብ ዘመድ ናቸው።
‎ - 30% ከ 65 ዓመት በላይ

‎ ስለዚህ ሴቶች ያገቡ ወይም ያላገቡ ወንዶችን በአክብሮት ይያዙ።

#አስገራም ታሪክ
***************
‎ በዓለም ዙሪያ የወንዶች እጥረት አለ ትኩረት ይስጡ! 😏😬🤲

በተዋናይ ሸዋፈራው ላይ "አናይም በቃ " የሚል Boycott ተጀምሯል አናይም በቃ እያላችሁ Comment ስር ፃፏ  ! 🙅‍♂️
25/08/2025

በተዋናይ ሸዋፈራው ላይ "አናይም በቃ " የሚል Boycott ተጀምሯል

አናይም በቃ እያላችሁ Comment ስር ፃፏ ! 🙅‍♂️

21/08/2025

"ሳልዋጋ አልነግስም" ያሉት የፋኖ አመራሮች
=================
ሸንቁጥ አየለ
---------------------------------
የፋኖ አመራሮች:የፋኖ ደጋፊዎች:በፋኖ ዙሪያ የተሰባሰባችሁ ማህበራት እግዚአብሄር ንገሱ ቢላችሁ እንደ ድሮ ነጋሲ "ሳልዋጋ አልነግስም" ብላችሁ ነገሩን ሁሉ በልዩነት:በጥላቻ:በአሉባልታ እና በሸምቅ ወደ ኋላ ጎተታችሁት::

በመላዉ የአማራ ክልል በወታደራዊ ሀይል ያሸነፋችሁትን ጠላት እንደገና እስትንፋስ ዘርታችሁ እንዲቀጥል እያደረጋችሁት ነዉ::እናንት በጠላት ላይ ሳይሆን ስራ እየሰራችሁ ያላችሁት እርስ በርስ እንዴት አንዱ ካንዱ እንደሚበልጥ ነዉ እየተራወጣችሁ ያላችሁት::

ዝሆን አክላለሁ ስትሉ እያንዳንዳችሁ በእርስ በርስ ፍትጊያ እራሳችሁን ወደ አይጥነት እያሳደጋችሁት ነዉ::
=========================
ደንጎራ መካሪያን ይዛችሁ እስክስታ መምታቱን ቀጥላችኋል::መጀመሪያ ጎንደርን ማጠንከር:መጀመሪያ ሸዋን ማጠንከር:መጀመሪያ ጎጃምን ማጠንከር:መጀመሪያ ወሎን ማጠንከር የሚል የሞተ እና የእንግዴ ልጅ የሆነ ሀሳብ ይዛችሁ እየተራወጣችሁ ነዉ::
=================
ይሄ ጎንደር:ጎጃም:ሸዋ:ወሎ የሚል የሞተ እና እንግዴ ልጅ የሆነ ሀሳብ ጥንቅቅ አድርጎ እርስ በርስ ያባላችኋል::ልቅም አድርጎ የሚያጠፋፋችሁ የክፍለ ሀገር አደረጃጀት መሆኑን ሽህ ጊዜ ጽፈናል::ብትሰሙም ባትሰሙም ለአንድ ሽህ አንድ ጊዜ አሁንም እንጽፋለን::ክፍለ ሀገር ላይ ተቸንክረህ የትም አትደርስም::
=========================
ግማሻችሁ ብቸኛ ነጋሲ ለመሆን:ግማሻችሁም ከእዬ ክፍለ ሀገራችሁ ንጉስና ነገስታት ለማዉጣት:ግማሻችሁም ከፋኖ ወንድሞቻችሁ ይልቅ ሻቢያ እና ህዉሃት የሚያነግሷችሁ መስሏችሁ:ግማሾቻችሁም ከፋኖ ወንድሞቻችሁ ይልቅ ኦነግ/ኦህዴድ ከፍ ያለ ጥቅም የሚሰጧችሁ መስሏችሁ:ግማሾቻችሁም የዘመነ መሳፍንት የስልጣን ክፍፍል ስሌት አንግባችሁ ወንዝ ወንዙን በመሮጥ ባከናችሁ:: እየባከናችሁም ነዉ::

ጆሮዋ ላይ እንደተኛች እንደተደገመባት እባብ አሁን ይሄን መልዕክት እንደማትሰሙ አዉቃለሁ:: ቢሆንም ነገ ስትጠፉ ከሚቆጨኝ ልጻፈዉ ብዬ ነዉ::
========================
ለማንኛዉም አሁንም ጊዜ አላችሁ::
------------------------
የኢትዮጵያ ህዝብ መከራ በዝቷል::ኢትዮጵያ አዲስ መሪዎች ለመቀበል እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ዘርግታ እግዚኦታ ላይ ነች::የኢኮኖሚዉ:የማህበራዊዉ:የመንፈሳዊዉ :የተቋማዊዉ:የፖለቲካዊዉ ቀዉስ ህዝቡን አስመርሮታል:: እግዚአብሄርር ኢትዮጵያን ለማዳን በአንድ ጊዜ አስነስቶ ቢያስታጥቃችሁ እናንተ ግን ገና ክፍለ ሀገር እያሰባችሁ ትንደፋንደፋላችሁ::
----------------------------------------------------------
መርገምት ሆኖባችሁ አንድ ብትሆኑ በሳምንታት ኢትዮጵያን መቆጣጠር እንደምትችሉ መረዳት ተስኗችኋል:: ይሄም ስላልገባችሁ አንዳንዶቻችሁ የወያኔን እና የሻቢያን እግር መሳለም ጀምራችኋል::አንዳንዶቻችሁ የሆነ ቀበሌን ለማዳን የኦነግና/ኦህዴድን ካልሲ ማጠብ ጀምራችኋል::
--------------------------------------------------
ኢትዮጵያን መቆጣጠር አቅም እያላችሁ እናንተ ስለ ቀበሌ ወይም ስለ ክፍለሀገር ወይም ስለ ብጥቅጣቂ ስልጣን ትጨነቃላችሁ !
----------------------------------------------------
ለማንኛዉም እግዚአብሄር አሁንም እየጠበቃችሁ ነዉ::
ጥቂት ጊዜ ሰጥቷችኋል::
አንድ ሆናችሁ እራሳችሁ ድናችሁ ሌላውን አዲኑ::
Shenkut Ayele Page

21/08/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! ሙከሚል ሀጂ ሁሴን, Habetamu Bhone

ኦርቶዶክስ ተዋህዶየራሷ⛪️ 1.ኢየሱስ⛪️ 2.ቀኖና⛪️ 3.ሥርዓት⛪️ 4.ትውፊት⛪️ 5.አስተምህሮ⛪️ 6. ዶግማ⛪️ 7. ነገረ ክርስቶስ⛪️ 8.ታሪክ⛪️ 9. ዜማ⛪️ 10.ንዋያተ ቅድሳት⛪️ 11...
18/08/2025

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

የራሷ

⛪️ 1.ኢየሱስ
⛪️ 2.ቀኖና
⛪️ 3.ሥርዓት
⛪️ 4.ትውፊት
⛪️ 5.አስተምህሮ
⛪️ 6. ዶግማ
⛪️ 7. ነገረ ክርስቶስ
⛪️ 8.ታሪክ
⛪️ 9. ዜማ
⛪️ 10.ንዋያተ ቅድሳት
⛪️ 11. ቋንቋ
⛪️ 12. ፊደል
⛪️ 13. ነጠላ
⛪️ 14. ጧፍ
⛪️ 15. እጣን
⛪️ 16. ጥምቀት
⛪️ 17. ቁርባን
⛪️ 18. ጌታ
⛪️ 19. ጳጳሳት
⛪️ 20. ቀሳውስት
⛪️ 21. ዲያቆናት
⛪️ 22. የቀን መቁጠሪያ
⛪️ 23.ሐዋርያዊ ቅብብሎሽ
⛪️ 24.መዝሙር
⛪️ 25. ሥግደት
⛪️ 26. ቅዳሴ
⛪️ 27. ሰዓታት
⛪️ 28. ንግስ
⛪️ 29.ገድላት
⛪️ 30. ተዓምራት
⛪️ 31. ፀበል
⛪️ 32. ነገረ ማርያም
⛪️ 33.ነገረ መላዕክት
⛪️ 34. መፅሃፍ ቅዱስ
⛪️ 35. የአባቶች አስተምህሮ
⛪️ 36.ሱባኤ
⛪️ 37. ወረብ
⛪️ 38. አፅዋማት
⛪️ 39. ችቦ
⛪️ 40. ደመራ
⛪️ 41. ከተራ
⛪️ 41. ጅራፍ
⛪️ 42. እምነት
⛪️ 43.ምፅዋት
⛪️ 44. ሻማ
⛪️ 45. ከበሮ
⛪️ 46. ዘቢብ
⛪️ 47. የፀሎት መፃህፍት
⛪️ 48. ማህተብ
⛪️ 48. ባንዲራ
⛪️ 49. መቋሚያ
⛪️ 50. ፀናፅል
⛪️ 51.አምልኮ
⛪️ 52. አለባበስ
⛪️ 53. ሠማያዊ ሥርዓት
⛪️ 54. በዓላት
⛪️ 55. ወግ
⛪️ 56. ምስጢራት
⛪️ 57. ሠማዕታት
⛪️ 58. ፃድቃን
⛪️ 59. ሜሮን
⛪️ 60. ስንክሳር
⛪️ 61.ግፃዌ
⛪️ 62. ምስባክ
⛪️ 62. ቅኔ

ያላት የማንንም የማትፈልግ ሰውች በምርጫ እንጂ በግዴታ የማይከተሏት ስንዱ እመቤት ናት!

ኦርቶዶክስ የገነት በር መሆኑዋን እዲሁ መረዳት ይችላል።

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻዋን ሀገር ናት!

ወስብሀት ለእግዚአብሔር

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

12/08/2025
★ ባንኮች በዚህ ሳምንት ያወጡዋቸው በርካታ ስራዎች {በ0 አመት እና በልምድ}● Commercial Bank Ethiopia ● Wegagen Bank ● Gadaa Bank● Enat Bank● Ahad...
09/08/2025

★ ባንኮች በዚህ ሳምንት ያወጡዋቸው በርካታ ስራዎች {በ0 አመት እና በልምድ}

● Commercial Bank Ethiopia
● Wegagen Bank
● Gadaa Bank
● Enat Bank
● Ahadu Bank
● Rammis Bank
● Dashen Bank
● Hijra Bank
● ZamZam Bank
● Zemen Bank
● Abay Bank
● Bunna Bank
● Nib Bank
● Awash Bank
● CBE Investment Bank (New Bank)
● Wegagen Capital-Investment Bank (New Bank)

https://effoysira.com/category/bank/
[ የማመልከቻ ጊዜው ሳይጠናቀቅ ያመልክቱ]

ሙሉ የስራዎቹን ዝርዝሩን ከስር ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ👇👇👇👇👇
https://effoysira.com/category/bank/

https://effoysira.com/category/bank/page/2/

🎈Telegram ☞ https://t.me/Big_Online_Marketing

የስራውን መረጃ ለጓደኛዎ ያጋሩ

Banking Jobs in Ethiopia, Search Banking and Insurance Jobs in Ethiopia.Apply Banking and Financial jobs in Ethiopia today! Search latest Banking and Financial job vacancies.

የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  ቋሚ ሲኖዶስ በጀልባ መገልበጥ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች አስመልክቶ የተሰማውን ኀዘን ገለጸ። *******************ነሐሴ  1 ቀን...
07/08/2025

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በጀልባ መገልበጥ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ ወገኖች አስመልክቶ የተሰማውን ኀዘን ገለጸ።
*******************
ነሐሴ 1 ቀን 2017ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስ ቋሚ ሲኖዶስ ሰሞኑን ወደ ውጪ ሀገር ሲጓዙ የጀልባ መገልበጥ አደጋ ደረሶባቸው ህይወታቸውን ያጡ ወገኖቻችንን አስልክቶ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውም መጽናናትን ተመኝቷል።

ቋሚ ሲኖዶሱ ዓለማችን በብዙ ሥጋቶችና አደጋዎች የተከበበ ቢሆንም ዘመድ ወገን በሌለበት ሥፍራ ላይ ይህንን የመሰለ አደጋ በመድረሱ ሀዘናችንን ከፍ ያድረገዋል። በመለት ገልጿል።

የቋሚ ሲኖዶስ መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል።

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ የኃዘን መግለጫ፤

“እግዚአብሔር አምላከ ሕያዋን ያነሥአክሙ በትንሣኤሁ
የሕያዋን አምላክ እግዚአብሔር በትንሣኤው ያስነሳችኋል"
(ማቴ 22፡31 ሮሜ6፡5፤ቅዱስ ያሬድ) ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር በአርአያውና በመልኩ የፈጠረው የሰው ልጅ እሾህና አሜከላ ወደምታበቅለው ምድር፣ ጥሮ ግሮ ወጥቶ ወርዶ ወደሚኖርበት ዓለም ከመጣ ጊዜ ጀምሮ መከራ ሥጋን ማስተናገድ መጀመሩ በቅዱሳት መጻሕፍትየተጻፈ፣በተግባርም የምንኖረው እውነታ ነው፡፡

የሰው ልጅ አካለ መኑ አድጎ ራሱን ማወቅ ሲጀምር ሕይወቱን ለማቃናት የተሻለ ነሮ ለመኖር፣ ነግዶ ለማትረፍ፣ ዘርቶ ለማጨድ፣ በሀገሩም ሆነ በሌላው ዓለም ሠርቶ ለማግኘት ብዙ ጥረቶችን ያደርጋል፡፡ በዚህ ሂደት ውስጥ ለተፈጥሮአዊና ለሰው ሠራሽ አደጋ መጋለጡ በሕይወቱ የሚያጋጥመው አሳዛኙ ክስተት ነው፡፡

ጥሮ ግሮ ፣ ወጥቶ ወርዶ ባፈራው ሀብቱ እና ንብረቱ ብቻ ሳይሆን ዳግም የማይተካ ሕይወቱንም ጭምር ለሚያጣው የሰው ልጅ በሕይወተ ነፍሱ ያለው መጽናኛ “የሕያዋን አምላክ እግዚአብሔር በትንሣኤው ያስነሣችኋል" የሚለው ሕያው ቃል ነው፡፡

የምንኖርበት ዓለም በብዙ ሥጋቶችና አደጋዎች የታጠረ በመሆኑ ዘመድ ወገን በሌለበት በባዕድ ምድር ሥጋችን ቢጣልም፣ በእግዚአብሔር ዘንድ የታወቅን፣ ነፍሳችንም ሕያው ከመሆኗ የተነሣ ጠፍታ የማትቀር መሆኑን ስናስብ እንጽናናለን፡፡ ልንጽናናም ይገባናል፡፡

በቅርቡ ከሀገር ወጥተው በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ ወገኖቻችን የጀልባ መገልበጥ አደጋ ደርሶባቸው ሕይወታቸው በማለፉ ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰማው ኃዘን ጥልቅ መሆኑን እየገለጸ፣ በአደጋው ምክንያት ለሞቱት ኢትዮጵውያን ወገኖቻችን እግዚአብሔር ዕረፍተ ነፍስን እንዲሰጣቸው ፣ለቤተስቦቻቸውና ለወዳጆቻቸውም ሁሉ መጽናናቱን እንዲያድላቸው ይጸልያል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በክረምቱ ወራት በሁሉም አቅጣጫ በአንድ በኩል በመሬት መንሸራተትና በድንገተኛ ጎርፍ ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የዝናብ እጥረትን በመሰሉ ሰው ሠራሽና የተፈጥሮ አደጋ ችግር እየገጠማቸው ለሚገኙ ወገኖቻችን ፣ ሁሉም የሰው ልጆች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ
ነሐሴ 1 ቀን 2017 ዓ/ም

"እኛ በየጊዜው ጾምን እንድንጾም ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት ፈቃደ ሥጋችንን በመግራት ለእግዚአብሔር ታዛዦች እንድንሆን ነው" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ‎እኛ በየጊዜው ጾምን እንድን...
06/08/2025

"እኛ በየጊዜው ጾምን እንድንጾም ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት ፈቃደ ሥጋችንን በመግራት ለእግዚአብሔር ታዛዦች እንድንሆን ነው" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ

‎እኛ በየጊዜው ጾምን እንድንጾም ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት ፈቃደ ሥጋችንን በመግራት ለእግዚአብሔር ታዛዦች እንድንሆን ነው፤ ጾም የኃጢኣት መግቻ መሳሪያ በመሆኑ ‹‹ልጓመ ኃጢኣት›› ተብሎ ይታወቃል ሲሉ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገልጸዋል፡፡

"በዚህም ሰውነታችንን ለግብረ ኃጢኣት ከሚያጋግሉ ምግቦች ኣርቀን በሰከነ መንፈስ እግዚአብሔርን እያሰብን ኃጢኣታችንንም እያስታወስን በንስሓ ወደ እርሱ ለመቅረብና ለሱ ለመታዘዝ እንጾማለን" ብለዋል ፓትሪያርኩ የጾመ ፍልሰታን መግባት አስመልክቶ ባስተላለፉት መልዕክት፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የ2017 ዓ.ም የጾመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል።

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ፡-
በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን፤

በሀገራችን በኢትዮጵያና በመላው ዓለም የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ፡-

የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓ.ም የቅድስት ድንግል ማርያም ጾመ ፍልሰታ በሰላም ኣደረሳችሁ!

‹‹ታዓብዮ ነፍስየ ለእግዚአብሔር፣ ነፍሴ እግዚአብሔርን እጅግ ታከብረዋለች›› (ሉቃ.፩÷፵፮)፤

ይህንን ዐረፍተ ነገር የተናገረችው ማኅደረ መንፈስ ቅዱስ የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፤ ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር ዓለምን ለማዳን በሰራው ስራ ሰውነታችንን ለመዋሓድ የመረጣት ምርጥ የፍጥረት ወገን ናት፤ፍጥረት ሁሉ በእግዚአብሔር ለእግዚአብሔር ተፈጥሮኣል፤ የእግዚአብሔርም ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያም መመረጥም በእግዚአብሔር ለሰው የተደረገ ምርጫ ነው፤

የሰው መዳን ከጥንቱ ከጠዋቱ በእግዚአብሔር ልዩ ኣሰራር እንደሚከናወን በነቢያት የተገለጸ ነበረ፣‹‹ኣኮ በተንባል ወኣኮ በመልኣክ ኣላ ለሊሁ እግዚእ ይመጽእ ወያድኅነነ፤ በኣማላጅም ኣይደለም፤ በመልኣክም ኣይደለም እሱ ራሱ ጌታ መጥቶ ያድነናል እንጂ›› የሚለው የነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ ትንቢትም ይህንን ያስረዳል፤ ቃለ ትንቢቱ ድኅነታችን በጌታ ቤዛነት እንደሚከናወን ያረጋግጣል፤ይህም ሊሆን የቻለው ከፍጡራን ወገን በደሙ ቤዛነት ፍጡራንን የሚያድን ስለሌለ ነው፤

ከዚህ ኣንጻር የሰው መዳን በእግዚአብሔር ኣሰራር በደም ቤዛነት ከሆነ፣ በደሙ ቤዛነትም ዓለምን ማዳን የሚችል ከፍጡር ወገን ከሌለ፣ መዳናችን በእግዚአብሔርና በእግዚአብሔር እጅ ብቻ የተንጠለጠለ ነበረ፤ እግዚአብሔር በደሙ ቤዛ ሆኖ ዓለምን ለማዳን ደግሞ ደም ሊኖረው ይገባ ነበር፤ በመሆኑም እግዚአብሔር በክዋኔው ደም የሌለው ስለሆነ ለቤዛ ዓለም የሚፈስ ደምን ገንዘብ ማድረግ ነበረበት፤ይህንን ደም ለመዋሓድ ቅድስት ድንግል ማርያምን መረጠ፤ ለዚህ ብቁ እንድትሆንም በእስዋ ላይ ስራውን ሰራ፤በምርጫውም መሠረት ከቅድስት ድንግል ማርያም ደማዊ ሥጋንና ነፍስን ተዋሕዶ ለቤዛዊ መሥዋዕት መንገዱን ኣመቻቸ፤

ቅድስት ድንግል ማርያም በነገረ ድኅነት መሰላል ለመሆን በእግዚአብሔር የተመረጠች በመሆኗ ኣንቀጸ ኣድኅኖ ወይም የድኅነት በር ትባላለች፤ቅድስት ድንግል ማርያም ለዚህ ታላቅ ነገረ ድኅነት መመረጥዋ እጅግ ታላቅ ዕድል መሆኑን ስለተገነዘበች ‹‹ታላላቅ ስራዎችን ሰርቶልኛልና›› በማለት እግዚአብሔርን በመዝሙር

06/08/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mengesha Getahun, ጄዚ ጄዚ, የኔእናት ማርያም ናት

Address

Addis Ababa

Telephone

+251913212792

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ፈጣን page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ፈጣን page:

Share