Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ

Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ We provide you the latest and fundamental information about Ethiopian Banking Sector.

ባንኮች በልዩ ኢኮኖሚ ዞን ቅርንጫፍ መክፈት ስለሚችሉበት ሁኔታ የሚደነግግ ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ቅርንጫፍ ለመክፈት የሚፈልጉ ባንኮች፣ በአጠቃላይ...
06/11/2025

ባንኮች በልዩ ኢኮኖሚ ዞን ቅርንጫፍ መክፈት ስለሚችሉበት ሁኔታ የሚደነግግ ረቂቅ መመሪያ ተዘጋጀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ቅርንጫፍ ለመክፈት የሚፈልጉ ባንኮች፣ በአጠቃላይ በአገሪቱ የሚገኙ ባንኮች ካላቸው ጠቅላላ ሀብት፣ በመጨረሻው የበጀት ዓመታቸው ሪፖርት መሠረት ቢያንስ ሁለት በመቶ የሀብት ድርሻ እንደሚይዙ ማሳየት የሚችሉ መሆን እንደሚገባቸው የሚደነግግ ረቂቅ መመርያ ተዘጋጀ፡፡

ብሔራዊ ባንክ የባንኮች ሥራ ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር በተመለከተ፣ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ቅርንጫፍ የሚከፍቱ ባንኮች ፈቃድ ለማግኘት ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎችን፣ የቁጥጥር ሒደትና የባንኮቹን የሥራ እንቅስቃሴ ለመደንገግ አዲስ ረቂቅ መመርያ ማዘጋጀቱ ተገልጿል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ባወጣው ሪፖርት (Financial Stability Report, November 2024) መሠረት፣ እስከ ሰኔ 2017 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ የተመዘገበ የባንኮች ጠቅላላ ሀብት 3.3 ትሪየን ብር መድረሱን ያሳያል፡፡

ረቂቅ መመሪያው በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖቹ ቅርንጫፍ የሚከፍቱ ባንኮች ማሟላት የሚጠበቅባቸውን የጠቅላላ ሀብት መጠን፣ የካፒታል ብቃት ምጣኔ (Capital Adequacy Ratio)፣ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት ምጣኔ (Liquidity ratio)፣ እንዲሁም የተበላሸ ብድር ምጣኔን የተመለከቱ ድንጋጌዎች ተካተውበታል።

ከድንጋጌዎቹ መካከል በዞኖቹ ቅርንጫፍ የሚከፍቱ ባንኮች ፈቃድ ለማግኘት ከሚያመለከቱበት ጊዜ ጀምሮ ወደኋላ ባሉት አራት ተከታታይ የበጀት ሩብ ዓመቶች ሪፖርት መሠረት፣ ከተጣራ የወጪና ዕዳ ኃላፊነት (net current liabilities) ላይ እንዲያስመዘግቡ በብሔራዊ ባንክ ከሚገደዱት የ15 በመቶ የጥሬ ገንዘብ ፍሰት ምጣኔ ተጨማሪ ሦስት በመቶ ከፍ ሊያደርጉ ይገባቸዋል ተብሏል፡፡

እንዲሁም የተበላሸ የብድር መጠናቸውም ከአምስት በመቶ ከፍ ሊል እንደማይገባው የተደነገገ ሲሆን፣ ቅርንጫፍ የሚከፍቱ ባንኮች በኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ ለሚንቀሳቀስ የትኛውም ግለሰብ ሆነ የንግድ አካላት፣ ሁሉንም የባንክ አገልግሎቶቻቸውን ማቅረብ የሚችሉ ሊሆኑ እንደሚገባቸውም በረቂቁ ተደንግጓል፡፡

በረቂቅ መመርያው ማንኛውም ባንክ በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ ቅርንጫፍ ከፍቶ ለመሥራት የግዴታ የብሔራዊ ባንክ ፈቃድ እንደሚያስፈልገው የተገለጸ ሲሆን፣ በዞኖቹ የመንቀሳቀስ ፍላጎት ያለው የትኛውም ባንክ የሚከፍተው ቅርንጫፍ የውጭ ምንዛሪ አገልግሎቶችን እንደሚያቀርብ ማረጋገጥ ይገባዋል ተብሏል፡፡

በአሁኑ ወቅት በልዩ ኢኮኖሚ ዞኖች ቅርንጫፎች ከፍተው አገልግሎት እየሰጡ ያሉ ባንኮች፣ ረቂቅ መመርያው ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ በሚኖር አንድ ዓመት ውስጥ፣ በረቂቁ ውስጥ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን ማሟላታቸውን ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ

ብርሀን ባንክ 50 ፎቅ ልሠራ ያሰብኩትን ትቼዉ 16 ፎቅ ልሰራ ነው ብሏል።
03/11/2025

ብርሀን ባንክ 50 ፎቅ ልሠራ ያሰብኩትን ትቼዉ 16 ፎቅ ልሰራ ነው ብሏል።

31/10/2025

የሞባይል ገንዘብ ከእርስዎ ወደ ተለያዩ ሰዎችና ተቋማት በቀላሉ እና በፍጥነት ለመክፈል የሚያስችልዎት ሲሆን በዚህም ከአገልግሎት መቋረጥና ከተጨማሪ ክፍያዎች ራስዎን ይጠብቃሉ፣ እንዲሁም ሞባይል ገንዘብ ሲጠቀሙ ገንዘብዎን ከስርቆት ይከላከላሉ ።

የፋይናንስ ዕውቀት ሳምንት 2018 National Bank of Ethiopia

100,000 አላነሠም?
29/10/2025

100,000 አላነሠም?

ቀልዱ እንደቀጠለ ነው 😂
28/10/2025

ቀልዱ እንደቀጠለ ነው 😂

የወጋገን ባንክ ያስመዘገበው ከፍተኛ ትርፍ እና ስጋቶቼ============================ባንኩ በጠቅላላ ጉባዔኤው እንዳሳወቀው እና በድረገፁ ላይ ባሳተመው የሂሳብ መግለጫ እጅግ በጣ...
27/10/2025

የወጋገን ባንክ ያስመዘገበው ከፍተኛ ትርፍ እና ስጋቶቼ
============================
ባንኩ በጠቅላላ ጉባዔኤው እንዳሳወቀው እና በድረገፁ ላይ ባሳተመው የሂሳብ መግለጫ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባል አፈፃፀም አስመዝግቧል።

✔️ ከታክስ በሁዋላ ያለውን ትርፍ በ73% አሳድጎ ከ1.6 ቢሊየን ወደ 2.77 ቢሊየን አድርሶታል
✔️ ያልተጣራ ገቢውንም በ46% አሳድጎ 9.7 ቢሊየን አድርሷል
✔️ ባለ አክሲዮኖችም 45.6% ትርፍ (EPS) አግኝተዋል። ከአምናው በ25% ይልቃል።
✔️ የአጠቃላይ ሀብቱም መጠን በ29% አድጎ 84.6 ቢሊየን ደርሷል
✔️የLoan/deposit ምጣኔውም ጤናማ በሚባል መጠን ላይ ነው 83%
✔️ ከ1.2 ቢሊየን ብር በላይ ትርፍ በዲቪደንድ ለባለ አክሲዮነ‍ኦች ከፍሏል

እንደ ስጋት…..

ከሂሳብ መግለጫው በመነሳት ባንኩ በብዙ መመዘኛዎች ጥሩ የሚባል አፈፃፀም አስመዝግቧል። ይሁን እንጂ እነዚህ ስጋቶችን አይቼበታለሁ

⚠️ ከገቢው ውስጥ ትልቁን ድርሻ የያዘው ማለትም ወደ 2 ቢሊየን ብር የሚጠጋው ከውጭ ምንዛሪ ለውጥ ጋር የተያያዘ ስለሆነ ቀጣይነት ያለው ትርፍ መሆኑ አጠራጣሪ ነው።

⚠️ ለሚበላሽ ብድር እንደ ወጪ የተያዘው Loan impairment charge ከአምናው ጨምሮ 465 ሚሊየን ደርሷል። ለመጪው አመት መጠባበቂያ ውስጥ የገባውም 2.64 ቢሊየን እንደ ትልቅ ስጋት የሚታይ ነው።

⚠️ በጣም እየጨመረ የመጣ ኦፐሬሽናል ወጪ።
Aminu Nuru

ብሔራዊ ባንክ የግል አካውንት ለንግድ የሚጠቀሙ ሠዎች ችግር እየፈጠሩብኝ ነው አለ።
24/10/2025

ብሔራዊ ባንክ የግል አካውንት ለንግድ የሚጠቀሙ ሠዎች ችግር እየፈጠሩብኝ ነው አለ።

የአማራ ባንክ ATM አማርኛ እና እንግሊዝኛ ብቻ ነው የሚሠራው? የሌሎቹ ባንኮች እኮ ሌሎች የአገራችንን ቋንቋዎች ይጠቀማሉ። 😶😶😶
20/10/2025

የአማራ ባንክ ATM አማርኛ እና እንግሊዝኛ ብቻ ነው የሚሠራው? የሌሎቹ ባንኮች እኮ ሌሎች የአገራችንን ቋንቋዎች ይጠቀማሉ። 😶😶😶

ብሔራዊ ባንክ  በየ15 ቀኑ ለማጫረት አስቦ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ከሁለት ወር በሁዋላ 150 ሚሊየን ዶላር ይዞ ለ31 ባንኮች ሻሞ ብሎ አንዱን ዶላር በ148.1007  ሸጧል።ነሐሴ 2024 ላይ...
14/10/2025

ብሔራዊ ባንክ በየ15 ቀኑ ለማጫረት አስቦ የነበረ ቢሆንም ዛሬ ከሁለት ወር በሁዋላ 150 ሚሊየን ዶላር ይዞ ለ31 ባንኮች ሻሞ ብሎ አንዱን ዶላር በ148.1007 ሸጧል።

ነሐሴ 2024 ላይ በ107.90 የጀመረው ጨረታ ዛሬ 148 ተሻግሯል። ባለፉት 5 ጨረታዎች ተከታታይ ጭማሪ እያሳየ ነው። በባንኮቹ Hidden cost ምክንያት ትክክለኛ መሸጫቸው ባይታወቅም፧ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች አንዱን ዶላር 163 ብር ገዝተው 166.26 እየሸጡ ነው። በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ የጨረታውም ዋጋ እየጨመረ መሄዱ አይቀርም።

ብሔራዊ ባንክ በወር እና በሁለት ወር ብቅ እያለ “አጫርታለሁ” የሚለው ነገር ብዙም ትርጉም አይሰጥም።

የዶላር ፍሰቱ በአግባቡ መጠናት አለበት።
via
via aminu nuru

ወሊፍ የኢንቨስትመንት እና ንግድ ስራዎች አ.ማ. CBE Capital investment bankን አጋሩ አድርጎ ተፈራርሟል።
10/10/2025

ወሊፍ የኢንቨስትመንት እና ንግድ ስራዎች አ.ማ. CBE Capital investment bankን አጋሩ አድርጎ ተፈራርሟል።

ታዋቂዎቹን ስታንዳርድ ቻርተርድ እና በርክሌይን ጨምሮ የውጭ ባንኮች ከአፍሪካ እየወጡ ነው፤ ለምን?ሐሙስ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም ( )ታዋቂዎቹን የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ ባንኮች ስታን...
07/10/2025

ታዋቂዎቹን ስታንዳርድ ቻርተርድ እና በርክሌይን ጨምሮ የውጭ ባንኮች ከአፍሪካ እየወጡ ነው፤ ለምን?

ሐሙስ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም ( )

ታዋቂዎቹን የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ ባንኮች ስታንዳርድ ቻርተርድ እና በርክሌይን ጨምሮ ጥቂት የማይባሉ የውጭ ባንኮች ከአፍሪካ እየወጡ መሆናቸውን ጥናት አመላከተ።

ዋና መቀመጫውን በአሜሪካ ኒው ዮርክ ሰቨን የዓለም የንግድ ማዕከል ያደረገውና ከተመሰረተ 116 ዓመታትን ያስቆጠረው የሀገራትንና የኩባንያዎችን እዳና ብድር በመለካት ዓለም አቀፉ “ሙዲስ/Moody’s/” ኩባንያ አዲስ ባወጣው ሪፖርት ዓለም አቀፍ የውጭ ባንኮች ከሀገረ ደቡብ አፍሪካና ከአፍሪካ እየወጡ መሆናቸውን አመላክቷል።

በአህጉሪቱ የአገር ውስጥ ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማትና አዳዲስ ዲጂታል ተገዳዳሪዎች ዘርፉን በበላይነት መቆጣጠራቸው ለውጭ ባንኮች ከአፍሪካ መውጣት ዋነኛው መንስኤ መሆኑን የጥናቱ ሪፖርት ገልጿል።

በዚህም የአገር ውስጥ የፋይናንስ ተዋናዮችና ሞባይል ባንኪንግንና ሌሎችንም ዲጊታል ባንኪንግ ዘዴዎች በመጠቀም በከፍተኛ ደረጃ ለሕብረተሰባቸው ብድርና ሌሎች የባንክ አገልግሎቶችን የሚያቀርቡ አዳዲስ የቴክኖ-ፋይናንስ ድርጅቶች ቀድመው በዘርፉ ጠንካራ መሠረት በመያዛቸው የተነሳ ዓለም አቀፍ የውጭ ባንኮች በደቡብ አፍሪካና በሌሎችም የአፍሪካ ክፍሎች የብድር አገልግሎቶችን በመስጠት ትርፋማ ለመሆን እየተቸገሩ መጥተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በአህጉሪቱ አሁንም ድረስ መሠረተ ልማት በበቂ ሁኔታ አለመስፋፋት፣ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ብሔራዊ የማንነት መለያ ሥርዓት አለመዘርጋትና መሰል መዋቅራዊ ተግዳሮቶች መኖራቸውና ይህም በዘርፉ ቀጣይነት ያለው ዕድገት ለማስመዝገብ ማነቆ መሆኑ ለውጭ ባንኮቹ ከአፍሪካ መውጣት በተጨማሪ መንስኤነት ቀርበዋል።

በመሆኑም በአውሮፓውያኑ ግንቦት 2024 ታዋቂው የፈረንይ ባንክ ቢ.ኤን.ፒ ፓሪባስ፣ በያዝነው ወር መጀመሪያ በመስከረም 1፣ 2025 ደግሞ ዝነኛው የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ ባንክ - ኤች.ኤስ.ቢ.ሲ ከደቡብ አፍሪካ ለቀው ወጥተዋል።

ታዋቂዎቹ የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ ባንኮች ስታንዳርድ ቻርተርድ እና በርክሌይስ ደግሞ በመላ አፍሪካ ኢንቨስትመንታቸውን እየቀነሱ መሆናቸውንና ከበርከታ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ለቀው መውጣታቸው በጥናቱ ተገልጿል።

በአጠቃላይ ከአውሮፓዊያኑ 2019 ጀምሮ በትንሹ ሰባት ትላልቅ የውጭ ዓለም አቀፍ ባንኮች በአፍሪካ ያላቸውን ኢንቨስትመንት እየቀነሱ ከአንዳንዶቹ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ ለቀው እየወጡ መሆናቸውን በመላው ዓለም በ165 ሀገራት የፋይናንስ ስጋት ትንተና ጥናቶችን በማቅረብ የሚታወቀው የ“ሙዲስ/Moody’s/” ኩባንያ የጥናት ሪፖርት አመላክቷል።

📢 CBE እና የኮሚሽን ጉዳይ፡ ከስህተቱ ጀርባ ያለው የሂሳብ ሚስጥር!በቅርቡ በሞባይል ባንኪንግ ግብይት ደረሰኞች ላይ እየታየ ያለውን ግራ የሚያጋባ የኮሚሽን መጠን ስህተት በሚገባ እንመልከተ...
01/10/2025

📢 CBE እና የኮሚሽን ጉዳይ፡ ከስህተቱ ጀርባ ያለው የሂሳብ ሚስጥር!
በቅርቡ በሞባይል ባንኪንግ ግብይት ደረሰኞች ላይ እየታየ ያለውን ግራ የሚያጋባ የኮሚሽን መጠን ስህተት በሚገባ እንመልከተው።

እኔ ለሙከራ 150 ብር ልኬ ነበር ከሲስተሙ በደረሰኙ ላይ "Commission of ETB 50.6" (50 ብር ከ60 ሳንቲም) የሚል አስደንጋጭ ጽሑፍ እያሳየ ነው። ብዙዎች “ለ150 ብር 50 ብር ኮሚሽን?!” ብለው በስሌቱ ግራ ተጋብተዋል።
ይህ የሲስተም ስህተት የመጣው ባሳለፍነው እሁድ በተደረገ ማሻሻያ የኮዲንግ ስህተት ይመስላል?
የስህተቱ መነሻ እና የሂሳብ ማብራሪያ
ይህ ችግር የባንኩ ሲስተም በውስጥ የሚሰራውን ትክክለኛ ስሌት ወደ ውጭ ባለው ደረሰኝ ማሳያ ላይ በተሳሳተ መንገድ ሲያወጣው የመጣ ነው።

ምሳሌው ላይ እንዳለው 150.00 ብር የተላከበት ግብይት ላይ፣ ደረሰኙ የሚከተሉትን ሁለት እውነታዎች ያሳያል፡
የተቆረጠው ጠቅላላ ገንዘብ (Total Debited): 156.44 ETB
የኮሚሽን ማሳያ (Displayed Commission): 50.6 ETB
🔢 እውነተኛው የሂሳብ ስሌት፡
ትክክለኛው የግብይት ክፍያ ይህን ይመስላል: 156.44 ETB−150.00 ETB= 6.44 ETB
የ 6.44 ብር ተቀናሽ ደግሞ ኮሚሽን እና 15% VAT የተካተተበት ነው። ይሄንን ስንተነትነው፡
ኮሚሽን (VAT ሳይጨመር): 6.44 ETB ÷1.15=5.60 ETB
VAT (15%): 5.60 ETB×0.15=0.84 ETB
ስለዚህ፣ የባንኩ ሲስተም ትክክለኛውን ኮሚሽን (5.60 ETB) እና ቫት (0.84 ETB) ሰርቷል።
💡 ስህተቱ የት ተፈጠረ?
ስህተቱ የተፈጠረው ሲስተሙ 5.60 (አምስት ብር ከስልሳ ሳንቲም) መሆን የነበረበትን ቁጥር፣ በስህተት 50.6 (ሃምሳ ብር ከስልሳ ሳንቲም) ብሎ በማሳየቱ ነው። ይህ ደግሞ "Decimal Point" ወይም "የአስርዮሽ ነጥብ" በስህተት መንቀሳቀስ ምክንያት የመጣ የማሳያ ችግር ነው።

በአጭሩ፡ ከሂሳብዎ የተቆረጠው 6.44 ብር ብቻ ነው፤ 50.6 ብር የሚለው ቁጥር የማሳያ ስህተት (Display Glitch) ነው።
📝 መታረም ያለበት ነገር (ጥሪ ለ CBE)
ምንም እንኳን ገንዘብ በስህተት ያልተቆረጠ ቢሆንም፣ ይህ ስህተት በደንበኞች ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ እና መተማመን ማጣት ስለፈጠረ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ይህንን ችግር በፍጥነት መፍታት አለበት።
የሲስተም እርማት (System Fix): ኃላፊነት ያላቸው ክፍሎች ኮዱን (Coding) በአስቸኳይ በመገምገም የአስርዮሽ ነጥቡ በትክክለኛው ቦታ ላይ እንዲቀመጥ ማስተካከል አለባቸው።
🙏 ይፋዊ ማብራሪያ:- ባንኩ ስለተፈጠረው ስህተት ለደንበኞቹ በይፋ ማብራሪያ መስጠት አለበት። ደንበኞች በስህተት ብዙ ገንዘብ ተቆረጠብን የሚል ስጋት ውስጥ እንዳይገቡ ግልጽ ማድረግ ያስፈልጋል።
via Asnake

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share