01/07/2025
የባንኮች የማበደሪያ ጣሪያ እስከ መስከረም ወር 2018 ዓም ይቀጥላል ተብሏል ።
ዌል እንግዲህ ።
በኢኮኖሚው ውስጥ የባንኮች ዋናው ሚና ሀብት እንዲፈጠር ማድረግ ነው ። ይህም የሚፈፀመው የገንዘብን አቅርቦት በብድር መልክ በመሥጠት ነው ።
ባንኮች እንዳያበድሩ ጣሪያ ተበጅቶላቸዋል ። Deposits mobilization በታክስና ግሽበት ምክንያት ከአስቀማጮች ኪስ ወጥቶ ብሔራዊ ባንክ ገብቷል ።
ባንኮች ደግሞ በበቂ ሁኔታ ገንዘብን ማቅረብ ካልቻሉ ሀብት ሊፈጠር አይችልም ። ሀብት ካልተፈጠረ ደግሞ ታክስ ሰብስቦ መንግሥት የሚፈለግበትን public goods ማቅረብ ይቸግረዋል ማለት ነው ። መንግሥትም ወጪውን ስለ መቀነስ የታሰበ ነገር እንዳለ ያለው ነገር የለም ።
እዚህጋ መንግሥት ወጭዬን ከታክስ እሰበስባለሁ ማለቱ መዘንጋት የለበትም ።
አሁን የተሰላው ዓመታዊ የግሽበት መጠን እንዳለ እንቀበለው ብንል እንኳን ደካማ ከሆነ ግብይት ወይም ገበያና ከመግዛት አቅም መዳከም ጋር ስለ አለመያያዙ ማረጋገጫ ማቅረብ መቻል ቀላል አይሆንም ።
የገበያ መዳከም ከሌሎች ምክንያቶች ጋር ተደምሮ አንደኛው ምክንያት የብድር ጣሪያ መኖሩ እንደሆነ ይነገራል ።
ብዙ ፕሮጄክቶች በፋይናንስ አቅርቦት ምክንያት እንደተስተጓጎለ ይገመታል ።
በአሁን ውሳኔ ባንኮች የቦንድ ግዴታ ግዢ 5 በመቶው እንዲቀርላቸው መደረጉ በአዎንታዊ መልኩ መታየት ይቻላል።
Via hailu