Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ

Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ We provide you the latest and fundamental information about Ethiopian Banking Sector.

01/07/2025

የባንኮች የማበደሪያ ጣሪያ እስከ መስከረም ወር 2018 ዓም ይቀጥላል ተብሏል ።

ዌል እንግዲህ ።

በኢኮኖሚው ውስጥ የባንኮች ዋናው ሚና ሀብት እንዲፈጠር ማድረግ ነው ። ይህም የሚፈፀመው የገንዘብን አቅርቦት በብድር መልክ በመሥጠት ነው ።

ባንኮች እንዳያበድሩ ጣሪያ ተበጅቶላቸዋል ። Deposits mobilization በታክስና ግሽበት ምክንያት ከአስቀማጮች ኪስ ወጥቶ ብሔራዊ ባንክ ገብቷል ።

ባንኮች ደግሞ በበቂ ሁኔታ ገንዘብን ማቅረብ ካልቻሉ ሀብት ሊፈጠር አይችልም ። ሀብት ካልተፈጠረ ደግሞ ታክስ ሰብስቦ መንግሥት የሚፈለግበትን public goods ማቅረብ ይቸግረዋል ማለት ነው ። መንግሥትም ወጪውን ስለ መቀነስ የታሰበ ነገር እንዳለ ያለው ነገር የለም ።

እዚህጋ መንግሥት ወጭዬን ከታክስ እሰበስባለሁ ማለቱ መዘንጋት የለበትም ።

አሁን የተሰላው ዓመታዊ የግሽበት መጠን እንዳለ እንቀበለው ብንል እንኳን ደካማ ከሆነ ግብይት ወይም ገበያና ከመግዛት አቅም መዳከም ጋር ስለ አለመያያዙ ማረጋገጫ ማቅረብ መቻል ቀላል አይሆንም ።

የገበያ መዳከም ከሌሎች ምክንያቶች ጋር ተደምሮ አንደኛው ምክንያት የብድር ጣሪያ መኖሩ እንደሆነ ይነገራል ።

ብዙ ፕሮጄክቶች በፋይናንስ አቅርቦት ምክንያት እንደተስተጓጎለ ይገመታል ።

በአሁን ውሳኔ ባንኮች የቦንድ ግዴታ ግዢ 5 በመቶው እንዲቀርላቸው መደረጉ በአዎንታዊ መልኩ መታየት ይቻላል።
Via hailu

ወጋገኑን ተከትሎ ብርሀን ወጥቷል። ብርሀን ባንክ ሠራተኞቹን በቦነስ እና በደሞዝ ጭማሪ አንበሻብሿል።
01/07/2025

ወጋገኑን ተከትሎ ብርሀን ወጥቷል። ብርሀን ባንክ ሠራተኞቹን በቦነስ እና በደሞዝ ጭማሪ አንበሻብሿል።

ወጋገን ባንክ የቦነሱን ወጋገን ፈንጥቆታል። ሌሎች ባንኮች ይጠበቃሉ። Wegagen Bank ስታፍ እንኳን ደስ አላችሁ።
30/06/2025

ወጋገን ባንክ የቦነሱን ወጋገን ፈንጥቆታል። ሌሎች ባንኮች ይጠበቃሉ። Wegagen Bank ስታፍ እንኳን ደስ አላችሁ።

ብሔራዊ ባንክ ተቀማጭ ገንዘባቸውን ማውጣት ለሚፈልጉ ደንበኞች ፈጣን ምላሽ የማይሰጡ ባንኮችን አስጠነቀቀ!! :ገንዘባቸውን ማውጣት ለሚጠይቁ ደንበኞች (Depositors) ቅድሚያ ሰጥተው በፍጥ...
29/06/2025

ብሔራዊ ባንክ ተቀማጭ ገንዘባቸውን ማውጣት ለሚፈልጉ ደንበኞች ፈጣን ምላሽ የማይሰጡ ባንኮችን አስጠነቀቀ!!
:
ገንዘባቸውን ማውጣት ለሚጠይቁ ደንበኞች (Depositors) ቅድሚያ ሰጥተው በፍጥነት ምላሽ የማይሰጡ ባንኮች ላይ ጥብቅ ዕርምጃ እንደሚወስድ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ አስታወቁ።
NBE-National Bank of Ethiopia National Bank of Ethiopia

በአዲስ አበባ የባንክ አካውንት ለመክፈት National ID ግድ እንደነበረ ይታወቃል። ከሀምሌ ስምንት ጀምሮ እነዚህ ከተሞች ይጨመራሉ።
28/06/2025

በአዲስ አበባ የባንክ አካውንት ለመክፈት National ID ግድ እንደነበረ ይታወቃል። ከሀምሌ ስምንት ጀምሮ እነዚህ ከተሞች ይጨመራሉ።

27/06/2025

በባንኮች መካከል የ 700 ቢሊዮን ብር ግብይት ተፈፅሟል - አቶ ማሞ ምህረቱ
***************************

ባለፉት 10 ወራት ባንኮች እርስ በርሳቸው 700 ቢሊዮን ብር መገበያየታቸውን የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለፁ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አፈጻጸም ጉዳዮችን አስመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

አቶ ማሞ ምህረቱ በማራሪያቸውም፤ በገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያው ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ የተደረገው ባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበት የገንዘብ ገበያ ምስረታ የባንኮችን አቅም ያሳደገ መሆነን ተናግረዋል፡፡

በማሻሻያው መሰረት የንግድ ባንኮች ወደ ብሔራዊ ባንክ መምጣት ሳይጠበቅባቸው በመገበያየት የጥሬ ገንዘብ ሲያጋጥማቸው መፍትሄ የሚያገኙበት ነው ብለዋል።

በዚህም ባለፉት 10 ወራት ባንኮች እርስ በርሳቸው 700 ቢሊዮን ብር መገበያየታቸውን ተናግረዋል።

በገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያው የአጭር ጊዜ የሰነድ ግብይት አሰራርን ተግባራዊ በማድረግም ባንኮች ከብሔራዊ ባንክ የሚገበያዩበት ሂደት እድል መመቻቸቱን ገልፀዋል።

ይህ አሰራር ገንዘብ በገበያ ውስጥ በስፋት በሚሰራጭበት ጊዜ ብሔራዊ ባንክ ገንዘቡን ከገበያ ውስጥ ይሰበስባል እንደሁኔታውም የኢኮኖሚ ሁኔታው በሚቀዛቀዝበት ጊዜ ብሔራዊ ባንክ ለንግድ ባንኮች በማበደር ኢኮኖሚው እንዲነቃቃ የሚያደርግበት መሆኑን ነው ያስረዱት።

እስካሁን ድረስ በዚህ መንገድ 530 ቢሊዮን ብር ግብይት መከናወኑንም ገልፀዋል።

እነዚህ የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያዎች የዋጋ ንረትን በተሻለ ደረጃ ለመቆጣጠር ያስቻሉ መሆናቸውንም ነው የገለፁት።

በጌታቸው ባልቻ of ebc

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለ...
26/06/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።

መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።

ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።

ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።

ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።

የውጭ ባንኮች ከዛሬ ጀምሮ በኢትዮጵያ መስራት ይችላሉ ይላል የብሔራዊ ባንክ መመሪያ።
National Bank of Ethiopia KCB Group

የውጭ ባንኮች ከዛሬ ጀምሮ በኢትዮጵያ መስራት ይችላሉ ይላል የብሔራዊ ባንክ መመሪያ። National Bank of Ethiopia KCB Group
26/06/2025

የውጭ ባንኮች ከዛሬ ጀምሮ በኢትዮጵያ መስራት ይችላሉ ይላል የብሔራዊ ባንክ መመሪያ።
National Bank of Ethiopia KCB Group

ገዳ ባንክ የኢትዮጵያ አክስዮን ገበያ ላይ እንዲሸጥ ፍቃድ አግኝቷል። ከዚህ በፊት ወጋገን ባንክ ፍቃድ ማግኘቱ ይታወሳል። Gadaa Bank Wegagen Bank National Bank of Et...
25/06/2025

ገዳ ባንክ የኢትዮጵያ አክስዮን ገበያ ላይ እንዲሸጥ ፍቃድ አግኝቷል። ከዚህ በፊት ወጋገን ባንክ ፍቃድ ማግኘቱ ይታወሳል። Gadaa Bank Wegagen Bank National Bank of Ethiopia

20/06/2025

Dashen Bank 👏👏👏👏 በደንብ ተለውጠዋል። the best customer service I have ever got. Shout out to the branch near InterLuxury hotel.

13/06/2025

ባንከሮች እያማረሩ ነው ሌሎቻችንስ?
የነዳጅ አበልን Fixed ያደረጉ ጨካኝ ባንኮች:
1,ንብ ባንክ ...ንብ ይብላቹ
2,ወጋገን ባንክ....ይጨልምባችሁ
3, ፀሀይ ባንክ.....ፀሀይ ይብላቹ
4,አዲስ ባንክ.... አሮጌ ልበሱ
5,ኦሮሚያ ባንክ.....አማራን ይጣልባችሁ
6,አማራ ባንክ.....ኦሮሞን ይጣልባችሁ
7,ደቡብ ግሎባል ባንክ....ሰሜን ይክተትህ
8,ሲዳማ ባንክ.....ወላይታን ይጣልብህ
9,ስንቄ ባንክ....ስንቃችሁ ይጥፋ
10,ፀደይ ባንክ....በልግ ያስገባችሁ
11,አሀዱባንክ....ሰይጣንን ይጣልባችሁ
12,ዘምዘም ሂጅራ ረሚስ.....ሾይጣንን ይጣልብህ
13,ቡና ባንክ....ሻይ ባንክ
14, ንግድ ባንክ.... ግድ ባንክ ቀበሌ
15,አባይ ባንክ...አዋሽ ይዉስድህ
16,አቢሲንያ ባንክ....ሳክስ ባንክ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Banking Information -EBI- የኢትዮጵያ የባንክ መረጃ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share