
13/06/2024
አወዛጋቢው ኢግል ሂልስ የቢሊዮኖች ዳላር ኮንትራት አገኘ
◉◉◉
በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለገሃር አካባቢ በሪል ስቴት ልማት ዘርፍ ላይ የተሠማራው እና ተቀማጭነቱ በአቡዳቢ ውስጥ ያደረገው ኢግል ሂልስ በ1.5 ቢሊየን ዶላር ባግዳድ ውስጥ የጎልፍ መጫወቻ ሪዞርት ሊገነባ ነው።
ኤግል ሂልስ ለጎልፍ መጫወቻ እና ለጤና መጠበቂያ ማዕከል መስሪያ የሚሆን መሬት በኢራቅ ዋና ከተማ ባግዳድ ውስጥ መረከቡን አስታውቋል።
ከዚህም በተጨማሪ የጎልፍ መጫወቻ ማዕከሉ የቅንጡ የመኖሪያ አፓርትመንቶች፣ ባለአምስት ኮከብ ሆቴል፣ ሪዞርት ክለብ ግንባታዎች ይኖሩታል።
መግለጫው ይፋ የተደረገው በኢራቅ ጠቅላይ ሚንስትር ሞሃመድ ሺያ አል ሱዳን እናመካከል
ሂልስ ሊቀመንበር ሞሃመድ አላባር መካከል ውይይት መካሄዱን ተከትሎ ነው።