Ethio channel

Ethio channel FOLLOW AND LIKE OUR CHANNEL TO GET NEW UPDATES

20/10/2023

የመዲናችን አዲስ አበባ ከንቲባ የሆኑት ወይዘሮ አዳነች. አቤቤ ስልጣኔን ለማስረከብ መልቀቂያ አስገብቻለሁ ማለታቸው ታውቋል. ይልቀቁኝ አይልቀቁኝ እርግጠኛ ባልሆንም ግን ካሉብኝ ግን ጫናዎች እና የጤና ሁኔታ አንጻር. ከዚህ በኋላ በሌላ ቀለል ባለ የሥራ መደብ ለማገልገል ዝግጁ ነኝ ማለታቸው መነጋገርያ ሆኗል.
https://youtu.be/Fe-fISLKOp4

ሰበር ዜናበደበረማርቆስ ከተማ በፋኖ አና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል ከባድ ትንቅንቅ እየተካሄደ ነው. የአገዛዙ ሰራዊት ከተማዋን በከባድ መሳሪያ እየደበደበ ነው.ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ሊንኩን...
20/10/2023

ሰበር ዜና
በደበረማርቆስ ከተማ በፋኖ አና በመከላከያ ሰራዊቱ መካከል ከባድ ትንቅንቅ እየተካሄደ ነው. የአገዛዙ ሰራዊት ከተማዋን በከባድ መሳሪያ እየደበደበ ነው.
ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ
https://youtu.be/MRLqF5npXJg

አይ ሳሮን
08/02/2022

አይ ሳሮን

ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች ከእነመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ************(ኢ.ፕ.ድ) መነሻውን ከአማራ ክልል ባህርዳር ልዩ ዞን ባህርዳር ከተማ ባደረገ  አይሱዙ  ተሽከርካሪ ...
27/01/2022

ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች ከእነመሳሪያቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ
************
(ኢ.ፕ.ድ)

መነሻውን ከአማራ ክልል ባህርዳር ልዩ ዞን ባህርዳር ከተማ ባደረገ አይሱዙ ተሽከርካሪ ውስጥ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ጭነው አዲስ አበባ በማስገባት ለሽያጭ ሲያቀርቡ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ሶስቱ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች በአይሱዙ ውስጥ ሻግ በመስራትና በውስጡ በማድረግ በቁጥር አምስት ሺህ ስድስት መቶ አስር የሚሆን የክላሽ ጥይት ወደ አዲስ አበባ ከተማ እንዲገባ አድርገዋል።

ግለሰቦቹ ይህንን መሳሪያ ለሽያጭ ሊያቀርቡ ሲሉ በተደረገ ክትትል የጦር መሳሪያውን (ጥይቱን) ጨምሮ ሶስቱም አዘዋዋሪዎች ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን የኢፕድ ምንጮች አስታውቀዋል።

የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል እርሰ መስተዳደር አቶ ለማ መገርሳ ዛሬ አዲስ አበባ ገቡ!!!
19/01/2022

የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል እርሰ መስተዳደር አቶ ለማ መገርሳ ዛሬ አዲስ አበባ ገቡ!!!

19/01/2022

በወለጋ ንፁሃን ገበሬዎች ተጨፈጨፉ!

ዓመቱን ሙሉ፣ ሙሉ ወራትና ሙሉ ሳምንታት ንፁሀን የሚታደረዱበት፣ የሰው ልጅ ቄራ ሆኗል።

በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ወለጋ ዞን በጊዳአያና ወረዳ በአንገር ጉትን ከተማ በመንደር 4 ቀበሌ ጥር 8 ቀን ለአዝመራ መሰብሰብ ወደ ማሳቸው ባቀኑ 10 አማራዎች ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ ተካሂዷል።

አመት ሙሉ የደከሙበትን አዝመራ ለመሰብሰብ ከወጡት አማራ አርሶአደሮች መካከል 10ሩ ሲገደሉ በርካቶች ቆስለዋል፣ ታግተዋል። ከተገደሉት አስር ንፁሀን አማራዎች መካከል፦
1ኛ- ዳውድ አቤ
2ኛ- አብዱ የሱፍ
3ኛ- መሐመድ ይመር
4ኛ- እብራሂም ገበየሁ
5ኛ -ተናኘወርቅ ንጉሴ
6ኛ- ወንድሙ ሀይሌ
7ኛ- ታደሰ ደምሌ እና ሌሎች 3 ስማቸው ያልደረሰን በግፈኞች ጭካኔ በተሞላበት ተገድለዋል።

በተመሳሳይ በምዕራብ ሸዋ ዞን ዳኖ ወረዳ 8 አማራዎች ሲገደሉ የሁለት ሰዎች አድራሻቸው አልታወቀም። እስካሁን የ5 ሰዎች አስከሬን ተገኝቶ ጥር 7 ቀን 2014 ስርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሕክምና ላይ የሚገኘውን አርቲስት አሊ ቢራን ጠየቁጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በዕለተ ጥምቀት በአዳማ ጄኔራል ሆስፒታል በሕክምና ላይ የሚገኘውን አንጋፋውን አ...
19/01/2022

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሕክምና ላይ የሚገኘውን አርቲስት አሊ ቢራን ጠየቁ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዛሬ በዕለተ ጥምቀት በአዳማ ጄኔራል ሆስፒታል በሕክምና ላይ የሚገኘውን አንጋፋውን አርቲስት ክቡር ዶ/ር አሊ ቢራን ጠይቀዋል።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ተገኝተዋል (ኦቢኤን)

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ******************(ኢ ፕ ድ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ፡፡ዋልያዎቹ ከምድቡ የመጨ...
17/01/2022

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ
******************
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር ተሰናበተ፡፡

ዋልያዎቹ ከምድቡ የመጨረሻ ጨዋታቸውን ከቡርኪናፋሶ አቻቸው ጋር ባደረጉት ጨዋታ በአንድ አቻ አጠናቀዋል። ቡድኑ በአንድ ነጥብ የምድቡን የመጨረሻ ደረጃ በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ድልድል ከቡርኪናፋሶ፣ ካሜሮንና ኬፕቬርዴ ጋር መደልደሉ ይታወሳል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ‼
ሀገርን በዘላቂነት እናልማ‼
የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ‼
ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ‼

16/01/2022

ልዩ መረጃ‼️

: ወራሪውና አሸባሪው ቡድን ለ7ኛ ጊዜ የሰሜናዊ የዞን ዋና ከተማና የዞኑ መቀመጫ የሆነችው ከመቀሌ 45 ኪሜ ርቀት ላይ በምትገኘው #አብአላ ላይ በተደራጀ መልኩ ጥቃት ከፍቷል። ሁሌም ዝግጁ ሆኖ የሚጠበቅው የአፋር ልዩሃይልና ህዝባዊ ሃይል ከጁንታው ጋር እልህ አስጨራሽ ውጊያ እያካሄደ ይገኛል። ጁንታው መድፍን ጨምሮ ከባድ መሳሪያ እየተጠቀመ በመሆኑና የአፋር ህዝባዊ ሃይህ ከባድ መሳሪያ ባይኖረውም እስካሁን ጠላት ከነበረበት እንዳይንቀሳቀስ አድርጎታል።

ድል ለአፋር አናብስቶች

በድሬዳዋ የሽብር ተግባር ሊፈጽሙ የነበሩ የአሸባሪው ሸኔ አባላትና የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉበድሬዳዋ ከተማ እና አካባቢው የሽብር ተግባር ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ነበር የተባሉ...
15/01/2022

በድሬዳዋ የሽብር ተግባር ሊፈጽሙ የነበሩ የአሸባሪው ሸኔ አባላትና የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በድሬዳዋ ከተማ እና አካባቢው የሽብር ተግባር ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ነበር የተባሉ የአሸባሪው የሸኔ አባላትና የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መምሪያ ዕዝ አስታወቀ።

የድሬዳዋ አስተዳደር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መመሪያ ዕዝ አባልና የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ እንደገለጹት÷ አሸባሪው የሸኔ ቡድን በምስራቅ ኢትዮጵያ በተለይም በድሬዳዋና አካባቢው ታህሳስ 11 ቀን 2014 ዓ.ም ልዩ ስሙ ገንደገበሬ በተሰኘው አካባቢ ግጭት ፈጥሯል፡፡

ይህን ተከትሎም የብሄራዊ መረጃና ደህንነት፣ የድሬዳዋ ፖሊስ፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ከሚሊሻና ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት በተደረገው ዘመቻ 4 የሽብር ቡድኑን አባላት የጦር መሳሪያዎቻቸውን በተለያዩ ስፍራዎች በመደበቅ እራሳቸውን ከህብረተሰቡ ጋር በማመሳሰል ለመንቀሳቀስ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አብራርተዋል፡፡

በቅርቡ የምስራቅ አካባቢ የሸኔ አዛዥና ጃል ኦዳ ኢብሳ በሚል ስያሜ የሚጠራው ፉአድ ሀሰን ከቢራ የተሰኘው የቡድኑ መሪ ሀረር ላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውሰዋል፡፡

በእነዚህ የሸኔ አባላት ላይ በተደረገው ምርመራ ለሽብር ተግባር ሲጠቀሙባቸው እና ሊጠቀሙባቸው የነበሩ የተለያዩ የጦር መሳሪዎች እንዲሁም 24 ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ዘርፍ የምስራቅ ቀጠና ዲቪዥን ሃላፊ ም/ኢንስፔክተር ለሜሳ መኮንን በበኩላቸው÷ የሽብርተኛው ሸኔ ቡድን አባላት ራሳቸውን ከህብረተሰቡ ጋር በማመሳሰል ለመሰወር ሲሞክሩ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት ብለዋል፡፡

በተጨማሪም 20 የክላሽንኮቭ መሳሪያዎች ከ2 ሺህ 648 ጥይቶች ጋር፣ 798 የብሬል ጥይቶች ፣ 38 የክላሽንኮቭ ካዝና፣ 2 ቦንቦች ፣ 1 ጂም ስሪ መሳሪያ ከ38 ጥይቶች ጋር፣ ወታደራዊ ትጥቆች፣ የመገናኛ ሬዲዮን ጨምሮ ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በተካሄደው ምርመራ ከቀበሩባቸው ስፍራዎች በፍተሻ መገኘታቸውንም አስታውቀዋል ሲል ድሬዳዋ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ዘግቧል።

"መንግሥት ፋኖን ትጥቅ ሊያስፈታ ነው የሚለው አሉባልታ መሰረተቢስና የአማራን ሕዝብ ለመከፋፈል የታለመ የጠላት ሴራ ነው" የአማራ ክልል መንግሥት መንግሥት ፋኖን ትጠጥቅ ሊያስፈታ ነው የሚለው...
14/01/2022

"መንግሥት ፋኖን ትጥቅ ሊያስፈታ ነው የሚለው አሉባልታ መሰረተቢስና የአማራን ሕዝብ ለመከፋፈል የታለመ የጠላት ሴራ ነው" የአማራ ክልል መንግሥት

መንግሥት ፋኖን ትጠጥቅ ሊያስፈታ ነው የሚለው አሉባልታ መሰረተቢስና የአማራን ሕዝብ ለመከፋፈል የታለመ የጠላት ሴራ መሆኑን የአማራ ክልል መንግሥት አስታውቋል።

የክልሉ መንግሥት ከፋኖ አደረጃጀት አባላት ጋር ተወያይቷል።

ፋኖ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ሀገርና ሕዝብን እየታደገ ያለ መከታ ኃይል ነው። ስለሆነም የፌደራልም ኾነ የክልል መንግሥት ፋኖን ትጥቅ የማስፈታት ሐሳብ የለውም፤ ሊኖረውም አይችልም ተብሏል በመድረኩ።

በቀጣይ የክልሉ መንግሥት የመሳሪያ አስተዳደር ሥርዓቱን ሊያሻሽል እንደሚችልም ተገልጿል።

ፋኖ በስምም ሆነ በግብሩ የአማራ ሕዝብ ክብር መገለጫ በመሆኑ በፋኖ ስም የሚነግዱ አካላትን ፋኖና መንግሥት በጋራ ይታገላሉ ተብሏል። ፋኖን ማደራጀትና ማጠናከር የክልሉ መንግሥት አቅጣጫና ተግባር ኾኖ ሳለ ትጥቅ ማስፈታት የሚለው አሉባልታ አማራን የመከፋፈል እርስ በርስ የማጋጨት የማዳከም ሴራ አካል መሆኑም ተገልጿል። (አሚኮ)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጋር የስልክ ውይይት አደረጉ*****************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጋር በወቅታዊ ጉ...
10/01/2022

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጋር የስልክ ውይይት አደረጉ
*****************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ግልፅ የስልክ ውይይት ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቡይ እንደገለጹት፤ በአገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይም ተመካክረዋል።

በውይይቱ አገራቱ በመከባበር ላይ የተመሰረተ ገንቢ ተሳትፎ ማድረግ ትልቅ ጥቅም እንዳለው መስማማታቸውንም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገፃቸው አስታውቀዋል።

"በቁጥጥር ስር የነበሩ እስረኞች በምህረት መለቀቃቸው በደስታ እንደተቀበሉት የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አስታወቁ****************** (ኢ.ፕ.ድ)በኢትዮጵያ ቁል...
08/01/2022

"በቁጥጥር ስር የነበሩ እስረኞች በምህረት መለቀቃቸው በደስታ እንደተቀበሉት የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አስታወቁ
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢትዮጵያ ቁልፍ የሚባሉ ተቃዋሚዎችን ጨምሮ በርካታ እስረኞች በምህረት መለቀቃቸውን በደስታ እንደተቀበሉት የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ገለጹ።

የ"እስረኞችን በምህረት መለቀቅ የምደግፈው ተግባር ነው" ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ ሁሉም ወገኖች በዚህ ውሳኔ ላይ በመመርኮዝ ዘላቂ የሆነ ሰላም ይመጣ ዘንድ እንዲተባበሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

“ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት በማድረግ፣ ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ ውይይትና እርቅ ሂደት እንዲጀምሩ ጥሪዬን አቀርባለሁ" ሲሉም ነው ዋና ጸሀፊው መልዕክታቸውን ያስተላለፉት።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅትም ለዚህ ተግባር አስፈላጊውን እገዛና ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

ባለፉት አመታት በነበረው ግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ለሚገኙና ለችግር ለተጋለጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች ሁሉን አቀፍ የሚደረገው የሰብዓዊ ድጋፍ ከፍተኛ መሻሻል ያሳያል ብለው እንደሚጠብቁም ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።

ዋና ጸሀፊው በዚሁ መልዕክታቸው መቋጫ ላይም ለኢትዮጵያዊያን መልካም የገና በዓል ሲሉ ምኞታቸውን ገልጸዋል።

በመሀመድ ሁሴን

07/01/2022

Subscribe to this channelLike Video 👍👍👍👍comment 💬💬Kana Television | Nahoo TV | Kana TV | Kana rama | Kana Television | EBS TV WorldWide | JTV Ethiopia...

ኬርያ ኢብራሂም አልተፈታችምከእሥር በምሕረት እንዲፈቱ የተወሰነላቸው የሚከተሉት ናቸው1. አቶ ስብሐት ነጋ2. ወሮ ቅዱሳን ነጋ 3. አቶ ዓባይ ወልዱ4. አቶ አባዲ ዘሙ5. ወሮ ሙሉ ገብረ እግ...
07/01/2022

ኬርያ ኢብራሂም አልተፈታችም

ከእሥር በምሕረት እንዲፈቱ የተወሰነላቸው የሚከተሉት ናቸው

1. አቶ ስብሐት ነጋ
2. ወሮ ቅዱሳን ነጋ
3. አቶ ዓባይ ወልዱ
4. አቶ አባዲ ዘሙ
5. ወሮ ሙሉ ገብረ እግዚአብሔር
6. አቶ ጁሐር መሐመድና በእርሱ መዝገብ የተከሰሱ ሁሉ
7. አቶ እስክንድር ነጋና በእርሱ መዝገብ የተከሰሱ ሁሉ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio channel posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share