ሸዋ Hub

ሸዋ Hub ሸዋ የትልቋ ኢትዮጲያ ማዕከልነቱን እንዳስጠበቀ ኅብረ ብሄራዊ ክልላዊ አስተዳደር ይዋቀራል፡፡

የሰማዕታት ክደት!• ታሪካችን በደም የተጻፈ ነው፦ ሸዋ፣ ወሎ፣ ጎጃም እና ጎንደር ላይ የወደቁት ጀግኖቻችን አባትና ልጅ፣ ወንድማማቾች እና ሙሉ የቤተሰብ አባላት በአንድነት የተሰዉበት ታሪክ ...
19/08/2026

የሰማዕታት ክደት!

• ታሪካችን በደም የተጻፈ ነው፦ ሸዋ፣ ወሎ፣ ጎጃም እና ጎንደር ላይ የወደቁት ጀግኖቻችን አባትና ልጅ፣ ወንድማማቾች እና ሙሉ የቤተሰብ አባላት በአንድነት የተሰዉበት ታሪክ ነው። [እነዚህ የቀረቡት ፎቶዎች ማሳያ ናቸው እንጂ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ለዚህ ትግል ወድቀዋል]።

• የአደባባዩ ውሸት፦ ዘመነ ካሴ ግን ከፈረንሳይኛ ጋዜጠኛ ጋር በነበረው ቃለ-መጠይቅ «ፋኖ ከህወሓት ጋር አልተዋጋም» ብሎ ሲዋሽ፣ ይህንን ቤት ሙሉ የፈሰሰውን የቤተሰብ ደም በአደባባይ ካደ።

• ቆመህም ሞተህም ይሸጥሃል፦ ይህ ሰው ቆመህም ይሸጥሃል፤ ሞተህም ታሪክህን፣ የሰራኸውን ስራና የፈጸምከውን ታላቅ ጀብድ ሙሉ በሙሉ የሚክድ የክህደት ባህሪ አለው።

• የጠላት ፈረስ፦ ውስጡ የሰረጸው የህወሓት ስነ-ልቦና ለጠላት ፈረስ መሆንን ስለሚያስገድደው፣ ዛሬ የሰማዕታቱን ደም የካደ ነገም ሙሉ አማራን አሳልፎ መሸጡ አይቀሬ ነው።

ከብዙ ትእግስት ቡኃላ የልቤ መሻት ተፈፀመልኝ የምትሉበት ቀን   ያቅርብላቹሁ❤🙏
18/08/2026

ከብዙ ትእግስት ቡኃላ የልቤ መሻት ተፈፀመልኝ የምትሉበት ቀን ያቅርብላቹሁ❤🙏

ከደብረብርሃን ከተማ አንጉለላ ቀበሌ ከእምዬ ምኒልክ የትውልድ ስፍራ የእምዬ ምኒልክ፣ እቴጌ ጣይቱ እና ፊታውራሪ ገበየሁ የልደት በዓል በድምቀት ተከበረ።
18/08/2026

ከደብረብርሃን ከተማ አንጉለላ ቀበሌ ከእምዬ ምኒልክ የትውልድ ስፍራ የእምዬ ምኒልክ፣ እቴጌ ጣይቱ እና ፊታውራሪ ገበየሁ የልደት በዓል በድምቀት ተከበረ።

ክርስቶስ ሰምራ !!ሸዋ ቡልጋ ሀገረማርያምቅዱስ ገዬ !! #አምላክን ከሰይጣን ጋር ለማስታረቅ የሞከረችው የኢትዮጵያዊቷ ሴት የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ የቅዱስ ጌዬ ደብረ ቤቴል ቅድስት ክርስቶስ...
17/08/2026

ክርስቶስ ሰምራ !!
ሸዋ ቡልጋ ሀገረማርያም
ቅዱስ ገዬ !!

#
አምላክን ከሰይጣን ጋር ለማስታረቅ የሞከረችው የኢትዮጵያዊቷ ሴት የቅድስት ክርስቶስ ሰምራ የቅዱስ ጌዬ ደብረ ቤቴል ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ አንድነት ገዳም ሲሆን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ የተወለደችው በሸዋ ቡልጋ አውራጃ ቅዱስጌየ በተባለ አካባቢ ሲሆን የአባቷ ስም ድርሳኒ እና የእናቷ ስም ደግሞ እሌኒ ይባላል፡፡

እነዚህ ቅዱሳን እናትና አባቷ አምላካቸውን የሚፈሩ በሃይማኖታቸው የጸኑ፣በበጎ ምግባራቸው የተከበሩ ነበሩና ልጃቸውን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራንም የአምላካቸውን ህግጋትና ስርዓት እያስጠኑ ብሉይና ሀዲስ ኪዳንን እያስተማሩ ካሳደጓት በኋላ ለኢየሱስ ሞኣ ልጅ ለሳምራ ጊዮርጊስ ድረዋት አስር ወንድ ልጅና ሁለት ሴት ልጆችን ወልዳለች፡፡

ከዚህ በኋላ ባለቤቷ ይሞትባታል እርሷም ወደ ጽድቅና ምናኔ ህይወት አመራች በዘመኑም አጼ ገብረ መስቀል የሚባል ደግ ንጉስ ነበርና ዝናዋን ሰምቶ 277 አገልጋዮችን ላከላት፡፡

ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ቅዱስ ሚካኤልን ልኮ ከሾላ ገበያ ከተማ በስተ ደቡብ ምስራቅ በግምት 10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ቅዱስ ጌየ ከተባለው ስፍራ የቅዱስ ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን ስሪ ፣አጽድ ትከይ እንደተባለችና የሚካኤል ታቦትም በእጇ ተሰጥቷት የሚካኤልን ቤተ-ክርስቲያንና የአሁኑን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ቤተ-ደናግል አንድነት ገዳም የጥንቱን የቃና ዘገሊላ ደብር እንደተቋቋመ የተለያዩ ድርሳናት ያወሳሉ፡፡

ቤተክርስቲያኑን ያሰራችው ከአፄ ገ/መስቀል በተሰጣት አገልጋዮች ነው፡፡ ጽድና ሀገር በቀል ዛፎችንም አስተከለች፡፡በቦታውም የቅዱስ ሚካኤልን ታቦት አስገባች፡፡

ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ከቡልጋ ቆይታዋ በኋላ ወደ ባህር ዳር ጣና ሀይቅ ገዳም ሄደች አስራ ሁለት አመት በባህር ላይ ስትጸልይ ቆየች፡፡
ብዙ ታምራትንም አየች ከዚህም በኋላ ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ከእግዚአብሄር ጻድቅነትን ከተቀዳጀች በኋላ ዲያቢሎስን (ሰይጣንን ) ከእግዚአብሄር ጋር ለማስታረቅ እንደሞከረች እና እግዚአብሄርም እሺ ካለሽ ጠይቂው አላትና ስትጠይቀውም ከፊቴ ዘወር በይ ብሎ ሊመታት ሲልም ቅዱስ ሚካኤልም ሰይጣንን እጁን በሰይፉ ብሎ እንዳስለቀቃት የቤተ-ክርስቲያናት ድርሳናት ይመሰክራሉ፡፡

የገዳሙ ክብረ በዓል የእረፍቷን ቀን አስመልክቶ በየአመቱ ነሐሴ 24 እና ጥር 12 ቃና ዘገሊላን አስመልክቶ ይከብራል፡፡
ነሐሴ 24 ቀን የገዳሙ ንግሰ በዓል ይከበራል !!
የበረከቱ ተካፋይ ያድርገን !!
አሜን /3/
ሰላም ለሁላችን !!
#
አቤል ወርቁ ዘ-ኮተቤ

የሸዋ 39ኙ ነገሥታት‎~~~~~~~~~~~~~~~‎በሽዋ የኢትዮጵያ ነገሥታት ስምና ዓ. ም‎~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~‎1/ አፄ ይኩኑ አምላክ (ከ1253_1268 ዓ/ ም)‎‎2/ አፄ  አ...
14/08/2026

የሸዋ 39ኙ ነገሥታት
‎~~~~~~~~~~~~~~~
‎በሽዋ የኢትዮጵያ ነገሥታት ስምና ዓ. ም
‎~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
‎1/ አፄ ይኩኑ አምላክ (ከ1253_1268 ዓ/ ም)

‎2/ አፄ አግብዓ ጽዮን (ከ1268_1277)

‎3/ አፄ ፅንፈ አርዕድ (ከ1277_1278)

‎4/ አፄ ሕዝበ አሠግድ (ከ1278_1279)

‎5/ አፄ ቅድመ አሠግድ (ከ1279_1280)

‎6/ አፄ ጃን አሠግድ (ከ1280_1281)
‎7/ አፄ ስበዓ አሠግድ (ከ1281_1282)

‎8/ አፄ ውድም አርዕድ (ከ1282_1297)

‎9/ አፄ ዓምደ ጽዮን 1ኛ (ከ1297_1327)

‎10/ አፄ ሰይፈ አርዕድ (ከ1327_1355)

‎11/ አፄ ውድም አስፈሬ (ከ1355_1365)

‎12/ አፄ ዳዊት (ከ1365_1395)

‎13/ አፄ ቴዎድሮስ 1ኛ (ከ1395_1399)

‎14/ አፄ ይስሐቅ (ከ1399_1414)

‎15/ አፄ እስክንድያስ (እስክንድር) (ከ1414_1414 በወራት ነው የነገሠው)

‎16/ አፄ ሕዝብናኝ (ከ1414_1418)

‎17/ አፄ በድልናኝ (ከ1418_1419)

‎18/ አፄ ዓምደ እያሱ "ዳዊት" (ከ1419_1426)

‎19/ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ (ከ1426_1460)

‎20/ አፄ በእደ ማርያም (ከ1460_1470)

‎21/ አፄ እስክንድር (ከ1470_1486)

‎22/ አፄ ዓምደ ጽዮን 1ኛ (ከ1486_1487)

‎23/ አፄ ናኦድ (ከ1487_1500)

‎24/ አፄ ልብነ ድንግል (ከ1500_1532)

‎25/ አፄ ገላውዲዎስ (ከ1532_1551)

‎26/ አፄ ሚናስ (ከ1551_1555 ዓ. ም)

የግራኝ ወረራን ተከትሎ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ ወደ ጎንደር ሲዛወር ‎በሸዋ ብቻ ንጉሥ የነበሩ እነዚ ናቸው

‎27/ አቤቶ ያዕቆብ

‎28/ አቤቶ ሥግው ቃል

‎29/ አቤቶ ነጋሲ(ነጋሲ ክርስቶስ)

‎30/ አቤቶ ስብስቴ(ሰብስቲያኖስ)

‎31/ መርድ አዝማች አብየ

‎32/ መርድ አዝማች አምሀየስ (አመኃ ኢየሱስ)

‎33/ መርድ አዝማች አስፋ ወሰን

‎34/ መርድ አዝማች ወሰን ሰገድ

‎35/ ንጉሥ ሣህለ ስላሴ

‎36/ ንጉሥ ኀይለ መለኮት

‎እንደገና ሙሉ ኢትዮጵያን ከሸዋ ያስተዳደሩ

37/ ንጉሠ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ አፄ ምኒልክ

38/ ንግስተ ነገስት ዘውዲቱ

39/ ንጉሰ ነገስት አፄ ኃይለ ሥላሴ

The 39 emperors / empress of ethiopia from Shewa

ዳየር ማሪያም  በሰ/ሸዋ ዞን ግሼ ወረዳ ዉስጥ  ከዋና ከተማዋ ራቤል በስተ ምዕራብ አቅጣጫ በ15 ከሜ ርቀት ላይ የምትገኘዉ እና በ700ዓ.ዓ የተመሰረተችዉ ጥንታዊቷ እና ታሪካዊቷ የዳየር ማ...
29/07/2026

ዳየር ማሪያም

በሰ/ሸዋ ዞን ግሼ ወረዳ ዉስጥ ከዋና ከተማዋ ራቤል በስተ ምዕራብ አቅጣጫ በ15 ከሜ ርቀት ላይ የምትገኘዉ እና በ700ዓ.ዓ የተመሰረተችዉ ጥንታዊቷ እና ታሪካዊቷ የዳየር ማሪያም ቤተክርስቲያን በየ አመቱ ህዳር 21 አመታዊ ክብረ በአሏ ነዉ ፡፡
ዋናዉን የወረኢሉን መንገድ ወደ ቀኝ ትተዉ ቅዱስ ባልወልድን ተሳልመው እና የቅዱስ ጊወርጊስን ቤተክርስቲያንን መንገዳችንን ሰላም አድርገዉ ብለው ተስለዉ ሚስቴን አደራ እና አብሮ ፈራጅን አለፍ እንዳሉ ከአንድ የገደል አፋፍ /ዳየር አፋፍ/ ላይ በድንገት ብቅ ይላሉ።
ታዲያ ነፋሻማዉን አየር እየተቀበሉ በእልልታ እና በዝማሬ ታጅቦ ሽቅብ ወደ ተራራዉ የሚተመዉን ሰዉ አሻግረዉ እያዩ እና በፈጣሪን ተዓምር እየተደነቁ እርስዎም ጉዞዎን ይቀጥላሉ። ታዲያ በቆይታዎ
➽ወደ ተራራዉ ሲወጡ በመንገድዎ ግራ እና ቀኝ በኩል ያሉ ጥንታዊ የንጉስ ዲሜጥሮስ ቤተመንግስት እና ጥንታዊ እስር ቤቶች ፍርስራሽ ቀልብዎን የመሳብ አቅም አለዉ፡፡
➽ቤተክርስቲያኗ ዙሪያዋን በገደል የተከበበች እና በግራ እና በቀኝ በዋየት እና ቀጭኔ ወንዞች ታጅባ መስቀለኛ ቦታ ላይ የተመሰረተች ጥንታዊ ቤተከርስቲያን ነች፡፡
➽ ወደ መስቀለኛዉ ቦታ መግቢያ እና ተራራዉን መዉጫ አንድ መንገድ/አንድ በር/ ብቻ ያለ መሆኑ
➽የጌታችን መድሃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ግማደ መስቀል ወደ ግሼን ደብረ ከርቤ ከመሄዱ በፊት መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር በተባለዉ መሰረት በዚህ መስቀለኛ ቦታ ለሰባት ቀን ማደሩ፡፡
➽ይህንን ምክንያት በማድረግ ለግማደ መስቀሉ እና ለአፄ ዘርዓያ ያዕቆብ መታሰቢያነት የተተከሉት 7/ሰባት/እድሜ ጠገብ ዛፎች ሌላዉ የቤተክርስቲያኗ ደምቀቶች ናቸዉ፡፡
➽ ከተተከሉት 7 የፅድ ዛፎች መካከል አንድኛዉ ፅድ ምንም ዝናብ በሌለበት በበጋ ወቅት የፅዱ መኃከለኛዉ ክፍል እና ቅርንጫፎቹ በመብረቅ ቢመቱም ዘፉ ግን እስካሁን ሳይወድቅ እንደቆመ መኖሩ።
➽ጠጅ ነሽ የምትባለዉ ስትሆን ይቺ ዛፍ በንጉስ ድሜጥሮስ መታሰቢያነት ጠጅ ብቻ እየጠጣች ያደገችዉ አስደናቂዋ ዛፍ ፡፡
➽ የቤተክርስቲያኗ የዉስጥ ክፍል በባህላዊ ቀለማት በትዋቡ ጥንታዊ የግድግደዳ ላይ ስእሎች
➽በጣሊያን ወረራ ወቅት የተሰዉት የደጃዝማች መሸሻ እና የልጃቸዉ ደጃዝማች ዳምጠዉ መሸሻ መቃብር መኖሩ
➽ የአፄ ናዖድ አፅም በ1508 በዚች ቤተክርስቲያን ዉስጥ በክብር ማረፉ
የቤተክርስቲያኗን ጥንታዊነት እና ታሪካዊነት የሚመሰክሩ መገለጫዎቿ ናቸው።

getasew

ደብረ ብርሃን ጠባሴ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል!የአፄ ዘርአያቆብ ከተማ 👌
27/07/2026

ደብረ ብርሃን ጠባሴ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል!

የአፄ ዘርአያቆብ ከተማ 👌

“መንዝ ሰው ሲሞት ሀዘን እጅግ ያጠብቃል። ሌላው ቀርቶ በቁሙ ተቸግሮ ጠይቆት ያማያውቀው የቅርብ ዘመዱ ሲሞት ጥልቅ ሀዘን ይገባዋል፡፡ ፊቱን ይነጫል፡፡ በለበሰው ጨርቅ ሞዥቆ ያቆስለዋል። ማቅ...
25/07/2026

“መንዝ ሰው ሲሞት ሀዘን እጅግ ያጠብቃል። ሌላው ቀርቶ በቁሙ ተቸግሮ ጠይቆት ያማያውቀው የቅርብ ዘመዱ ሲሞት ጥልቅ ሀዘን ይገባዋል፡፡ ፊቱን ይነጫል፡፡ በለበሰው ጨርቅ ሞዥቆ ያቆስለዋል። ማቅ (ጥቁር አሮጌ ዝተት) ይለብሳል፡፡ ሴቶቹ ከል (የልብሱ ነጭነት እንዲጠፋ ቀለም ያለው ቅጠል ተወቅጦና ተበጥብጦ ይነከራል) ይለብሳሉ። ለተወሰኑ ወራት አልጋ ላይ አይተኙም:: ለቅሶ ያልደረሰ ዘመድ ቢኖር ለቅሶዬን በላ ተብሎ እስከወዲያኛው ይቆራረጣሉ። ቢታረቁም እንኳን ለያዥ ለገናዥ አቅተው ነው:: ያገር ሽማግሌ ተጠርቶ ነው:: የነፍስ አባት የሚያስፈልግበትም ጊዜ አለ፡፡

የመንዝ ገበሬ ሰው ሲሞትበት ሊሰማ እስከሚችልበት ርቀት ድረስ በከፍተኛ ድምፅ ጥሪ ይደረጋል፡፡ ለዚህ ኃይለኛ ድምፅ ያለው ሰው ይመረጣል። ከርቀት የጥሪ ድምፅ በተሰማ ጊዜ ሁሉም አጣርቶ ለመስማት ጆሮውን ያቆማል። ከዚያ መንደርም እንዲሁ ኃይለኛ ድምፅ ያለው ሰው እንደገና ወደ አልተሰማበት የዘመድ አካባቢ በቅብብሎሽ ጥሪ ይደረጋል:: ጥሪው ጆሮው የገባለት ሁሉ አልተሰማም ወደሚልበት ወዳጅ ዘመድ ሁሉ ያስተላልፋል:: ከጥሪ በኋላ ለቅሶ አልሰማሁም ማለት አይቻልም:: የለቅሶ ጥሪ ከርቀት ሲሰማ ማንኛውም ሰው የማን ለቅሶ እንደሆነ የማዳመጥና ባጋጣሚ ድምፁ አልተሰማው ከሆነ ካካባቢው ጠይቆ የመረዳት ማኅበራዊ ግዴታ አለበት፡፡

ታዲያ የሟች የቅርብ ዘመድ የሆነ መጀመሪያ ባካባቢው ላለው ወዳጅ ዘመድ የሞተበት ምኑ እንደሆነ ጠቅሶ "ሞቶብኛልና ተከተሉኝ" የሚል መልዕክት ያስነግራል። ንፍሮውን ያስቀቅልና፣ እንጀራውን ያስጋግርና በአህያ አስጭኖ ወይም ለቀስተኛው እየተጋገዘ በሸክም የሰዓታት ጉዞ አድርጎ ለቀብር ይደርሳል። ከቀብር መልስ ሀዘንተኛውን አጅበው የመጡት ሰዎች ወደየመጡበት ይመለሳሉ እንጂ በጣም አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር አስከሬን ወደ ወጣበት ቤት አይሄዱም:: በመልስ ላይ እያሉ አመቺ ቦታ ሲያገኙ ያመጡትን ንፍሮና እንጀራ ይመገቡና መንገዳቸውን ይቀጥላሉ። አስከሬን ከቤቱ የወጣበት ሰው ምግብ የሚያዘጋጀው እዚያው በመንደሩ ላሉት ሰዎች ብቻ ነው፡፡

የሞተው ሰው ታዋቂ ሆኖ በቅሎ ወይ ፈረስ፣ ጠመንዣና አሽከር ያለው ከሆነ እሱን ሆኖ የሚተውን ሰው ወይ በራሱ ተነሳሽነት ይመሰላል፤ አለያም ሰዎች እንዲመሰል ይጠይቁታል። እገሌ ሟችን ተመሰለ ይባላል:: ልክ እንደ ሟች ይለብሳል፣ በቅሎ ይጫንለትና ተቀምጦባት በለቀስተኛው መሀል ወዲያ ወዲህ ይመላለሳል። ሰዎች ጠመንዣቸውን በትከሻቸው ተሸክመው ግራና ቀኝ በመሆን ከበቅሎዋ ጋር እንዳሽከር እየሮጡ ያጅቡታል። ለቀስተኛው ከጩኸቱ ታቅቦ ተመሳዩን ያያል። በሄደ በተመለሰ ቁጥር የሟችን መልዕክት ጮክ ባለ ድምፅ ያስተላልፋል። ለምሳሌ ወዲያ ሲሄድ "ልጆቼን አደራ ብሏችኋል" ይላል። ሲመለስ ደግሞ "ልጆቼ በሀብት እንዳትጣሉ አደራ ብሏችኋል" እያለ ይቀጥላል:: ብቻ ሆድ ሊያባባና እንባ ሊያሰመጣ የሚችል ግን ከሰውየው ተግባር ጋር የሚሄድ መሆን ይኖርበታል። እንዲተላለፍ የሚፈለገውን ቁም ነገር እስከሚጨርስ ድረስ ይናገራል:: እያንዳንዱ መልዕክት ሲነገር አብዛኛው ሰው ከንፈሩን እየመጠጠ የለቅሶ ጩኸቱን ያቀልጠዋል፡፡ ልክ አስለቃሽ ስትኖር እንደሚሆነው ማለት ነው፡፡

ይህ ሲያልቅ ፉከራ ይቀጥላል። በየፉከራው መሀል ጠመንዣ የያዘና በል ያለው ወደ ሰማይ ይተኩሳል። በለቅሶም ሆነ በሠርግ ወይም በሌላ ድግስ ጠመንዣ ያለው ሰው ይዞ መገኘት የተለመደ ነው:: የውበት፣ የሀብት እና የጀግንነት መግለጫ ተደርጎ ስለሚታይ መደነቂያና መከበሪያ ነው:: "አይ የእገሌ ጠመንዣ አያያዝ፣ አይ ቁመና፣አይ ሙስና” ይባልለታል።
@@@@@
ህይወቴ ከቆቆ እስከ ከርቸሌ፣ተድላ ድረሴ

"የደብረ ብርሃን ሕዝብ በግርማዊነታቸው ቸርነት ከውኃ ችግር ስለመዳኑ።" 🟢🟡🔴ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት በደብረ ብርሃን የሚኖረው ሕዝባቸው በውኃ ረገድ መቸገሩን ተመልክተው ፥ ይህነኑ ችግሩን ለማ...
23/07/2026

"የደብረ ብርሃን ሕዝብ በግርማዊነታቸው ቸርነት ከውኃ ችግር ስለመዳኑ።"
🟢🟡🔴
ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት በደብረ ብርሃን የሚኖረው ሕዝባቸው በውኃ ረገድ መቸገሩን ተመልክተው ፥ ይህነኑ ችግሩን ለማራቅ መልካም ሐሳባቸው በመሆኑ ፥ ከከተማው ርቆ ከሚገኘው ከአፄ ዘርአ ያዕቆብ ምንጭ ውኃው በሞተር ተጎትቶ በቤተ መንግሥቱ አጠገብ በተዘጋጀው በውኃ መጠራቀሚያ ገብቶ ሕዝቡ ከውኃ ጥሙ እንዲረካና በዚህ ረገድ ያለው ችግሩ እንዲወገድ ስላደረጉት ፤ ታላቅ ፍሥሓ አድርጓል።
ይህነንም ሒዶ ለመመረቅና ውኃውን ለመክፈት ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ግንቦት ፲፭ ቀን ከጧቱ በ፫ ሰዓት ክቡር ራስ እምሩን ፤ ክቡር ራስ አደፍርሰውን ፤ ክቡር ደጃዝማች ዓምዴን ፤ ክቡር ደጃዝማች መስፍንን ፥ ክቡር ኰሎኔል ዓቢይን ፤ ክቡር ደጃዝማች ዓባይንና ክቡር ደጃዝማች በቀለ ወያን ፥ ክቡር ማጆር ተድላ መኰንንን አስከትለው ወደ ደብረ ብርሃን ጉዞ ጀመሩ።
ከደብረ ብርሃንም ሊደርሱ አቅራቢያ ፤ በሥራ ምክንያት ወደ ትግሬ ሒደው የነበሩት ክቡር ራስ አበበ አረጋይ የጦር ሚኒስትር ፤ በዚሁ ቀን ደብረ ብርሃን ይገኙ ስለነበረ ፤ ከከተማው ፳፬ ኪሎ ሜትር መጥተው ተቀበሏቸው።
ወዲያው ላ፭ ሰዓት ሩብ ጉዳይ ሲሆን ከታሰበበት በደረሱ ጊዜ ፥ የደብረ ብርሃን አገረ ገዥ ይጠባበቁ ስለነበረ ፤ የውኃ ሞተር ወደ ቆመበት ወደ አፄ ዘርአ ያዕቆብ ምንጭ ሒደው ጎበኙ።
ከዚህ በኋላ ወደቤተ ክርስቲያን ሒደው ተሳልመው ወደቤተ መንግሥቱ ገብተው ጥቂት እንደቆዩ ፤ የደብረ ብርሃን ሕዝብ ብዙ ዘመን ተቸግሮበት የነበረውን የውኃ ችግር ለማስወገድ ወደአዘጋጁለት የውኃ ማጠራቀሚያ ሒዶ በናፍቆት ግርማዊነታቸውን ይጠባበቅ ነበርና የጦር ሠራዊቱ ግራና ቀኝ ተሰልፎ በቆመበት ማህል ሒደው በተዘጋጀው ስፍራ በቆሙ ጊዜ የታየው ደስታና ክብር በጣም ከፍ ያለ ነው። ካህናቱ ልብሰ ተክህኖዋቸውን ፤ መዘምራኑ የማዕርግ ልብሳቸውን ለብሰው፦
አብርሂ አብርሂ ደብረ ብርሃን
ንጉሥኪ በጽሐ ኃይለ ሥላሴ
ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ።
እያሉ ቃናው በሚያምር ዜማ ባለዘቡ ጊዜ ደብረ ብርሃን አማን በአማን ደብረ ብርሃን ሁና ታየች።
ቀጥሎም የደብረ ብርሃን ተማሪ ቤት ተማሪዎች ለበዓሉ የተስማማ መዝሙር ዘምረው ሲጨርሱ የከተማው ሹም አለቃ ገብረ አጋእዝት ከዚህ በታች ያለውን ዲስኩር ተናገሩ።
ያለቃ ገብረ አጋዕዝት ዲስኩር።
ግርማዊ ሆይ።
የደብረ ብርሃን ከተማ የተቆረቆረው በሺ አራት መቶ ፳፮ ዓመት ባፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥት ነው። ዛሬ ፭፻፲ ዓመት ይሆነዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየጊዜው የሚነግሡት ነገሥታት ጥንታዊነቱን በመመልከት ምንም ክብሩን ባይቀንሱበት ለሕዝቡ የሚጠቅም ፤ አገሩን የሚያለመልም ይኸንን የመሰለ ወሀ እከተማ ውስጥ እንዲገባ ታስቦለት አይታወቅም ነበረ። ስለ ወኃው ችግር ሕዝቡም እያነሰ ፥ ከተማነቱንም እየተቀነሰ ፤ ይሔድ ጀመረ።
የግርማዊነታቸው ሰፊ ችሮታ።
ግርማዊነትዎ የኢትዮጵያን ባላደራነት ከእግዚአብሔር በተቀበሉ ጊዜ ኢትዮጵያ ከጎረቤቶቿ የምትተካከልበትን በሰፊው ሲመሠርቱ የዚህንም የደብረ ብርሃንን ሕዝብ ውኃ ችግር ተመልክተው ባ፲፱፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ክቡር ቢትወደድ መኰንን የንግድ ሚኒስትር ነበሩና ለደብረ ብርሃን ከተማ ወኃ ለማስገባት ከምን ቦታ እንደሚገኝ በመሐንዲስ እንዲያስመረምሩ ታዝዘው ሙሴ ሚናስ የሚባለው መሐንዲስ መርምሮ ጉናጉኒት የሚባለውን ለማስገባት ይቻላል ፤ ግን ብዙ ቧንቧ ያስፈልጋል ስላለ ለጊዜው ቢዘገይም ግርማዊነትዎ በልቡናዎ የሚያስቡት ፤ ባንደበትዎ የሚናገሩት እንደማይቀር ከእግዚአብሔር የተፈቀደ ስለሆነ አሁን ከኢትዮጵያ ትንሣኤ በኋላ በሺ፱፻፴፭ ዓመተ ምሕረት ደብረ ብርሃንን ለማደስ ወሀ ማግባት ያስፈልጋል ብለው ግርማዊነትዎ ያዘዘውን ለመፈጸም በክቡር ደጃዝማች መንገሻ አስታዋሽነትና በደብረ ብርሃን ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሹም አሳሳቢነት ፤ ያገር ግዛት ሚኒስቴር የማዘጋጃ ቤቶች ጽሕፈት ቤት ሹም መሐንዲሶች ይዘው እንዲመረመር ሆኖ ለዚህም የመጡት መሐንዲሶች የአፄ ዘርአ ያዕቆብን ምንጭ በሞተር ለማግባት ይቻላል ብለው ካስረዱ በኋላ ፤ የማዘጋጃ ቤቶች ዲረክተር በየካቲት ወር ፲፱፻፴፮ ዓመተ ምሕረት ብራንካ የሚባለውን የወኃ መሐንዲስ ይዘው መጥተው እንደተባለው ለመሠራት መቻሉንና የሚሠራበትም ዋጋ አስር ሺህ ሰባት መቶ ሰላሣ ስድስት ሺሊንግ ካርባ ሣንቲም መሆኑን አረጋግጠው ሥራው እንዲጀመር ሆኖ ግርማዊነትዎ የካቲት ፲፯ ቀን መጥተው የሞተሩን አኳኋን ከተመለከቱት በኋላ ፤ የሚያስፈልገው መሣሪያ ሁሉ ቢገኝ ከዚሁ ፥ ቢታጣም ካዲስ አበባ እየመጣ እንዲፈጸም አዝዘው ስለነበረ ይኸው በተጀመረ በ፫ ወር እፍጻሜ ደረሰ።
ከደብረ ብርሃን ላይ በአፄ ዘርአ ያዕቆብ ዘመን ብርሃን ወረደ ፤ ወርቅ ዘነመ ቢባል ለዓይን ለርእይና ለታምራት ብቻ ነው እንጂ እንደዚህ ለሕዝብ ጥቅም የሚሆን አልተሠራበትም። ግርማዊነትዎ ዛሬ የሠሩላት ውለታ ለምንጊዜም የማይዘነጋ በሺ ከሚቆጠረው ካለፈው ታሪክዎ ተጨማሪ ታሪክ ሆኖ የሚቆጠር ከመሆኑ በላይ በዛሬ ቀን ሕያዋኑ ይቅሩና በዓፀደ ነፍስ ያሉ ምውታን ሊያመሰግኑ የሚገባ በሆነ ነበረ። የደብረ ብርሃን ሕዝብ ከርደተ ቀላይ ከጽመዓ ማይ እንዲድን ባቆሙት በውለታዎ ውሥጥ ያለውን ወሀ ከግርማዊነትዎ እጅ ለመቀበል ሕዝቡ በአንቃዕድዎ ይመለከታል ብለው ጨረሱ።
ከዚህም በኋላ ከተማሪዎቹ አንዱ ከዚህ በታች ያለውን አጭር ቃል ተናገረ።
ግርማዊ ሆይ።
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሳምራዊትን እኔ ከምሰጠው ውኃ የሚጠጣ ሁሉ ለዘለዓለሙ አይጠማም ፤ ይኸውም ውኃ ለዘለዓለም የሚሆን የሕይወት ምንጭ ነው ብሎ እንደተናገራት ዦሮአችን ሰምቶት ስለነበረ የመስማት ፍጻሜው ማየት ነውና ለዘለዓለም የማይደርቅ የሕይወት ምንጭ በደብረ ብርሃን ሲአፈሱልን አየን ፤
ዕድሜ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ፥
ኢትዮጵያ በነፃነቷ ለዘላለም ትኑር።
ከዚህ በኋላ ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ይህን ከዚህ በታች ያለውን ብዙ ፍሬ ነገር ያለበትን ቃል ለመናገር በጀመሩ ጊዜ ሁሉም ዕዝነ ልብናውን ወደፍሬ ነገሩ መለሰ።
የግርማዊነታቸው ንግግር።
የደብረ ብርሃንን ከተማ ታሪክ በዚህ ከተሰበሰበው ሕዝብ ሕፃናቱ በመስማት ፤ ታላላቁም ታሪክ በመመልከት የማያውቀው የለም።
በዛሬ ቀን ታሪካዊ የሆነውን የደብረ ብርሃንን ውኃ ለመክፈት በመምጣታችን ደስ ሲለን ባንድ ወገን ደግሞ ስንመለከተው ደስታችን ግማሽ ነው።
ደስታችን ግማሽ ነው ያልንበትም ምክንያት ፤ ምንጩም ብረቱም ፤ ድንጋዩም ፤ ይኸንኑም የመሳሰለው ሁሉ ከአገራችን ሲገኝ ፤ የተሠራው በሰው አገር ሰው እጅ ስለሆነ ነው። ነገር ግን በመዳለል ብቻ ከመኖር ሠርቶ ማሳየት ፍሬ ያለው ስለሆነ ፥ እንደዚሁም ሕፃናቱም እየተማሩ አገራቸውን እንዲረዱ ልጆቻችሁን የአገራችንን ትምህርት ከተማሩ በኋላ የውጭ አገር ትምህርት ለመቀበል የታረሰ መሬት እንደመዝራት ያህል ፥ የለሰለሰ ምድር ዘር እንደሚቀበል ይሆንላቸዋል።
ሰው ማግኘቱ ሕይወቱን እንዲረዳበት ነው። መቅበር ፣ ማስቀመጥ ለሕይወት የማይረዳ ሲሆን መድከምና ማግኘት ከንቱ ነው። ጌታችንም በወንጌል እንደተናገረው ፤ ወርቁን እንደ ደፈነ እንደ ገብር ሐካይ ነው ፤ ይህም አሁን ከፍተን የምንሰጣችሁ ውኃ ለመጠጥ ከመሆኑ በላይ ልብሳችሁን እያጠባችሁ ንጽሕና ስታገኙ በየደጃፋችሁም ለዕለት አትክልት እንድትተክሉበት እንድትችሉ ነው። በእጣቢው እንኳ የዕለት አትክልት ለመትከል ስለሚቻል ባንድ በኩል ይህ በመሆኑ ደስታችን ሙሉ ነው ለማለት ይቻላል። ለውኃው ሥራ እርዳታ ማድረጋችሁን ሰምተናል። ዝርዝሩንም ደጃዝማች መንገሻ እንዲያቀርብልን ነግረነዋል።
ይኸው ዛሬ የነበረባችሁን የወኃ ችግር ለማስወገድ ወኃውን ከፍተንላችኋል ብለው ግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ይህን ቃል ተናግረው ሲጨርሱ ጭብጨባው አስተጋባ።
ከዚህ በኋላ ፥ ያን ሲናፈቅ የኖረውን ውኃ መዘውሩን ከፍተው ባጎረፉለት ጊዜ ፤ ሕዝቡ ከደስታው የተነሣ እስራኤል በበረሃ ሳሉ እግዚአብሔር ውኃ ከጭንጫ ያፈልቅላቸው የነበረውን ያህል ፤ ተአምራት ነው እያለ ያደንቅ ጀመር።
ለሰሚ ቀላል ይመስላል።
የደብረ ብርሃን ሕዝብ የነበረበት የወኃ ችግር በጣም ብዙ እንደነበረ የታወቀ ነው። አሁንሳ ውኃ በመዘውር ከደጁ ድረስ ሒዶ እንደልቡ ሲረካ የተሰማው ደስታ ምን ያህል ይበዛ።?
ከዚህ በኋላ ወደ ቤተ መንግሥቱ ተመለሱና በ፯ ሰዓት በከተማው ለሚገኙት ሰዎችና ለጦር አለቆች ፥ ለሕዝቡም ሁሉ ግብር አደረጉለት።
ከግብር በኋላ ፤ በ፱ ሰዓት ተኵል ከቢሮ ተቀምጠው የተቸገረውን ሕዝባቸውን ጉዳይ እየሰሙ መሬት ለለመነ መሬት ፤ ገንዘብ ለለመነ ገንዘብ ሲቸሩና ሲናኙ ቆዩ። ከዚህ በኋላ ፤ በ፲ ሰዓት ተኵል ሆስፒታሉንና ስመ ጥሩውን በቀድሞ ጊዜ ገባያ የነበረውን ቡሎ ወርቄን ጎብኝተው ተመለሱ።
ግንቦት ፲፮ ቀን ከጧቱ ወደ ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሒደው ጸሎት አድርሰው ተመልሰው ከ፪ ሰዓት ተሩብ ሲሆን ካንድ ሺ ለሚበልጡ ለኢትዮጵያ አርሚ የጦር ሠራዊትና ለፖሊሶች ፥ ለሹማምንቶችና ለታላላቅ ሠራተኞች ሙሉ ግብር አድርገው ሲያበሉ ቆይተው በ፭ ሰዓት ተሩብ ወደመናገሻ ከተማቸው ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ።
በመንገዳቸውም ግራና ቀኝ ለገበሬዎችና ለሕፃናት ፥ ለሽማግሌዎች የገንዘብ ችሮታ እያዘነሙ ደስ በሚያሰኝ አኳኋን ከቤተ መንግሥታቸው ገቡ።
ሐተታ።
ግርማዊነታቸው ለደብረ ብርሃን ሕዝብ ማየ ሕይወት ባፈለቀበት ቀን ያፈለቀው ቃለ ሕይወት ብዙ የማይረሳ ፍሬ አለበት።
ከብዙውም ጥቂቱ እንደሚከተለው ነው።
"በመዳለል ብቻ ከመኖር ሠርቶ ማሳየት ፍሬ ያለው ስለሆነ ፤ ሕፃናቱ እየተማሩ አገራቸውን እንዲረዱ ልጆቻቸሁን የአገራችንን ትምህርት ማስተማር አትንፈጓቸው ፤ የአገራቸውን ትምህርት ከተማሩ በኋላ የውጭ አገር ትምህርት ለመቀበል የታረሰ መሬት እንደ መዝራት ያህል ፤ የለሰለሰ ምድር ዘር እንደሚቀበል ይሆንላቸዋል" ብለው የተናገሩት ከዚህ ቀደም ከ፱ ዓመት በፊት እንዲሁ ለተማሪዎች ምክር ሲሰጡ "ያገርን ትምህርት ሳይማሩ የውጭ አገር ትምህርት እማራለሁ ማለት በድቡሽት ላይ የቤትን መሠረት መጣል ነው" ብለው ከተናገሩት ጋራ አንድ ነው። ይህንም ደኅና አድርጎ መስማትና የፍሬውን ፍጻሜ ለማግኘት መጣር እጅግ መታደል ነው።
ግንቦት ፳፫ ቀን ፲፱፻፴፮ ዓ.ም.
🟩🟨🟥
🌼 🌸 🌻 🌹
🟢🟡🔴
🥰💚💛💕 ሞዓ አንበሳ 🦁 💚💛💕
አሸናፊው የይሁዳ አንበሳ 🦁
💞💞💞👑👑👑🙏🙏🙏 👑 💚💛❤️ 👑
════༺❀༻༺❀༻════╗
💚💛❤️ ✍ ዕዝራ ሱቱኤል
የጥናትና ምርምር ማዕከል።
╚════༺❀༻༺❀༻════╝

Address

Addis Ababa
WWW.MULTIETHNICSHOA.COM

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሸዋ Hub posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share