ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

  • Home
  • ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ Ethio world አለምአቀፋዊ እና የሀገር ውስጥ ትኩስ መረጃ

ተመድ ጥልቅ ማሻሻያ ያስፈልገዋል - ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶሃን******************የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግዳጁን በትክክል ለመወጣት ጥልቅ ማሻሻያ ያስፈልገዋል ሲሉ የቱርኪዬ ፕ...
12/08/2025

ተመድ ጥልቅ ማሻሻያ ያስፈልገዋል - ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶሃን
******************

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግዳጁን በትክክል ለመወጣት ጥልቅ ማሻሻያ ያስፈልገዋል ሲሉ የቱርኪዬ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ተናገሩ፡፡

ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን የተመድ 80ኛ አመት የምስረታ በዓል አስመልክቶ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልእክት፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተጣለበትን አደራ መወጣት እንዲችል ከፍተኛ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው ግልፅ ነው ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ኤርዶሃን፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አለም አቀፋዊ ፍትህን የሚወክል መድረክ እንዲሆን ለማድረግ የጋራ ሀላፊነት አለብን ሲሉም ተናግረዋል።

ከ80 ዓመታት በፊት ለዚህ ድርጅት መሠረት የጣሉት መስራቾች ባሳዩት ቁርጠኝነት የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን በማጠናከር ዓለም አቀፋዊ ሰላም፣ ብልጽግና፣ የጋራ መተማመን እና መተሳሰብ ዳግም እንዲሰፍን እና ወደ ፊትም እንዲቀጥል ለማድረግ እርምጃዎች መወሰድ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የበለጠ ውጤታማ፣ ቀልጣፋ እና በፋይናንስ አቅሙ ጠንካራ እንዲሆን በሚደረገው ጥረት ሀገራቸው በንቃት ለመሳተፍ ቁርጠኛ መሆኗንም ጠቅሰዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን እንደ ሰው ልጆች ተስፋ የሚመለከቱ አባል ሀገራት አፋጣኝ እርምጃዎችን እንዲወስዱ አሳስባለሁ ማለታቸውን አናዶሉ ዘግቧል።

በፈረንጆቹ 2025 የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት እያከበረ ያለው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ታሪካዊ የሚሆነውን 80ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በመጪው መስከረም የሚያደርግ ይሆናል፡፡


ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

🇺🇦🇷🇺🇺🇸 Ukrainian President Volodymyr Zelensky is warning that Russia will attempt to deceive the United States during up...
12/08/2025

🇺🇦🇷🇺🇺🇸 Ukrainian President Volodymyr Zelensky is warning that Russia will attempt to deceive the United States during upcoming talks between US President Donald Trump and Russian President Vladimir Putin. The meeting is scheduled to take place in Alaska on August 15, 2025. Zelensky expressed his concerns, stating that Ukraine understands Russia's intentions to manipulate America and vowed that his country will not allow this to happen. Zelensky's warning comes as part of Ukraine's efforts to ensure that the US is aware of Russia's true intentions regarding the ongoing war. He emphasized that Russia's desire for war and manipulation is the root cause of the killings in the conflict, and Ukrainians have endured over three years of full-scale war. The Trump-Putin meeting is set to take place in Alaska on August 15, 2025. Zelensky fears Russia will try to convince the US that Ukraine is the obstacle to peace. Zelensky assured that Ukrainians will defend their state and independence, and appreciate the help they receive. Trump has expressed that he thinks the meeting with Putin could be both good and bad. 🇺🇦🇷🇺🇺🇸













ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ኢራን የእስራኤልን የፖለቲካና የደህንነት ከፍተኛ አመራሮችን ኢላማ ያደረገ የግድያ ዝርዝር ይፋ ማድረጓን አስታውቃለች። ይህንንም ተከትሎ የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር ካትዝ "የኢራኑ መሪ አ...
11/08/2025

ኢራን የእስራኤልን የፖለቲካና የደህንነት ከፍተኛ አመራሮችን ኢላማ ያደረገ የግድያ ዝርዝር ይፋ ማድረጓን አስታውቃለች። ይህንንም ተከትሎ የእስራኤሉ የመከላከያ ሚኒስትር ካትዝ "የኢራኑ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሚኒ ከበንከር ሲወጡ ሰማዩን እንዲመለከቱና ማንኛውንም ድምፅ በትኩረት እንዲያዳምጡ እመክራለሁ" ሲሉ ጠንካራ የማስጠንቀቂያ ምላሽ ሰጥተዋል።

የሁለቱ ሀገራት የረጅም ጊዜ ጥላቻ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በይፋዊ ዛቻና የማስፈራሪያ መግለጫዎች የታጀበ አዲስ ምዕራፍ ላይ የደረሰ ይመስላል። የኢራን መንግስት ይፋ ያደረገው ዝርዝር፣ በእስራኤል የፖለቲካ ውሳኔ ሰጪነትና የደህንነት ተቋማት ውስጥ ያሉ ቁልፍ ሰዎችን ለማጥቃት ያለመ መሆኑን ያመላክታል። ይህ ድርጊት በእስራኤል በኩል ከፍተኛ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ ምላሽም ሀገራቸው ለማንኛውም ጥቃት ከመከላከል ወደ ማጥቃት ልትሸጋገር እንደምትችል የሚያመላክት ሆኗል።

የመከላከያ ሚኒስትር ካትዝ ያስተላለፉት መልዕክት ቀጥተኛና ግልጽ ሲሆን፣ የኢራንን ከፍተኛ መሪ በግል በመጥቀስ የተሰነዘረው ዛቻ የእስራኤልን የአጸፋ እርምጃ ምን ያህል ከባድ ሊሆን እንደሚችል የሚያሳይ ነው። "ረጅሙ ክንዳችን ቴህራን ሊደርስ ይችላል" ሲሉ በተለያዩ ጊዜያት ሲናገሩ የነበሩት የእስራኤል ባለስልጣናት፣ አሁንም ተመሳሳይ ዝግጁነት ላይ መሆናቸውን በድጋሚ አረጋግጠዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ውጥረት በንግግር ብቻ የተወሰነ አይደለም። ከጥቂት ቀናት ወዲህ በተለያዩ ሳይበራዊ ጥቃቶች እና የስለላ ሙከራዎች ጭምር የታጀበ ሲሆን፣ ሁለቱም ወገኖች በተለያዩ ግንባሮች እርስ በእርስ ሲሞካከሩ ቆይተዋል። በተለይም ኢራን በሊባኖስ፣ በሶሪያ እና በሌሎች የአካባቢው ሀገራት በሚገኙ ተላላኪዎቿ በኩል በእስራኤል ላይ ስጋት እንደምትፈጥር እስራኤል በተደጋጋሚ ትከሳለች።

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሁለቱን ሀገራት ፍጥጫ በስጋት እየተመለከተው ሲሆን፣ ሁኔታው ተባብሶ ወደ ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭት እንዳያመራ ስጋቱን ገልጿል። ይሁን እንጂ፣ የኢራን የቅርብ ጊዜ ዛቻ እና የእስራኤል ጠንካራ ምላሽ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው የደህንነት ሁኔታ ምን ያህል ስስና አደገኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በድጋሚ አመላካች ሆኗል።




ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

👉‎ኢራን በአዘርባይጃን እና በአርሜኒያ መካከል በተደረገው የሰላም ስምምነት ተከትሎ በካውካሰስ ሊዘረጋ የታቀደውን የትራንስፖርት ኮሪደር እንደምትዘጋና ድርጊቱም ኢራንን አቅም ለማሳጣት የአርሜ...
10/08/2025

👉‎ኢራን በአዘርባይጃን እና በአርሜኒያ መካከል በተደረገው የሰላም ስምምነት ተከትሎ በካውካሰስ ሊዘረጋ የታቀደውን የትራንስፖርት ኮሪደር እንደምትዘጋና ድርጊቱም ኢራንን አቅም ለማሳጣት የአርሜኒያን የግዛት አንድነት ለመናድ ያለመ ከጀርባዬ የተሰራ "የፖለቲካ ክህደት"ስትል ገልፃዋለች ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።

👉‎የኢራን ከፍተኛ መሪ ከፍተኛ አማካሪ አሊ አክባር ቬላያቲ ቅዳሜ ስምምነቱ ውስጥ የተካተተውን የትራንስፖርት ኮሪደር በመጥቀስ እንደተናገሩት ቴህራን ኮሪደሩን “ከሩሲያ ጋርም ሆነ ” ከአርሜኒያ ጋር ያላትን አጋርነት ለማበላሸት የምትገናኝበትን ስትራቴጂካዊ ኮሪደር እንደሚያደናቅፍ የታለመ መሆኑን ተናግረዋል ።

‎አርብ እለት በዋይት ሀውስ በተካሄደው የፊርማ ስነ ስርዓት ላይ ይፋ የሆነው የስምምነቱ ውል፣ በአርሜኒያ በኩል አዘርባጃንን ከናክቺቫን ጋር የሚያገናኘው መስመር ላይ የአሜሪካ ልማት መብቶችን ያጠቃልላል።

👉‎የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ካውካሰስ ለ99 ዓመታት ለአሜሪካ ሊከራይ የሚችለው ብለው ያስባሉ” ሲሉ ቬላያቲ የሰላም ስምምነቱ ከጀርባው አሜሪካ የራሷን ጥቅም ለማስከበር እና አካባቢው ላይ እግሮቿን ለመትከል ያደረገችው መሆኑን ገልፀዋል ።

‎"ይህ በሰላም ስምምነት ስም የታቀደው እቅድ አይሳካም ለትራምፕ ቅጥረኞች መግቢያ አይሆንም መቃብራቸው ይሆናል" ሲሉ የገለፁት አክባር ‎አክለውም በሃይል መቆጣጠር ያቃታት ዩናይትድ ስቴትስ በቀጠናው በሰላም ስም ለመዉረር እየሸረበች ያለውን ሴራ በዛዋ እንደማያዩት አስጠንቅቋል ።

‎ቬላያቲ ኮሪደሩ ኔቶ እራሱን በኢራን እና በሩሲያ መካከል "እንደ እፉኝት" እንዲያቆም መንገድ ይከፍታል ሲል ተከራክሯል።

👉‎የትራምፕ መንገድ ለአለም አቀፍ ሰላም እና ብልጽግና (TRIPP) የሚል ስያሜ የተሰጠው ኮሪደሩ በአርሜኒያ ህግ የሚሰራ እና ወደ ኢራን ድንበር ተጠግቶ የሚያልፍ ሲሆን ይህም የቴህራንን ስጋት አሳድሯል።

👉‎የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድንበሯ አቅራቢያ "የትኛውም የውጭ ጣልቃ ገብነት አሉታዊ መዘዞች" ስጋት እንዳደረበት ገልጿል። ሚኒስቴሩ የሰላም ስምምነቱን ሲቀበል፣ በኢራን ድንበሮች አቅራቢያ ያሉ ፕሮጀክቶች “ብሔራዊ ሉዓላዊነትን እና የግዛት አንድነትን ማክበር አለባቸው፣ እና ያለ የውጭ ጣልቃ ገብነት” ሲል አፅንዖት ሰጥቷል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ ቱርክ የታቀደው የመተላለፊያ ኮሪደር በደቡብ ካውካሰስ በኩል ወደ ውጭ የሚላኩ የኃይል እና ሌሎች ሀብቶችን እንደሚያሳድግ ተስፋ ገልጻለች። አንካራ አዘርባጃንን ከአርሜኒያ ጋር ባላት ግጭት ጠንከር ያለ ድጋፍ ሰጥታለች ነገርግን የመጨረሻውን የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ከየርቫን ጋር ያለውን ግንኙነት ለመመለስ ቃል ገብታለች።

👉‎ሩሲያ በበኩሏ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ባወጣችዉ መግለጫ የዋሽንግተን ስብሰባን ጨምሮ በአካባቢው መረጋጋትን እና ብልጽግናን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ ስምምነቱን አድንቃለች ። ይሁን እንጂ ሞስኮ ከውጪ ጣልቃ ገብነትን አስጠንቅቃለች ።

‎"ከክልል ውጪ ያሉ ተጫዋቾችን ማሳተፍ የሰላም አጀንዳውን ማጠናከር እንጂ አዲስ መለያየት መፍጠር የለበትም" ያለው ሚኒስቴሩ፣ በምዕራቡ ዓለም የሚመራውን የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት አፈታት "በጥንቃቄ "እንደሚደረግ ተስፋ እንዳለው ገልጿል ።‎ለዘገባው አልጀዚራ ሞስኮ ታይምስ ዘሚዲሊስትን ተጠቅመናል ።





ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

09/08/2025

I got over 3,000 reactions on my posts last week! Thanks everyone for your support! 🎉

አዘርባጃንና አርሜኒያ የ40 ዓመታት ደም አፋሳሽ ግጭታቸውን በሰላም ስምምነት ቋጩ| አዘርባጃንና አርሜኒያ የአራት አሥርት ዓመታት ደም አፋሳሽ ግጭታቸውን በአሜሪካ አሸማጋይነት በሰላም ስምምነ...
09/08/2025

አዘርባጃንና አርሜኒያ የ40 ዓመታት ደም አፋሳሽ ግጭታቸውን በሰላም ስምምነት ቋጩ
| አዘርባጃንና አርሜኒያ የአራት አሥርት ዓመታት ደም አፋሳሽ ግጭታቸውን በአሜሪካ አሸማጋይነት በሰላም ስምምነት ቋጭተዋል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአርሜኒያ እና አዘርባጃን መሪዎች በዋይት ሀውስ አቀባበል አድርገው ለአራት አስርት ዓመታት ደም አፋሳሽ ግጭት ከተፈጠረ በኋላ በአጎራባች ደቡብ ካውካሰስ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት መደበኛ ለማድረግ የተነደፈውን የሰላም ማዕቀፍ ተፈራርመዋል ሲል ዘ ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዓርብ ማታ በዋይት ሀውስ በተፈራረሙት ስምምነቶች መሰረት አዘርባጃን እና አርሜኒያ ለዘለቄታው የተኩስ ማቆም እና የሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት መከበር ቁርጠኝነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

ትራምፕ ከአዘርባጃን ፕሬዝዳንት አሊዬቭ እና ከአርሜኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሺንያን ጋር በዋይት ሀውስ የሶስትዮሽ ስነ ስርዓት ላይ ለዚህ ስምምነት ምስጋና ይግባውና በመጨረሻም ሰላም አግኝተናል ብለዋል።

ትራምፕ አክለውም "አርሜኒያ እና አዘርባጃን ሁሉንም ግጭቶች በዘላቂነት ለማቆም፣ የንግድ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን ለመመስረት እና አንዳቸው የሌላውን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ለማክበር ቁርጠኛ ናቸው ብለዋል።

የአዘርባይጃን ፕሬዝዳንት አሊዬቭ በበኩላቸው በአርሜኒያ ያላቸውን እምነት እና አዘርባጃን ለማስታረቅ ድፍረት እና ኃላፊነት ለማሳየት ፈቃደኛ መሆኗን ገልፀዋል። ይህም የግጭት ምዕራፉን እንዲዘጉ እና በደቡብ ካውካሰስ ሰላም እንዲሰፍን ያስችላል ብለዋል።

የአዘርባጃኑ ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ሁለቱ ሀገራቶች ለአስርት ዓመታት የዘለቀውን ግጭት ለማስቆም የሚያስችል ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኖቤል የሰላም ሽልማት እንዲሰጣቸው እንሰራለን ብለዋል።

አሊዬቭ በዋይት ሀውስ በተካሄደው የመሪዎች ጉባዔ ላይ “ከጠቅላይ ሚኒስትር ኒኮል ፓሺንያን ጋር ለኖቤል ኮሚቴ ለፕሬዚዳንት ትራምፕ የኖቤል የሰላም ሽልማት እንዲሰጥ በጋራ ይግባኝ ለማለት እስማማለሁ” ብለዋል።

የአርሜኒያውም ጠቅላይ ሚኒስትር ፓሺንያን፣ ትራምፕ የኖቤል የሰላም ሽልማት ይገባቸዋል ብዬ አምናለሁ ብለዋል ሲል አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።

ዩክሬን መሬቷን አሳልፋ አትሰጥም !ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪየዩክሬይን ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ ፕረዚደንት ትራምፕ በመጨው አርብ ከሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ሊያካሄዱት ያቀዱ...
09/08/2025

ዩክሬን መሬቷን አሳልፋ አትሰጥም !ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ

የዩክሬይን ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ ፕረዚደንት ትራምፕ በመጨው አርብ ከሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ሊያካሄዱት ያቀዱት ንግግር «የዩክሬንን ሉአላዊ ግዛት የሚቆርስ ነው» ሲሉ ተቃዎሞአቸውን አሰሙ። ሁለቱም ፕረዚደንቶች የዩክሬይንን ግዛት በሩስያ ሥር እንዲቆይ የሚል ስምምነት ካደረጉ «ተግባራዊ ሊሆን የማይችል ነውም ብለዋል።

ፕረዚደንቱ በተንቀሳቃሽ ምስል ተቀርጾ ባሰራጩት መልዕክታቸው «ዩክሬይን መሬቷን ለወራሪዎች አሳልፋ አትሰጥም» ሲሉ ተደምጠዋል። «ለግዛታዊ አንድነታችን የሚሆን ምላሽ በሕገ-መንግስታችን አለ» ያሉት ዘለንስኪ ከዚህ የሚያፈነግጥ የለም ሲሉ አክለዋል። በዩክሬይን ሰላምን ለማምጣት በሚደረጉ ውይይቶች ለመካፈል ዝግጁ ነን ያሉት ፕረዚደንት ዘለንስኪ ዩክሬይን ያገለለ ንግግር «ጸረ ሰላም ነው» ሲሉ ተቃውመዋል።

የፑቲንና የትራምፕ ንግግር በሩስያ የተያዙ የዩክሬይን ግዛቶችን በሩስያ ሥር እንዲቆዩ የሚያደርግ መሆኑን የገለጹት ዘለንስኪ ይህ ደግሞ «ተግባራዊ ሊሆን የማችል » ብለውታል።
የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲንና የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የፊታችን አርብ በአላስካ ለመገናኘት ቀጠሮ መያዛቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
DW





ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

"ለሱማሌላንድ እዉቅና ለመስጠት አስበናል" ! /ትራምፕ/ ‎‎ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዩኤስ ለሶማሊላንድ የሉአላዊነት ነፃነቷን እና እውቅና ለመስጠት ፍላጎት እንዳላት መግለፃቸው ተነገረ።‎‎...
09/08/2025

"ለሱማሌላንድ እዉቅና ለመስጠት አስበናል" ! /ትራምፕ/

‎ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዩኤስ ለሶማሊላንድ የሉአላዊነት ነፃነቷን እና እውቅና ለመስጠት ፍላጎት እንዳላት መግለፃቸው ተነገረ።

‎ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያሉት ቅዳሜ እለት የረጅም ጊዜ ተቀናቃኞች ሆነው የቆዩትን በአዘርባጃን እና በአርሜኒያ መሪዎች መካከል የሰላም ስምምነት እያፈራረሙ በነበሩበት ወቅት ስለ ጉዳዩ ተጠይቀው ለጋዜጠኞች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነዉ።

‎ጋዜጠኞች ክቡር ፕሬዘዳንት ለረጂም አመታት የሀገርነት ጥያቄ እየጠየቀች የምትገኘዉ የሱማሌላንድ ጉዳይ እንዴት ያዩታል ? የሚል ጥያቄ ሲመልሱ

‎ "ጥሩ ጥያቄ ነዉ "አሁን ለሶማሊላንድ እዉቅና የምንሰጥበትን መንገድ እየተመለከትን ነው. በእውነቱ ጉዳዩ ውስብስብ ቢሆንም ነገር ግን በዛ ላይ አሁን እየሰራን ነው" በማለት ትረምፕ ምላሽ ሰጥተዋል ።

‎ይህ የትራምፕ ንግግር ለአለም አቀፍ እውቅና ለማግኘት እየሞከሩ የሚገኙት የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን መሀመድ አብዲላሂ ኢሪን ለዩኤስ ስትራቴጂካዊ የወደብ ከተማ በርበራ ወታደራዊ ሰፈር እንዲሰጥ እና ሊቲየምን ጨምሮ ጠቃሚ የማዕድን ሃብቶችን እንዲያገኙ ያቀረቡትን ሀሳብ ተከትሎ ነው።

‎ፕሬዝዳንት ኢርሮ ከብሉምበርግ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሶማሊላንድ ከሁለቱም የዩኤስ የመከላከያ ሚኒስቴር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር "ጥሩ ግንኙነት" ገንብታለች፣ ይህም በራስዋ ራሷን በምታወጀው ሪፐብሊክ እና በዋሽንግተን መካከል ያለው ግንኙነት እያደገ መሆኑን ያሳያል። ብለዋል ።

‎ኢርሮ ትራምፕን አስተዳደራቸው በቅርበት መስራት የሚችሉበት “ቢዝነስ-አስተሳሰብ” መሪ ሲሉ ገልጸው አሜሪካ ለሶማሌላንድ እውቅና በመስጠት የመጀመሪያዋ ሀገር እንደምትሆን ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።

‎እ.ኤ.አ. በ1991 ጀምሮ ሶማሊላንድ ከሶማሊያ የተነጠለች ሉአላዊነት ሀገር እንደሆነች ብትናገርም በየትኛውም ሀገር እውቅና ሳታገኝ ቆይታለች ።

‎ከጥቂት ወራት በፊት በሶማሊያ የአሜሪካ አምባሳደር ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቱ በዋሽንግተን እና በሞቃዲሾ መካከል ያለውን ግንኙነት ሊያሻክር እንደሚችል በማስጠንቀቅ ዩኤስ በጉዳዩ ላይ የሚያደርጉትን ውይይት እንድታቆም ማሳሰቡ ይታወሳል ።
‎በዚህ መልክ የቆየዉ የሱማሌላንድ ጉዳይ ዳግም ወደ መድረኩ ተመልሶ የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እዉቅና የመስጠት ሃሳብ እንዳላቸው መናገራቸውን ምናልባት ሀገር የመሆኗ ጉዳይ አይቀሬ መሆኑ ማሳያ ተደርጓል ።

‎ምክንያቱም በስልጣን ላይ ያሉ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ስለ ሶማሌላንድ "እዉቅና መስጠት "ጉዳይ በይፋ ለመገናኛ ብዙሃን ሲናገሩ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ። ተብሏል ።

‎ለዘገባው ታይም ኦፍ እስራኤል TRT GLOBAL አልጀዚራን ተጠቅመናል ።




ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ለቀጣዩ አርብ ቀጠሮ የተያዘለተ የፑቲን እና ትራምፕ ውይይት በአላስካ ይደረጋል የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የፊታችን አርብ በአላስካ ተገናኝ...
09/08/2025

ለቀጣዩ አርብ ቀጠሮ የተያዘለተ የፑቲን እና ትራምፕ ውይይት በአላስካ ይደረጋል

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የፊታችን አርብ በአላስካ ተገናኝተው ስለ ዩክሬን ጦርነት እንደሚወያዩ ተገለጸ።

ነሐሴ 9/2017 ዓ. ም. መሪዎቹ እንደሚገናኙ ትራምፕ በማኅበራዊ ሚዲያቸው ገልጸዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይም ማረጋገጫ ሰጥተዋል።

አላስካ ለሩሲያ ቅርብ ስለሆነች ምቹ ቦታ እንደሆነም ተገልጿል። በዩክሬን በኩል እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

ዩክሬን ጦርነቱን ለመግታት ግዛቶች መስጠት ይኖርባታል የሚል ሐሳብ ከትራምፕ ከተደመጠ በኋላ ነው ስለ ውይይቱ የተሰማው።

"በሦስት ዓመት ተኩል ውስጥ ለዚህ ግዛት ብዙ ሩሲያውያንና ዩክሬናውያን ሞተዋል።

ውስብስብ ጉዳይ ነው። የተወሰኑትን እናስመልሳለን። የምንለዋወጣቸው ግዛቶችም ይኖራሉ። ለሁለቱም ወገን የሚበጀው ይሄ ነው" ብለዋል ትራምፕ።





ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ግብፅና እስራኤል በታሪካቸው ትልቁን ስምምነት ተፈራረሙ !!‎‎የመካከለኛው ምስራቅ ሀገሯ እስራኤል እና የአረብ ሊግ መሪዋና አፍሪካዊቷ ሀገር ግብፅ በታሪካችን ትልቅ የተባለው የተፈጥሮ ጋዝ ሽ...
08/08/2025

ግብፅና እስራኤል በታሪካቸው ትልቁን ስምምነት ተፈራረሙ !!

‎የመካከለኛው ምስራቅ ሀገሯ እስራኤል እና የአረብ ሊግ መሪዋና አፍሪካዊቷ ሀገር ግብፅ በታሪካችን ትልቅ የተባለው የተፈጥሮ ጋዝ ሽያጭ ስምምነት መፈራረማቸው ተሰምቷል ።

‎የእስራኤል ሌዋታን የተፈጥሮ ጋዝ ማዉጫ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ ትልቁን የኤክስፖርት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፥ እስከ 2040 ድረስ 35 ቢሊየን ዶላር የሚደርስ ዋጋ የሚያወጣ ጋዝ ለግብፅ ለማቅረብ ተስማምቷል። ይህ አዲስ ስምምነትም በግብፅ ያለውን የሃይል ቀውስ ያቃልላል ተብሏል ።

‎ ግብፅ እ.ኤ.አ. በ 2022 ጀምሮ በከርሰ ምድሯ የሚገኘዉ የተፈጥሮ ጋዝ ማሽቆልቆሉን ተከትሎ ጉድለቶቿን ለማካካስ ወደ እስራኤል ፊቷን ማዞሯ ይታወቃል ።

‎ይህን ተከትሎም አዳዲስ ስምምነቶችን እያደረገች ሲሆን ሐሙስ በተገለጸው ውል መሠረት፣ በ ሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ፣ 600 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ክምችት ያለው ሌዋታን ጋዝ ማዉጫ ተቋም እስከ 2040 ድረስ 130 ቢ.ሲ.ሜ ጋዝ ለግብፅ ለማቅረብ ታቅዷል ።

‎በሀሙሱ ውል መሰረት እ.ኤ.አ. በ2020 ጀምሮ የሀገሪቱን ፍላጎት እያሟላ የሚገኘዉ የሌዋታን ማጠራቀሚያ ለግብፅን እያቀረበበት በሚገኘው በሁለቱ ሀገራት በቧንቧ መስመር በኩል 2026 መጀመሪያ ጀምሮ እስራኤል የመጀመሪያውን ደረጃ 20 ቢ.ሲ.ሜ ጋዝ ለግብፅ የሚያደርስ ሲሆን በሁለተኛው ምዕራፍ አዳዲስ መስመሮችን በመዘርጋት በእጥፍ ያቀርባል ።

‎በአሁኑ ስምምነት መሰረትም በሚቀጥለው አመት መጀመሪያ ላይ ከእስራኤል ወደ ግብፅ የሚደረገውን የጋዝ አቅርቦት ፍሰቱን ከ4.5 ቢ.ሴ.ሜ ወደ 6.5 ቢ.ሴ. ያድጋል ። ይህ ደግሞ የጋዝ ምርቷን ለማሳደግ አቅርቦት ለማግኘት ስትታገል ለቆየችው ግብፅ ከነበረዉ በእጥፍ 40% በማደግ የአቅርቦት እጥረት እንዳይገጥማት እፎይታ ያስገኛል ተብሏል ።

‎የኒውሜድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዮሲ አቡ ሐሙስ ዕለት ለሮይተርስ በሰጡት ቃለ ምልልስ “ከሌሎች LNG አማራጮች በተሻለ ይህ ከእስራኤል ጋር ያደረግነው ስምምነት እጅግ በጣም ጥሩ ነው ፣ እናም በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ዶላሮችን ለግብፅ ኢኮኖሚ ያድናል” ብለዋል ።

‎የእስራኤል ጋዝ አቅርቦት ከ15-20% የሚሆነውን የግብፅ ፍጆታ ይይዛል የሚለዉ ኢኒሼቲቭ የተገኘው ከጋራ ድርጅቶች መረጃ የሚያሳይ ሲሆን ወደ 2.4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋው የሌቪያታን ማስፋፊያ እየገነባች የምትገኘው እስራኤል ለዮርዳኖስና ከግብፅ በተጨማሪ ለጎረቤቶቿ ምርትና አቅርቦቶችን መፍቀድ አለበት ሲል ተንታኙ ኒውሜድ ለሮይተርስ ተናግሯል።





ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

‎የፍልስጤም ጠባቂ እንደሆነ የሚናገረው ሃማስ ‎አርብ ዕለት የእስራኤል የጸጥታ ካቢኔ ጋዛ ከተማን ለመያዝ ያስተላለፈውን ውሳኔ ፍልስጤማውያን ላይ “የጦርነት ወንጀል እና የዘር ማፅዳት ተግባር...
08/08/2025

‎የፍልስጤም ጠባቂ እንደሆነ የሚናገረው ሃማስ
‎አርብ ዕለት የእስራኤል የጸጥታ ካቢኔ ጋዛ ከተማን ለመያዝ ያስተላለፈውን ውሳኔ ፍልስጤማውያን ላይ “የጦርነት ወንጀል እና የዘር ማፅዳት ተግባር” ሲል ማዉገዙ ተነገረ ።

‎የአለማችንን የፖለቲካ እሳተ ገሞራ እንደሆነ የሚነገርለት የምድሪቱ የነዳጅ ጥም የሚቆርጠዉ ፖለቲካዊ ስሱነት ያለበት የቀላሉ ግጭት የሚነሳበትና ከልዕልለ ሀያላኑ እስከ ገለልተኞቹ በኢኮኖሚ አቅማቸው ከፈረጠሙት ለማደግ እስከሚዉተረተሩት ድረስ አይንና ጀሮአቸዉን ሰጥተዉ ዉሎ አዳሩን የሚከታተሉት መካከለኛው ምስራቅ አንዱ ተዋናይ የሆነው ሃማስ የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና መንግስታቸዉን በጋዛ ላሉ የእስራኤል ታጋቾች ምንም አይነት ስጋት የሌለዉና እርህራሄ ያላሳዩ ሲሉ ከሰሷቸዋል።

‎ቡድኑ ባወጣው መግለጫ የእስራኤል ወረራ "የሽርሽር አይሆንም" እና በጋዛ ላሰበችዉ ወታደራዊ ጀብዱ ላይ "ከባድ ዋጋ እንደምትከፍል "ማወቅ አለባት ሲል አስጠንቅቋል ።

‎ቡድኑ በከተማዋና ወደ 1 ሚሊዮን በሚጠጉ ፍልስጤማውያን ላይ ለምታደርገው ወንጀል ህጋዊ ተጠያቂነትን ለማስወገድ “ወረራ” የሚለውን ቃል በ “ቁጥጥር” ስር ስትል ግልጽ ያልሆነ ስም ሰጥታዋለች ለመተካት ያደረገውን አለምን "የማጭበርበር " ሙከራ ውድቅ አድርጎታል።

‎የእስራኤል የደኅንነት ካቢኔ ሆን ብሎ የጋዛን ሰርጥ በመጥቀስ “ወረራ” የሚለውን ቃል ከመጠቀም ተቆጥቧል ዛሬ ባፀደቀው ዉሳኔ በምትኩ “ቁጥጥር” የሚል ቃል በመጠቀም በፍልስጤም ሲቪሎች ለሚደርሰው ጉዳት ከዓለም አቀፍ የሕግ ተጠያቂነት ለማምለጥ ያለመ ማወናበድ ፈፅሟል ብለዋል ሲል የዘገበዉ ዘ ሚዲሊስት የዜና ወኪል ነዉ ።



ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ዋይት ሐውስ ትራምፕ ከሩሲያው እና ከዩክሬኑ መሪ ጋር ለመነጋገር "ዝግጁ" ናቸው አለዶናልድ ትራምፕ መልዕክተኛቸው ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር "በጣም መልካም የሆነ ውይይት" ሲሉ የገለፁ...
07/08/2025

ዋይት ሐውስ ትራምፕ ከሩሲያው እና ከዩክሬኑ መሪ ጋር ለመነጋገር "ዝግጁ" ናቸው አለ

ዶናልድ ትራምፕ መልዕክተኛቸው ከፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር "በጣም መልካም የሆነ ውይይት" ሲሉ የገለፁትን ውይይት ካደረጉ በኋላ ከሩሲያ እና ከዩክሬን መሪዎች ጋር ለመገናኘት "መልካም ዕድል" እንዳለ ተናገሩ።

በዋይት ሐውስ ሁለቱ መሪዎች ለእንዲህ ዓይነቱ የመሪዎች ጉባዔ ተስማምተው እንደሆን የተጠየቁት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት "በጣም ጥሩ ተስፋ አለ" ሲሉ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ክሬምሊን ቀደም ሲል በፑቲን እና በስቲቭ ዊትኮፍ መካከል ስለተካሄደው ውይይት ግልጽ ያልሆነ መግለጫ ያወጣ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ረዳት ኃላፊው ሁለቱ ወገኖች በሞስኮ "ገንቢ" የሆነው ውይይት ማካሄዳቸውን እና "መልዕክቶችን" መለዋወጣቸውን ተናግረዋል።

የትራምፕ መልዕክተኛ ፕሬዚዳንት ፑቲንን አግኝተው ያናገሩት፣ ሩሲያ በዩክሬን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማድረግ የተቀመጠላት ቀነ ገደብ ከማለቁ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ሲሆን ካልሆነ አዲስ ማዕቀብ ይጠብቃታል።

ትራምፕ ረቡዕ ዕለት በኦቫል ኦፊስ አስተያየት የሰጡት በትሩዝ ሶሻል ገጻቸው ላይ ለአንዳንድ የአውሮፓ አጋሮቻቸው ውይይቱን በሚመለከት ማብራሪያ መስጠታቸውን የሚገልጽ ጽሑፍ ከለጠፉ በኋላ ነው።







ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

Address

Addis Abeba

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share