ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ Ethio world አለምአቀፋዊ እና የሀገር ውስጥ ትኩስ መረጃ

👉ሩሲያ በዩክሬን ላይ አዳሩን ''ግዙፉን የአየር ጥቃት'' አደረሰች።በጥቃቱ መላ ዩክሬን ዒላማ ውስጥ የገባ ሲሆን ከ810 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮንስ)  ፣አራት ባሊስቲክ እና ዘጠ...
07/09/2025

👉ሩሲያ በዩክሬን ላይ አዳሩን ''ግዙፉን የአየር ጥቃት'' አደረሰች።

በጥቃቱ መላ ዩክሬን ዒላማ ውስጥ የገባ ሲሆን ከ810 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮንስ) ፣አራት ባሊስቲክ እና ዘጠኝ ክሩዝ ሚሳዔሎች በዩክሬን ሰማይ ላይ ሲያንዣብቡ አድረዋል።

ለመጀመሪያ ጊዜም በኪዬቭ መንግስት ህንጻ ተመ ቷል።

በጥቃቱ ቢያንስ ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን ሲያጡ የአደጋ መቷል ድምጽ ሰጭ ደውሎች ለ11 ሰዓታት ያህል የተጠንቀቁ ድምፅ አሰምተዋል።

ለ11 ስዓታት የዘለቀው የአየር ላይ ጥቃት ሩሲያ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ችግሩን ለመፍታት ፍላጎቱ እንደሌላት ያሳያል በሚል አስወቅሷታል።

የዩክሬን አየር ኃይል እንዳስታወቀው"54 ሰው አልባ አውሮፕላኖችና ዘጠኝ ሚሳዔሎች በመላ ዩክሬን ዒላማቸውን መተዋል "።

ሩሲያ በዩክሬን ላይ ጦር ካዘመተች በኋላ ግዙፉን የአየር ጥቃት በኪዬቭ ላይ ስትፈጽም መሆኑ ነው።

ሐምሌ ላይ ሞስኮ ግዙፍ ወይንም በጦርነቱ ላይ አድርጋው የማታውቀውን መጠነ ሰፊ የአየር ጥቃት ማድረሷ ይታወሳል።

የአዳሩ የአየር ጥቃት ደግሞ " ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ ነው" ተብሏል።

የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሜር ዘለንስኪ አስከፊው ጥቃት ነው ያሉት ሲሆን ሞስኮ ሆነ ብላ ጦርነቱን ለማራዘም የምታደርገው ነው ሲሉም ወቅሰዋል።

በዲፖሎማሲያዊ መንገድ ጦርነቱ እንደማይፈታ ጠቋሚ ነውም እየተባለ ይገኛል።

ዘገባው የ ዘ ዋሽንግተን ፖስት ነው።





ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

የባቫሪያን ግዛት ጠቅላይ ሚንስትር  የጀርመን ወታደሮች ወደ ዩክሬን መላክን ተቃወሙ።የክርስቲያን ሶሻል ዲሞክራቲክ  CSU መሪ  የሆኑት ማርከስ ሶደር - የባቫሪያን እህት ፓርቲ የባቫሪያን ግ...
06/09/2025

የባቫሪያን ግዛት ጠቅላይ ሚንስትር የጀርመን ወታደሮች ወደ ዩክሬን መላክን ተቃወሙ።

የክርስቲያን ሶሻል ዲሞክራቲክ CSU መሪ የሆኑት ማርከስ ሶደር - የባቫሪያን እህት ፓርቲ የባቫሪያን ግዛት መሪ ፤ ማርከስ ሶደር፤ ከራይኒሼ ፖስት ጋዜጣ ጋር ቃለ ምልልስ የጀርመን ወታደሮች የኪቪን የደህንነት ዋስትና ለማስከበር የኔቶ አካል ሆነው መሄዳቸው ጥያቄ የሚያስነሳ ነው ሲሉ ተቃውመዋል። የባቫሪያን ግዛት መሪ ሶደር፤ የመራሄ መንግስት ፍሪድሪሽ ሜርዝ ፓርቲ የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ህብረት (ሲዲዩ) እህት ፓርቲ የሆነው፤ የክርስቲያን ሶሻል ዲሞክራቲክ CSU መሪም ናቸው። ሶደር፤ከራይኒሼ ፖስት ጋዜጣ ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፤የጀርመኑ መራሄ መንግስት ፍሪድሪሽ ሜርዝ በፓሪስ ከተካሄደው "የፍቃደኞች ጥምረት" ስብሰባ ለዩክሬን ተጨማሪ ወታደራዊ ድጋፍ ከመስጠት እንደሚቆጠቡ ቃል ከገቡ በኋላ ነው።"የኔቶ ወታደሮች እዚያ እንደሚሰፍሩ መገመት ይከብደኛል" ያሉት ሶደር ዩክሬን ኔቶን ለመቀላቀል ቀዳሚ እርምጃ በመሆኑ "ሩሲያ ይህን በፍፁም አትቀበለውም።በማለት ለራይኒሽ ፖስት ገልፀዋል። የጀርመን ጦር ለእንደዚህ አይነቱ እርምጃ ዝግጁ መሆኑን የተጠራጠሩት የ58 አመቱ የባቫሪያን ግዛት መሪ ሶደር፤ጉዳዩ ወደ ወታደራዊ ምልመላ መመለስን ይጠይቃል ብለዋል።


ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

06/09/2025

ፔንታጎን ወደ ጦር ሚኒስቴር ፤ ከመከላከል ወደ ማጥቃት

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፔንታጎን መጠሪያው "የጦር ሚኒስቴር" እንዲሆን አዘዙ።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ መከላከያ ሚኒስቴሩን ወደ ጦር ሚኒስቴር ስሙን ሲለውጡ ምክንያታቸው አሳማኝ መሆኑን አሳውቀዋል።

በዖቫል ኦፊስ ለጋዜጠኞች ሀሳባቸውን የሰጡት ትራምፕ የፔንታጎንን የስም ለውጥ ዓለም አሁን ካለችበት ሁኔታ አንጻር ተስማሚ ነው ብለውታል።

ሪፐብሊካኑ የይፈጸም ትዕዛዝ (executive order ) የፈረሙ ሲሆን ዋሽንግተን በዓለም ፖለቲካ ላይ ለውጥ እንዳደረገችም የሚጠቁም ሆኗል።

በአሁኑ ሰዓት ዓለም ያለችበት ሁኔታ ለስያሜው ለውጥ ተስማሚ አማራጭ እንደሆነ ይፋ ያደረጉት ዶናልድ ትራምፕ በዓለም ላይ ጠንካራው ጦር ያለን እኛ ነንም ብለዋል።

ትዕዛዙ የመከላከያ ሚኒስትሩን፣ የመከላከያ ክፍሉን፣ አጋዥ ዓባላትን እንዲሁም ቢሮዎችን ሁለተኛ ማዕረጉን እንዲጠቀሙ ያደርጋል።

የጦር ሚኒስትር፣ የጦሩ ምክትል ሚኒስትር እና መሰል ማዕረጎችን በአደባባይ ፖለቲከኞች ለመጠቀም ይገደዳሉ።

ባለስልጣናቱ ወዲያውኑ ጥቅም ላይ ማዋልም ጀምረዋል።

የፔንታጎን ድረ ገጾች ሳይቀሩ ከ defense.gov ወደ war.gov ተለውጠዋል።

ከመከላከያ ሚኒስቴር (DOD ) ወደ ጦር ሚኒስቴር (DOW ) ተለውጧል።

ይህ ደግሞ ዋሽንግተን ስትራቴጂዋን ወደ ጦር እንደለወጠችው ማሳያ ነው ተብሏል።

አሜሪካ ከመከላከል ፖሊሲ ወደ ማጥቃት መግባቷን ያሳየ ነውም በሚል የጦር ሚኒስትሩ ፔት ሀገሰት አረጋግጠዋል።

ዘገባው የኤን ቢ ሲ ኒውስ እና ሲ ኤን ኤን ነው።
Donald J. Trump
ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

👉ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ መፃዒ ተስፋዋ ነው ሲሉ የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለፁ።ሕዳሴ ግድብ ከኃይል ማመንጨት በዘለለ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት ኢንጂነር ...
05/09/2025

👉ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ መፃዒ ተስፋዋ ነው ሲሉ የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ገለፁ።

ሕዳሴ ግድብ ከኃይል ማመንጨት በዘለለ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች እንዳሉት ኢንጂነር ክፍሌ ገልፀዋል።

ግድቡ በዓመት 15 ሺህ 760 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል እንደሚያመነጭ ጠቅሰው፤ በዚህም 1 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያስገኝ ነው የተናገሩት።

ከሽያጭ ከምናገኘው ገቢ በላይ ግድቡ በሀገሪቱ ልማት ላይ ከፍተኛ አዎንታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ነው ያሉት።

ለአብነትም ታዳሽ ኃይል የሚያመነጨው ፕሮጀክቱ አምራች እና አገልግሎት ሰጪ ዘርፎች እንዲነቃቁ እና እንዲዘምኑ ያደርጋል ብለዋል።

ከኃይል አቅርቦት በተጨማሪ ግድቡ ከፍተኛ የዓሳ ምርት ክምችት እንዳለው ተናግረዋል።

በውስጡ 70 ደሴቶች ያሉትና 270 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው “ንጋት” ሐይቅ ለቱሪስት ፍሰት መጨመር ብሎም ለሆቴል እና መስተንግዶ ዘርፍ መስፋፋት አስተዋፅዖ እንደሚኖረውም ነው ያመላከቱት።

ሕዳሴ ግድብ ከኢትዮጵያ አልፎ ለታችኛው የናይል ተፋሰስ ሀገራት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልፀዋል።

ውኃው በቋሚነት የሚፈስ በመሆኑ በበጋ ወቅት የውሃ እጥረት እንዳያጋጥማቸው እንዲሁም የጎርፍ አደጋ እንዳይከሰት ይከላከላል ብለዋል።

በሜሮን ንብረት

#ሕዳሴግድብ

ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ዩክሬን የፕሬዚዳንት ፑቲንን ጥሪ ውድቅ አደረገች******************ዩክሬን የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በሞስኮ ለመገናኘት ያቀረቡ...
04/09/2025

ዩክሬን የፕሬዚዳንት ፑቲንን ጥሪ ውድቅ አደረገች
******************

ዩክሬን የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር በሞስኮ ለመገናኘት ያቀረቡትን ሀሳብ ውድቅ አድርጋለች።

ዘለንስኪ የሰላም ድርድር ለማድረግ ወደ ሞስኮ መምጣት እንደሚችሉ ቭላድሚር ፑቲን በቤጂንግ ለጋዜጠኞች ገልጸው ነበር።

ስብሰባው በጥሩ ሁኔታ ከተዘጋጀ እና አዎንታዊ ውጤት ካስገኘ ብቻ እንደሚካሄድም በወቅቱ ተናግረው ነበር።

ይሁን እንጂ የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሬይ ሲቢጋ በኤክስ ገጻቸው ላይ “በሞስኮ የሚደረግ ስብሰባ ተቀባይነት የለውም” በማለት ፑቲን “ሁሉንም ሰው የሚያበሳጩ” ሀሳቦችን እያቀረቡ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።

አንድሬይ ሲቢጋ " በአሁኑ ወቅት ቢያንስ ሰባት ሀገራት ፑቲን እና ዘለንስኪን ለማገናኘት ዝግጁ ናቸው።ዘለንስኪም ለዚህ በማንኛውም ጊዜ ዝግጁ ናቸው፤ ሆኖም ግን ፑቲን ሆን ብለው ተቀባይነት የሌላቸው ሀሳቦችን ማንሳት ቀጥለዋል" ብለዋል።

"ዜሌንስኪ ለሰላም ዝግጁ ከሆኑ ወደ ሞስኮ ይምጡ"፦ ፕሬዚዳንት ፑቲን******************የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ጋር በአካል ተገናኝተ...
03/09/2025

"ዜሌንስኪ ለሰላም ዝግጁ ከሆኑ ወደ ሞስኮ ይምጡ"፦ ፕሬዚዳንት ፑቲን
******************

የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከዩክሬኑ አቻቸው ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ጋር በአካል ተገናኝተው ለመነጋገር ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ፑቲን ከዜሌንስኪ ጋር በአካል ተገናኝተው የሰላም ድርድር ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀው የዩክሬኑ አቻቸው ሞስኮን እንዲጎበኙ ጋብዘዋል።

ፕሬዚዳንት ፑቲን በቤጂንግ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፥ ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በቅርቡ በአላስካ ባደረጉት ውይይት የባላንጣዎቹ ሀገራት መሪዎች በአካል ተገናኝተው መወያየት እንዳለባቸው መግባባት ላይ ደርሰው እንደነበር አንስተው፤ አሁን ለውይይቱ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።



ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ፕላኔቷ ላይ ከጫፍ እስከጫፍ ጥቃት መፈፀም እችላለሁ !/ ቤጂንግ /‎‎ለልዕለ ሃያሏ ሀገር ቻይና ዋሽንግተንን ያስበረገገ የአዉሮጳ ህብረትን ያስደነገጠ ጠላቶቼ የምትላቸዉን ምዕራባውያን ላይ ፍ...
03/09/2025

ፕላኔቷ ላይ ከጫፍ እስከጫፍ ጥቃት መፈፀም እችላለሁ !/ ቤጂንግ /

‎ለልዕለ ሃያሏ ሀገር ቻይና ዋሽንግተንን ያስበረገገ የአዉሮጳ ህብረትን ያስደነገጠ ጠላቶቼ የምትላቸዉን ምዕራባውያን ላይ ፍርሃት ያጫረ ወዳጆቿን ሩሲያና ሰሜን ኮርያን ያስደሰተ በአይነቱ ልዩ የሆነ ወታደራዊ ትርኢት አደረገች ።

‎የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ያበቃበትን 80ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ቻይና ለአሜሪካ እና ለአጋሮቿ ግልፅ መልእክት ነው ብለው በገለፁት ታላቅ ሰልፍ ላይ የተለያዩ አዳዲስ የጦር መሳሪያዎችን ፣የሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና ሌሎች ወታደራዊ መሳሪያዎችን ይፋ አድርጋለች።

ለ‎ዝግጅቱ ዢ ጂንፒንግ ከ 20 በላይ የውጭ ሀገራት መሪዎችን ያስተናገደ ሲሆን ከነዚህም መካከል የሩሲያው ቭላድሚር ፑቲን እና የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ ኡን ጨምሮ ከቻይና ጋር ጠንካራ ኢኮኖሚያዊ ግኑኝነት ያላቸው ሀገራት መሪዎች ተገኝተዋል ከአፍሪካም የግብፅ መሪዎች መገኘታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል ።

‎በአለም መድረክ ላይ የቻይናን የማይደፈር ኃያልነት ያሳያል በተባለው ወታደራዊ ትርኢቱ አስፈሪውን DF-5C የኒውክሌር ሚሳኤል አዳዲስ ሰው ሰው አልባ አውሮፕላን Guam Killer" Dongfeng-26D የተባሉ
‎የአሜሪካ ወታደራዊ ካምፖችን ማጥፋት የሚችሉ መካከለኛ ርቀት ሚሳኤል ፣ እንደ YJ-17 እና YJ-19 ያሉ ብዙ ሃይፐርሶኒክ ፀረ-መርከብ ሚሳኤሎች እና የሮቦት ተዋጊዎች ጨምሮ በርካታ መሳርያዎችን ለእይታ አብቅታች ።

‎ሚሳኤሎችን እና የሮኬት ሃይሎችን የመከላከያ ስትራቴጂዋ ቁልፍ አካል ያደረገችው ቻይና የአሜሪካን የባህር ኃይል የበላይነት ለመመከት የሚያስችሉ አሀጉራትን አቆራርጦ አዉሮጳን ማደባየት የሚችሉ የአምስተኛው ትውልድ ስውር ተዋጊ ጄቶች ጨምሮ ተንታኞች ለመገልፅ የከበዷቸዉ ዘርፈ ብዙ የሆኑ ወታደራዊ መሳርያዎችን ለአለም አሳይታለች ።

‎DF-5C የተሰኘው ስትራቴጂካዊ አህጉር አቋራጭ የኒውክሌር ሚሳኤል የጦር ጭንቅላት 4 ሜጋ ቶን ምርት እንዳለው የተዘገበ ሲሆን በሄሮሺማ እና ናጋሳኪ ላይ ከተወረወረው የአቶሚክ ቦንብ በ200 እጥፍ ብልጫ እንዳለው ስፑትኒክ ዘግቧል።
‎ የሚሳኤሉ የማጥቃት ብቃቱ አጠቃላይ ፕላኔቷን ይሸፍናል ።ይህም የቻይናን ስትራቴጅካዊ አቅሞችን ያሳያል።ተብሏል ።




ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ


ቻይናና ሩሲያ ፍትሀዊነት ለማስፈን እየሰሩ ነዉ !/ ፑቲን/‎‎ የሞስኮ እና ቤጂንግ አለም አቀፍ ጉዳዮችን ለመፍታት "አድሎአዊ ማዕቀቦችን" በመቃወምና በመታገል እንዲሁም የ BRICS ቡድን የ...
01/09/2025

ቻይናና ሩሲያ ፍትሀዊነት ለማስፈን እየሰሩ ነዉ !/ ፑቲን/

‎ የሞስኮ እና ቤጂንግ አለም አቀፍ ጉዳዮችን ለመፍታት "አድሎአዊ ማዕቀቦችን" በመቃወምና በመታገል እንዲሁም የ BRICS ቡድን የአባል ሀገራቱን እና የሰፊውን አለም አቀፉን ማህበረሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት እንቅፋት ናቸው ያሉትን ተቃውሞ በማሳየት አንድነታቸውን "በማጠናከር" በምዕራባውያን የሚመራዉ አለም ተገዳዳሪ ለመሆን አንድ መሆናቸውን እናረጋግጣለን ሲሉ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን መናገራቸው ተሰማ ።

‎በቻይና ቲያንጂን ማዘጋጃ ቤት ከሚካሄደው 25ኛው የሻንጋይ የትብብር ድርጅት (SCO) የመሪዎች ጉባኤ ቀደም ብሎ ከዚንሁዋ የዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የሩስያው ፕሬዝዳንት ብሪክስን ወደ “ዓለም አቀፋዊ የስነ-ህንፃ ቁልፍ ምሰሶ” በማሸጋገር እና የዓለም የገንዘብ ተቋማት ማሻሻያዎችን በመደገፍ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን ትብብር አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አፅንኦት ተሰጥተው ተናግረዋል ።

‎"የዓለም አቀፋዊ የስነ-ህንፃ ቁልፍ ምሰሶነት ሚናዋን ለማስፋት ከቻይና ከ BRICS ጋር ተቀራርበን እየሰራን ነው። በጋራ በመሆን ለአባል ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ዕድሎችን ለማስፋት ስትራቴጂካዊ ዘርፎች የጋራ መድረኮችን መፍጠርን ጨምሮ በእኩልነት በፍትሀዊነት የተመሰረተች አለም እንዲፈጠር የሚያስችሉ አማራጭ ሀሳቦች እናራምዳለን" ሲሉ ፑቲን ተናግረዋል ።

‎"BRICS አንገብጋቢ የሆኑ አለምአቀፋዊ ተግዳሮቶችን የመፍታት፣ በአህጉራዊ እና አለምአቀፍ ደህንነት ላይ ተመሳሳይ አመለካከቶችን ለመለዋወጥ እና የአባሎቻችንን እና የመላው አለምን ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ እድገት የሚያደናቅፉ አድሎአዊ ማዕቀቦችን ለመታገል በጋራ ለመስራት የሚያስችል አቅምን ለማጠናከር አንድነታችንን እንቆማለን።ብለዋሕ

‎የሩሲያው ፕሬዝዳንት በዛሬዉ እለት በሚካሄደው 25ኛው የኤስ.ኦ.ኦ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ በቻይና ይገኛሉ።በጉባኤው ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

‎ከሺንዋ የዜና አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ፑቲን የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የዓለም ባንክን ለማሻሻል ድጋፋቸውን ደጋግመው በመግለጽ "በእውነተኛ ፍትሃዊነት" ላይ የተመሰረተ "አዲስ የፋይናንስ ሥርዓት" እና ለሁሉም ሀገራት እኩል ተጠቃሚነት ጥሪ አቅርበዋል.

‎የሩሲያ ፕሬዝዳንት የገንዘብ መሳሪያዎችን እንደ “ኒዮ-ቅኝ ግዛት” ብለዉ የገለፁ ሲሆን BRICS “ግሎባል አብላጫውን” የሚጠቅም ሁሉን አቀፍ እድገት ይፈልጋል ብለዋል።

‎"ከቻይና አጋሮቻችን ጎን ለጎን የአለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት እና የአለም ባንክን ማሻሻያ እንደግፋለን ። አዲስ የፋይናንሺያል ስርዓት በግልፅነት እና በእውነተኛ ፍትሃዊነት ላይ የተመሠረተ መሆን አለበት ፣ ለሁሉም ሀገሮች እኩል እና አድሎአዊ ያልሆነ ተደራሽነት ያለው እና በአለም ኢኮኖሚ ውስጥ የአባል መንግስታትን ትክክለኛ አቋም የሚያንፀባርቅ መሆን አለበት በሚለው አመለካከት አንድ ነን ። የአለም አቀፍ ኢኮኖሚን ​​ዋና ዋና መሳሪያዎች ፋይናንስን መጠቀምን ማቆም አስፈላጊ ነው ። በተቃራኒው እኛ ለሁሉም የሰው ልጅ ጥቅም እድገት እንፈልጋለን ሲሉ ፑቲን ተናግረዋል ሲል ዢንዋ የዜና አገልግሎት አስነብቧል ።





ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ከትራምፕ ጋር መግባባት ላይ ደርሰናል - ፑቲንየሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አላስካ ውስጥ ባደረጉት ስብሰባ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በዩክሬን ጦርነት ማብቂያ ላይ መግ...
01/09/2025

ከትራምፕ ጋር መግባባት ላይ ደርሰናል - ፑቲን

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አላስካ ውስጥ ባደረጉት ስብሰባ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በዩክሬን ጦርነት ማብቂያ ላይ መግባባት ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን በትራምፕ አደራዳሪነት ከዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር የሰላም ድርድር መቼ ለማድረግ እንደወሰኑ አልገለጹም፡፡

በቻይና በተካሄደው የመሪዎች ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ፑቲን ዩክሬን ላይ እያደረጉት ያለውን ጥቃት ያስተባበሉ ሲሆን ምዕራባውያኑን ግን ወንጅለዋል።

ፑቲን በሻንጋይ በተዘጋጀው የትብብር ድርጅት ስብሰባ ላይም ከዢ ጂንፒንግ እና ናሬንድራ ሞዲ ጋር የተገናኙ ሲሆን የቻይናና የህንድ መሪዎች ላደረጉት ድጋፍ እንዲሁም የተፈጠረውን ቀውስ ለመፍታት ላደረጉት ጥረት አመስግነዋል።

J. Trump
ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

የብሪክስ አባል ሀገራት የዓለም አቀፍ ሥርዓት መሪ ምሰሶ ናቸው፡- ቭላድሚር ፑቲንየሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን  ቻይናን በይፋ ከመጎብኘታቸው በፊት ከሺንዋ የዜና ወኪል ጋር ቃለ ምልልስ ...
31/08/2025

የብሪክስ አባል ሀገራት የዓለም አቀፍ ሥርዓት መሪ ምሰሶ ናቸው፡- ቭላድሚር ፑቲን

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቻይናን በይፋ ከመጎብኘታቸው በፊት ከሺንዋ የዜና ወኪል ጋር ቃለ ምልልስ አድርገዋል።

ፕሬዝዳንቱ እንዳሉት ሩሲያ እና ቻይና የብሪክስን ሚና በማጠናከር ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓቱን በማሻሻል እና አዲስ ፍትሃዊ ስርዓት በመፍጠር ላይ በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ፑቲን አዲሱ የፋይናንስ ሥርዓት ማንኛውንም ሀገር የማይለይ እና እኩል ተደራሽነትን የሚያሰፍን መሆን አለበት ብለዋል።

ይህም ፋይናንስን እንደ መሳሪያ መጠቀም ለማስቆም ያለመ እንደሆነ አብራርተዋል።

ሩሲያ እና ቻይና የዓለም አቀፉን የገንዘብ ተቋም (IMF) እና የዓለም ባንክ (World Bank) ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ይስማማሉ።

ይህንንም የሚያደርጉት ዓለም አቀፉን ሥርዓት ይበልጥ ፍትሃዊ እና ብዙ ምሰሶዎች ያሉት ለማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል።


ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

ሩሲያ ለሊቱን በሰሜናዊ እና ደቡባዊ ዩክሬን በሚገኙ መሠረተ-ልማቶች ላይ በድሮኖች በፈጸመችው ጥቃት 60,000 ገደማ የሚሆኑ ደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋረጠ። በሩሲያ ውስጥ ጥቃት እ...
31/08/2025

ሩሲያ ለሊቱን በሰሜናዊ እና ደቡባዊ ዩክሬን በሚገኙ መሠረተ-ልማቶች ላይ በድሮኖች በፈጸመችው ጥቃት 60,000 ገደማ የሚሆኑ ደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋረጠ።

በሩሲያ ውስጥ ጥቃት እንዲፈጸም ትዕዛዝ የሰጡት ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ ሀገራቸው እንደምትበቀል ዝተዋል።
ሦስት ዓመት ከመንፈቅ የተዋጉት ሁለቱ ሀገሮች ባለፉት ሣምንታት አንዳቸው በሌላኛው ላይ የሚፈጽሟቸውን ጥቃቶች አጠናክረዋል። ሩሲያ የዩክሬን የኃይል እና የመጓጓዣ መሠረተ-ልማቶችን ዒላማ ስታደርግ ዩክሬን በፊናዋ የሩሲያ የነዳጅ ማጣሪያዎች እና ቧምቧዎችን እያጠቃች ትገኛለች።
ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ መከላከያ ሚኒስትራቸው ጄኔራል ኦሌክሳንደር ሲርስኪን ካነጋሩ በኋላ ሀገራቸው የምትፈጽማቸውን ጥቃቶች “ዩክሬንን ለመከላከል በሚያስፈልገው መንገድ እንቀጥላለን” ብለዋል። ለተልዕኮው የሚያስፈልጉ ኃይሎች እና መሣሪያዎች ዝግጁ መሆናቸውን የገለጹት ዜሌንስኪ በሩሲያ “ውስጥ የሚፈጸሙ አዳዲስ ጥቃቶች ታቅደዋል” ሲሉ በኤክስ ባሠፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
ሩሲያ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 112 የዩክሬን ድሮኖች ማክሸፏን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀ ኢንተርፋክስ የዜና ወኪል ዘግቧል። በዘገባው መሠረት ሩሲያ ዩክሬን ለወታደራዊ አገልግሎት የምትጠቀምበትን ወደብ መትቻለሁ ብላለች።
ምዕራባውያኑ ጦርነቱ በድርድር እንዲቆም ግፊት እያደረጉ ቢሆንም የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር ቫለሪ ጌራሲሞቭ ሀገራቸው በዩክሬን የምታካሒደውን ወረራ በመቀጠል አዲስ ከመስከረም እስከ ሕዳር ባሉት ወራት አዲስ የጥቃት ዕቅድ ይፋ ማድረጋቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት ዘግቧል። ዩክሬን እና ሩሲያ በሚዋጉባቸው የጦር አውድማዎች የሚፈጸሙ ጥቃቶች እንደቀጠሉ መሆናቸውን የገለጹት ጄኔራል ቫለሪ ጌራሲሞቭ የሀገራቸው ጦር ከመስከረም ሕዳር ባሉት ወራት የሚያከናወናቸው ተግባራት እየታቀዱ መሆናቸውን ተናግረዋል።
Dw


ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

👉ጀርመን ፈረንሳይና እንግሊዝ በኢራን ላይ አዲስ ማዕቀብ ለመጣል ማቀዳቸው ተነግሯልነገር ግን የአውሮፓ ሀገራት በኢራን ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ከውሳኔ ላይ ከደረሱ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ው...
29/08/2025

👉ጀርመን ፈረንሳይና እንግሊዝ በኢራን ላይ አዲስ ማዕቀብ ለመጣል ማቀዳቸው ተነግሯል

ነገር ግን የአውሮፓ ሀገራት በኢራን ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ከውሳኔ ላይ ከደረሱ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ደረጃ ሊያባብሰው እንደሚችል ባለሙያዎች ተናግረዋል።

ሶስቱ የአውሮፓ ሀገራት ማዕቀቡን ለመጣል እንደ ዋና ምክንያት ሰበብ ያደረጉት በ2015 ኢራን የገባችውን የኒውክለር ስምምነት አላከበረችም በሚል ነው ተብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ከሰሞኑ በኢራን ላይ የሚደረግ ማንኛውም ማዕቀብ ከፍተኛ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አስጠንቅቀዋል።

ሶስቱ የአውሮፓ ሀገራት አዲሱን ማዕቀብ ከመጣላቸው በፊት የ30 ቀናት የጊዜ ቀነ ገደብ መስጠታቸው አልጀዚራ ዘግቧል።

እስራኤል በኢራን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ሶስት የኒውክለር ጣቢያዎችን በቦምብ የደበደበችው አሜሪካ የ3ቱ የአውሮፓ ሀገራትን አዲስ ውሳኔ መደገፏን አስታውቃለች።

ነገር ግን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከኢራን ጋር በኒውክለር ጉዳይ ላይ ለመነጋገር በሯ ክፍት እንደሆነ ተናግረዋል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ በሰጡት መግለጫ በኢራን ኒውክለር ጉዳይ ላይ ሰላማዊና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት አሜሪካ የቀጥታ ግንኙነት ከኢራን ጋር ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።

እስራኤል በኢራን ላይ ባደረሰችው ጥቃት ምክንያት አሜሪካ ከኢራን ጋር ልታደርገው የነበረው የኒውክለር ድርድር መቋረጡ ይታወሳል።




ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share