
07/09/2025
👉ሩሲያ በዩክሬን ላይ አዳሩን ''ግዙፉን የአየር ጥቃት'' አደረሰች።
በጥቃቱ መላ ዩክሬን ዒላማ ውስጥ የገባ ሲሆን ከ810 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮንስ) ፣አራት ባሊስቲክ እና ዘጠኝ ክሩዝ ሚሳዔሎች በዩክሬን ሰማይ ላይ ሲያንዣብቡ አድረዋል።
ለመጀመሪያ ጊዜም በኪዬቭ መንግስት ህንጻ ተመ ቷል።
በጥቃቱ ቢያንስ ሁለት ሰዎች ህይወታቸውን ሲያጡ የአደጋ መቷል ድምጽ ሰጭ ደውሎች ለ11 ሰዓታት ያህል የተጠንቀቁ ድምፅ አሰምተዋል።
ለ11 ስዓታት የዘለቀው የአየር ላይ ጥቃት ሩሲያ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ችግሩን ለመፍታት ፍላጎቱ እንደሌላት ያሳያል በሚል አስወቅሷታል።
የዩክሬን አየር ኃይል እንዳስታወቀው"54 ሰው አልባ አውሮፕላኖችና ዘጠኝ ሚሳዔሎች በመላ ዩክሬን ዒላማቸውን መተዋል "።
ሩሲያ በዩክሬን ላይ ጦር ካዘመተች በኋላ ግዙፉን የአየር ጥቃት በኪዬቭ ላይ ስትፈጽም መሆኑ ነው።
ሐምሌ ላይ ሞስኮ ግዙፍ ወይንም በጦርነቱ ላይ አድርጋው የማታውቀውን መጠነ ሰፊ የአየር ጥቃት ማድረሷ ይታወሳል።
የአዳሩ የአየር ጥቃት ደግሞ " ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ ነው" ተብሏል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሜር ዘለንስኪ አስከፊው ጥቃት ነው ያሉት ሲሆን ሞስኮ ሆነ ብላ ጦርነቱን ለማራዘም የምታደርገው ነው ሲሉም ወቅሰዋል።
በዲፖሎማሲያዊ መንገድ ጦርነቱ እንደማይፈታ ጠቋሚ ነውም እየተባለ ይገኛል።
ዘገባው የ ዘ ዋሽንግተን ፖስት ነው።
ABM WORLD ኤቢኤም ወርልድ