AM ኤኤም ወርልድ

AM ኤኤም ወርልድ Ethio world አለምአቀፋዊ እና የሀገር ውስጥ ትኩስ መረጃ

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከአላስካው የሰላም ስምምነት እያፈገፈጉ ነው ስትል ሩስያ ከሰሰች። የሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርገይ ላብሮቫ ይህን ክስ ያቀረቡት ፕሬዝዳን ትራምፕ ...
27/10/2025

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከአላስካው የሰላም ስምምነት እያፈገፈጉ ነው ስትል ሩስያ ከሰሰች።

የሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርገይ ላብሮቫ ይህን ክስ ያቀረቡት ፕሬዝዳን ትራምፕ በሩስያና ዩክሬይን መካከል የሚካሄደው ጦርነት በአስቸኳይ ይቁም ማለታቸውን ተከትሎ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለአንድ የሐንጋሪ መገናኛ ብዙኀን የሰጡትን ቃለ ምልልስን ጠቅሶ የጀርመን ዜና አገልግሎት እንደዘገበው የአላስካው ስምምነት ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት ማድረግን ዓላማ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ትራምፕ ግን በተጻራሪው አሁን አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ መፈለጋቸውን ወቅሰዋል።

ላቭሮቭ አክለውም የሩስያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን የአላስካው ስምምነትን በተመለከተ የአሜሪካን አቋም የተቀበሉት ለድርድርና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያስችላል በሚል መንፈስ መሆኑንና ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እንዳልሆነም ነው የገለጹት።

የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ከአላስካው ስምምነት በኋላ ሩስያ በዩክሬይን የፈጸመቻቸውን ጥቃቶች እንደሚያሳስባቸው በመግለፅ በሩስያ ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ መጣላቸው ይታወሳል።

Donald J. Trump AM ኤኤም ወርልድ

እስራኤል በጋዛ አውቶቡስ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 11 ሰዎች ተገደሉበሰሜን ጋዛ ከእስራኤል ታንክ በተተኮሰ ጥይት በአንድ አውቶቡስ ተሳፍረው የነበሩ 11 የአንድ ቤተሰብ አባላት መገደላቸውን በሐ...
19/10/2025

እስራኤል በጋዛ አውቶቡስ ላይ በፈጸመችው ጥቃት 11 ሰዎች ተገደሉ

በሰሜን ጋዛ ከእስራኤል ታንክ በተተኮሰ ጥይት በአንድ አውቶቡስ ተሳፍረው የነበሩ 11 የአንድ ቤተሰብ አባላት መገደላቸውን በሐማስ የሚመራው የሲቪል መከላከያ አስታወቀ።
የአቡ ሻባን ቤተሰብ አባላት ናቸው የተባሉት ሟቾች አርብ ምሽት ላይ በጋዛ ከተማ ዜይቱን ሰፈር የሚገኝ ቤታቸውን ለማየት እየሄዱ ነበር ተብሏል።
ይህ ከስምንት ቀናት በፊት የተኩስ አቁም ስምምነት ከተጀመረ ወዲህ በጋዛ በእስራኤል ጦር የተፈጸመ እጅግ አስከፊው ክስተት ነው።
የእስራኤል ጦር ወታደሮቹ በጋዛ የእስራኤል ጦር የሚገኝበትን እና ቢጫ መስመር በሚል የተከለለውን አካባቢ ያለፈ "አጠራጣሪ መኪና" ላይ መተኮሳቸውን ገልጿል።
በመጀመሪያው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት የእስራኤል ወታደሮች ከግማሽ በላይ በሚሆነው የጋዛ ሰርጥ እንደተቆጣጠሩ ይቆያሉ።

የሲቪል መከላከያ ቃል አቀባይ ማህሙድ ባሳል ለኤኤፍፒ የዜና ወኪል እንደተናገሩት ግለሰቦቹ የተገደሉት በአካባቢው የሚገኘውን ቤታቸውን ለማየት ሲሞክሩ ነው።
ከሟቾቹ መካከል ሴቶች እና ሕጻናት እንደሚገኙበት የሲቪል መከላከያው አስታውቋል።

የእስራኤል መከላከያ ኃይል አርብ ዕለት "አጠራጣሪ መኪና የእስራኤል ወታደሮች በሚንሳቀሱበት በሰሜን ጋዛ ሰርጥ ቢጫውን መስመር አቋርጦ እየቀረበ እንደነበር ተለይቷል" በማለት በተሽከርካሪው ላይ "የማስጠንቀቂያ ጥይቶችን" መተኮሱን ተናግሯል።
ተሽከርካሪው "ወደ ወታደሮቹ ተጨባጭ ስጋት በሚፈጥር መልኩ መጠጋቱን በመቀጠሉ" እና "በተደረሰው መግባባት መሠረት ወታደሮች ጥቃቱን ለማስወገድ ተኩስ ከፍተዋል" ብሏል።

ሐማስ ቤተሰቡ ያለምክንያት ዒላማ እንደተደረገ ተናግሯል።
የእስራኤል መከላከያ ፍልስጤማውያን በጋዛ በቁጥጥሩ ስር ባሉ አካባቢዎች እንዳይገቡ አስጠንቅቋል።
የኢንተርኔት አገልግሎት ውስን በመሆኑ ብዙ ፍልስጤማውያን የእስራኤል ወታደሮች ያሉበት እና ቢጫ መስመር የተባለው የቱ እነደሆነ አያውቁም።
ይህ መስመር በመሬት ላይ ባለመካለሉ አውቶብሱ የቱ ጋር መስመሩን አንዳቋረጠ ግልጽ አይደለም።
ቢቢሲ አደጋው የተፈጸመበትን ስፍራ የሚያመለክት ኮኦርዲኔትስ እንዲሰጠው የእስራኤል ጦርን ጠይቋል።
የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ አርብ ዕለት ሠራዊቱ የመስመሩን ቦታ የሚጠቁሙ የሚታዩ ምልክቶችን እንደሚያስቀምጥ ተናግረዋል ።
በዩናይትድ ስቴትስ አደራዳሪነት በተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት መሠረት እስራኤል 250 ፍልስጤማውያን እስረኞችን እና 1,718 ከጋዛ በመውሰድ ያጎረቻቸውን ሰዎች ለቅቃለች።
ሐማስ በበኩሉ በሕይወት ያሉ 20 ታጋቾችን በሙሉ ወደ ለእስራኤል አስረክቧል።
መስከረም 26/2016 ዓ.ም. ሐማስ በደቡባዊ እስራኤል በፈጸመው ድንገተኛ ጥቃት 1,200 ሰዎቸን ሲገድል 251 ግቶ ወስዷል።
የእስራኤል ጦር ይህንን ተከትሎ በከፈተው መጠነ ሰፊ ወታደራዊ እርምጃ ቢያንስ 67,900 ሰዎች መገደላቸውን የሐማስ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

BBC
Benjamin Netanyahu - בנימין נתניהו



"ግብፅ እጇን አጣጥፋ አትመለከትም"በኢትዮጵያ እና በግብፅ መካከል ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት የውዝግብ ምክንያት ሆኖ የቆየው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጠናቀቀ በኋላ ግብፅ ...
18/10/2025

"ግብፅ እጇን አጣጥፋ አትመለከትም"

በኢትዮጵያ እና በግብፅ መካከል ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት የውዝግብ ምክንያት ሆኖ የቆየው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከተጠናቀቀ በኋላ ግብፅ በከፍተኛ ባለሥልጣናቷ አማካኝነት በኢትዮጵያ ላይ የምታቀርበውን ክሰ አጠናክራ ቀጥላለች።
ኢትዮጰያ፣ ግብፅ እና ሱዳን ከግድቡ ግንባታ አንስቶ በውሃ ሙሌት እና በግድቡ አስተዳደር ላይ ድርድር ሲያደርጉ ቢቆዩም ከስምምነት ላይ ሳይደርሱ የሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ ሥራ ጀምሯል።
በተለይ ከአባይ ወንዝ የሚመነጨውን አብዛኛውን ውሃ የምትጠቀመው እና ወንዙ "የኅልውናዬ መሠረት ነው" የምትለው ግብፅ፣ ግድቡ የውሃ ድርሻያን ይቀንሰዋል በማለት ስትከራከር ቆይታለቸ።
በኢትዮጵያ በኩል ግን ግደቡ የኃይል ማመንጫ በመሆኑ ለታችኛው ተፋሰስ አገራት የሚደርሰውን ውሃ የተመጣጠነ ያደርገዋል ስትል ትከራከራለች።
ግብፅ ግድቡ ኢትዮጵያ የውሃን ፍሰት እንድተቆጣጠረው በማድረግ የበላይነትን ይሰጣታል በሚል ስጋት ከግንባታው ወቅት አንስቶ አስገዳጅ ሕጋዊ ስምምነት እንዲፈረም ስትጥር የቆየች ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ በኩል ግን ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱ ይታወቃል።

ከግድቡ ምረቃ ከሳምንታት በኋላ በሱዳን የደረሰው የጎርፍ መጥለቅለቅ ግብፅ እያሰማችው ላለው ተቃወሞ አዲስ በር የከፈተላት ሲሆን፣ ለተከሰተው ጎርፍ እና ለደረሰው ጉዳት ግዙፉን የኢትዮጵያ ግድብ ተጠያቂ አድርጋለች።
በኢትዮጵያ በኩል ግን ይህ ተቀባይነትን አላገኘም።
ይልቁንም የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መኖር በሱዳንም ሆነ በግብፅ ሊደርስ ይችል የነበረን ከባድ ጉዳት አስቀርቷል በማለት የቀረበውን ክስ አጣጥላዋለች።
ኢትዮጵያ አሁንም በድርድሩ ለመቀጠል እና ሁሉንም ከሚጠቅም ስምምነት ላይ ለመድረስ ፍላጎት እንዳላት እየገለጸች ቢሆንም ከግብፅ በኩል ግን እየተሰማ ያለው ምላሽ ወደ ፍጥጫ ያዘነበለ ይመስላል።
ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ገንብታ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን ካስመረቀችው በኋላ የግብፅ ፕሬዝዳንትን ጨምሮ የአገሪቱ ዲፕሎማቶች እና ከፍተኛ ባለሥልጣናት ዛቻ አዘል ንግግሮችን በይፋ እየተናገሩ ነው።

ከቀናት በፊት የግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል ሲሲ ካይሮ ውስጥ በተካሄደ 8ኛው የውሃ ሳምንት ስብሰባ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት አገራቸው ብሔራዊ ጥቅሟን አና የውሃ ደኅንነቷን ለማስጠበቅ አስፈላጊ የሆኑትን ሁሉንም እርምጃዎችን ትወስዳለች ብለዋል።
ይህ የፕሬዝዳንቱ ንግግር የአፍሪካ ኅብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት እና የሁለቱ አገር ወዳጅ የሆነችው አሜሪካ ከሚያረምዱት አቋም አንጻር ለንግግር የሚኖረውን ዕድል የሚያደናቅፍ ሊሆን ይችላል።
ፕሬዘዳንቱ ኢትዮጵያ በግዛቷ ውስጥ ገንብታ ሥራ ላይ ያዋለችውን ግድብ አስተዳደርን በተመለከተ ግብፅ ደስተኛ አለመሆኗን ጠቅሰው ይህንን "ኃላፊነት የጎደለው" ያሉትን ሁኔታ አገራቸው "እጇን አጣጥፋ አትመለከትም" ብለዋል።
ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በሰጠው ምላሽ የፕሬዝዳንቱ ንግግር ግብፅ የአባይ ወንዝን በበላይነት ለመቆጣጠር ያላት ፍላጎት መገለጫ መሆኑን በመጠቀስ፣ እንዲህ ያለው ንግግር ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ የመጠቀም መብቷን አሳልፋ እንድትሰጥ የሚያደርጋት እንዳልሆነ በመግለጽ ተቃውሞውን ገልጿል።
ከዚህ ከፕሬዝዳንቱ ንግግር ቀደም ብሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ በተካሄደበት ወቅት የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ የታላቁ ሕዳሴ ግድብን ጉዳይ አንስተው አገራቸው ኢትዮጵያን ወደ ዓለም አቀፉ የፍትሕ ፍርድ ቤት እንደምትወስድ ገልጸው ነበር።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ "በአባይ ላይ የተናጠል እርምጃ ወስዳ ግድብ በመገንባት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የግብፅ እና የሱዳን ሕዝቦችን ሕይወት አደጋ ላይ ጥላለች" በማለት ከመከሰሳቸው በተጨማሪ ኢትዮጵያ የተናጠል እርምጃ በመወሰድ በቀጣናው "አደጋ ደቅናለች" ብለዋል።
ይህንን ክስ ተከትሎም በተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ምክትል ቋሚ ተወካይ የሆኑት አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ በሰጡት ምላሽ "ግብፅ ስለ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ያደረገችው ንግግር መሠረት አልባ እና አሳሳች ነው" በማለት "ግብፅ ከቅኝ ግዛት ስምምነት የተወረሰ 'ታሪካዊ መብት' አለኝ በሚል የተፋሰሱን አገራት አግልላች" ብለዋል።

አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተቋማት እንዲሁም አገራት ኢትዮጵያ እና ግብፅ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ንግግር በማድረግ ከስምምነት እንዲደርሱ እየጠየቁ ባለበት በአሁኑ ጊዜ በግብፅ በኩል ግን ሌሎች አማራጮችን ለመፈለግ አዝማሚያ እንዳለ የሚያመለክቱ ንግግሮች እየተሰሙ ነው።
"ግብፅ በአባይ ወንዝ ላይ አትደራደርም"
ፕሬዝዳንት አልሲሲ አገራቸው በአባይ ውሃ ላይ ያላትን ጥቅም ለማስከበር ማንኛውንም እርምጃ እንደሚወስዱ በተናገሩበት መድረክ ላይ የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞሰጣፋ ማደቡሉ የግብፅ የውሃ ደኅንነት ጉዳይ "የኅልውና ጉዳይ ስለሆነ ለድርድር የሚቀርብ አይደለም" ማለታቸው ተዘግቧል።
ፕሬዝዳንት አልሲሲ በመክፈቻው ላይ ንግግር ባደረጉበት 8ኛው የውሃ ሳምንት ጉባኤ ማብቂያ ላይ ንግግር ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኢትዮጵያ ጋር የማያስማማቸውን "ታሪካዊ እና ሕጋዊ" መብትን አንስተዋል።
የግብፅ የውሃ ደኅንነት ጉዳይ የፖለቲካ ወይም የድርድር ቦታ አይደለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ግብፅ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን ታሪካዊ እና ሕጋዊ መብት ለድርድር ታቀርባለች ብሎ ማሰብ ተራ ቅዥት ነው" በማለት ለግብፅ የኅልውና ጉዳይ በሆነው በአባይ ውሃ ላይ ድርድር እንደማይኖር ተናግረዋል።

ይህ ግብፅ ከአባይ ወንዝ የምታገኘው የውሃ መጠን እንዳይነካባት የምትጠቅሰው "ታሪካዊ እና ሕጋዊ" ድርሻ ሌሎችን አገራት ያገለለ እና ኢትዮጵያን ጨምሮ በቀሪዎቹ የናይል ተፋሰስ አገራት ተቀባይነት የሌለው የቅኝ ግዛት ስምምነት ነው።
ይህ በአውሮፓውያኑ 1959 በቀኝ ገዢዋ ብሪታኒያ የተፈረመው እና የአብዛኛውን የውሃውን ድርሻ ለግብፅ የሚሰጠው የቅኝ ግዛት ስምምነት አብዛኛውን የተፋሰሱን ውሃ ለግብፅ የሚሰጥ ነው።
ስምምነቱ ለ85 በመቶ በላይ ውሃን ለወንዙ የምታመነጨውን ኢትዮጵያን ያላካተተ ሲሆን፣ ግብፅ 55.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃ እንዲሁም ሱዳን 18.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ውሃ እንዲያገኙ የሚፈቅድ ነው።

በየዓመቱ በናይል ወንዝ ላይ ከሚፈሰው 84 ቢሊዮን ኩዩቢክ ውሃ 12 በመቶው በትነት የሚያልቅ ሲሆን፣ አብዛኛውን ቀሪ ውሃ ለግብፅ በመስጠት በወቅቱ ግብፅን ትገዛ የነበረችው ብሪታንያ ለጥጥ ምርቷ እንድትጠቀምበት የሚያመቻች ነው።
ኢትዮጵያ ይህ የቅኝ ግዛት ዘመን ስምምነት እሷን ያገገለለ ከመሆኑ በተጨማሪ ፍትሐዊነት የጎደለው በመሆኑ እንደማትቀበለው በመገለጽ በተፋሰሱ አገራት መካከል ድርድር ተደርጎ አዲስ ሁሉንም የሚያስማማ ስምምነት ላይ እንዲደረስ ስትጠይቅ ቆይታልቸ።
ኢትዮጵያ የሕዳሴ ግድብ ግንባታን ከጀመረች በኋላ በአገራቱ፣ በአፍሪካ ኅብረት፣ በአሜሪካ እና በዓለም ባንክ አማካኝነት በተደጋጋሚ እየተቋረጠ ድርድር ሲካሄድ ቆይቷል።
ነገር ግን ግብፅ ያቀረበችው አስገዳጅ እና ሕጋዊ ስምምነት እንዲፈረም መጠየቋ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ድርድሮቹ ውጤት አላስገኙም።
ግድቡ ተገንብቶ በውሃ ከተሞላ እና ሥራ ከጀመረ በኋላም ድርድር እንዲካሄድ የተለያዩ ወገኖች እየወተወቱ ባለበት ጊዜ ኢትዮጵያ ዝግጁነቷን ብትገልጽም የግብፅ ፕሬዝዳንትን ጨምሮ የአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት የሚያደርጉት ንግግር ግን ለድርድር በር የሚከፍት አይደለም።

ፕሬዝዳንቱ የግብፅን ጥቅም ለማስከበር ማንኛውንም እርምጃ እንደሚወስዱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደግሞ በናይል ውሃ ላይ ድርድር የሚታሰብ እንዳልሆነ በአንድ ሳምንት ውስጥ በተከታታይ ማሳወቃቸው በሕዳሴ ግድብ ግንባታ ወቅት የነበረው ውጥረት አሁንም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሚያመለክት ነው።
ባለፉት ሳምንታት የግብፅ ከፍተኛ ባለሥልጣናት የሚያደርጓቸው ንግግሮችን እየተከታተለች ምላሽ እየሰጠች ያለችው ኢትዮጵያ ግብፅ አሉታዊ ዘመቻ መክፈቷን በመጥቀስ ተቃውሞዋን አሰምታለች።
የኢትዮጵያ ውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዳለው "ግብፅ ከዓባይ ወንዝ እና ከታላቁ ሕዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ ላይ የከፈተችውን ዘመቻ አጠናክራ ቀጥላለች" በማለት ገልጾታል።





Abiy Ahmed Ali
AM ኤኤም ወርልድ

ትራምፕ ህንድ የሩሲያ ዘይት መግዛቷን ለማቆም ተስማምታለች ቢሉም የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏልየሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛ...
17/10/2025

ትራምፕ ህንድ የሩሲያ ዘይት መግዛቷን ለማቆም ተስማምታለች ቢሉም የህንድ መንግስት ስለ ጉዳዩ ምንም የማዉቀዉ ነገር የለም ብሏል

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የሩሲያን ነዳጅ ላለመግዛት መስማማታቸውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትናንት ነበር የተናገሩት፡፡

ህንድ በበኩሏ የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት የሩስያን ዘይት ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት ለማቆም ተስማምታለች ሲሉ የሰጡትን አስተያየት ተቃዉማለች፡፡

ይህም ምናልባት ግንኙነታቸዉን ያሻከረ እና በቅርቡ እልባት ያገኛል ተብሎ የማይታሰብ ጉዳይ ነዉ ተብሏል፡፡

ትራምፕ ትናንት ባደረጉት ንግግር፤ ሕንድ "በአጭር ጊዜ ውስጥ" ከሩሲያ ነዳጅ መግዛት እንደምታቆም ከሞዲ ማረጋገጫ ማግኘታቸውን እና ይህም 'ትልቅ እቀባ' መሆኑን ገልጸዋል።

የአገሪቷ መንግሥት ቃል አቀባይ ለትራምፕ ንግግር በሰጡት ምላሽም " ከሕንድ ጋር የኢነርጂ ትብብሩን ለማጠናከር ፍላጎት ካሳየው የአሜሪካ አስተዳደር ጋር ውይይቶች እየተካሄዱ ነው" ብለዋል።

ነገር ግን ሐሙስ ዕለት የሕንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ራንዲር ጃይስዋል ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፤ በትራምፕ እና በሞዲ መካከል “ምንም ዓይነት የተደረገ ውይይት መኖሩን አላውቅም” ያሉ ሲሆን፤ የሕንድ መንግስት ከሩሲያ ዘይት መግዛቱን ለማቆሙ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ እንደሌላቸው ተናግረዋል።

ህንድ ከክሬምሊን ጋር የጠበቀ ግኑኝነት ያላት ሲሆን፤ በዚህ ዓመት መጨረሻ ላይ የሩሲያውን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን ተቀብላ ታስተናግዳለች።

በ2022 ሩሲያ ዩክሬንን ከወረረች በኋላም ከሞስኮ ከፍተኛ የነዳጅ ገዢዎች አንዷ ሆና ብቅ ብላለች።

ጦርነቱ በሞስኮ የነዳጅ ኢንዱስትሪ ላይ ከፍተኛ ማዕቀብ ያስከተለ ሲሆን፤ ዋጋዎችንም አሽቆልቁሏል።

አሜሪካ የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም የሚደረጉት ጥረቶች አካል በማድረግ በክሬሚሊን ላይ የኢኮኖሚ ጫናዎችን ማሳደር ትፈልጋለች።

የአሜሪካው ፕሬዚደንት ሕንድ ከሩሲያ ነዳጅ መግዛቷን ለማስቆም ቢፈልጉም፤ደልሒ ግን እስካሁን ይህንን ሳትቀበል ቆይታለች ሲል ሲ ኤን ኤን ዘግቧል።



Donald J. Trump

Narendra Modi

AM ኤኤም ወርልድ

👉ሁቲዎች እስራኤል  ለፈፀመችው ወንጀል ተገቢውን ቅጣት ትቀበላለች  ሲሉ አስጠንቅቀዋል ።የየመን ሁቲዎች የጦር አዛዥ እና ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣን በእስራኤል ጥቃት ትናንት መገደላቸው ተገ...
17/10/2025

👉ሁቲዎች እስራኤል ለፈፀመችው ወንጀል ተገቢውን ቅጣት ትቀበላለች ሲሉ አስጠንቅቀዋል ።

የየመን ሁቲዎች የጦር አዛዥ እና ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣን በእስራኤል ጥቃት ትናንት መገደላቸው ተገልጿል።
ወታደራዊ ባለስልጣን ሙሀመድ አብዱል ከሪም አል ገማሪን ወታደራዊ አመራር ላይ በነበሩበት ወቅት እንደተገደሉ የየመን ሁቲዎች ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

መግለጫውን ተከትሎ እስራኤል ለግድያው ሀላፊነት ወስዳለች ።

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትስ አል ገማሪ የተገደሉት በእስራኤል የአየር ጥቃት መሆኑን ተናግረዋል።

ወደ ፊት ከየመን ሁቲዎች ለሚደርሱ ማንኛውንም ጥቃት ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስዱም ዝተዋል።

የየመኑ ሁቲ ከእስራኤል ጋር ያለው ጦርነት ገና እንዳላበቃ እና እስራኤል በመሪያችን ላይ ላደረሰችው ጥቃት ተገቢ የሆነ ምላሽ በቅርቡ እንደሚጠብቃት ተናግሯል።

በሀማስ እና እስራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ሰድስተኛ ቀናት ካስቆጠረ በኋላ የተፈፀመ ጥቃት መሆኑ ተነግሯል

እስራኤል በፍልስጥኤማውያን ንፁሃን ላይ የምታደርሰውን የዘር ጭፍጨፋ በመቃወም ሁቲዎች ከጥቅምት 2023 ጀምሮ ከጋዛ ጉን በመቆም እስራኤልን በድሮን እና በሚሳኤል እያጠቁ ነበር

የየመኑ ሁቲዎች ከዚህ በተጨማሪም በቀይ ባህር በኩል የሚንቀሳቀሱ ከእስራኤል ጋር ቅርበት ያላቸውን መርከቦች ኢላማ በማድረግ ለጋዛውያን አጋርነታቸውን በማሳየት የአለም አቀፍ የመርከብ መስመሮችን መዝጋታቸው ይታወሳል።



AM ኤኤም ወርልድ

👉የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ኢስላማባድ ከአፍጋኒስታን ያደረጉት ዉጊያ መቆሙን ገለፁ ።የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ሐሙስ ዕለት እንዳስታወቁት ኢስላማባድ ከአፍጋኒ...
16/10/2025

👉የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ
ኢስላማባድ ከአፍጋኒስታን ያደረጉት ዉጊያ መቆሙን ገለፁ ።

የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ሐሙስ ዕለት እንዳስታወቁት ኢስላማባድ ከአፍጋኒስታን ጋር ያላቸውን ግጭት ለመፍታት በጊዜያዊነት የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረጋቸውን የገለፁ ሲሆን ስምምነቱ በቀድሞዎቹ አጋሮች መካከል የተደረገውን ከባድ ውጊያ ያስቆመ ነው። ብለዋል

የደቡብ እስያ ጎረቤቶች ለ 48 ሰአታት እርቅ ስምምነት ከመስማማታቸው በፊት በመሬት ላይ በታንክ የታገዘ ውጊያና ፓኪስታን ከምድሩ ባሻገር የአየር ድብደባ በመሰንዘር በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎችን ገድለዋል እና በመቶዎች የሚቆጠሩ አቁስለዋል ።

ከስምምነቱ በኋላ ሻሪፍ በኢስላማባድ ለሚገኘው ለካቢኔው እንደተናገሩት ፓኪስታን ተከታታይ ታጣቂ ጥቃቶችን ተከትሎ በአፍጋኒስታን ላይ ትዕግስት በማጣቱ “አጸፋ ወስደዋል” ብለዋል።

ሻሪፍ "በትክክለኛ ሁኔታ ላይ ለመነጋገር ከፈለጉ እና በውይይት ለመፍታት ከፈለጉ እኛ ለዚያ ዝግጁ ነን" ሲሉ ተናግረዋል ።

"ይህ የሰላም ሀሳብ ትናንትም ዛሬም አቋማችን ነዉ አሁን ኳሱ በሜዳቸው ውስጥ ነው." ነገር ግን "ይህ የተኩስ አቁም ጊዜ ለመግዛት ብቻ ከሆነ አንቀበለውም" ሲሉም አክለዋል።

የአፍጋኒስታን መከላከያ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢናያቱላህ ክሆዋራዝሚ የተኩስ አቁም ስምምነቱ እስካሁን እየተካሄደ ነው ብለዋል።

የአፍጋኒስታን ታሊባን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ካሊፋ ሲራጅዲን ሃቃኒ የኢራን ከፍተኛ ባለስልጣናትን አግኝተው አፍጋኒስታን ከሁሉም ሀገራት በተለይም ከጎረቤቶቿ ጋር መልካም ግንኙነት እንደምትፈልግ ነግሯቸዋል።

"የሌሎችን ሉዓላዊነት እና ክብር እንደምናከብር ሁሉ ለእኛም ተመሳሳይ በጎ ፈቃድ እና አክብሮት እንጠብቃለን" ሲል ሃቃኒ ዘግቧል።

ምንም እንኳን ጎረቤቶች ባለፈው ጊዜ እርስ በርስ የተጋጩ ቢሆንም፣ የአሁኑ ጦርነት ከአስርተ አመታት በፊት የገጠማቸው የከፋ ነው። ተብሏል

በቅርቡ በእስላማዊ አገሮች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት የተፈጠረው ኢስላማባድ ካቡል በፓኪስታን ውስጥ ጥቃት ያደረሱ ታጣቂዎችን በአፍጋኒስታን ከሚገኙ መጠለያዎች እንደሚንቀሳቀሱ በመግለጽ እንዲቆጣጠር ከጠየቀ በኋላ ነው።

ታሊባን ክሱን ውድቅ አድርጎ የፓኪስታን ጦር ስለ አፍጋኒስታን የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት፣ የድንበር ውጥረትን በማስነሳት እና ከአይኤስ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ታጣቂዎች በማስጠለል መረጋጋትንና ሉዓላዊነቷን ለመናድ ሲል ከሰዋል።
ኢስላማባድ በበኩሉ ክሱን ውድቅ አድርጓል።

ከጥቅምት 10 ጀምሮ በተካሄደው ጦርነት ቢያንስ 18 ንፁሀን ዜጎች ተገድለዋል ከ360 በላይ ቆስለዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ተልዕኮ (UNAMA) ገልጿል። ሲል የዘገበው ሮይተርስ ነዉ ።


AM ኤኤም ወርልድ

👉የጋዛ የሰብዓዊ መብት ተመልካቾች ቡድን  እስራኤል ከተኩስ አቁም ስምምነቱ በኋላ 36 የስምምነት ጥሰቶች መፈጸሟን አረጋግጧል።ቡድኑ በግብጽ ካይሮ የተደረሰው ስምምነት እንደፈረንጆቹ አቆጣጠር...
16/10/2025

👉የጋዛ የሰብዓዊ መብት ተመልካቾች ቡድን እስራኤል ከተኩስ አቁም ስምምነቱ በኋላ 36 የስምምነት ጥሰቶች መፈጸሟን አረጋግጧል።

ቡድኑ በግብጽ ካይሮ የተደረሰው ስምምነት እንደፈረንጆቹ አቆጣጠር ጥቅምት 10 ቀን እኩለ ቀን ላይ ተግባራዊ ከተደረገ በኋላ እስራኤል በተደጋጋሚ የተኩስ አቁም ጥሰት ፈጽማለች ብሏል። ቡድኑ ፍልስጤማውያን ሲቪሎች መሞታቸውንና በርካቶች መቁሰላቸውን ይፋ አድርጓል።

የጋዛ ሰብዓዊ ማዕከል ባወጣው መግለጫ በሐማስ እና እስራኤል መካከል ስምምነት ቢደረግም ከቅርብ ቀናት ወዲህ የእስራኤል ሃይሎች በተለያዩ አካባቢዎች የአየር ድብደባ ፣ በመድፍ የታገዘ ጥቃት እና የተኩስ ልውውጥን የመሳሰሉ ጥሰቶች መፈጸሟን አስታውቋል።

እንደ ቡድኑ ዘገባ የእስራኤል ድሮን በምስራቃዊ ጋዛ ሹጃያ አካበቢ ባደረሰው ጥቃት አምስት ፍልስጤማውያን መሞታቸውን የገለጸ ሲሆን ነገር ግን ተጎጂዎቹ በእስራኤል ወታደሮች ላይ ምንም አይነት ስጋት እንዳልፈጠሩ ገልጿል።

ከካን ዩኒስ በስተምስራቅ በምትገኘው አል ፋሃሪ ከተማ ላይ በተፈፀመ የአየር ድብደባ ሌላ ንጽሃን ዜጋ መሞቱን እና አንድ ሰው መቁሰሉን የገለጸው መግለጫው ሌሎች ጥቃቶችን ተከትሎ በጃባሊያ እና ራፋህ ተጨማሪ ጉዳቶች ተመዝግበዋል ብሏል።

የሰብዓዊ ተሟጋቾቹ መግለጫ እንደሚያሳየው ሌሎች ጥሰቶችን ጨምሮ ረቡዕ ማለዳ ጀምሮ በተለይም በምስራቃዊ እና ሰሜናዊ ጋዛ ሰርጥ የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ ወደቤታቸው በመመለስ ላይ ባሉ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ያነጣጠረ ተደጋጋሚ ተኩስ እና የተኩስ ጥቃት እየተፈጸመባቸው ይገኛል ብሏል።

ጥቃቶቹ እየተፈጸሙ የሚገኙት ኢፍትሃዊ በሆነ መንገድ ሲሆን ወታደራዊ እርምጃውም በትክክል ጥሰት መሆኑን አረጋግጫለሁ ያለው መግለጫው እስራኤል የወረራ እንቅስቃሴዋን ለማስቀጠል እና ሆን ብላ ፍርሃትን እና ውዥንብርን ለመፍጠር የፈጸመችው ተግባር ነው ብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እስራኤል በቅርብ ቀናት ውስጥ ወደጋዛ እንዲገባ ከሚጠበቀው በግምት 1,800 ውስጥ 173 የጭነት መኪናዎች ብቻ ናቸው መግባት የቻሉት ብሏል




AM ኤኤም ወርልድ

ሐማስ የታጋቾችን አስከሬን ለመለየት ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለሐማስ ረቡዕ ዕለት የተጨማሪ ሁለት ታጋቾችን አስከሬን ማስረከቡን ገልጾ፣ ነገር ግን የሌሎችን አስከሬን ከጋዛ ፍርስራሾች ውስጥ...
16/10/2025

ሐማስ የታጋቾችን አስከሬን ለመለየት ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገኛል አለ

ሐማስ ረቡዕ ዕለት የተጨማሪ ሁለት ታጋቾችን አስከሬን ማስረከቡን ገልጾ፣ ነገር ግን የሌሎችን አስከሬን ከጋዛ ፍርስራሾች ውስጥ ለማውጣት ተጨማሪ ጊዜ እና የዘመኑ መሳሪያዎች ያስፈልጉኛል አለ።

የቡድኑ ወታደራዊ ክንፍ ባወጣው መግለጫ ላይ ለሰላም ስምምነቱ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቆ እስካሁን ማስረከብ የቻለው የታጋቾች አስከሬን ሊደርስባቸው የቻላቸውን ብቻ መሆኑን ገልጿል።

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሐማስ ለስምምነቱ ተገዥ ካልሆነ እስራኤል በጋዛ የምታካሄደውን ወታደራዊ ዘመቻ ልትቀጥል ትችላለች ብለዋል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በበኩሉ በቀይ መስቀል በኩሉ የታጋቾችን አስከሬን መቀበሉን ገልጾ ማንነታቸውን የመለየት ሥራ ይቀራል ብሏል።

የእስራኤል ጦር ሕዝቡ በትዕግሥት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቦ "የታጋቾቹን ማንነት የማረጋገጥ ሥራ ተሰርቶ በመጀመርያ ለቤተሰቦቻቸው እንደሚያሳውቅ" ገልጿል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።



AM ኤኤም ወርልድ

ኢራን የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቴላቪቭን ከቴህራን ጋር ለማስታረቅ ያቀረቡትን የሰላም ስምምነት ጥሪ እንደማትቀበል ገለፀች ። በሰኔ ወር በኢራን የኒውክሌር ቦታዎች ላይ ያደረሰችውን ...
15/10/2025

ኢራን የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቴላቪቭን ከቴህራን ጋር ለማስታረቅ ያቀረቡትን የሰላም ስምምነት ጥሪ እንደማትቀበል ገለፀች ።

በሰኔ ወር በኢራን የኒውክሌር ቦታዎች ላይ ያደረሰችውን ጥቃት በመጥቀስ "በዩኤስ ፕሬዝዳንት የተገለፀው የሰላም እና የውይይት ፍላጎት አሜሪካ በኢራን ህዝብ ላይ ካላት የጥላቻ እና የወንጀል ባህሪ ጋር ይቃረናል" ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው ተናግሯል።

ቴህራን ይህን ምላሽ የሰጠችው
ሰኞ ዕለት በእስራኤሉ ክኔሴት ንግግር ላይ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሰላም ስምምነት እንደሚፈልጉ እና ማንኛውም ስምምነት እንዲፈፀም ኳሱ በቴህራን ፍርድ ቤት እንዳለ መናገራቸውን ተከትሎ ነዉ ።

ኢራን በመግለጫዋ ጥሪውን ውድቅ አድርጋለች።

በፖለቲካዊ ድርድር ውስጥ በአንድ ሀገር የመኖሪያ አካባቢዎችን እና የኒውክሌር መስሪያ ቤቶችን ማጥቃት፣ ከ1,000 በላይ ሰዎችን ንፁሃን ሴቶችን እና ህጻናትን ገድሎ ሰላምና ወዳጅነትን እንዴትስ ጠየቀ?" ሲል መግለጫዉን የጀመረው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ።

የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
በኢየሩሳሌም በሚገኘው ክኔሴት ያደረጉትን ንግግር “ኃላፊነት የጎደለው እና አሳፋሪ” በማለት ዩናይትድ ስቴትስ “የሽብርተኝነት ግንባር ቀደም ተዋናይ እና የአሸባሪው እና የዘር ማጥፋት የጽዮናውያን አገዛዝ ደጋፊ ናት” ስትል ወቅሳለች።

የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር “ዩናይትድ ስቴትስ… ሌሎችን ለመወንጀል የሞራል ብቃት የላትም” ብሏል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የገለፁት የሰላም ፍላጎት እና የውይይት ፍላጎት አሜሪካ በኢራን ህዝብ ላይ ካላት የጥላቻ እና የወንጀል ባህሪ ጋር ይቃረናል ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አስታውቋል።

እንደሚታወሰው በሰኔ ወር አጋማሽ እስራኤል በኢራን ላይ ታይቶ የማያውቅ የቦምብ ጥቃት የኒውክሌር እና ወታደራዊ ተቋማትን እንዲሁም የመኖሪያ አካባቢዎችን በመምታት ከ1,000 በላይ ሰዎችን ገድሏል።

ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ቁልፍ የሆኑትን የኒውክሌር መስሪያ ቤቶችን የመታበት የ12 ቀን ጦርነት ከእስራኤል ጋር በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል የነበረውን ከፍተኛ የኒውክሌር ድርድር ውድቅ ቢያደርገዉም
ከሰኔ 24 ጀምሮ በኢራን እና በእስራኤል መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረጉ ይታወሳል ።

ለዘገባዉ ጀሩሳሌም ፖስት ሮይተርስ ቴህራን ፖስንት ተጠቅመናል ።





AM ኤኤም ወርልድ

👉የሶሪያው ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራራ ከሞስኮ ጋር "ግንኙነቱን ወደነበረበት ለመመለስ እና እንደገና ለማስተካከል"እንደሚፈልጉ መናገራቸው ተሰማ ።የሶሪያው ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራራ ለሩ...
15/10/2025

👉የሶሪያው ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራራ ከሞስኮ ጋር "ግንኙነቱን ወደነበረበት ለመመለስ እና እንደገና ለማስተካከል"እንደሚፈልጉ መናገራቸው ተሰማ ።

የሶሪያው ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራራ ለሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እንደተናገሩት የረዥም ጊዜ የክሬምሊን አጋርና ከስልጣን ከተባረሩት የበሽር አል አሳድ ቁልፍ ወዳጄ ከሆነችው ከሞስኮ ጋር "ግንኙነቱን ወደነበረበት ለመመለስ እና እንደገና ለማስተካከል" እንደሚፈልግ ተናግረዋል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል ።

የሶሪያው ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በጥቅምት 15 ሩሲያ ሞስኮ በተካሄደ ስብሰባ ላይ በሶሪያ የባህር ዳርቻ የአየር እና የባህር ሃይል ጦር ሰፈሯን እንዲሁም የባህር ዳርቻዎችን እንድትጠብቅ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል ።

አል ሻራ ይህን የገለፀው ከ10 ወራት በፊት ከሶሪያ ከተሰደደበት ጊዜ አንስቶ አል አሳድን በምታስተናግድበት የመጀመሪያ ጉብኝቱ በሞስኮ ከፑቲን ጋር በተገናኘበት ወቅት ነው።

"በታደሰዉ ግንኙነታችን በማሳደግና በአዲስ መንገድ በመመለስ እንደገና ለመወሰን እየሞከርን ነው ስለዚህም ለሶሪያ ነፃነት, ሉዓላዊቷ እና የግዛት አንድነት እንዲሁም የደህንነት መረጋጋት እንሰራለን " ሲል የክሬምሊን መንግስት ቃል ገብቷል ።

ሶሪያ የሩሲያን ግንኙነት 'እንደገና ለመወሰን' ትፈልጋለች ያሉት የሶሪያ መሪ ደማስቆ ከሞስኮ ጋር ያለፉትን ስምምነቶች ሁሉ እንደምታከብር አረጋግጠዋል። "ከሩሲያ ጋር የሚያስተሳስሩን የሁለትዮሽ ግንኙነቶች እና የጋራ ፍላጎቶች አሉ, እና ከእሱ ጋር የተደረጉ ስምምነቶችን ሁሉ እናከብራለን" ብለዋል.

ፑቲን የአል-ሻራውን 'ታላቅ ስኬት' አወድሰው
በሁለቱ ሀገራት መካከል ለአስርተ አመታት የቆየውን "ልዩ ግንኙነት" አድንቀው ሞስኮ ሁል ጊዜ በሶሪያ ህዝብ ፍላጎት እንደምትሰራ እና መንግስታቸውም ማስፋት እንደሚፈልግ ተናግረዋል።

አክለዉም ሩሲያ በበኩሏ በሶሪያ የባህር ዳርቻ የአየር እና የባህር ሃይል ጦር ሰፈሯን እንዳቆየች እና ክሬምሊን የባህር ዳርቻዎችን ለመጠበቅ ስምምነት ለመደራደር ተስፋ እንዳለው በመግለፅ ወደ ሶሪያ የነዳጅ ጭነቶችን መላክ መጀመራቸውን ገልፀዋል ተብሏል።

ሶሪያ በአሁኑ ጊዜ በአስቸጋሪ ጊዜያት ውስጥ ብትሆንም, ሆኖም ግን በሩሲያ ድጋፍና እርዳታ በሶሪያ ውስጥ በሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች መካከል ያለውን ግንኙነት እና ትብብር ያጠናክራል" ብለዋል ፑቲን ሲሉ ያስነበቡት አልጀዚራ እና ሞስኮ ታይምስ ናቸዉ ።




AM ኤኤም ወርልድ

ግብፅ ፣ ኳታር ፣ ቱርክ እና አሜሪካ በጋዛ ሰርጥ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ተፈራረሙየግብፅ ፣ የኳታር ፣ የቱርኪ እና የአሜሪካ መሪዎች በጋዛ ሰርጥ የታየውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ቁረጠኛ...
14/10/2025

ግብፅ ፣ ኳታር ፣ ቱርክ እና አሜሪካ በጋዛ ሰርጥ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ተፈራረሙ

የግብፅ ፣ የኳታር ፣ የቱርኪ እና የአሜሪካ መሪዎች በጋዛ ሰርጥ የታየውን ሰላም በዘላቂነት ለማስቀጠል ቁረጠኛ ውሳኔ ባሳለፉበት የመግባቢያ ሰነድ ላይ መፈራረማቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

ሀገራቱ የጋዛን የተኩስ አቁም ስምምነት ለማጠናከር እና በቀጠናው "ዘላቂ ሰላም" ለማምጣት ወሳኝ ስምምነት ማድረጋቸውን ያስታወቁት ዛሬ ማክሰኞ በካይሮ በሰጡት የጋራ መግለጫ ነው።

ዛሬ ይፋ በሆነው መግለጫ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ፍልስጤማውያን እና እስራኤላውያን እኩል መብት ይገባቸዋል" ማለታቸው ከፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር ያልተለመደ እና በአለም አቀፍ ጫና የመጣ እንድሁም በመካከለኛው ምስራቅ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት ወሳኝ ምዕራፍ ነው ተብሏል።

ትራምፕ በዚህ ንግግራቸው ለፍልስጤም እውቅና የሰጡ ሲሆን በተጨማሪም የሁለት ሀገርነት መፍትሔንም እውን ለማድረግ እንደሚሰሩም ተናግረዋል።

በጋዛ የሰላም እቅድ ትግበራ ወታደሮችን ከማሰማራት ጀምሮ ገለልተኛ የሰላም ቦርድ ለማቋቋም እና የፍልስጤምን መንግስት ለመመስረት በጋራ ለመስራት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በኳታር ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል ታኒ፣ የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እና የግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ ኤል ሲሲ የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል።

ከ20 ሀገራት በላይ የተሳተፉበት በግብፅ ሻርም አል ሼክ የተካሄደው አለም አቀፍ ስብሰባ በጋዛ ሰርጥ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት በሐማስ እና እስራኤል ላይ ጫና በማሳደር ወሳኝ የሚባለውን እርምጃ ማሳለፋቸውን ሀገራቱ በጋራ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።




Donald J. Trump
Recep Tayyip Erdoğan
AM ኤኤም ወርልድ

Peace deal finally signed and sealed in the middle of east. Finally, peace had been restored...It's the person that make...
13/10/2025

Peace deal finally signed and sealed in the middle of east. Finally, peace had been restored...

It's the person that makes the fire that knows the secret to quench 🧯🧯 it.... Donald Trump thank you for putting off the fire earlier ignoted
Donald J. Trump
Benjamin Netanyahu - בנימין נתניהו
Recep Tayyip Erdoğan
Emmanuel Macron
AM ኤኤም ወርልድ

Address

Addis Abeba
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AM ኤኤም ወርልድ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share