Sbahe Tube

Sbahe Tube Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sbahe Tube, Digital creator, Addis Ababa.

23/10/2025

ውድ ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ
ቴሌግራም ላይ አንድ ድንቅና ብርቅ የሆነ ትምህርት በቅርቡ ሊጀመር ነው፡
(ግሩም ግእዝ)ይላል የቴሌግራም ስያሜው ኑና ተቀላቀሉ‼️

እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የአባታችን አቡነ አረጋዊ ምልጃና ጸሎት አይለየን !!!
23/10/2025

እንኳን ለጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
የአባታችን አቡነ አረጋዊ ምልጃና ጸሎት አይለየን !!!

💚💛❤️መንፈሳዊ ሰው ማን ነው??

--  ✝️-----ኦ ሚካኤል ------✝️----፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨‟ቀዊሚየ ቅድመ ሥዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ፡በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዓኒ ቃለ።”‟ሚካኤል ሆይ ...
22/10/2025

-- ✝️-----ኦ ሚካኤል ------✝️----
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
‟ቀዊሚየ ቅድመ ሥዕልከ ሶበ አወትር ስዒለ፡በብሂለ ኦሆ ፍጡነ አስምዓኒ ቃለ።”

‟ሚካኤል ሆይ በሥዕልህ ፊት ቆሜ ልመናዬን በማቀርብበት ጊዜ ሁሉ አለሁልህ አይዞህ በማለት ፈጥነህ ድምፅህን አሰማኝ።”

◉በያላችሁበት ሥፍራ የሚካኤል ጥበቃ አይለያችሁ

✝️ ርቱዕ ተስፋ(እውነተኛ ተስፋ)✝️በመ/ር ገብረ መድኀን እንየው፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨✍️አንድ ሰው የሚኖረው በሚያምነው ልክ ነው።ጽድቅ ወይም ኀጢአት እንደሆነ በ...
21/10/2025

✝️ ርቱዕ ተስፋ(እውነተኛ ተስፋ)✝️
በመ/ር ገብረ መድኀን እንየው
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
✍️አንድ ሰው የሚኖረው በሚያምነው ልክ ነው።
ጽድቅ ወይም ኀጢአት እንደሆነ በሚረዳው ልክ ተግባራዊነቱ ይገለጣል።
✍️በእውነት እና በሀሰት መካከል ሦስተኛ ማዕከላዊ ሀሳብም ዓለምም የለም።
ከእውነት ከወጡ ሀሰት ነው።ከሀሰት ከተለዩም እውነት ነው።
በጽድቅና በኃጢአት መካከል ያለ ማዕከላዊ ሦስተኛ ሰውና ሦስተኛ ቦታ የለም።
(ኢዘከረ መጽሐፍ ሠለስተ ዓለማተ አላ ክልኤተ)
✍️ለርቱዓዊ ሰው ውስጣዊ የተስፋ መርኁ በተስፋ ወንጌል የተሞላ ውስጣዊ የመረዳት አስተሳስብ ነው።
እንደ ክርስትና ያ አስተሳስብ ኦርቶዶክሳዊ የተስፋ ማያና የተገለጠ የመስቀል እውነት ነው።
✍️ኦርቶዶክሳዊ ማያ ስለሁሉም ነገር የሚወስን የመገለጥ ሕግ እና ጠባይዓዊ ህሊና የተባበሩበት ግብር ነው፡፡
ያ አስተሳስብ በተፈጥሮተ ሰብእናችን ላይ የከሥቶ ሃይማኖት በዚያ ላይ በነጻ ፈቃድ ውሳኔን ብይነን የምንመላለስበት የአስተሳስብ በሀል ወይም ኑሮ ነው።
✍️ኦርቶዶክሳዊ የመዳን ሕይወት የማገኘው ከዚህ ርቱዕ እሳቤ በመነሣት ነው።
✍️የርቱዓዊ ሰው የአኗኗር ዘይቤውና የትሩፋት ሥውርት እና የትሩፋት አፍአዊ መገለጫው ሁል ጊዜም የፈጠረውን እግዚአብሔር ማዕከል ያደረገ ነው።
✍️ከልደቱ እስከሞቱ ድረስ እንደ ሰገኖ በትሩፋት ሥውርትና በትሩፋት አፍአዊ የፈጠረውን እየተመለከተ የሚኖር ስለሆነ ተስፋው የተጠበቀ ነው።
ሰውን የምናውቀው የተገለጠውን እና ከፊላዊውን ነው።ሙሉ በሙሉ ገሐዳዊ የሚሆነው በአምላኩ ፊት ነውና።
✍️ከሂደታዊ ዓለም ላይ ያለ ሰው ከዋናው ምዕራግ ለባሴ ክርስቶስነት ሕይወት፤ከመስቀል መሠዊያ ላይ የሚወርድ እና የሚለይ ውስጣዊም ሆነ አፍአዊ ግብር የለውም።ያለዚያ ግን ርቱዓዊ ክርስቶሳዊ መንገዱን መሳቱ ነው።
✍️ፍጥረታት በስበት ምግብና ይኖራሉ እንዲሉ ርቱዓዊ ሰውም መስቀሉን የሕይወቱ ምግብናዊ ስበት ማዕከል ያደረገ የሕይወት ዑደት ያስፈልገዋል።አርአያ ክርስቶስን ስቶ ከመሥዋዕቱና ከመሠዊያው ሲለይ ከመንፈስ በድን ይሆናል።
✍️ጨረቃ በብድር ብርሃን እንድትኖር ሰውም የሕይወት ብርሃኑን የሚያገነው ሰጪ ከሆነው ከእግዚአብሔር ነው፡፡
✍️ርቱዓዊ ሰው በማይለወጥ በተገለጠ የትምህርት ፍጻሜ በአዝማነ መንግሥተ ሰማያት የማይለወጥ ሰማያዊ የሕይወት ፍጽምና የተገባው ክቡር ፍጥረት ነው፡፡
✍️ከእግዚአብሔር የተገለጠውን እውነት የሚማረውና የተማረው በተፈጥሮ ማዕከላዊ የሆነ ርቱዕ ልቡን ጠባይዓዊ ሀብቱን ሊያቀናበት ነው።
✍️በልቡ እምነቱ የተሣለ ይሆናል።በርቱዕ እምኑቱ ሲኖር ሰውየው በርቱዓዊ የሕይወት ግብር አድርጎ በለባሴ ክርስቶስነት ግብር መገለጡ የጸና ይሆናል።
✍️ርቱዓዊ ሰው በዚህ ዓለም የሚኖረውም እንደ ሐዋርያዊ ቀኖናው በቀኖና ሕይወት ነው ወይም በሕይወታዊ ቀኖና ነው።የኦርቶዶክሳዊነት አኗኗር በቀኖናዊነት የተቃኘ ነው እንጂ መርህ የለሽ አይደለምና።
✍️የርቱዕነት አስኳሉ፣የሀሳብ ልዕልናው የሚገኘው የእግዚአብሔር ለቅዱሳን መገለጥ እና የጉባኤ ቤተ ክርስቲያን ጉባኤያዊ ርቱዓዊነት ነው።
✍️ስለዚህ ሁል ጊዜም ከዋናው የጸጋ ምንጭ ዘንድ በሃይማኖት እና በኅብረት ተስቦ ሂዶ ማሰብና መዋሐድ አለበት።
✍️የእምነቱ ምሥጢር የተገለጠ ነገረ መለኮቱም የተመስጦ ትምህርት ሲሆን የሚፈጸም ተስፋ ያለው በሂደት የሚሆን የቃል ሕይወት ነው እንጂ ተራ የቃላት አጠቃቅስ አይደለም።
✍️ሁልጊዜም ያለ ተመትሮ እየተማርህ ወደተገለጠው የትምህርት ባለቤት በጸጋ ልምምድ በሂደታዊ ገድል መገሥገስ ሲኖር ከሰሚ ርቱዕነት ወደ ተከሥቶ ርቱዕነት መድረስ ይገኛል።
✍️በቁርጥ ህሊና በትሁት ሰብእና ለመሄድ የውስጥ መነካት የውስጥ ፍቅር የውስጥ ተስፋ ያስፈልገዋል።እንዲያ ሲሆን ተመስጦውም ተስፋውም ፍጹም ይሆናል።
✍️የርቱዓዊ ሰው የእምነት መነሻው ቢታወቅም የጸጋ መድረሻው ወሰን የለውም። ከእግዚአብሔር የሚሆነው ሁሉ በሥጋዊ በደማዊ ፍጥረት ህሊና ይታመናል እንጂ በድርስ መረዳት ጨርሶ አይታወቅምና።
✍️ኦርቶዶክሳዊነት በዚህ ዓለም በክርስቶስ አርአያነት እስከ ፍጻሜ መስቀል የሚሄዱበት ርቱዕ ጎዳና ሲሆን የተስፋ ሕይወቱ ዘኢየሐልቅ ነው።እግዚአብሔር ዘአልቦ መዋዕል(ዘመን የለሽ)እንደሆነ ሁሉ ተስፋው የጸና ኦርቶዶክሳዊ ሰውም ከትንሣኤው በኋላ ዘአልቦ መዋዕል(ዘመን የለሽ) ነው።
✍️ርቱዓዊ ኦርቶዶክሳዊነትን በማወቅ በመዝለቅ ጨረስሁት የሚል ሰው በፍጹም የለም።ኦርቶዶክሳዊነት ለዘለዓለማዊነት የሚኖር እንጂ የሚፈጸም አይደለምና።
✍️በምሳሌ ሲገለጽ ከግብር ቅዳሴ እስከ ዕትው ያለው ነው። ዕትው ከተባለ በኋላ መልስ የለውም።በሰላም በሃይማኖት በፍቅር አንድነት ወደ ቤታችሁ ወደ መንግሥተ ሰማያት ግቡ ማለት ነውና።መንግሥተ ሰማያት ከገቡ መውጣት ካገኙ ማጣት የለባታም።
✍️ንዑ ኀቤየ-እናንተ የአባቴ ቡሩካን ኑ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ።"ሜቴ.፳፭፥፴፬ የሚለው ቃል እስከ የት ድረስ ነው?ቢባል
መልሱ ከትንሣኤ በኋላ ከእግዚአብሔር ጋራ መኖር ፍጻሜ የለውም የሚል ነው።
✍️የቃልና የሥጋ የባሕርይ ተዋሕዶ ለዘለዓለሙ የጸና እንደሆነ ከትንሣኤ ሙታን በኋላ የምእመን እና የሙሽራዋ የክርስቶስ የጸጋ ተዋሕዶም ለዘለዓሙ የጸና ነው።፪.ቆሮ.፲፩፥፪
✍️ንጹሓት የሚሆኑ የእግዚአብሔር የባሕርይ መገለጫዎቹን በጸጋ ገንዘብ ያደረጉ ቅዱሳን ሁሉ እርሱን በመምሰል ይገለጻሉ።
አሚንን፣ጽድቅን፣ፍቅርን፣ቅድስናን፣ሕያውነትን፣ንጹሕ ዕውቀትን፣ቸርነትን፣ሂሩትን፣ፍጹምነትን..በዘለዓለማዊነት ገንዘብ ያደርጋሉ።እግዚአብሔር ወሰን እንደሌለው ማደሪያው ምእመንም በአሁናዊነት አትበየንም።ለዘለዓለማዊነቷም ፍጻሜ የለውም።
✍️ለሕይወት የተጠራነው ወደዚህ ቅዱስ የሕይወት አዳራሽ ነው።ከዚህ ቤት ሁሉ አለ፣ሙሽራው ክርስቶስ አለ፣አዕላፍ መላእክት አሉ፣በጸጋው የከበሩ ነቢያት እና ሐዋርያት አሉ፣በሕይወታቸው የመሰከሩ ሰማዕታት እና ሰማዕታተ ትሩፋት መነኮሳት አሉ።ንጹሓን መሃይምናን እና ርቱዓነ ሃይማኖት ሊቃውንት አሉ፣የማይፈጸም ጸጋ አለ፣ሁሉም በዘለዓለማዊነት የተዋጠ ነው።
✍️"ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፤ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፤ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፤በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፤ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፤ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች ደርሳችኋል።"ዕብ.፲፪፥፳፪-፳፬እን.
✍️እንዲህ ያለ የጸና ተስፋ የሌለበት ሥራና የሕይወት እስትንፋስ የሌለው በድን አንድ ነው።
አማኝነት እንዲህ ያለ ተስፋና አስተሳስብ ከሌለው ባዶውን የወረቀት ጥቅስ በድን ነው። ሕያው የሚሆነው በፍቅረ ክርስቶስ ክንውን ውስጥ በኅበረታዊት ቤተ ክርስቲያን አንድነት የሚሠራ በተስፋው የጸና አካል ካለው ነው።
✍️የተስፋ ልብና የሕይወት መንፈስ የሌላቸው አካላት የተስፋ ልብና የሕይወት መንፈስ ካላቸው አካላት ጋራ በኅብረታዊነት ለመገናዘብ ይከብዳቸዋል።
ሆድና አፍ የሥጋ ፈቃድ ማስቀጠያዎች ናቸው እንጂ ከተስፋ ልብና ከሕይወት መንፈስ ጋራ ርቀታቸው ሀ እና ፐ ናቸው።
በጽኑ ዘለዓለማዊ ተስፋ ላይ መቀለድ ግን ራስ ጠልነት ነው።

#ሼር

✝️‟ ”✝️=============================የኪዳን ሦስተኛ ምዕራፍ ነው።ይኽ ክፍል ስለ አብ የሚናገር ክፍል ነው። ታድያ በዚኽ ክፍል እንዲህ የሚል ቃል አለ።◉‟ ” በልጅህ ሞት...
19/10/2025

✝️‟ ”✝️
=============================
የኪዳን ሦስተኛ ምዕራፍ ነው።ይኽ ክፍል ስለ አብ የሚናገር ክፍል ነው። ታድያ በዚኽ ክፍል እንዲህ የሚል ቃል አለ።
◉‟ ” በልጅህ ሞት ዓለምን ያዳንህ።ምንም እንኳ ዓለምን የማዳን ሥራ የአብ ፈቃድ፡የራሱ የወልድ ፈቃድ ፣እንዲሁም የመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ቢሆንም ውረድ ተወለድ፡ተሰቀል፣ሙት ብሎ የላከው አብ ነውና ስለ አብ ይናገራል።

◉. ” አለ.ምክረ ከይሲ ሰምቶ ሕግን በመተላለፍ ከዘጠና ዘጠኙ ነገደ መላእክት ኅብረት ተለይቶ የነበረ አዳምን በልጅህ ህልው ሁነህ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር የፈለግኽ አንተን አብን እኛ አገልጋዮችህ እናመሰግንሃለን ሕዝቡም ሁሉ አንተን ያመሰግንሃል።

◉.ያጠፋ የጠፋ አዳምን እስከ ሞት የፈለገ አምላክ በግብረ ዓለም ተውጠን ለጠፋን ለእኛም መንፈሱን ልኮ ከጠፋንበት ሥፍራ ይመልሰን አሜን።

◉.ሠናይ ዕለተ ሰንበት!!!!!!

ሼር ‼️

✝️ዛሬ በጥያቄ መጣሁባችሁ✝️፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨⛪⛪⛪፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፩.ቅድስት ቤተክርስቲያንን ⛪ ስንቶቻችን በውል እናውቃታለን?፪.የምናውቃት በአሻጋሪ ወይስ በቅርበት?፫.ስንቶቻችን ለሕጓ...
18/10/2025

✝️ዛሬ በጥያቄ መጣሁባችሁ✝️
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨⛪⛪⛪፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
፩.ቅድስት ቤተክርስቲያንን ⛪ ስንቶቻችን በውል እናውቃታለን?
፪.የምናውቃት በአሻጋሪ ወይስ በቅርበት?
፫.ስንቶቻችን ለሕጓና ለሥርዓቷ ታዛዦች ነን?

NB◉.ሐሳባችሁን በጨዋ ደንብ ግልጽ በሆነ ማብራሪያ መልሱ።
◉በንቃት የምትሳተፉ ከሆነ ጥያቄው ቀጣይነት ይኖረዋል።
◉.እግዚአብሔር ቢፈቅድ እየገባንም እንማማራለን!!!

 YouTube ላይ ያገኙታል!!  Visit the Link ‼️
18/10/2025

YouTube ላይ ያገኙታል!!
Visit the Link ‼️

የቅዳሜ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ

❝ሐዘን ብየ አምጣነ በዝኃ  ሥላሴ ዘዮም ወዘአሜሃበጽባሕ ኀቡኒ ፍስሐ።❞‟የመከራው ሌሊት በኔ ላይ በዝቶ ሐዘን በጸናብኝ ጊዜየትላንቱን መከራ የምታሳልፉ፣ዛሬም ለሚመጣውም የምትጠብቁ የማታንቀላ...
17/10/2025

❝ሐዘን ብየ አምጣነ በዝኃ
ሥላሴ ዘዮም ወዘአሜሃ
በጽባሕ ኀቡኒ ፍስሐ።❞

‟የመከራው ሌሊት በኔ ላይ በዝቶ ሐዘን በጸናብኝ ጊዜ
የትላንቱን መከራ የምታሳልፉ፣ዛሬም ለሚመጣውም የምትጠብቁ የማታንቀላፉ ሥሉስ ቅዱስ ሆይ የመከራው ሌሊት አሳጥራችሁ በማለዳ ደስታን ስጡኝ።”

የቅድስት ሥላሴ በረከት በቤታችሁ ይደር!!!!

🦅.ለተሳትፎ ስለምን ቅድስት ተብለው ይጠራሉ????

«ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለትመዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙሕ ትዕግሥት ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኲሉ ሰዓትእንበለ ንስሐ ኪያነ እይንሥአነ ሞት።» ◉ቅድስት ቤተክርስቲያ...
16/10/2025

«ሰላም ለክሙ ጻድቃን ወሰማዕት
እለ አዕረፍክሙ በዛቲ ዕለት
መዋዕያነ ዓለም አንትሙ በብዙሕ ትዕግሥት
ሰአሉ ቅድመ ፈጣሪ በኲሉ ሰዓት
እንበለ ንስሐ ኪያነ እይንሥአነ ሞት።»

◉ቅድስት ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ ዘወትር ከማታስታጉለው ልመና አንዱ፡በቅዳሴ መጨረሻ ወይም ከእግዚኦታ በኋላ ወይም ድርገት ከመውረዱ በፊት የምትጸልየው ጸሎት ነው።❝በብዙ ትዕግሥት ይኽንን ዓለም ድል ነስታችሁ፡አረፍተ ዘመን ገድቧችሁ በዚች ዕለት ከኃላፊው ዓለም ወደ ማያልፈው ዘለዓለማዊ ሕይወት የተሸጋገራችሁ፡ቅዱሳን ሆይ በአጸደ ሥጋ ላለን ለኛ በንስሐ ሳንመለስ በሞት እንዳንወሰድ በመልካም መመለስ እንድንመለስ ከባሕረ ምሕረት አምላክ ዘንድ ዘወትር ለምኑልን እያለች ዕለት ዕለት ትማጸናለች።❞

◉.የቤተክርስቲያን መሪዋ ክርስቶስ ነው፣ሠሪዋም ክርስቶስ ነው፣የልመናዋም መዳረሻ ክርስቶስ ነው።ስለሆነም አስቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ አድሮ፦

«በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ የማይጠፋም የዘለዓለም ስም እሰጣቸዋለሁ።»ኢሳ.፶፮÷፭ ብሎ እንደተናገረ ቤተክርስቲያንም መታሰቢያቸውን ታደርጋለች፡ በስማቸውም ትማጸናለች።

◉.የቅዱሳኑ ምልጃና በረከት አይለየን!!!

🔴visit my YouTube channel‼️
16/10/2025

🔴visit my YouTube channel‼️

Ethiopian Orthodox Tewahdo song_Amlak atitewen of kinetibeb

አጋንንት የሚለማመዱት ጸሎት አለ🤔
15/10/2025

አጋንንት የሚለማመዱት ጸሎት አለ🤔

🔴በእንተ ጸሎት| በሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮነ መልአክ|2025

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sbahe Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Sbahe Tube:

Share