ዘሀገረ ኢትዮጵያ

  • Home
  • ዘሀገረ ኢትዮጵያ

ዘሀገረ ኢትዮጵያ ወቅታዊ እና ፈጣን መረጃዎች፣
የመዝናኛ እና ስፖርታዊ ዜናዎች፣
የምሁራን እይታዎች እና መፅሀፍቶች፣
ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ!!

ተሻሻለ ተብሎ ወዲያው ግን ወደባሰ ሁኔታ ውስጥ የገባው የሀዋሳ የቤንዚን እጥረት (መሠረት ሚድያ)- በሀዋሳ ከተማ ቤንዚን ከጠፋ በርካታ ሳምንታት ማስቆጠሩ ይታወቃል፣ ይሁንና ከሰሞኑ መስተካከ...
26/12/2024

ተሻሻለ ተብሎ ወዲያው ግን ወደባሰ ሁኔታ ውስጥ የገባው የሀዋሳ የቤንዚን እጥረት

(መሠረት ሚድያ)- በሀዋሳ ከተማ ቤንዚን ከጠፋ በርካታ ሳምንታት ማስቆጠሩ ይታወቃል፣ ይሁንና ከሰሞኑ መስተካከል እንዳሳየ ተዘግቦ ነበር።

ከሰሞኑ ደግሞ ችግሮ ተመልሶ ወደነበረበት ብቻ ሳይሆን ወደባሰ ሆኔታ ውስጥ መግባቱን መሠረት ሚድያ ሰምቷል።

"ቤንዚን ለመቅዳት ህዝቡ ከሌሊቱ 10:30 ጀምሮ ነው የሚሰለፈው፣ ነገር ግን ተሰልፎም የማይቀዳበት ሁኔታዎች በብዙ ይስተዋላሉ" የሚሉት ለሚድያችን ጥቆማቸውን የሰጡት ነዋሪዎች የከተማው የመንግስት ቢሮዎች እና አመራሮች አሁንም ከማደያዎችና ከጥቂት ግለሰቦች ጋር የጥቅም ጉዳይ መኖሩን የሚያሳዩ ነገሮች አሉ ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀዋሳ የተሰራውን የኮሪደር ልማት ለማስመረቅ ይመጣሉ ተብሎ በዕለቱ ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ቤንዚን ለመቅዳት የተሰለፉ ሰዎችን ጠዋት 4:00 ሰዓት አካባቢ ፖሊስ "ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ስለሚመጣ ተበተኑ" ብሎ በፈጠረው ግብግብ ሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል ብለዋል።

"ፖሊስ ወጣቶችን በፓትሮል ሲበትን በጠዋት ተነስተው በራቸው ላይ ስፖርት እየሰሩ የነበሩ ልጆች ተገጭተዋል፣ ከባድ የሚባል የአካል ጉዳትም የደረሰባቸው አሉ" ያሉት ነዋሪዎች ጉዳዩ ከምሬትም በላይ እንደሆነባቸው ይናገራሉ።

የከተማ አስተዳደሩ ንግድና ኢንዱስትሪ ቢሮ ነዳጅ የሚቀዳባቸውን ማደያዎችና ምደባ በቴሌግራም ቻናል ያሳውቃል።

"ቤንዚን ለመቅዳት ሁሉም ከለሊት 10:00 ጀምሮ በየማደያው ይሰለፋል፣ ግን ቴሌግራም ላይ ሲለቀቅ ሁሉም ቤንዚን ወደአለበት ወደ ተመደበበት ማደያ በሚያደርገው እሽቅድድም ባጃጆች እተገለበጡ እየተጋጩ ነው፣ ሰው ከሞተር ላይ እየወደቀ እየተጎዳ ነው የቤት መኪኖች እተጋጩ ነው" ብለው ምሬታቸውን አቅርበዋል።

"በዛ ላይ በሌሊት 10:00 ሰዓት ላይ ወጥተህ በግምት ማደያ አካባቢ ስትቆም 'አስፓልቱን ልቀቅ' ተብለህ በፖሊስ ትደበደባለህ፣ በዛ ብርድ በዱላ ነው የሚመቱህ። በሀዋሳ ከተማ ከቤንዚን ጋር ተያይዞ ያለው ጉዳይ በጣም አስቸጋሪ ነው" በማለት ሁኔታውን ለመሠረት ሚድያ አስረድተዋል።

መረጃን ከመሠረት!

11/12/2024
ሐዋሳ የሚገኘው የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦትና አገልግሎት መድኃኒት በድሮን ለማድረስ ሙከራ አደረገየኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦትና አገልግሎት ሐዋሳ ቅርንጫፍ አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ በማዘመን ...
11/12/2024

ሐዋሳ የሚገኘው የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦትና አገልግሎት መድኃኒት በድሮን ለማድረስ ሙከራ አደረገ

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅርቦትና አገልግሎት ሐዋሳ ቅርንጫፍ አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ በማዘመን ኢመርጀንሲ የሆኑ እና አንዳንድ የመንገድ ችግር በሚስተዋልበት ወቅት ለጤና ተቋማት ክትባቶችን ማድረስ የሚያስችል የድሮን አገልግሎት ሙከራ በተሳካ ሁኔታ እያደረገ ይገኛል።

ድሮኗ በዋናነት ክትባቶችን የምታጓጉዝ ሲሆን ከ15 ደቂቃ ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በተፈለገው ስፍራ አድርሳ ትመለሳለች። በቀጣይ ከፍተኛ ክብደት ያለው በርካታ ክትባቶችን የሚያደርስ ድሮን ለማቅረብም በዝግጅት ላይ ይገኛል።

ለዚህ ትልቅ ተግባር የሚተጉ የድርጅት መስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊዎችና የሐዋሳ ከተማ መድኃኒት አቅርቦትና አገልግሎት ዋና ኃላፊ የሆኑት አቶ ዘመን ለገሰ ሊመሰገኑ ይገባል።

Via: ኤፍሬም

ሲዳማ ክልል ሐዋሳ ከተማን ጨምሮ በሰባት ወረዳዎች ላይ የወባ በሽታ መከሰቱ ተገለጸበሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማን ጨምሮ በሰባት ወረዳዎች ላይ የወባ በሽታ መከሰቱን የክልሉ የሕብረተሰብ ጤና ኢን...
06/11/2024

ሲዳማ ክልል ሐዋሳ ከተማን ጨምሮ በሰባት ወረዳዎች ላይ የወባ በሽታ መከሰቱ ተገለጸ

በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማን ጨምሮ በሰባት ወረዳዎች ላይ የወባ በሽታ መከሰቱን የክልሉ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቋል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዳመነ ደባልቄ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የወባ በሽታ ያለባቸውን ሰዎች ልየታ በማድረግ እና ወደ ጤና ተቋም እንዲሄዱ በማድረግ አስፈላጊውን ሕክምና እንዲያገኙ እየተደረገ ነው።

የመከላከያ ኬሚካል በሀገር ውስጥ መመረት በመቆሙ ምክንያት እጥረት መኖሩን ገልጸው በአራት ወረዳዎች ላይ ርጭት ተደርጓል ብለዋል። ተጨማሪ ኬሚካል እና አጎበሮች እንዲላክ ለጤና ሚኒስቴር ጥያቄ መቅረቡን አክለው ገልጸዋል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት አዲስ ባወጣው ሪፖርት እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ ከታህሳስ 23፣ 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ከ7.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ በሽታ መጠቃታቸውን እና ከእነዚህም መካከል 1,157 ሰዎች መሞታቸውን ገልጿል።

እንደ ዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ከሆነ ወባ አሁንም አሳሳቢ የጤና ስጋት ሲሆን 75 በመቶ የሚሆነው የአገሪቱ መሬት እና 69 በመቶ የሚሆነው በነዚህ አከባቢዎች የሚኖረው ህዝብ በተለይም ህጻናት ለከፍተኛ አደጋ ተጋላጭ መሆናቸውን ጠቁሟል።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዘሀገረ ኢትዮጵያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ዘሀገረ ኢትዮጵያ:

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share