
08/08/2025
በኬንያ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ።
JMN Amharic ነሃሴ 02/2017 ዓ.ም።
በኬንያ ዋና ከተማ ከሚገኘው ናይሮቢ አውሮፕላን ማረፍያ ተነስቶ ወደ ሶማሌላንድ ሲጓዝ የነበረው አነስተኛ አውሮፕላን ከዋና ከተማዋ ወጣ ብሎ በሚገኘው ኪምቡ ግዛት መከስከሱ የተገለጸ ሲሆን በአደጋውም የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።
በሰዎች መኖርያ አካባቢ የተከሰከሰው ይህ አነስተኛ አውሮፕላን የአየር ላይ አምቡላንስ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ባለቤትነቱም አምረፍ ፍላዪንግ ዶክተርስ የተሰኘ የህክምና ተቋም እንደሆነ ተገልጿል።
የህክምና ተቋሙ የደረሰውን አደጋ ይፋ ሲያደርግ በአደጋው የደረሱ ጉዳቶችን እንዲሁም የአደጋውን ምክንያት ምን እንደሆነ ባይገልጽም የኬንያ ቀይ መስቀል በአደጋው የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን አስታውቋል።
አደጋው የተከሰተው በኬንያ እና ሶማሌላንድ ድንበር አካባቢ መሆኑን ተከትሎ የአገሪቱ ወታደሮች እና ፖሊሶች በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን ከተቋሙ እንዲሁም ከኬንያ መንግስት በኩል ስለጉዳዩ በዝርዝር የተባለ ነገር አለመኖሩን አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል።