JMN Amharic

JMN Amharic አዳዲስ ወጎች ይቀርቡበታል
(2)

ኢሬቻ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው ገዳ ስርዓት አንዱ እሴት የሆነው ኢሬቻ የሰላምና የምስጋና በዓል ነው።በዓሉ የ...
01/10/2025

ኢሬቻ በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው ገዳ ስርዓት አንዱ እሴት የሆነው ኢሬቻ የሰላምና የምስጋና በዓል ነው።

በዓሉ የኦሮሞ ህዝብ ለፈጣሪ ምስጋና የሚያቀርብበትና የሚፈልገውን ፈጣሪ እንዲፈጽምለት የሚጠይቅበት ነው:: ኢሬቻ በሁለት የተለያዩ ጊዜ እና ስፍራ ይከበራል። አንዱ ኢሬቻ መልካ ሲሆን፤ ሌላኛው ደግሞ ኢሬቻ ቱሉ ነው።

የጭለማ፣ ጭጋጋማ እና ከባዱ የክረምት ወቅት አልፎ ወንዞች ጎድለው የውሃ ሙላት ካለፈ በኋላ መሬቱ ጠገግ ሲል የሚከበረው ኢሬቻ መልካ ክረምት እና የውሃ ሙላት የለያያቸው ሰዎች መገናኘት የሚጀምሩበት ነው፡፡

ክረምቱን በእርሻ ስራ የደከመ ሰው የሚያርፍበት እና የላቡን ተስፋ በሰብሉ ማበብ ማየት በሚጀምርበት ወቅት የሚከበረው ኢሬቻ መልካ በመስከረም ወር መጨረሻ ውሃ በሚገኝበት ስፍራ ሲከበር ለፈጣሪ ምስጋና ይቀርባል።

ኢሬቻ ቱሉ ዝናብ ሲርቅ፣ ወንዞች ሲደርቁ፣ መሬት ለከብቶች ሳር ስትነሳ፣ ድርቅ እና ረሃብ በሰውና በእንስሳት ላይ ሲያይል ዝናብ እንዲጥል ወደ ተራራ በመውጣት ለፈጣሪ ልመና የሚቀርብበት ነው።

"ኢሬቻ በተፈጥሮ ምስጢር ሰዎችን የሚያስታርቅ ፈጣሪ እና ፍጡርን የሚያቀራርብ ነው"  ሲሉ ኃይሉ አዱኛ ገለፁ።JMN Amharic መስከረም 20/2018 ዓ.ም።45ኛው የጉሚ በለል የውይይት መድ...
30/09/2025

"ኢሬቻ በተፈጥሮ ምስጢር ሰዎችን የሚያስታርቅ ፈጣሪ እና ፍጡርን የሚያቀራርብ ነው" ሲሉ ኃይሉ አዱኛ ገለፁ።

JMN Amharic መስከረም 20/2018 ዓ.ም።

45ኛው የጉሚ በለል የውይይት መድረክ ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት በሚል መሪ ሀሳብ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ጽፈት ቤት እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኦሮሚያ ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ኢሬቻ የኦሮሞ ህዝብ ላለፈው አምላኩን የሚያመስግነበት፣ ለመጪው የሚለምንበት እና ተስፋ የሚያደርግበት የምስጋና በዓል ነው ብለዋል።

ኢሬቻ በማህበረሰቦች መካከል ሰላም እና አንድነትን በመፍጠሩ ረገድ ያለው አስተዋጽኦ የጎላ መሆኑ ተገልጿል።

በዓሉ የኦሮሞ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ብሔር ብሔረብ፣ ለሁሉም ቋንቋ ተናጋሪ እና ለሁሉም ሀይማኖቶች ክፍት የሆነ የምስጋና በዓል መሆኑ ተመላክቷል።

በተጨማሪም ኢሬቻ ማህበረሰቡ ከተፈጥሮ ጋር ያለውን ጥብቅ ቁርኝት የሚያሳይ ነው ተብሏል።

የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል በሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥረት በራስ ሀብት የተገነባው የህዳሴው ግድብ ምርቃት ሰሞን መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው ተነስቷል።

የ2018 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል በመጪው ቅዳሜ እና አሁድ እንደሚከበር ይታወቃል።

የሽንት ቤት ወረቀት ለማግኘት ማስታወቂያ መመልከት ግዴታ ሆነ።JMN Amharic መስከረም 20/2018 ዓ.ም።በቻይና አንዳንድ የሕዝብ መጸዳጃ ቤቶች፣ የሽንት ቤት ወረቀትን ለመስጠት ቅድመ ሁ...
30/09/2025

የሽንት ቤት ወረቀት ለማግኘት ማስታወቂያ መመልከት ግዴታ ሆነ።

JMN Amharic መስከረም 20/2018 ዓ.ም።

በቻይና አንዳንድ የሕዝብ መጸዳጃ ቤቶች፣ የሽንት ቤት ወረቀትን ለመስጠት ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠ አዲስ ሥርዓት መዘርጋታቸው ዓለም አቀፍ ትኩረት አግኝቷል። ይህ ሥርዓት ተጠቃሚዎች ወረቀቱን ከማግኘታቸው በፊት አጭር የማስታወቂያ ቪዲዮ እንዲመለከቱ ያስገድዳል።

ይህ አሰራር በዋነኛነት የተጀመረው የወረቀት ብክነትን ለመቀነስ እና አንዳንድ ጎብኚዎች ከመጠን በላይ ወረቀት በመውሰድ የሚያስከትሉትን ስርቆትና ወጪ ለመግታት ነው። ኃላፊዎች፣ ሥርዓቱ ሀብት በማዳን ረገድ ውጤታማ መሆኑን ይገልጻሉ።

ተጠቃሚዎች ወረቀት የሚሰጠውን ማሽን ለመጠቀም መጀመሪያ QR ኮድ በስማርት ስልካቸው ይቃኛሉ። ኮዱ ከተቃኘ በኋላ፣ ማሽኑ የሽንት ቤት ወረቀቱን ከመልቀቁ በፊት አጭር የማስታወቂያ ቪዲዮ በስልኩ ላይ ያሳያል። ተጠቃሚዎች ማስታወቂያውን መመልከት ካልፈለጉ፣ አብዛኛውን ጊዜ ትንሽ ገንዘብ በመክፈል ወረቀቱን ማግኘት ይችላሉ።

ይህ አሰራር ሀብትን ከማዳን አኳያ ጠቃሚ ቢሆንም፣ የዜጎችን ምቾት እና ግላዊነት በሚመለከት ከፍተኛ ውዝግብ ፈጥሯል። ተቃዋሚዎች እንደ ግላዊ ንፅህና ያሉ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ከማስታወቂያ ንግድ ጋር ማያያዙ ያልተለመደ እና አንዳንዶች እጅግ በጣም የከፋ ማኅበራዊ ሥርዓት ሲሉ እየተቹት ነው። በተለይ ስልካቸው ኃይል የጨረሰባቸው ወይም ኢንተርኔት የሌላቸው ሰዎች ለአስቸጋሪ ሁኔታ ሊዳረጉ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

ይህ የቻይናው የቴክኖሎጂ ሙከራ የዕለት ተዕለት ሕይወት መሠረታዊ ገጽታዎችን እንዴት በንግድ እና በቁጥጥር ማዕቀፍ ውስጥ ማዋል እንደሚቻል የሚያሳይ አስገራሚ ምሳሌ ሆኗል።

የኦሮሞ ጥናት ማህበር በፊንፊኔ ጠቅላላ ጉባኤ እያካሄደ ነው።JMN፣ ፊንፊኔ (መስከረም 18፣2018)የኦሮሞ ጥናት ማህበር (ORA)  ከሶስት አመት በፊት መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ.ም በ3...
28/09/2025

የኦሮሞ ጥናት ማህበር በፊንፊኔ ጠቅላላ ጉባኤ እያካሄደ ነው።

JMN፣ ፊንፊኔ (መስከረም 18፣2018)

የኦሮሞ ጥናት ማህበር (ORA) ከሶስት አመት በፊት መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ.ም በ33 አባላት የተመሠረተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በርካታ አባላትን እያፈራ በኦሮሞ ምርምር ስራዎች ላይ እየሰራ ይገኛል።

ማህበሩ በዛሬው እለት ፊንፊኔ በ Ilili ኢንተርናሽናል ሆቴል ጠቅላላ ጉባኤውን እያደረገ ይገኛል።

እየተካሄደ ባለው ጣቅላላ ጉባኤ ላይ በማህበሩ የታተሙ 4 መጽሃፍትም እንደሚመረቁ ተገልጿል።

ዘገባ፦ ኤቢሳ ጅሩ

ሖራ ፊንፊኔ የኦሮሞ ሕዝብ ከ150 ዓመታት በፊት የኢሬቻ (የምስጋና) ሥነ-ሥርዓትን የሚያከናውንበት ሐይቅ/ምንጭ ነው። ፊንፊኔ የዚህ ምንጭ ስም ሲሆን፣ ይህ ምንጭ አሁን "ፊልውሃ" ተብሎ በሚ...
26/09/2025

ሖራ ፊንፊኔ የኦሮሞ ሕዝብ ከ150 ዓመታት በፊት የኢሬቻ (የምስጋና) ሥነ-ሥርዓትን የሚያከናውንበት ሐይቅ/ምንጭ ነው። ፊንፊኔ የዚህ ምንጭ ስም ሲሆን፣ ይህ ምንጭ አሁን "ፊልውሃ" ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ይገኛል። ታላቅ ኃይልን ይዞ ከመሬት የሚፈልቅ ምንጭ ነው። ሽማግሌዎች እንደሚናገሩት፣ በዚህ ምክንያት ነው ፊንፊኔ የሚለው ስም የተሰጠው። ይህ የመጀመሪያው ስሙ ነው።

ይህ ሖራ ፊንፊኔ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ፣ በተለይም በቱለማ ኦሮሞ ዘንድ፣ እንደ ቅዱስ ሐይቅ ተደርጎ ይቆጠራል። እንዲሁም "ሖራ ሆርማታ" (የመራባት ሐይቅ/ምንጭ) በመባል ይታወቃል። ይህም የኦሮሞ ከብቶች ውሃ የሚጠጡበት፣ የሚባዙበትና የሚለመልሙበት ቦታ ስለነበር ነው። ሖራ ፊንፊኔ ለኢሬቻ ሥነ-ሥርዓት መፈጸሚያና ለከብቶች መጠጫ ቦታ ብቻ ሳይሆን፣ የኦሮሞ ሕዝብ በመታጠብ ከተለያዩ በሽታዎች የሚፈወሱበት፤ ጤንነታቸውን የሚጠብቁበት ቦታም እንደነበር ይነገራል።

ባለፉት የፊውዳል አገዛዞች ግፊት ሳቢያ፣ የኦሮሞ ህዝብ ፊንፊኔን ለቀው እንዲወጡና ቀደምት እና ዋነኛው የኢሬቻ ስፍራቸው ሲነጠቅ፣ ሖራ ሃርሳዲ ለኦሮሞ ዋናው የኢሬቻ ሥፍራ ሆኖ እንድመረጠ ተደረገ። ይህ ሐይቅ መልካም ዕድል የሚገኝበት፣ ኦሮሞዎችም አንድነታቸውን እንደገና ያጠናከሩበት ቦታ በመባልም ይታወቃል።"ኢሬቺ ኢሬ ኦሮሞቲ" (ኢሬቻ የኦሮሞ ጥንካሬ ነው) የሚለው አባባል የመጣውም ከዚሁ ነው።

የለውጡ መንግሥት (የአሁኑ አስተዳደር) የሕዝባችን ቀደምት ባህልና ወግ ለመመለስ እንዲሁም የሰብቦኑማ-ዲሞክራሱማ ( ዲሞክራሲያዊ- ብሔርተኝነትን) ይህን ትዉልድ በማነፅ መጪዉ ን ትዉልድ የበለጸገእ ኢትዮጵያን ለማውርስና ለማስተላለፍ የባህል ህዳሴን በማወጅ ታሪካዊ ሥራን በመስራት ላይ ይገኛል።

ፍጹም እና ዘላቂ ሰላምን የምንሻ ከሆነ ይቅርታን እና ዕርቅን፣ እኩልነትን እና አንድነትን፣ ፍትህን እና ርትዕን ማረጋገጥ ይገባል አሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊ...
26/09/2025

ፍጹም እና ዘላቂ ሰላምን የምንሻ ከሆነ ይቅርታን እና ዕርቅን፣ እኩልነትን እና አንድነትን፣ ፍትህን እና ርትዕን ማረጋገጥ ይገባል አሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት።

የ2018 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ በተለያዩ ሀይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቶች እየተከበረ ነው።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ እንኳን ለ2018 ዓ.ም በዓለ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

በእግዚአብሔር ኃይል በጢሰ እጣን አመልካችነት ከተቀበረበት ጉድጓድ የወጣው መስቀል እስከዛሬ ድረስ የእውነት መስካሪ እና የድኅነት ምልክት ሆኖ ቀጥሏል ነው ያሉት።

ዛሬ ላይ ሕገ እግዚአብሔር በድፍረት ይጣሳል፣ የዚህ ውጤትም ዓለምን በአጠቃላይ በመኖር እና ባለመኖር መካከል እየከተተ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ፍጹም እና ዘላቂ ሰላምን የምንሻ ከሆነ ይቅርታን እና ዕርቅን፣ እኩልነትን እና አንድነትን፣ ፍትህን እና ርትዕን ማረጋገጥ ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።

የዘንድሮው የመስቀል በዓል አከባበር እግዚአብሔር የሰጠን የውሃ ጸጋችን ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ለመጠቀም በአንድነት ባካሄድነው ተግባር ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድባችንን አጠናቀን ባስመረቅንበት ማግስት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

ይህ ክስተት ለሀገራችን የዳግም ልደትን ያበሰረ ነው ብንል ማጋነን አይሆንም ያሉት ብጹዕነታቸው፤ በግድቡ ግንባታ ስራ ላይ ታሪካዊ አሻራቻውን ያሳረፉትንም ሁሉ ማመስገን እንደሚገባ ገልጸዋል።

በቀጣይ ሀገራችን ልትሰራቸው በዕቅድ የያዘቻቸውን ታላላቅ ስራዎች በፍጥነት እና በጥራት ተሰርተው ለሕዝባችን ጥቅም እንዲውሉ ሁላችንም መረባረብ ይኖርብናልም ነው ያሉት።

ታላላቅ እና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሁም ችግር አስወጋጅ ስራዎች እውን ሊሆኑ የሚችሉት ሕዝቡ በአንድነት እና በሕብረት ሲሰራ እንደሆነ ገልጸው፤ በግድቡ የታየው ትብብር እና ተነሳሽነት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ጠቁመዋል።

አለመግባባቶችን በዕርቅ እና በይቅርታ በማለፍ እኩልነትን፣ ፍትህን እና ርትዕን በማረጋገጥ እንዲሁም ለሰላም መስፈን ረዥም ጉዞ በመሄድ ሕዝቡን ወደ አንድነት ማምጣት እንደሚገባም አመላክተዋል።

የመስቀሉ መልዕክት የሰው ልጅን ሁሉ በሰላም፣ በሕይወት፣ በእኩልነት፣ በአንድነት ማኖር መሆኑን በመገንዘብ ከመጠፋፋት ይልቅ በጋራ መልማትን ምርጫ ማድረግ ይገባል ሲሉም አሳስበዋል።

በሚቀጥሉት ቀናት በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራል።JMN Amharic መስከረም 14/2018 ዓ.ም።በሚቀጥሉት ቀናት በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከባድ መጠን...
24/09/2025

በሚቀጥሉት ቀናት በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራል።

JMN Amharic መስከረም 14/2018 ዓ.ም።

በሚቀጥሉት ቀናት በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢኒስቲትዩት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢኒስቲትዩት ከመስከረም 11 ቀን እስከ መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሚኖረውን የአየር ሁኔታ አዝማሚያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በላከው መግለጫ አስታውቋል።

በዚህም በሚቀጥሉት ቀናት ዝናብ ሰጭ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ቀጣይነት እንደሚኖራቸው ተመላክቷል፡፡

በመሆኑም በደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ሰሜን ምዕራብ፣ እንዲሁም በመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ይኖራቸዋል።

በተጨማሪም በፀሐይ ሀይል ታግዞ ከሚጠናከሩ የደመና ክምችቶች ላይ በመነሳት በምዕራብ፣ በመካከለኛዉ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ አልፎ አልፎ በሚኖሩት ቀናት በ24 ሰዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።

በሌላ በኩል በጋ ሁለተኛ የዝናብ ወቅታቸው በሆኑት በደቡብና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀን ወደ ቀን የደመና ሽፋን እንደሚጨምር ይጠበቃል።

በዚህም በአብዛኛዎቹ የበጋ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡

በደሴ ዙሪያ ወረዳ በደረሰ የትራፍክ አደጋ የ12 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 49 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደረሰ።JMN Amharic መስከረም 14/2018 ዓ.ም።በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን...
24/09/2025

በደሴ ዙሪያ ወረዳ በደረሰ የትራፍክ አደጋ የ12 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 49 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደረሰ።

JMN Amharic መስከረም 14/2018 ዓ.ም።

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ህይወት አለፈ፡የወረዳው ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር መሀመድ ሰይድ፥ በዛሬው እለት መነሻውን ከመካነ ሰላም ያደረገ የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ ደሴ ዙሪያ ወረዳ ልዩ ቦታው ዳባ መግለቢያ አካባቢ አደጋ ደርሶበታል ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በዚህም በአደጋው የ12 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ሌሎች 49 ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች ህክምና እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፥ የአደጋው መንሰኤ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የዘገበው ኤፍ ኤም ሲ ነው፡፡

ኬንያ ዜጎቿ የሩሲያ ሠራዊትን ተገድደው እንደሚቀላቀሉ ለማጣራት ምርመራ ጀመረችJMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም። ኬንያ ዜጎቿ ወደ ሩሲያ በግዳጅ እየተወሰዱ በዩክሬን ጦርነት ውስ...
22/09/2025

ኬንያ ዜጎቿ የሩሲያ ሠራዊትን ተገድደው
እንደሚቀላቀሉ ለማጣራት ምርመራ ጀመረች

JMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም።

ኬንያ ዜጎቿ ወደ ሩሲያ በግዳጅ እየተወሰዱ በዩክሬን ጦርነት ውስጥ እንዲሳተፉ ይደረጋሉ መባሉን ተከትሎ ምርመራ መጀመሯ ተሰምቷል፡፡

ምርመራው ኬንያዊው አትሌት ኢቫንስ ኪቤት፣ የሩሲያ ሰራዊትን እንድቀላቀል ተታልዬ ነበር ማለቱን ተከትሎ የመጣ ነው ተብሏል፡፡

የኬንያ ባለስልጣናት እውነታውን እንዲሁም የተጎጂዎችን ደህንነት ለማረጋገጥ፣ ከሩሲያና ከዩክሬን ባለስልጣናት ጋር እየተነጋገሩ መሆኑ ተዘግቧል፡፡

ይህ ሁኔታ በግጭት ቀጠና ውስጥ የውጭ ሀገር ዜጎችን ኢላማ ያደረገ ቅጥር ላይ ያለውን ስጋት አጉልቶ እንደሚያሳይ ተጠቁሟል፡፡

ኬንያ አንዳንድ ዜጎቿ ወደ ሩሲያ ጦር ሰራዊት በግዳጅ እንደገቡና አሁን በዩክሬን የጦር ምርኮኞች ሆነው እንደሚገኙ የሚገልጽ ዘገባ ከወጣ በኋላ ነው የማጣራት ምርመራውን የከፈተችው፡፡

ሂዩማን ራይትስ ዎች መንግሥት "ከምርጫው አስቀድሞ" ጋዜጠኞች ላይ "የሚያደርገው አፈና አጠናክሯል" አለ።JMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም።ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተ...
22/09/2025

ሂዩማን ራይትስ ዎች መንግሥት "ከምርጫው አስቀድሞ" ጋዜጠኞች ላይ "የሚያደርገው አፈና አጠናክሯል" አለ።

JMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም።

ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋም ሂዩማን ራይትስ ዎች፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ከመጪው አጠቃላይ "ምርጫ አስቀድሞ ገለልተኛ ድምጾች ላይ" የሚያደርገውን "አፈና አጠናክሯል" ሲል ከሰሰ። የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከነሐሴ አንስቶ "በርካታ ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን በዘፈደቀ" እንዳሰሩም አስታውቋል።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ተቋም፤ ይህንን ክስ ያቀረበው በአገሪቱ "የጨመረውን የጋዜጠኞች እስር" በተመለከተ ሰኞ መስከረም 12/2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ነው። የሂዩማን ራይትስ ዎች የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር የሆኑት ላቲሺያ ባደር፤ "የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ገለልተኛ ዘገባን ለማፈን እንደ አዲስ ጥረት የጀመሩት ተጠያቂነት ለማስቀረት ነው" በማለት እንደተናገሩ በመግለጫው ላይ ተጠቅሷል።

የኢትዮጵያ መንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከነሐሴ ወር ጀምሮ "በዘፈቀደ በርካታ ጋዜጠኞች እና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎችን በዘፈቀደ እንዳሰሩ" ሂዩማን ራይትስ ዎች በመግለጫው አስረድቷል። "ቢያንስ ስድስት" የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች "በዘፈቀደ መታሰራቸውን" የገለጸው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ተቋም፤ ከእነዚህ ውስጥ "ከሰው እንዳይገናኙ የተደረጉ ወይም ያለ ክስ ለረዥም ጊዜ የታሰሩ" እንዳሉ አስታውቋል።

በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችው የማለፊያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች በሙሉ የትምህርት ሚኒስትር ማሳሰቢያ፤JMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም።በ20...
22/09/2025

በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችው የማለፊያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች በሙሉ የትምህርት ሚኒስትር ማሳሰቢያ፤

JMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም።

በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ፡-

1. የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫችሁ ውስጥ ማካተት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

2.አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 4 ልጆችን ተገላገለች።JMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም። በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጎባ ሪፈራል ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆችን በሰላ...
21/09/2025

አንዲት እናት በአንድ ጊዜ 4 ልጆችን ተገላገለች።

JMN Amharic መስከረም 12/2018 ዓ.ም።

በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጎባ ሪፈራል ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ልጆችን በሰላም ተገላግላለች።

ወ/ሮ ጠይባ ሀሰን በዛሬው ዕለት በሆስፒታሉ በተደረገላት ቀዶ ጥገና 2 ወንድ እና 2 ሴት ልጆችን በሰላም መገላገሏን የዩኒቨርሲቲው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወ/ሮ ጠይባ ሀሳን የሀሮ ዱማል ከተማ ነዋሪ ስትሆን ከዚህ በፊት ሰባት ልጆች እንዳሏት ተጠቁሟል፡፡

ለአንድ ወር ከ10 ቀን በሆስፒታሉ ውስጥ እንድትቆይ በማድረግ ክትትል ሲደረግላት እንደነበር ተጠቅሷል፡፡

በአሁኑ ሰዓት እናትና የተወለዱት አራቱ ሕጻናት በሆስፒታሉ የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙም ተገልጿል፡፡

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when JMN Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to JMN Amharic:

Share