JMN Amharic

JMN Amharic አዳዲስ ወጎች ይቀርቡበታል
(2)

በኬንያ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ።JMN Amharic ነሃሴ 02/2017 ዓ.ም።በኬንያ ዋና ከተማ ከሚገኘው ናይሮቢ አውሮፕላን ማረፍያ ተነስቶ ወደ ሶማሌላንድ ሲጓ...
08/08/2025

በኬንያ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ።

JMN Amharic ነሃሴ 02/2017 ዓ.ም።

በኬንያ ዋና ከተማ ከሚገኘው ናይሮቢ አውሮፕላን ማረፍያ ተነስቶ ወደ ሶማሌላንድ ሲጓዝ የነበረው አነስተኛ አውሮፕላን ከዋና ከተማዋ ወጣ ብሎ በሚገኘው ኪምቡ ግዛት መከስከሱ የተገለጸ ሲሆን በአደጋውም የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።

በሰዎች መኖርያ አካባቢ የተከሰከሰው ይህ አነስተኛ አውሮፕላን የአየር ላይ አምቡላንስ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ባለቤትነቱም አምረፍ ፍላዪንግ ዶክተርስ የተሰኘ የህክምና ተቋም እንደሆነ ተገልጿል።

የህክምና ተቋሙ የደረሰውን አደጋ ይፋ ሲያደርግ በአደጋው የደረሱ ጉዳቶችን እንዲሁም የአደጋውን ምክንያት ምን እንደሆነ ባይገልጽም የኬንያ ቀይ መስቀል በአደጋው የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን አስታውቋል።

አደጋው የተከሰተው በኬንያ እና ሶማሌላንድ ድንበር አካባቢ መሆኑን ተከትሎ የአገሪቱ ወታደሮች እና ፖሊሶች በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን ከተቋሙ እንዲሁም ከኬንያ መንግስት በኩል ስለጉዳዩ በዝርዝር የተባለ ነገር አለመኖሩን አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል።

ቻይና ጠፈር ላይ ሆስፒታል ልትገነባ ነው።JMN Amharic ነሃሴ 02/2017 ዓ.ም።በቻይና የሚገኙት የሼንዘን ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የሻንጋይ ኢንጂነሪንግ ማይክሮ ሳተላይቶች ማዕከል በቅ...
08/08/2025

ቻይና ጠፈር ላይ ሆስፒታል ልትገነባ ነው።

JMN Amharic ነሃሴ 02/2017 ዓ.ም።

በቻይና የሚገኙት የሼንዘን ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የሻንጋይ ኢንጂነሪንግ ማይክሮ ሳተላይቶች ማዕከል በቅርቡ በጠፈር ላይ ሆስፒታል በጋራ ለመገንባት የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል።

ፕሮጀክቱ የጠፈርተኞችን ጤና ለማጎልበት እና በምህዋሩ ውስጥ የህክምና ክትትል ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል።

የወደፊቱ የጠፈር ሆስፒታል በአይሮስፔስ፣ በህክምና እና በባዮሎጂ መስኮች ላይ እድገት በማስመዝገብ የጤና ድጋፍን በተመለከተ የላቀ ምርምር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።

እንዲሁም ከጠፈር ተመራማሪዎች በተጨማሪ ወደ ጠፈር የሚጓዙ መደበኛ ሰዎችን ጤና ለመደገፍም ምርምር ያደርጋል ነው የተባለው።

እንደ ሲጂቲኤን ዘገባ በስምምነቱ መሰረት ሆስፒታሉን ለማቋቋም ሁለቱም ወገኖች በህክምና መሳሪያዎች፣ በፈጠራ የህክምና ቴክኖሎጂዎች እና በኤሮስፔስ ሳይንስ ላይ ተባብረው በመስራት ሆስፒታሉን እንደሚገነቡ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሶማሊያ ወታደሮች ስትራቴጂክ ጠቀሜታ ካላት የሶማሊያ ከተማ በ72 ሰዓታት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጠ።JMN Amharic ነሃሴ 02/2017 ዓ.ም።የኢትዮጵ...
08/08/2025

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የሶማሊያ ወታደሮች ስትራቴጂክ ጠቀሜታ ካላት የሶማሊያ ከተማ በ72 ሰዓታት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጠ።

JMN Amharic ነሃሴ 02/2017 ዓ.ም።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጦር አዛዦች የሶማሊያ ፌደራል መከላከያ ሠራዊት በጌዶ ክልል በሌድ ሀዎ ከተማ ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ መስጠታቸው ተሰምቷል።

የኢትዮጵያ ሠራዊት አመራሮች ቁልፍ ወታደራዊ ጠቀሜታ ካላት ኢትዮጵያን ከኬኒያ ከምትዋሰነው በደቡባዊ ሶማሊያ ከምትገኘው በሌድ ሀዎ ከተማ በ72 ሰዓት ውስጥ የሶማሊያ ፌደራል ኃይሎች ለቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ መስጡትን ከሶማሊያ ምንጮች ተሰምቷል።

በኢትዮጵያ በኩል በከተማዋ የግብጽ ወታደሮች ለመስፈር እየመጡ ናቸው የሚል ሰበብ መቅረቡን ምንጭች ጨምረው ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ዛሬ ጧት ከተማዋን ከፌደራል መንግሥት ጋር ግጭት ውስጥ የገባው የጁባ ላንድ አስተዳደር ከባድ መሳሪያዎችን በማስገባት በከተማዋ ዙሪያ መስፈሩ ተገልጿል።

አስተያየት ሰጪዎች የኢትዮጵያ ወታደራዊ አዛዦች ሁለቱ የሶማሊያ ኃይሎች ከተማዋን ለመቆጣጠር በሚፋለሙበት በዚህች ቁልፍ ከተማ ወደ ግጭት እንዳይገቡ በማሰብ የፌደራል ሠራዊቱ እና የሠራዊቱ አጋር ኃይሎች ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ የ72 ሰዓት ቀነ ገደብ ያቀስመጡት ሲሉ ግምታቸውን አስቀምጠዋል።

ማልያዊቷ እናት በአንድ ጊዜ 9 ዘጠኝ ጤነኛ ህጻናትን በመውለድ ታሪክ ሰርታለች ተባለ።JMN Amharic ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም።ማሊያዊቷ ሃሊማ ሲሴ በአንድ ጊዜ ዘጠኝ ጤነኛ ህጻናትን በመው...
07/08/2025

ማልያዊቷ እናት በአንድ ጊዜ 9 ዘጠኝ ጤነኛ ህጻናትን በመውለድ ታሪክ ሰርታለች ተባለ።

JMN Amharic ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም።

ማሊያዊቷ ሃሊማ ሲሴ በአንድ ጊዜ ዘጠኝ ጤነኛ ህጻናትን በመውለድ ታሪክ ሰርታለች ተብሏል። ይህ ያልተለመደ እና አስገራሚ ተፈጥሯዊ ክስተት ሲሆን፣ በአንድ ልደት ውስጥ በህይወት ለተረፉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህጻናት የ ጊነስ ወርልድ ሪከርድን እንድትይዝ አድርጓታል ነው የተባለው።

ሃሊማ አምስት ሴት እና አራት ወንድ ልጆችን የያዙትን ዘጠኝ ልጆቿን በ 30 ሳምንታት የእርግዝና ጊዜ ውስጥ፣ በ ሲ-ሴክሽን በሚባል ቀዶ ጥገና ወልዳለች የተባለ ሲሆን ይህ አስደናቂ ክስተት በህክምና ታሪክ ውስጥ እጅግ አበረታች እና ተአምራዊ ጊዜ ሆኖ ተመዝግቧል ነው የተባለው።

ከሩሲያ ነዳጅ ዘይት በመግዛቷ ምክንያት ትራምፕ በህንድ ላይ የጣሉትን ቀረጥን ወደ 50% አሳደጉ።JMN Amharic ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም።የመጀመሪያው 25% ቀረጥ ከነገ  ጀምሮ የሚጸና ሲ...
07/08/2025

ከሩሲያ ነዳጅ ዘይት በመግዛቷ ምክንያት ትራምፕ በህንድ ላይ የጣሉትን ቀረጥን ወደ 50% አሳደጉ።

JMN Amharic ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም።

የመጀመሪያው 25% ቀረጥ ከነገ ጀምሮ የሚጸና ሲሆን፣ ተጨማሪው ቀረጥ ደግሞ ከ21 ቀናት በኋላ ተግባራዊ ይሆናል።

‎የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ  ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በሚቀጥለው ሳምንት ሊገናኙ መሆኑ ተነገረ።JMN Amharic ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም።‎ትራምፕ  ከፑቲን ጋር ለመገናኘት እና በ...
07/08/2025

‎የአሜሪካዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር በሚቀጥለው ሳምንት ሊገናኙ መሆኑ ተነገረ።

JMN Amharic ነሃሴ 01/2017 ዓ.ም።

‎ትራምፕ ከፑቲን ጋር ለመገናኘት እና በቀጣይም የሩሲያውን መሪ እና ዘለንስኪን ያካተተ የሶስትዮሽ ግንኙነት ለመከታተል እንዳሰቡ ለአውሮፓ መሪዎች መናገራቸውን ዘገባዎች አመልክተዋል።

ኢሰመኮ ዓመታዊ ሪፖርቱን እንዲያቀርብ ፓርላማው እንዳልጠራው አስታወቀ።JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዓመታዊ ሪፖርቱን እንዲያቀርብ ...
06/08/2025

ኢሰመኮ ዓመታዊ ሪፖርቱን እንዲያቀርብ ፓርላማው እንዳልጠራው አስታወቀ።

JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዓመታዊ ሪፖርቱን እንዲያቀርብ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥሪ እንዳልተደረገለት፣ ኮሚሽነሩ አቶ ብርሃኑ አዴሎ አስታወቁ፡፡

ኮሚሽነሩ ይህንን ያስታወቁት የ2017 ዓ.ም. የኮሚሽኑን ዓመታዊ የሰብዓዊ መብቶችን አያያዝ የተመለከተ ሪፖርት ሰኞ ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ለጋዜጠኞች ሲያብራሩ ነው፡፡

የቀድሞውን ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) ተክተው በጥር 2017 ዓ.ም የተሾሙት ኮሚሽነር ብርሃኑ፣ ከተሾሙ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በተደረገ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ፓርላማው የኮሚሽኑን ሪፖርት ለማዳመጥ ጥሪ አለማድረጉን ተናግረዋል፡፡

የተከዜ ግድብ ሲሞላ ውሃ ስለሚለቀቅ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የ...
06/08/2025

የተከዜ ግድብ ሲሞላ ውሃ ስለሚለቀቅ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የተከዜ ግድብ ውሃ በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት ውስጥ እንደሚለቀቅ አስታውቋል።

ስለሆነም በግድቡ ግራና ቀኝ የሚገኙ ነዋሪዎች ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው ብሏል። ከኤጀንሲው ደብዳቤ እንደመለከትነው ነዋሪዎቹ የመጓጓዣ ድልድይ እንዲጠቀሙ መክሯል።

ይህ የቅድመ ጥንቃቄ መልዕክት ውሃው በሚለቀቅበት ጊዜ ከግድቡ በታች ባሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ጉዳት እንዳያደርስ ነው።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የተከዜን ግድብ የሚያቋርጡ እንስሳትና ሰዎች እንዲሁም በግድቡ ዙሪያ በመስኖ ልማት ስራ ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮች ውሃው በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት ውስጥ የሚለቀቅ በመሆኑ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

06/08/2025

የቀን መረጃ ሐምሌ 30/2017 ዓ.ም።

ከናይሮቢ - አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት ተጀመረ።JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት በቅርቡ ...
06/08/2025

ከናይሮቢ - አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት ተጀመረ።

JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።

አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች' የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት በቅርቡ ከናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ የአውቶብስ ጉዞ መጀመሩን አስታውቋል።

አንድ የአውቶብስ ትኬት ዋጋ 7,500 የኬንያ ሽልንግ ሲሆን፣ ለደርሶ መልስ ጉዞ ደግሞ 15,000 የኬንያ ሽልንግ ያስከፍላል። ይህ ዋጋ በኢትዮጵያ ብር ሲሰላ 16,000 ብር ገደማ ይሆናል።

ይህ አገልግሎት የተጀመረው በአውሮፕላን ትኬት መወደድ ምክንያት በአውቶብስ ትራንስፖርት ላይ የነበረውን ክፍተት ለመሙላት መሆኑን የድርጅቱ ዳይሬክተር ሚካኤል ጄምስ ተናግረዋል።

ኩባንያው በአሁኑ ጊዜ ስምንት አውቶብሶች ያሉት ሲሆን፣ በቀን አንድ ጊዜ ከናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ እንዲሁም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ጉዞ ያደርጋል።
አውቶብሱ 46 ተሳፋሪዎችን የመያዝ አቅም ያለው ሲሆን፣ ለተሳፋሪዎች ምቾት ሰፋፊ ወንበሮች፣ የኢንተርኔትና የመዝናኛ አገልግሎቶች እንዲሁም የተለያዩ መጸዳጃ ቤቶች ተዘጋጅተዋል።

የጉዞው መስመር ከናይሮቢ ተነስቶ ሞያሌንና የተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞችን አቋርጦ አዲስ አበባ ይደርሳል። የደህንነት ስጋት እንዳለበት ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ሚካኤል የፀጥታ ስጋት አጋጥሞኝ አያውቅም ብለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በመንገዱ ላይ የመንገዱን ደኅንነት በተመለከተ መረጃ ወስደን ነው የምንጓዘው ብለዋል። በኢትዮጵያ ድንበር ውስጥ በምሽት ጉዞ አናደርግም ያሉ ሲሆን ድርጅቱ ለወደፊት የአውቶብሶችን ቁጥር ወደ 16 የማሳደግ እቅድ እንዳለውም ገልጿል።

06/08/2025

በሰደድ እሳት እየፈተናት ያለችው ፈረንሳይ

JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።

በደቡባዊ ፈረንሳይ በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት የሰደድ እሳት መከሰቱ ተገልጿል::

ሰደድ እሳቱ እስካሁን 11 ሺህ ሄክታር አካሎ በርካታ መኖሪያ ቤቶችን አውድሟል::

የአካባቢው ባለስልጣናት እንዳስታወቁት እስካሁን በ8 ሰዎች ላይ ጉዳት ሲደርስ በአንድ ሰው ላይ ግን ከባድ ጉዳት ደርሷል::

ሰደድ እሳቱ የተከሰተው በፈረንሣይ እና ስፔን ድንበር ሜዴትራኒያን ባሕር አጠገብ በሚገኘው ኮር ቢርስ ተራራ ላይ ነው::

ሰደድ እሳቱ በሰዎች ላይ ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርስ በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎችን የማሸሽ ስራ እየተከናወነ ይገኛል::

የሀገሪቱ የአየር ትንበያ ባለስልጣን በአካባቢው ያለው ከባድ ንፋስ እሳቱ እንዲስፋፋ ሊያደርግ ስለሚችል ወደ አካባቢው የሚያመሩ መንገዶች እንዲዘጉ ማዘዛቸውን ፍራንስ 24 ዘግቧል።

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በአዋሽ ወንዝ ሙላት ሳቢያ ከ5,000 በላይ ሰዎች ሲፈናቀሉ 2,400 ሄክታር ሰብል ወደመ።JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ...
06/08/2025

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በአዋሽ ወንዝ ሙላት ሳቢያ ከ5,000 በላይ ሰዎች ሲፈናቀሉ 2,400 ሄክታር ሰብል ወደመ።

JMN Amharic ሀምሌ 30/2017 ዓ.ም።

በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ኢሉ እና ሰበታ ሃዋስ ወረዳዎች ባሳለፍነው ቅዳሜ ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ አዋሽ ወንዝ በመሙላቱ ከ5,000 በላይ ሰዎች ሲፈናቀሉ ከ2,400 ሄክታር በላይ የእርሻ መሬት ላይ ጉዳት መድረሱን የአካባቢው ባለስልጣናት ተናገሩ።

የኢሉ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ተስፋዬ ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት ባሳለፈነው ቅዳሜ ምሽት አዋሽ ወንዝ በአራት አቅጣጫዎች ሞልቶ በመፍሰሱ ወሬርሶ ቀሊና እና ሙሉ ሳተዩ በተባሉ ሁለት ቀበሌዎች ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ አስገድዷል።
ከፍተኛ መጠን ያለው ሰብል እና እንደ ዶሮ፣ ፍየል እና በግ ያሉ እንስሳት በጎርፉ ምክንያት ጉዳት ደርሶባቸዋል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው የጠፉት አጠቃላይ የእንስሳት ብዛት አሁንም በመጣራት ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

የሰበታ ሀዋስ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ አሸናፊ ንጉሴ በበኩላቸው የአዋሽ ወንዝ ሞልቶ ወደ አዋሽ ባሎ ቀበሌ በመግባቱ 240 አባወራዎች ከመኖሪያቸው መፈናቀላቸውንና በሰብል እንዲሁም በእንስሳት ላይ ጉዳት መድረሱን አስታውቀዋል። አያይዘውም የአከባቢው ነዋሪዎች ጎርፉን ይባባሳል በሚል በስጋት ላይ መውደቃቸውን ጠቁመዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when JMN Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to JMN Amharic:

Share