JMN Amharic

JMN Amharic አዳዲስ ወጎች ይቀርቡበታል
(2)

21/08/2026

በአሜሪካ የተሰረቀው ፊሌም አለምን እያነጋገረ ይገኛል

በናይጄሪያ በጀልባ መስመጥ አደጋ አብዛኛዎቹ ህጻናት የሆኑ ቢያንስ 50 ሰዎች ሞቱበሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ ሶኮቶ ግዛት ሃሙስ እለት አቅም በላይ መጫኗ የተነገረች ጀልባ በመስመጧ አብዛኛዎቹ ህ...
21/08/2026

በናይጄሪያ በጀልባ መስመጥ አደጋ አብዛኛዎቹ ህጻናት የሆኑ ቢያንስ 50 ሰዎች ሞቱ

በሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ ሶኮቶ ግዛት ሃሙስ እለት አቅም በላይ መጫኗ የተነገረች ጀልባ በመስመጧ አብዛኛዎቹ ህጻናት የሆኑ ቢያንስ 50 ሰዎች መሞታቸው ተነገረ። የነፍስ አድን ጥረቱ አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን የአካባቢው ባለስልጣን ገልጸዋል።አክለዉም ወደ 40 የሚጠጉ ህጻናት አስከሬኖች መገኘታቸውን ተነግሯል፡፡

በጀልባዋ ላይ የነበሩት በአብዛኛው ከ10 እስከ 15 ዓመት የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሲሆኑ 16 ሰዎች በህይወት መትረፋቸውንም ባለስልጣናቱ አክለው ገልጸዋል።

ሮይተርስ የዓይን እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው ከሚፈጸመው የቀብር ስነ-ስርዓት በፊት በርካቶቹ በሰሌን እና በባህላዊ ልብሶች የተጠቀለሉ 50 አስከሬኖች በአካባቢው መስጊድ አደባባይ ላይ ተዘርግተው መመልከቱን ገልጿል።

አቅም በላይ መጫን ደካማ ጥገና እና የደህንነት ህጎችን በአግባቡ አለማስከበር በሀገሪቱ ወንዞች እና የውሃ መንገዶች ላይ በተለይም በዝናብ ወቅት ለአደጋዎች አስተዋፅዖ በሚያደርጉባት ናይጄሪያ ውስጥ ገዳይ የጀልባ አደጋዎች በአንጻራዊነት እየተበራከቱ ነው። ባለፈው ጥር ወር በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ ዮቤ ግዛት፣ ቀዳዳ የነበራት ጀልባ በመስመጧ ቢያንስ 25 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።

ኤል ኒኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ስጋት እንደደቀነ ተገለፀበፓሲፊክ ውቅያኖስ ላይ እየተከሰተ ያለው የኤል ኒኖ ክስተት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ከተመዘገቡት ሁሉ የበለጠ ጠንካራ ሊሆን እንደ...
21/08/2026

ኤል ኒኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ስጋት እንደደቀነ ተገለፀ

በፓሲፊክ ውቅያኖስ ላይ እየተከሰተ ያለው የኤል ኒኖ ክስተት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ከተመዘገቡት ሁሉ የበለጠ ጠንካራ ሊሆን እንደሚችል የዩናይትድ ኪንግደም ብሔራዊ የአየር ሁኔታ እና የአየር ንብረት አገልግሎት (ሜት ኦፊስ) አስጠንቅቋል።

ይህ ሃይለኛ የተፈጥሮ የአየር ንብረት ክስተት የአለም አቀፍ የሙቀት መጠንን የሚጨምር ሲሆን፤ለከባድ የአየር ንብረት መዛባቶች ያለውን ስጋትም ከፍ ያደርገዋል።

ሜት ኦፊስ እንደገለጸው፤ ይህ ተፈጥሯዊ ክስተት ከሰው ሰራሽ የአየር ንብረት ለውጥ ጋር በመደራረብ 2027ን በአለም አቀፍ ደረጃ በታሪክ ከተመዘገቡት ሁሉ የበለጠ ‹‹ሞቃታማ ›› ዓመት የመሆን እድሉን ይጨምረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም የሚታዩ የአየር ንብረት ሁኔታዎች በክስተቱ መጎዳታቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ይገኛሉ፤ በሕንድ ዝቅተኛ የዝናብ መጠን መመዝገቡ እና በአትላንቲክ ውቅያኖስ በኩል የሃሪኬን አውሎ ንፋስ እንቅስቃሴ መቀነሱ ለዚህ ማሳያዎች ናቸው።

በተጨማሪም ኤል ኒኖ በዩናይትድ ኪንግደም በኩል ለዝናባማ እና አውሎ ንፋሳማ የበጋ ወቅት መንስኤ ሊሆን እንደሚችልና በረጅም ጊዜ ትንበያዎች ላይ ያልተረጋጋ የአየር ጠባይ ምልክቶች እየታዩ መሆናቸውን ዘገባው ያመላክታል።

በእንግሊዝ ሜት ኦፊስ የረጅም ጊዜ ትንበያ ክፍለ ኃላፊ ፕሮፌሰር አዳም ስካይፍ ‹‹ይህ ክስተት አስቀድሞ ታይቶ የማይታወቅ ሁነቶች ስብስብ መሆኑን በግልጽ ልንገነዘብ ይገባል››ብለዋል።

አክለውም ‹‹በትንበያዎቻችን ውስጥ እንደዚህ ያለ ከፍተኛ የኤል ኒኖ ስጋት ምልክት አይቼ አላውቅም›› ብለዋል።

ምንም እንኳ የአየር ንብረት ለውጥ የኤል ኒኖ ክስተቶችን ያባብሳል ለማለት የሚያስችል ግልጽ ማስረጃ ባይኖርም፤እየሞቀች በመጣችው ዓለም ውስጥ ግን የክስተቱ ተፅዕኖዎች የበለጠ ከባድ እና አደገኛ እየሆኑ መጥተዋል።

የኦሮሞ ወጣቶች የክረምቱን መውጣትና የብርሃን ማብሰሪያ የሆነውን የ“ጎቤ” እና “ሺኖዬ” ባህላዊ በዓል እያከበሩ ይገኛል በኦሮሞ ባህል ውስጥ የክረምቱ ጨለማና ጭጋግ ተጠናቆ የተስፋና የብልጽግ...
21/08/2026

የኦሮሞ ወጣቶች የክረምቱን መውጣትና የብርሃን ማብሰሪያ የሆነውን የ“ጎቤ” እና “ሺኖዬ” ባህላዊ በዓል እያከበሩ ይገኛል

በኦሮሞ ባህል ውስጥ የክረምቱ ጨለማና ጭጋግ ተጠናቆ የተስፋና የብልጽግና ወቅት የሆነው የበጋ (የብርሃን) መባቻ የሚበሰርበት የ“ጎቤ” እና “ሺኖዬ” ወቅታዊ የባህል ሥርዓት በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።

አሮጌው ዓመት ተጠናቆ አዲሱ ምዕራፍ ሲተካ፣ ምድር በለምለም ዕፅዋትና በአበቦች የምታጌጥበት ይህ ወቅት፣ ማህበረሰቡ ከክረምቱ አስቸጋሪ የሥራ ጫና አርፎ አዲስ ተስፋን የሚቀበልበት እንደሆነ ተገልጿል።
በዓሉ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች እንደየአካባቢው ባህላዊ ትውፊት በተለያዩ ማራኪ የአቀራረብ ስልቶችና ጨዋታዎች እየተከናወነ ይገኛል።

በዕለቱ ወጣቶችና ኮረዶች ውብ የሆኑ የባህል ልብሶችን በመልበስ፣ በባህላዊ ዜማዎችና ጭፈራዎች የታጀበ ደስታቸውንና መልካም ምኞታቸውን እየገለጹ ነው።
በዚህ የሽግግር ሥርዓት ላይ፣ ለተገኘው አዲስ ተስፋና ሰላም ለፈጣሪና ለተፈጥሮ ያላቸውን የላቀ ምስጋና ኮረዶች በ“ሺኖዬ” ዜማ፣ ወጣቶች (ፎሌዎች) ደግሞ በ“ጎቤ” ጨዋታ እየገለጹት ይገኛሉ።

ወጣቶቹ በዜማዎቻቸው ጀግንነትን፣ ልማትንና ማህበራዊ ሰላምን የሚያወድሱ ሲሆን፣ ልጃገረዶች ደግሞ ለምለም ቅጠል በእጃቸው ይዘው በየመኖሪያ መንደሩ ሰላም፣ ብልጽግና እና መረጋጋት እንዲሰፍን፣ የልዩነት ጨለማ አልፎ የእርቅ ብርሃን እንዲበራ ጥሪ እያቀረቡ ነው።
ይህ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ የመጣው እሴት ዕድሜያቸው ከ12 እስከ 25 ዓመት በሆኑ ላላገቡ ወጣቶች ብቻ የሚከናወን ሲሆን፣ አዲሱን ትውልድ ወደ ቀደመው ጥንታዊ ማንነቱ ለመመለስ፣ ማህበራዊ ትስስርን ለማጠናከር እና የክልሉን የቱሪዝም መስህብ ለማሳደግ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው የባህል ተመራማሪዎች ይገልጻሉ።

JMN Afaan Oromoo

የሶላር ኃይል አቅርቦት ባላቸው አካባቢዎች ለአዲስ የመኖሪያ ቤት ደንበኞች ነፃ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ አገልግሎት ተጀመረየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዋናው ግሪድ ርቀው በሶላር ኃይል ማመንጫ...
21/08/2026

የሶላር ኃይል አቅርቦት ባላቸው አካባቢዎች ለአዲስ የመኖሪያ ቤት ደንበኞች ነፃ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ አገልግሎት ተጀመረ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዋናው ግሪድ ርቀው በሶላር ኃይል ማመንጫዎች አገልግሎት በሚያገኙባቸው አካባቢዎች ላሉ አዲስ የመኖሪያ ቤት ደንበኞች ነፃ የኤሌክትሪክ ቆጣሪ መግጠም መጀመሩን አስታወቀ።

የኮሙዩኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዋር አብራር እንደገለጹት፤ አዲሱ አሠራር በተለይም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የገጠር ማኅበረሰቦች በኢኮኖሚ አቅማቸው ሳቢያ ከኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዳይገለሉ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

አሠራሩ በሥራ ላይ ከዋለ በኋላም ባሉት ሁለት ሳምንታት ብቻ 3 ሺህ 364 ደንበኞች ነፃ ቆጣሪ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተቋሙ ገልጿል።

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እስካሁን ባከናወናቸው ሥራዎች 54 የሶላር ኃይል ማመንጫዎችን በመገንባት ከ11 ሺህ በላይ አባወራዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አቶ አንዋር አብራርተዋል፡፡

በመሆኑም ዜጎች እነዚህን መሠረተ ልማቶች በአግባቡ እንዲጠብቁና የፍጆታ ክፍያቸውን በወቅቱ እንዲከፍሉ ተቋሙ ጥሪ አቅርቧል።

የተወዳጁ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲስ የውድድር ዘመን በሻምፒዮኑ አርሰናል እና ኮቨንተሪ ሲቲ ጨዋታ ይጀመራልምሽት አራት ሰዓት ላይ አርሰናል ከኮቨንተሪ ሲቲ ጋር በኤምሬትስ ስታዲየም ጨዋታው...
21/08/2026

የተወዳጁ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አዲስ የውድድር ዘመን በሻምፒዮኑ አርሰናል እና ኮቨንተሪ ሲቲ ጨዋታ ይጀመራል

ምሽት አራት ሰዓት ላይ አርሰናል ከኮቨንተሪ ሲቲ ጋር በኤምሬትስ ስታዲየም ጨዋታውን ያደርጋል።

አርሰናል የወቅቱ የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ነው። ተጋጣሚው ኮቨንተሪ ሲቲ ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊግ ተመልሷል።

ሁለቱ ቡድኖች በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለ19ኛ ጊዜ ነው።

ከዚህ ቀደም ባደረጓቸው 18 ጨዋታዎች አርሰናል 10ሩን በማሸነፍ የበላይነቱን ይዟል። ኮቨንተሪ ሲቲ ሦስት ጊዜ ሲያሸንፍ በቀሪ አምስት ጨዋታዎች አቻ ተለያይተዋል።

አርሰናል በ18ቱ ጨዋታዎች ላይ 25 ጎሎችን ሲያስቆጥር ኮቨንተሪ ሲቲ 13 ግቦችን ከመረብ ላይ አሳርፏል።

ሁለቱ ቡድኖች ለመጨረሻ ጊዜ በሊጉ የተገናኙት እ.አ.አ በ2001 ነበር።

በወቅቱ ባደረጉት ጨዋታ አርሰናል በዴኒስ ቤርካምፕ ጎል 1 ለ 0 አሸንፏል። ኮቨንተሪ ሲቲ በዛው ዓመት ከሊጉ ወርዷል።

ኮቨንተሪ በፍራንክ ላምፓርድ እየተመራ በሻምፒዮንሺፑ በ95 ነጥብ አንደኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ ከ25 ዓመታት በኋላ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ተመልሷል።

በማይክል አርቴታ የሚመራው አርሰናል የሻምፒዮንነት ክብሩን የማስጠበቅ ጉዞውን ከአዲስ አዳጊው ክለብ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ይጀምራል።

ኮቨንተሪ ሲቲ በመጀመሪያው የሊግ ጨዋታው ከሊጉ የወቅቱ የዋንጫ ባለቤት ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል።

የ36 ዓመቱ ቶም ብራሞል የመክፈቻውን ጨዋታ በዋና ዳኝነት ይመራሉ።

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት መርሐ ግብር እስከ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ይቆያል።

አሜሪካ የኢራንን አገዛዝ “የሚያፈርሱ” ማዕቀቦችን እንደምትጥል ዛተች አሜሪካ የኢራንን ኢኮኖሚ ሙሉ በሙሉ ለማዳከም እና አገዛዙን ለመለወጥ የሚያስችሉ ከባድ ማዕቀፎችን እና አዲስ የኢኮኖሚ ጦ...
21/08/2026

አሜሪካ የኢራንን አገዛዝ “የሚያፈርሱ” ማዕቀቦችን እንደምትጥል ዛተች

አሜሪካ የኢራንን ኢኮኖሚ ሙሉ በሙሉ ለማዳከም እና አገዛዙን ለመለወጥ የሚያስችሉ ከባድ ማዕቀፎችን እና አዲስ የኢኮኖሚ ጦርነት እቅድ ይፋ ማድረጓን አስታወቀች።

ኢራን ይህንን ዘመቻ ዋሽንግተን ላይ “ተጨማሪ ሽንፈት” የሚያስከትል ስትል አጣጥለዋለች፡፡

የአሜሪካ ግምጃ ቤት ኃላፊ ስኮት ቤሰንት፤ አገራቸው በኢራን ላይ ልትወስድ ያሰበችው እርምጃ “በዓለም ታሪክ ውስጥ ትልቁ የተቀናጀ ኢኮኖሚያዊ የማግለል” ዘመቻ አካል መሆኑን ገልጸዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

ከኢራን ጋር የንግድ ግንኙነት የሚፈጽሙ፣ ገንዘብ የሚያዘዋውሩ ወይም ነዳጅ የሚገዙ ማናቸውም አገራት ላይ ጠንካራ የአሜሪካ ማዕቀፍ እንደሚጣል አስጠንቅቀዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በበኩላቸው፣ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በቴህራን ላይ የከፈተው የኢኮኖሚ ጦርነት በአሜሪካ ላይ ተጨማሪ ሽንፈት የሚያስከትል እና ዓለም አቀፍ ምጣኔ ሀብት ላይ አደጋ የሚደቅን “ኢኮኖሚያዊ ሽብርተኝነት” ነው ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

አራግቺ በኤክስ ገጻቸው ላይ ” ‘የኢኮኖሚ ጦርነት’ የሚባለው ከአሜሪካ ቀውስ ትኩረትን ለማስቀየር” የተወሰደ እንደሆነ በመግለፅ የአገሪቱ ብሔራዊ ዕዳ 40 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱን ከቀውሶቹ አንዱ አድርገው ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በመከላከያ እና ደህንነት መስኮች ሁለንተናዊ ስትራቴጂካዊ ትብብር ለመመስረት ታሪካዊ ስምምነት ላይ ደረሱ።በሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ የተመራው ከፍተኛ የኢትዮጵያ ወታደራ...
21/08/2026

ኢትዮጵያ እና አሜሪካ በመከላከያ እና ደህንነት መስኮች ሁለንተናዊ ስትራቴጂካዊ ትብብር ለመመስረት ታሪካዊ ስምምነት ላይ ደረሱ።

በሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ የተመራው ከፍተኛ የኢትዮጵያ ወታደራዊ ልዑካን ቡድን በአሜሪካ ፔንታጎን ያካሄደውን ይፋዊ ጉብኝት ማጠናቀቁን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

በፔንታጎን የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ረዳት የመከላከያ ሚኒስትር ብራያን ጄ. ኤሊስ እና በሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ የተመራው ውይይት፣ የሁለቱን አገራት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ላቀ ስትራቴጂካዊ ደረጃ ለማሸጋገር አስችሏል ።

የስምምነቱ ማዕቀፍ ዘላቂ ብሔራዊ ጥቅምንና የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ፣ መተማመንን ለማጠናከር እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድና ቀጣናው ሰላም እና መረጋጋትን ለማስፈን ያለመ ነው ተብሏል።

ሁለቱም ወገኖች የተደረሱትን ስምምነቶች በፍጥነት ወደ ተግባር በመቀየር የወደፊት አጋርነታቸውን ለማጠናከር ጽኑ ቁርጠኝነት ማሳየታቸውን ተሰምቷል።

ልዑካን ቡድኑ በቆይታው ከሌሎች የአሜሪካ መከላከያ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይቶችንና የመስክ ጉብኝቶችን ማድረጉም ተነግሯል።

በናይጄሪያ በደረሰ የጀልባ አደጋ ቢያንስ 46 ሰዎች ሞቱበሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ ሶኮቶ ግዛት ውስጥ በደረሰ የጀልባ መገልበጥ አደጋ ቢያንስ የ46 ሰዎች ሕይወት አለፈ።ከ70 በላይ ሰዎችን ይዞ...
21/08/2026

በናይጄሪያ በደረሰ የጀልባ አደጋ ቢያንስ 46 ሰዎች ሞቱ

በሰሜን ምዕራብ ናይጄሪያ ሶኮቶ ግዛት ውስጥ በደረሰ የጀልባ መገልበጥ አደጋ ቢያንስ የ46 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

ከ70 በላይ ሰዎችን ይዞ ሲጓዝ የነበረው ጀልባ ከጫናቸው ሰዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ ሕጻናት እንደነበሩ ተገልጿል።

ጎሮንዮ በተባለው የአገሪቱ አካባቢ የ46 ሰዎች አስከሬን መገኘቱን የፖሊስ ቃል አቀባይ አህመድ ሩፋኢ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ቃል አቀባዩ የ16 ሰዎችን ሕይወት ማትረፍ እንደተቻለ፤ ነገር ግን 15 ሰዎች እስካሁን ደብዛቸው እንደጠፋ አስረድተዋል።

የነፍስ አድን ሥራው አሁንም መቀጠሉን ባለሥልጣናት ገልጸዋል።

ወደ አካባቢው መጓዝ አዳጋች መሆኑን የሚናገሩት ሩፋኢ፣ የጸጥታ አካላት እና የአደጋ ሠራተኞች እየተንቀሳቀሱ መሆኑን አክለዋል።

ሮይተርስ የዜና ወኪል ያነጋገራቸው አንድ የዓይን እማኝ፣ ጀልባው ላይ ተሳፍረው የነበሩት ሕጻናት የሩዝ እርሻ ላይ ለመስራት ሲጓዙ ከነበሩ የእርሻ ባለቤቶች እና የጉልበት ሠራተኞች ጋር አብረው ነበሩ ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።

በአቅራቢያው የሚገኝ መስጊድ ውስጥ የቀብር ሥነ ሥርዓት ከመፈጸሙ በፊት፣ በምንጣፍ እና በባህላዊ አልባሳት የተጠቀለሉ የ50 ሰዎች አስከሬኖችን መመልከታቸውን የዓይን እማኙ ተናግረዋል።

የናይጄሪያ የአደጋ አስተዳደር ኤጀንሲ ቃል አቀባይ ኢዚኬል ማንዞ "ጎራኡ በጣም ሩቅ ቦታ ነው . . . ቡድናችን ወደዚያ ገጠራማ ሥፍራ ተጉዟል" ሲሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

‎"78 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ዲጂታል ይደረጋሉ"ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የባህል፣ የኪነ-ጥበብ እና የእንቁ እሴቶች ሀብቶች በአግባቡ በማልማት ለሀገር ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ትስስር የሚውሉበትን አ...
21/08/2026

‎"78 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ዲጂታል ይደረጋሉ"

ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የባህል፣ የኪነ-ጥበብ እና የእንቁ እሴቶች ሀብቶች በአግባቡ በማልማት ለሀገር ኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ትስስር የሚውሉበትን አዲስ የሦስት ዓመት የልማት እና ኢንቨስትመንት አቅጣጫ መዘርጋቱን የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

‎የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር የስትራቴጂ ጉዳዮች ሥራ አስፈጻሚ አቶ እንድሪስ አብዱ እንደገለጹት፣ ይፋ የሆነው የሦስት ዓመት የልማት እና ኢንቨስትመንት ዕቅድ የሀገሪቱን ባህልና ኪነ-ጥበብ ወደ ተሻለ ደረጃ ከማሸጋገር ባለፈ ተቋማዊ አቅምን ለመገንባትና የአሰራር ስርዓቶችን ለማዘመን ያለመ ብለዋል።

‎በዚሁ መሠረት ሚኒስቴሩ ባለፉት ዓመታት ያከናወናቸውን ሀገራዊ ጥናቶች መነሻ በማድረግ በህብረተሰቡ ዘንድ ተሸሽገው የቆዩ የባህል እሴቶችን፣ የባህላዊ እርቅና ሽምግልና ስርዓቶችን እንዲሁም በርካታ የቋንቋ ሀብቶችን ለህዝብ ለህዝብ ትስስርና ለሀገር ገጽታ ግንባታ የማዋል ሰፊ ስራዎች ተቀይሰዋል።

‎​በተለይም ሀገሪቱ በ2030 ለያዘችው የዲጂታል ኢኮኖሚ ራዕይ ስኬት ባህልና ቋንቋ ወሳኝ መሆናቸውን በመገንዘብ፣ እስካሁን ዲጂታላይዝ ከተደረጉ 30 የሀገሪቱ ቋንቋዎች በተጨማሪ በቀጣይ የስትራቴጂ ዓመታት ሁሉንም 78 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ዲጂታል የማድረግ አቅጣጫ ተቀምጧል።

‎ከዚህ ጎን ለጎን ቤተ-መጻሕፍትንና የጥበብ ክበባትን በማስፋፋት አዲስ የሚያነብ ትውልድ የመፍጠር፣ ሀገር በቀል እውቀቶችንና ባህላዊ ህክምናዎችን ለኢኮኖሚ ጥቅም የማዋል እንዲሁም የኢትዮጵያን ሀብት የኪነ-ጥበብ ባህል በአፍሪካና በአለም አቀፍ መድረክ በማስተዋወቅ ዲፕሎማሲን የማጠናከር ተግባራት ዋና ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when JMN Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to JMN Amharic:

Shortcuts

Share